ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 695 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 017,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 152

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 695 名订阅者。

根据 31 八月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 142,过去 24 小时变化为 2,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 30.85%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.42% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 842 次浏览,首日通常累积 2 578 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 10

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 01 九月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 695
订阅者
+224 小时
+237
+14230
帖子存档
የተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች የኮይሻ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ጎበኙ .......///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ፕሮጀክትን የሥራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል። የሥራ ኃላፊዎቹ የዋናውን ግድብና የኃይል ማመንጫ ቤቱን የግንባታ ሥራ እንዲሁም የግንባታ ግብዓት  ማምረቻ ወርክ ሾፖችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል። በጉብኝቱ ፕሮጀክቱ የደረሰበትን ደረጃና የአሰራር ሂደት፣ ፕሮጀክቱ እያከናወነ ስላለው የማህበራዊ አገልግሎት ሥራዎች እንዲሁም ግንባታውን በተያዘለት መርሃ ግብር ለማጠናቀቅ በቀጣይ መከናወን ስለሚኖርባቸው ሥራዎች የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ መብራቱ ተሾመ ለሥራ ኃላፊዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል። ሥራ አስኪያጁ በማብራሪያቸው ፕሮጀክቱ በፋይናንስና ችግር ምክንያት ተጓቶ የነበረ ቢሆንም በተቋሙና በመንግስት በተወሰዱ እርምጃዎች አሁን የግንባታ ሥራው በጥሩ ሂደት ላይ ይገኛል ብለዋል። በዚህም በአሁኑ ወቅት የዋናው ግድብ የጥቅጥቅ ኮንክሪት ሙሌት 70 በመቶ፣ የማመንጫ ቤቱ  የመጀመሪያ ደረጃ የአርማታ ኮንክሪት 68 በመቶ እንዲሁም የግድቡ የውሃ ማስተንፈሻ የስትራክቸራል ኮንክሪት ሥራ 30 በመቶ ላይ መድረሱን አብራርተዋል። ግድቡ ሲጠናቀቅ ከሚኖረው 201 ሜትር ከፍታ አሁን ላይ በአማካኝ ከ120 ሜትር በላይ መድረሱን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈፃፀም ደግሞ 72 በመቶ ላይ ደርሷል ነው ያሉት። በቀጣይ በኤሌክትሮ ሜካኒካልና ሀይድሮሊክ ስቲል ስትራክቸር ገጠማ ሥራዎች ላይ ትኩረት ተደርጎ እንደሚሰራና ይህም የከፍተኛ አመራሩን የቅርብ ክትትልና ድጋፍ እንደሚጠይቅ አስገንዝበዋል። እንደ አቶ መብራቱ ገለፃ ጉብኝቱ የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ፕሮጀክቱ የደረሰበትን ደረጃ ተመልክተው በቀጣይ ለሚከናወኑ ሥራዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ እና ለችግሮቹ አፍጣኝ እርምጃዎችን እንዲሰጡ ያስችላል። ከጅማ እስከ ጭዳ ባለው መንገድ ላይ የሚስተዋለው ችግር በፕሮጀክቱ ዕቃዎች ማጓጓዝ ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ በመሆኑ ከፍተኛ ሥራ አመራሩ ችግሩ እንዲቀረፍ እያከናወነ ያለውን ሥራ አጠናክሮ እንዲቀጥልም አሳስበዋል። በጉብኝቱ ላይ የተሳተፉት የጄነሬሽን ቢዝነስ  ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወ/ ኪዳን እና የኮርፖሬት ፋይናንስና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ የፋይናንስ ችግር ገጥሞት  እንደነበር በማስታወስ የግንባታ ሥራውን ለማስቀጠል ተቋሙ አሁን ላይ አብዛኛውን ክፍያዎች በራሱ እየሸፈነ ስለመሆኑም ገልፀዋል። የመስክ ምልከታው  የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ የደረሰበትን ደረጃና ያጋጠሙ ችግሮችን በጋራ ለይቶ ለችግሮቹ ወቅታዊ መፍትሔ በመስጠት የፕሮጀክቱን አፈፃፀም ለማሻሻል እንደሚያግዝ ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪም ጉብኝቱ በቀጣይ መከናወን ስለሚኖርባቸው ሥራዎች  አቅጣጫ ለማስቀመጥ የሚያስችል ሲሆን ምልከታው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 25 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

photo content

በተለያዩ የትምህርት መስኮች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ የፕሮጀክቱ ሠራተኞች የምረቃ ሥነ -ሥርዓት እየተካሄደ ነው የጅማ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ከዊ ቢውልድ ኩባንያ ጋር በመተባበር በሁለተኛ ዲግሪ ያስተማራቸውን 37 የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሠራተኞችን በዛሬው ዕለት እያስመረቀ ነው፡፡ በምረቃ ሥነ -ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወካይና በተቋሙ የጄኔሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወ/ኪዳን እና የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጀማል አባፊጣን(ዶ/ር) ጨምሮ ሌሎች የተቋሙ ከፍተኛ  የሥራ ኃላፊዎች፣  የዩኒቨርሲቲው የሴኔት አባላት፣ የኮንታና ጎፋ ዞኖች ዋና አስተዳሪዎችና ሌሎች የአካባቢው የመስተዳድር አካላት የፕሮጀክቱ  የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች፣  የተመራቂ ቤተሰቦች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ተቋሙ በኃይል ማመንጫ ጣቢያ እና በፕሮጀክቶች ላይ የሚገኙ ሠራተኞች በየአካባቢያቸው ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመተባበር ከመደበኛ ሥራቸው ጎን ለጎን በሥራ ቦታቸው ላይ ሆነው የትምህርት ዕድል የሚያገኙበትን ምቹ ሁኔታ እየፈጠረ ሲሆን በዛሬው ዕለት የሚመረቁ የኮይሻ ፕሮጀክት ሠራተኞችም የዚሁ ተጠቃሚ ናቸው። ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ለፕሮጀክቱ ሠራተኞች የተሰጠው የትምህርት እድል በኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የተመቻቸ ስለመሆኑም ተገልጿል። ከተመራቂዎች መካከል አስሩ በኮንስትራክሽን ኢንጂነሪንግና ማኔጅመንት፣ 14 በፕሮጀክት ማኔጅመንት እና ፋይናንስ እንዲሁም 13 በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን የትምህርት መስክ የተከታተሉ ናቸው። ከዚህ ውስጥ 33 ወንድና ሦስቱ ሴቶች ናቸው። ሠራተኞች በሥራ ቦታቸው ላይ ሆነው ትምህርታቸውን መከታተላቸው በሥራ ቦታዎች ላይ የሠው ኃይል እጥረት እንዳያጋጥም ያግዛል። ከሠራተኞች ምርቃት በተጨማሪ በተመራቂ ሠራተኞች አስተባባሪነት የተገነባ ትምህርት ቤት ምርቃት እንዲሁም የኃይል ልማት ዘርፉን ለማሳደግ በተቋሙና በዩኒቨርሲቲው መካከል ያለው የትብብር ሥራ ተጠናክሮ በሚቀጥልበት መንገድ ላይ ውይይት ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 25 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+6

ኬንያ ከውጭ ከምትገዛው ኤሌክትሪክ 83 በመቶውን የምትገዛው ከኢትዮጵያ ነው ….…///….… ኬንያ ከውጭ ከምትገዛው አጠቃላይ የኃይል አቅርቦቷ ውስጥ 83 በመቶው ከኢትዮጵያ የተገኘ መሆኑን ካፒታል ኤፍ ኤም የተሰኘው የሀገሪቱ ሬዲዮ ገለጸ፡፡ የመረጃ ምንጩ የሀገሪቱን የኢነርጂና ነዳጅ ተቆጣጣሪ ባለሥልጣን ጠቅሶ እንደዘገበው ኬንያ  እስከ ሰኔ ወር 2017 ዓ.ም. ድረስ ከውጭ ካስገባችው ጠቅላላ የኤሌክትሪክ ኃይል 83 በመቶው ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተገኘ ነው፡፡ ኬንያ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር በፈጠረችው የኃይል ትስስር ከዚህ ቀደም ሀገራዊ የኤሌክትሪከ ፍላጎቷን ለማሟላት ለነዳጅ እና ለሌሎች አማራጭ የኃይል ምንጮች የምታወጣውን ከፍተኛ ወጪ አስቀርቶላታል ፡፡ በዚህም ኬንያ በዓመት 10 ሚሊየን ዶላር ገደማ  ማዳን መቻሏን ሬዲየው አስታውቋል፡፡ የኬንያው ቢዝነስ ዴይሊ አፍሪካ ጋዜጣ በበኩሉ የኢትዮጵያ  የኃይል  አቅርቦት  በኬንያ ሊፈጠር የሚችለውን የኃይል ቀውስ በመከላከል ረገድ ወሳኝ  መሆኑን በመጥቀስ “ኢትዮጵያ ኬንያን ከመብራት መጥፋትና ከፈረቃ ታድጋለች” ሲል ዘግቧል፡፡ ኢትዮጵያ እና ኬንያ ቀደም ሲል በተፈራረሙት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ስምምነት መሰረት ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ በቀን በከፍተኛ ጭነት ሰዓት 200 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለኬንያ እያቀረበች ትገኛለች፡፡ ኢትዮጵያ ቀጣናውን በኃይል ትስስር ለማጠናከር በያዘችው ዕቅድ መሰረት ከኬኒያ በተጨማሪ በአሁኑ ወቅት ከጂቡቲ፣ ሱዳን እና ታንዛኒያ ጋር የኤሌክትሪክ ኃይል ትስስር ፈጥራለች፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 21 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

ዋና ሥራ አስፈጻሚው ከቻይናው የጂሲኤል ኢነርጅ ቴክኖሎጂ ኩባንያ ሊቀመንበር ጋር ተወያየዩ ……..///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እና የቻይናው ጂሲኤል ኢነርጅ ቴክኖሎጂ ኩባንያ ሊቀመንበር ሚስተር ዡ ጎንግሃን ሁለቱ ተቋማት በትብብር በሚሰሩባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡ የሲጂኤል ኢነርጂ ቴክኖሎጂ ኩባንያ ሊቀመንበር ሚስተር ዡ ጎንግሃን ኩባንያቸው በታዳሽ ኃይል ልማትና ኦፕሬተርነት፣ በሲልከን፣ ሊቲየም እና በሌሎች ማዕድናት ምርትና ማቀነባበር ላይ በስፋት እየተሳተፈ ስለመሆኑ ለኢንጂነር አሸብር አስረድተዋል፡፡ ኩባንያቸው በኢትዮጵያም በቅርቡ በድሬደዋ ከተማ አካባቢ በአሉሚኒየም፣ ኮባልትና ኮፐር ማቀነባበር ላይ ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳለው ገልፀው ለዚህም አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡ ፋብሪካው በአጭር ጊዜ ውስጥ 4 ሺ ሜጋ ዋት እንዲሁም በሚቀጥሉት አምስትና ስድስት ዓመታት 6 ሺ ሜጋ ዋት ኃይል እንደሚያስፈልገው ጠቅሰው ፋብሪካው ውጤታማ እንዲሆን ተቋሙ ይህን ኃይል ዝግጁ እንዲያደርግላቸውም ሊቀመንበሩ ጠይቀዋል፡፡ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር ለፋብሪካው ከሚያስፈልገው የኃይል አቅርቦት ባለፈ በተለያዩ የኃይል ልማት ዘርፎች፣ በዳታ ማይኒንግ፣ በኤሌክትሪክ ተሸከርካሪ ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያ ግንባታ እና በአቅም ግንባታ ጉዳዮች ላይ ለመሳተፍና ከተቋሙ ጋር በትብብር ለመስራት  ፍላጎት እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በበኩላቸው ተቋሙ ከኩባንያው ጋር በትብብር ለመስራት ፈቃደኛና ደስተኛ እንደሆነ ገልፀው ውይይቱ ፍላጎቶቹን ወደ ተግባር ለመለወጥ እንደሚረዳም ተናግረዋል፡፡ የዳታ ማይኒንግ ለኢትዮጵያ አጠቃላይ ሀገራዊ ምርት (GDP) እያበረከተ ያለው አስተዋጽዖ አነስተኛ በመሆኑ ተቋሙ አሰራሮቹን እንደገና ለማደራጀት እየሰራ ስለመሆኑም ተናግረዋል፡፡ የሁለቱን ተቋማት በጋራ የመስራት ፍላጎት ወደ ተግባር ለመለወጥ ሥራውን የሚያስተባብር የቴክኒክ ቡድን እንዲቋቋም ከስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 21 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+6

አብዛኞቹ ግድቦች በቂ ውሃ ይዘዋል ………///……….. አብዛኞቹ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድቦች በክረምቱ የዝናብ ወቅት በቂ ውሃ መያዛቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግድብ ደህንነት ክትትል እና ቁጥጥር ሥራ አስኪያጅ ገልፀዋል። ሥራ አስኪያጁ አቶ ኤሊያስ ደላሽ እንደተናገሩት የታላቁ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ የተከዜ፣ጊቤ አንድ፣የፊንጫ እና ቆቃ ግድቦች መያዝ የሚጠበቅባቸውን የውሃ መጠን ሙሉ በሙሉ ይዘዋል። ለበለስ ኃይል ማመንጫ ጥቅም ላይ የሚውለው የውሃ ከፍታ ከሚጠበቀው 1787 ሜትር በላይ በሳንቲም ሜትሮች ከፍ ማለቱን ሥራ አስኪያጁ አስታውቀዋል። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተመርቆ ሙሉ በሙሉ ወደ አገልግሎት መግባቱ ለሌሎች ግድቦች ውሃ የመያዝ ሥራዎችን ያሳለጠ መሆኑን አቶ ኤሊያስ ተናግረዋል። ግድቦቹ ሳይንሳዊ በሆነ ስሌት ዓመቱን በሙሉ ጥቅም ላይ እንደሚውሉም ነው የገለፁት። ኢትዮጵያ ከምታመነጨው የኤሌክትሪክ ኃይል 95 ከመቶ በላይ ከውሃ ኃይል ምንጭ መሆኑ ይታወቃል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 19 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+4

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ! የ2018 የመስቀል በዓል የሰላም እንዲሆንላችሁ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ስም ልባዊ ምኞቴን እገልፃለሁ፡፡ በዓሉ የሠላም፣ የጤናና የአብሮነት እንዲሆን
እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ! የ2018 የመስቀል በዓል የሰላም እንዲሆንላችሁ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ስም ልባዊ ምኞቴን እገልፃለሁ፡፡ በዓሉ የሠላም፣ የጤናና የአብሮነት እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ፡፡ አሸብር ባልቻ (ኢንጂነር) ዋና ሥራ አስፈፃሚ

ግድቡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ልማት ወሳኝ ነው …….///…….. ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ልማት ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀስላሴ ተናገሩ፡፡ ፕሬዝዳንቱ በ80ኛው የተባበሩት መንግስታት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በአዲስ ዓመት ዋዜማ በይፋ መመረቁን አስታውሰዋል፡፡ ግድቡ ከ5 ሺህ ሜጋ ዋት በላይ የማመንጨት አቅም እንዳለው የገለፁት አምባሳደር ታዬ በማገዶ እጥረት ለሚሰቃዩ የኢትዮጵያ እናቶች ኃይል በማቅረብ እፎይታ ይሰጣል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም ይህ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነትን ለማሳደግ እንደሚረዳም ለጉባኤው አስገንዝበዋል፡፡ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የሌላቸው ከ60 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያንን የኃይል ተደራሽ ለማድረግ ታልሞ እየተሰራ ሲሆን የህዳሴ ግድብ ግንባታ የዕቅዱ አንዱ አካል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ፕሬዝዳንት ታዬ እንደገለፁት ግድቡ ከሀገር ውስጥ ፍጆታ ባሻገር ለቀጣናዊ የኃይል ትስስርም ጉልህ አስተዋጽኦ አለው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+1

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ የኑክሌር ልማት ፕሮጀክት ስምምነት ተፈራረሙ …….///…….. በኢትዮጵያ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ልማት ዙሪያ በሩሲያ አቶሚክ ኢነርጂ ኮርፖሬሽን(ሮሳቶም) እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መካከል የድርጊት መርሃ ግብር ተፈረመ። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) እና የሮሳቶም ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሌክሲ ሊካቼቭ ፊርማቸውን ባኖሩበት የፊርማ ሥነ-ሥርዓት ላይ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ተገኝተዋል፡፡  በፊርማ ሥነሰሥርዓቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደተናገሩት በሩሲያ ያደረጉት ጉብኝት የሁለትዮሽ ግንኙነቱን የሚያጠናክር ነው። ኢትዮጵያ ለሁሉን አቀፍ እድገት የሚውል የኑክሌር ልማት ፕሮጀክት ለመጀመር የረጅም ጊዜ ልምድ ካላት ሩሲያ ጋር ተባብራ ለመስራት ያላትን ቁርጠኝነትም ገልፀዋል። የኒውክሌር ኃይል የረጅም ጊዜ ልማትን ለማስጠበቅ፣ የኃይል ምንጮችን ለማብዛት እና የኢትዮጵያን አቅም ለማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል። የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በበኩላቸው በሩሲያ እና ኢትዮጵያ መካከል ያለው የሁለትዮሽ ግንኙነት በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ መሆኑን ጠቁመዋል። ሩሲያ በኒክሌየር ቴክኖሎጂ እና በሌሎች መስኮች ያላትን ልምድ ለኢትዮጵያ በማካፈል ለጋራ እድገት በትብብር እንደምትሰራ ጠይቀዋል፡፡ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በበኩላቸው በሩሲያ እና ኢትዮጵያ መካከል ያለው የሁለትዮሽ ግንኙነት በተረጋጋ ሁኔታ እያደገ መሆኑን  ተናግረዋል። የሀገራቱ ግንኙነቶች በዘላቂ ሁኔታ እያደጉ እና የንግድ ትስስሩም እየጨመረ ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጳጉሜ 4 ቀን 2017 ዓ.ም የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምርቃት ላይ የታላቁ የሕዳሴ ግድብን የሚስተካከል ለሰላማዊ ዓላማ ብቻ የሚውል የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ግንባታ በቅርቡ እንደምትጀምር መግለጻቸው ይታወሳል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+1

ኢትዮጵያ በኃይል ልማት ዘርፍ ሪፎርም እውቅና አገኘች .......///...... ከ80ኛው የተባበሩት መንግስታት ጉባኤ ጎን ለጎን በተካሄደ መርሀግብር ኢትዮጵያ በኃይል ልማት ዘርፍ ባከናወነችው ስኬታ
+2
ኢትዮጵያ በኃይል ልማት ዘርፍ ሪፎርም እውቅና አገኘች .......///...... ከ80ኛው የተባበሩት መንግስታት ጉባኤ ጎን ለጎን በተካሄደ መርሀግብር ኢትዮጵያ በኃይል ልማት ዘርፍ ባከናወነችው ስኬታማ ሪፎርም ከዓለም ባንክ እውቅና አግኝታለች። ይህን ተከትሎ የዓለም ባንክ፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ እና ሌሎች የልማት አጋር ድርጅቶች በጋራ ሶስት መቶ ሚሊዮን አፍሪካውያንን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ በያዙት ኢንሼቲቭ ኢትዮጵያ እንድትካተት ተደርጓል። ኢትዮጵያ 30 ቢሊዮን ዶላር መዋዕለ ነዋይ በሚጠይቀው በዚህ ኢንሼቲቭ መካተቷ በኢነርጂ ዘርፍ ያላትን እምቅ ሀብት ይበልጥ ለመጠቀም  እንደሚረዳት የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት በትዊተር ገፁ አስታውቋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 15 ቀን 2018 ዓ.ም

ሪጅኑ የህፃናት ማቆያ ከፈተ …….///……. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምስራቅ 1 ሪጅን የህፃናት ማቆያ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አስታወቀ፡፡ የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ በድሩ አህመድ ማቆያ ማዕከሉ ለህፃናት ምቹ የሆነ ክፍል እና የተለያዩ ቁሳቁሶች የተሟሉለት መሆኑን ተናግረዋል። የማቆያ ማዕከሉ የተቋሙ ሴት ሠራተኞችን የስራ ጫና ከመቀነስ ባሻገር የስራ ተነሳሽነታቸውንም እንደሚያሳድግ ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡ በሪጅኑ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ተወካይ ወ/ሮ መሠረት ካሳ በበኩላቸው የማዕከሉ መከፈት ሴት ሠራተኞች ልጆቻቸውን በቅርበት እየተከታተሉ መደበኛ ሥራቸውን በአግባቡ እንዲያከናውኑ ይረዳል ብለዋል። ለማዕከሉ እውን መሆን የተቋሙ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ፤ የሪጅኑ የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማድረጋቸውን የተናገሩት ደግሞ የሪጅኑ የሰው ሀብት፣የንብረት አስተዳደር  እና ጠቅላላ አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ አቶ አለማየሁ ተገኝ ናቸው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 15 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+5

የሥራ ኃላፊዎቹ የአይሻ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ጎበኙ ........///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጀነሬሽን ቢዝነስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ገብረኪዳን የተመራ ሥራ ኃላፊዎች ቡድን በሶማሌ ክልል አይሻ ከተማ አቅራቢያ የተገነባውን የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ጎብኝቷል። የሥራ መሪዎቹ ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት የጀመሩትን የንፋስ ተርባይን ጀነሬተሮች፣ የመሰረት ቁፋሮና የግንባታ ሥራቸው ተጠናቆ የተርባይ ተከላ የሚቀራቸውን ግንባታዎች፣ የኃይል መቆጣጠሪያ ክፍሎች እና የሠራተኞች የመኖሪያ ቤቶችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል። ከሠራተኖች ጋርም በፕሮጀክቱ እና በኦፕሬሽን ሥራዎች እንዲሁም በሥራ ሂደት በሚገጥሟቸው ችግሮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል። ከውይይቱ በኋላ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ኢንጂነር ኤፍሬም ገብረኪዳን እንደተናገሩት የፕሮጀክቱ ሠራተኞች ፈታኝ የአየር ሁኔታን ተቋቁመው ፕሮጀክቱ 80 ሜጋ ዋት እንዲያመነጭ በማድረጋቸው ሊመሰገኑ ይገባል። የቀሪውን 40 ሜጋ ዋት የግንባታ ሂደት በማጠናቀቅ ወደ ሥራ ለማስገባት እንደተቋም በሚደረገው ርብርብ ሠራተኞቹ በጽናት ጥረታቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል። የተቋሙ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ በበኩላቸው ሠራተኞች በሥራ ሂደት የሚገጥሟቸውን ችግሮች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ለመፍታት ጥረት እንደሚደረግ አረጋግጠዋል። የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት 120 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ሲኖረው 80 ሜጋ ዋቱ ተጠናቆ ከብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ወይም ከግሪድ ጋር ተገናኝቷል።   💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 14 ቀን 2018 ዓ.ም