en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 553 subscribers, ranking 8 395 in the Technologies & Applications category and 2 164 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 553 subscribers.

According to the latest data from 22 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 5 over the last 30 days and by 1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.99%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.38% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 043 views. Within the first day, a publication typically gains 2 393 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 9.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 23 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 553
Subscribers
+124 hours
+47 days
+530 days
Posts Archive
photo content
+2

በበጀት ዓመቱ ከሙስና እና ብልሹ አሰራር ጋር በተያያዘ ከቀረቡ ጥቆማዎች ለ17ቱ የውሳኔ ሀሳብ ቀርቧል፤ …..///….. በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት ከሙስናና ብልሹ አሰራር ጋር በተያያዘ ከቀረቡ ጥቆማዎች ውስጥ ለ17ቱ የውሳኔ ኃሳብ ለሚመለከተው ክፍል መቅረቡን በተቋሙ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ መምሪያ ገለፀ፡፡ በመምሪያው የሙስና ተጋላጭነት ጥናት እና ሥልጠና ሥራ አስኪያጅ አቶ መንግስቱ አባይነህ እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ ከግዢ ሂደት፣ ከፕሮጀክት አመራር፣ ከጥቅም ግጭት፣ ከካሳ ክፍያ አፈፃፀም እና ከአስተዳደር ጋር የተያያዙ 18 ጥቆማዎች ቀርበዋል፡፡ ከቀረቡት ጥቆማዎች መካከል በ17ቱ ላይ አስፈላጊውን የማጣራት ሥራ በማከናወን ለሚመለከተው አካል የውሳኔ ሀሳብ መቅረቡን ተናግረዋል፡፡ ሥራ አስኪያጁ አክለውም ለቢሮው የቀረቡ 3 የአስቸኳይ የሙስና መከላከል ጥቆማዎች ተጣርተው የማስተካከያ እርምጃዎች መወሰዳቸውንም አብራርተዋል፡፡ ቢሮው ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች በሥነ-ምግባር የታነጹ እንዲሆኑ፣ ሙስናን እንዲጸየፉ እና ኢንዲከላከሉ የሚያስችል የስልጠና ሞጁል በማዘጋጀት በሙስና ተጋላጭነት እና በሥነ-ምግባር ጽንሰ ሀሳብና ሙስና መከላከል ስትራቴጂ ዙሪያ ለ60 የሥራ ኃላፊዎች እና ለ120 ሠራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠቱን አስታውሰዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ 1 ሺ 572 የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ሀብታቸውን ማስመዝገባቸውን የጠቆሙት አቶ መንግስቱ ከፌዴራል የሥነ-ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን፣ ከገንዘብ ሚኒስቴር እና ኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ጋር በመተባበር የፀረ-ሙስና ንቅናቄ ሥራዎችን ቢሮው እያከናወነ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ በተጨማሪም የጥቅም ግጭትን ለመከላከል የሚያግዝ ጥናት ለማካሄድ መረጃዎች ተሰብስበው ለኮሚሽኑ መላካቸውን አስገንዝበዋል፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ደረጀ አጥናፌ በበኩላቸው የጥቅም ግጭት፣ ከሠራተኞች ሥነ-ምግባር እና ሙስናን ከመታገል አኳያ የአመራር ቁርጠኝነትን፣ ከጠቋሚዎች ከለላ እና ከጉቦ መከላከል ጋር በተያያዘ የተዘጋጁ ፖሊሲዎች በቅርቡ ወደ ሥራ ይገባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል፡፡ የሙስና ጥቆማ መቀበያውን ለማዘመንና ተደራሽ ለማድረግ ሶፍትዌር የበለፀገ ሲሆን ወደ ሥራ በሚገባበት ዙሪያ በቀጣይ ከኤ.ሲ.ቲ. እና ከሳይበር ደህንነት የሥራ ክፍሎች ጋር በትብብር እንደሚሰራ ገልፀዋል፡፡ በስራ ክፍሉ ያለው የሰው ኃይል በቂ ባለመሆኑ ሁሉም ሪጅኖች ላይ ተደራሽ መሆን አለመቻል፣ የግንዛቤና የመረጃ እጥረት መኖር በበጀት ዓመቱ የታየ ክፍተት መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ አቶ ደረጀ በቀጣይ በጀት ዓመት ለሁሉም የሥራ ኃላፊዎች ሥልጠና በመስጠት፣ ሕግና አሰራሮችን በመፈተሽ፣ ጠንካራ የክትትልና የቁጥጥር ሥርዓት በመዘርጋት እና ቅንጅታዊ አሰራርን በማሳደግ ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል ብለዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 16 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

photo content

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት ፋይናንስ የተሰራ ነው ….///…. ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት ትብብር ያለምንም የውጭ ብድር እና እርዳታ የተገነባ መሆኑን የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡ የማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤቱ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወይዘሮ ፍቅርተ ታምር እንደገለጹት በተለያዩ አካላት የግድቡ ወጭ በሦስተኛ ወገን እንደተሸፈነ ተደርጎ የሚተላለፈው መረጃ የተሳሳተ ነው፡፡ በዚህም ከሀገር ውስጥና በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የዲያስፖራ አባላት የቦንድ ሽያጭ እና ስጦታ ከ23 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ ተሰብስቦ ለግድቡ ግንባታ መዋሉንና ቀሪው ደግም በመንግስት መሸፈኑን ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም የሕዳሴ ግድብ በኢትዮጵያውያን ገንዘብ የተገነባ የዚህ ትውልድ የወል ትርክት ሆኖ የተመዘገበ የዘመናች ዓድዋ ነው ብለዋል። የግድብ ግንባታው በአሁኑ ወቅት እየተጠናቀቀ መሆኑን በመግለፅ ይህም ከተባበርን በራስ አቅም ፕሮጀክት መቅረጽና መምራት እንዲሁም በሕብረት ጀምረን ማጠናቀቅ እንደምንችል ማሳያ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቆ ሙሉ በሙሉ ማምረት ሲጀምር 5 ሺ 150 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ይኖረዋል፡፡ በኢትዮጵያ የሚገነቡ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን በዋናነት ፋይናንስ የሚያደርገው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሆኑን ጠ/ሚኒስቴር ዐቢይ አሕመድ በቅርቡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መናገራቸው ይታወሳል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 15 ቀን 2017 ዓ.ም

የሀገሪቱን ኢኮኖሚ የሚደግፍ የኃይል አቅርቦትን ታሳቢ ያደረገ ሥራ መስራት ይገባል ….///…  የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት ዓመት የሀገሪቱን ኢኮኖሚ የሚደግፍ የኃይል አቅርቦትን ታሳቢ ያደረገ ሥራ እንዲሰራ የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አብርሃም በላይ (ዶ/ር) አሳሰቡ። የሥራ አመራር ቦርድ የተቋሙን የ2018 በጀት ዓመት የፊዚካል እና የበጀት ዕቅድ ገምግሟል፡፡ የበጀት ዓመቱን ዕቅድ ለሥራ አመራር ቦርዱ ያቀረቡት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለፁት ተቋሙ በአደረጃጀት፣ በአሰራር እና በሰው ሀብት ልማት እንዲሁም የፋይናንስ ቁመናውን በማሳደግ ዙሪያ ተከታታይ የለውጥ ሥራዎችን እያከናወነ ነው፡፡ ከኃይል መሠረተ ልማት ስርቆት ጋር በተያያዘ እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችል አሰራር ዘርግቶ ወደ ትግበራ እንደሚገባም ገልፀዋል። በኃይል መሠረተ ልማት ስርቆት ሳቢያ በተቋሙ ላይ እየደረሰ ያለውን ኪሳራ ከመሰረቱ ለማስቀረት ከክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች ጋር ዘላቂ ግንኙነት የመፍጠር ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ነው ያስታወቁት፡፡ እንደ ኢንጂነር አሸብር ገለፃ በበጀት ዓመቱ ነባርና አዳዲስ ፕሮጀክቶችን ወጪ ቆጣቢ በሆነ አሰራር በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ በጥራት እንዲጠናቀቁ ለማድረግ ዕቅድ ተይዟል፡፡ ተቋሙ የተጣለበትን ሀገራዊ ኃላፊነት ለመወጣት እንዲችል የኃይል ማመንጨት፣ ማስተላለፍ እና ማከፋፈል አቅምን ለማሳደግ እንደሚሰራም ነው የገለፁት፡፡ የፕሮጀክቶች ግንባታ፣ ኦፕሬሽን እና ኮርፖሬት ሰርቪስ ሥራዎች የተሻለ አፈፃፀም እንዲያስመዘግቡ ለማድረግ የአሰራር ሥርዓቶችን ማዘመን እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ የፋይናንስ ቁመናን ከማሳደግ አኳያ የኃይል ብክነትን የመቀነስ፣ የአሰራር ቅልጥፍናን የማሻሻል፣ ከውጭ የኃይል ሽያጭ እና ከሌሎች የሚገኝ ገቢን በአግባቡ የመሰብሰብ እንዲሁም የቢዝነስ አማራጮችን የማስፋት ሥራዎች እንደሚሰሩም ነው የጠቆሙት፡፡ የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አብርሃም በላይ (ዶ/ር) በበኩላቸው የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ የሚደግፍ የኃይል አቅርቦትን ታሳቢ ያደረገ መሆን እንዳለበት አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡ የሰለጠነ የሰው ኃይል ስብጥርን ከማመጣጠን እንዲሁም ሀብትን በተገቢው መንገድ ከማስተዳደር አንፃር በትኩረት መሰራት እንዳለበትም ነው ያሳሰቡት፡፡ የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ አባል የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ አቶ ፈቃዱ ደግፌ በበኩላቸው ተቋሙ የፋይናንስ ቁመናው እንዲሻሻል በማድረግ የዕዳ ጫናዎቹን በራሱ ገቢ ለመሸፈን ዕቅድ ይዞ መንቀሳቀስ አለበት ብለዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 15 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

የኃይል ተደራሽነትን ለማሳደግ ተቋማቱ በቅንጅት እየሠሩ ነው ....///.... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በመልካ ዋከና ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ዙሪያ የሚገኙ ቀበሌዎችን የኃይል ተደራሽ ለማድረግ በቅንጅት እየሰሩ እንደሚገኙ ተገለፀ። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመልካ ዋከና የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ በቀለ እንደገለፁት ግድቡ በሚሰራበት ወቅት ከቦታቸው እንዲነሱ ለተደረጉ ነዋሪዎች የተለያዩ መሠረተ ልማቶችን ማሟላት አስፈልጓል። በዚህም መነሻነት ተቋሙ ከአሁን ቀደም ለአካባቢው ማህበረሰብ የንጹህ መጠጥ ውሃ፣ የጤና፣ የትምህርት እና የመንገድ ግንባታ ሥራዎችን በማከናወን ማህበራዊ ኃላፊነቱን ሲወጣ መቆየቱን አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅትም በህብረተሰቡ ሲነሳ የነበረውን የኃይል አቅርቦት ጥያቄዎች ለመመለስ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሆነ አቶ ቴዎድሮስ ገልፀዋል። በዚህም ሁለቱ ተቋማት በ40/60 የወጭ መጋራት አሰራር መሠረት ከ550 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ በጣቢያው ዙሪያ ለሚገኙ 12 ቀበሌዎች የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ ለማድረግ እየሰሩ ይገኛሉ ብለዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራው የአካባቢው ማህበረሰብ በጣቢያው ላይ ያለውን የእኔነት ስሜት አሳድጓል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኦሮሚያ ገጠር ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም የሻሸመኔ ቅርንጫፍ ማስተባበሪያ ኃላፊ አቶ ሁሴን ቴሲሶ በበኩላቸው ተቋማቱ በጣቢያው ዙሪያ የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎችን የኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ በቅንጅት እየሰሩ መሆኑን አብራርተዋል። በዚህም 12 ቀበሌዎችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ ከታቅደው እስከ አሁን 8 ቀበሌዎችን በከፊል ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የጠቆሙት ኃላፊው ቀሪዎቹን በአጭር ጊዜ ተጠቃሚ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል። በሁሉም ቀበሌዎች ከሚተከሉ ትራንስፎርመሮች 46 በመቶ፣ የመካከለኛ መስመር ምሰሶ ተከላ 82 በመቶ እንዲሁም የዝቅተኛ መስመር ምሰሶ ተከላ ሥራ 72 በመቶ መጠናቀቁን አቶ ሁሴን አስረድተዋል። አጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈፃፀም ከ60 በመቶ በላይ መድረሱንም ጠቁመዋል። እንደ ኃላፊው ገለፃ በማመንጫ ጣቢያው እየተከናወነ ያለው የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራ አገልግሎቱ እንደ ሀገር የኃይል ተደራሽነት ሽፋንን እና የገቢ አሰባሰቡን ለማሳደግ የያዛቸውን ዕቅዶች ለማሳካት ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል። ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የአካባቢውን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ በማሳደግ፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የማህበረሰቡን የአኗኗር ዘይቤ በመቀየና የመረጃ ባለቤት እንዲሆን በማስቻል የራሱን አስተዋፅዖ እንደሚያበረክት የተናገሩት የሥራ ኃላፊዎቹ ፕሮጀክቱ ውጤታማ እንዲሆን ሁለቱ ተቋማት ከማህበረሰቡና ከመስተዳድር አካላት ጋር በቅንጅት እየሠሩ ስለመሆኑም ጠቅሰዋል። በቀበሌዎቹ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ ለማድረግ ከተያዘው ከ550 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ውስጥ 60 በመቶው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ቀሪው 40 በመቶው ደግሞ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሚሸፈን ነው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 15 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

"ተቋሙ ያስመዘገባቸው ውጤቶች በመንግሥት ድጋፍ የመጡ ናቸው"  አብርሃም በላይ (ዶ/ር) ....///.... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2017 በጀት ዓመት ያስመዘገባቸው ውጤቶች በመንግሥት ድጋፍና ክትትል የተገኙ መሆናቸውን የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አብርሃም በላይ (ዶ/ር) አስታወቁ። የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ የ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀም ላይ በስካይ ላይት ሆቴል ግምገማ አካሂዷል። ግምገማው ተቋሙ በበጀት ዓመቱ በሰው ኃይል ልማት፣ በፋይናንስ፣ በኃይል ማመንጨት፣ በማስተላለፊያ፣ በማመንጫና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታና የጥገና ሥራዎች እንዲሁም በሪፎርም ሥራዎች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው። የቦርድ ሰብሳቢው አብርሃም በላይ (ዶ/ር) በግምገማው ወቅት እንደገለፁት የተቋሙን የ2017 ዕቅድ አፈፃፀም መታየት ያለበት ከቁጥሮች በላይ በመመዘን ነው። መንግሥት የተቋሙን የዕዳ ጫና በማቃለል እንዲሁም የታሪፍ ማሻሻያዎች እንዲደረጉ አቅጣጫ በማስቀመጥ አወንታዊ ለውጦች እንዲመዘገቡ ማድረጉን ተናግረዋል። ተቋሙ በበጀት ዓመቱ በፕሮጀክት ግንባታ አፈፃፀም፣ በኦፕሬሽን እና በኃይል ሽያጭ ዘርፍ እንዲሁም በሪፎርም ሥራዎች ላይ መሻሻል ማሳየቱን ተናግረዋል። ከዚህ በኋላ በኃይል ልማት ዘርፉ የሚገነቡ አዳዲስ ፕሮጀክቶች በቦርዱ ይሁንታ ሳያገኙና የጋራ መግባባት ላይ ሳይደረስባቸው ግንባታቸው እንደማይጀመርም ነው የገለፁት። የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አምባሳደር ግርማ ብሩ በበኩላቸው እንደገለፁት በሀገር ደረጃ እንደ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ትልቅ ሀብት የፈሰሰበት ተቋም የለም። አዲሱ የተቋሙ ስትራቴጂክ ዕቅድ የሚቀጥሉትን አምስት ዓመታት የሀገሪቱን የኃይል ፍላጎት ጥያቄዎች ሊመልስ የሚችል መሆን እንዳለበትም ነው በአፅዕኖት የተናገሩት። እንደ ምክትል ሰብሳቢው ገለፃ በበጀት ዓመቱ በዕቅድ ተይዘው ላልተጠናቀቁ ሥራዎች ተጠያቂነትን ማስፈን የሚያስችል አሰራር መዘርጋት አለበት። የተቋሙ ሥራ አመራር ቦርድ አባል የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል በበኩላቸው በበጀት ዓመቱ በኦፕሬሽን ሥራዎች ላይ የተገኘው ውጤት ለኃይል ሽያጭ ዕድገቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልፀዋል። ከኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ስርቆት ጋር በተያያዘ ለቦርድ አመራሩ በየጊዜው ሪፖርት የሚቀርብ ቢሆንም የቅርብ ክትትል ተደርጎ አፈፃፀማቸውን መገምገም ላይ ክፍተቶች እንደሚስተዋሉ ጠቁመዋል። በበጀት ዓመቱ የካሳ ክፍያ ጥያቄዎች የመቀነስ አዝማሚያ ማሳየታቸውን የጠቆሙት አቶ መላኩ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ከሚመለከታቸው የፌዴራል እና የክልል መስተዳድር አካላት ጋር በቅንጅት ሊሰራ ይገባል ብለዋል። የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ አባል የመከላከያ ሚኒስትሯ ወ/ሮ አይሻ መሐመድ በበኩላቸው በበጀት ዓመቱ በኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ወይም የራስ ኃይል በኩል የተሰሩ ሥራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባል አንስተዋል። የረጲ የደረቅ ቆሻሻ የኃይል ማመንጫ ጣቢያን ወደ ኦፕሬሽን ለማስገባት ሥራዎች እየተሰሩ ቢሆንም የጥገና ሥራው አዋጭነቱ መታየት እንዳለበት አፅዕኖት ሰጥተው ተናግረዋል። የሥራ ላይ ደህንነት መሳሪያዎችን አቅርቦት ከማሻሻል ባለፈም የግንዛቤ ፈጠራ ሥራዎች መሰራት እንዳለባቸውም ነው የጠቆሙት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 14 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

የተቋሙ ሥራ አመራር ቦርድ ዓመታዊ አፈፃፀሙን እየገመገመ ነው .....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ ቦርድ የተቋሙን የ2017 በጀት ዓመት  የዕቅድ አፈፃፀም በስካይ ላይት ሆቴል መገምገም ጀምሯል። ግምገማው ተቋሙ በበጀት ዓመቱ በሰው ኃይል ልማት፣ በፋይናንስ፣ በኃይል ማመንጨት፣ በማስተላለፊያ፣ በማመንጫና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታና የጥገና ሥራዎች እንዲሁም በሪፎርም ሥራዎች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው። የበጀት ዓመቱን የአስራ ሁለት ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ያቀረቡት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለፁት ተቋሙ አራቱን የስትራቴጂክ  የትኩረት መስኮች ለማሳካት በርካታ ሥራዎች አከናዉኗል። በበጀት ዓመቱ በኃይል ማመንጨት፣ ማከፋፈል፣ ማስተላለፍ እና ሽያጭ እንዲሁም በዋና ዋና ፕሮጀክቶች አፈፃፀም ላይ አበረታች ለውጦች መታየታቸውን ጠቁመዋል። በዘርፉ ለዘመናት የተከማቸውን ዕዳ በተወሰነ ደረጃ ወደ ሌላ ተቋም በማዘዋወር የዘርፉን ዕዳ ማቃለል መቻሉን የጠቀሱት ኢንጂነር አሸብር ለ12 ዓመታት ሳይከለስ የቆየውን የኤሌክትሪክ ታሪፍ በማሻሻል ተቋሙ የተሻለ ገቢ እንዲኖረው ተደርጓልም ብለዋል። በበጀት ዓመቱ የተቋሙን የአሰራር ሥርዓት ለማዘመንና ለማሻሻል የሚያስችሉ ሥራዎች መከናወናቸውንም ነው የጠቀሱት። በበጀት ዓመቱ የኃይል ምርት እና ሽያጭ ከ2016 በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር ዕድገት ማስመዝገቡንም ነው ዋና ሥራ አስፈፃሚው የገለፁት። በበጀት ዓመቱ በፕሮጀክቶች አፈፃፀም ላይ የነበሩ ችግሮችን በመፍታት በታቀደላቸው ጊዜ ተጠናቀው ወደ አገልግሎት እንዲገቡ የማድረግ ሥራ መሰራቱን ኢንጅነር አሸብር ተናግረዋል። የፕሮጀክቶችን ክትትል ዲጂታል በሆነ የአሰራር ሥርዓት ማዘመን መቻሉን የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈፃሚው ከፕሮጀክቶች የሚገኙ ትርፍ ምርቶችን ወደ ገቢ ለመቀየር ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በበጀት ዓመቱ ዓለም አቀፍ ዕውቅና ካላቸው የሲስተም ኦፕሬተሮች ጋር በጥገና እና ኦፕሬሽን ሥራዎች ላይ በትብብር ለመስራት የሚያስችሉ አሰራሮች መዘርጋታቸውን አንስተዋል። ሠራተኞችን በውስጥ አቅም ማብቃት መቻሉ እና የመለዋወጫ አቅርቦት በተለያዩ አማራጮች እንዲገዙ መደረጉ እንዲሁም ቆመው የነበሩ ዩኒቶች ተጠግነው ሥራ መጀመራቸው በበጀት ዓመቱ የታዩ የለውጥ ሥራዎች መሆናቸውን ገልፀዋል። አንድ አጠቃላይ የኃይል መቋረጥ በግሪድ ሥርዓቱ ላይ ማጋጠሙ፣ በግዥ የአሰራር ሥርዓቶች የውሳኔ አሰጣጥ ሂደቶች ላይ ድክመት መታየቱ፣ የመቆጣጠሪያ ሥርዓቶችን የማዘመንና ወጥነት ያለው ሥራ አለመሰራቱ እና በቴክኖሎጂ የተደገፉ አሠራሮችን በተሟላ ሁኔታ መተግበር አለመቻሉ በበጀት ዓመቱ የታዩ ክፍተቶች መሆናቸውም ኢንጅነር አሸብር ተናግረዋል። በቀረበው ሪፖርት ላይ ውይይት በመካሄድ ላይ ነው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 14 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በፋርማሲስት 1ኛ እና 2ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር በቁጥር ኢ.ኤ.ኃ/8.4/215/17 ሰኔ 05 ቀን 2017 ዓ.ም የውጪ ማስታወ
+2
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በፋርማሲስት 1ኛ እና 2ኛ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር በቁጥር ኢ.ኤ.ኃ/8.4/215/17 ሰኔ 05 ቀን 2017 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ በዚህም መሰረት ስም ዝርዝራችሁ ከላይ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ ሐምሌ 18 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 7፡30 የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ ብረታብረት ፊትለፊት በሚገኘው የድርጅቱ ዋና መ/ቤት የስብሰባ አዳራሽ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡

የገፈርሳ-ሙገር የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር የማሻሻያ ፕሮጀክት ከ86 በመቶ በላይ ተጠናቀቀ ....///.... የገፈርሳ - ሙገር ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር የማዘመን ሥራ ከ86 በመቶ በላይ መጠናቀቁን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ አንድ ሪጅን መምሪያ አስታወቀ። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ደረጀ ገዛኸኝ እንዳስታወቁት መስመሩ ለረጅም ዓመት አገልግሎት በመስጠቱ  በተደጋጋሚ ለሚከሰት የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ ምክንያት በመሆኑ ነባሩን በአዲስ ኮንዳክተር የመቀየር ሥራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል:: በ1975 ዓ.ም ለሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካው ኃይል ለማቅረብ የተዘረጋው የገፈርሳ-ሙገር የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር በአሁኑ ወቅት ለደርባና ሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካዎች እንዲሁም በአካባቢው ለሚገኙ ወረዳዎች አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። ቀደም ሲል እስከ ሐበሻና ዳንጎቴ ሲሚንቶ ፋብሪካዎች ድረስ አገልግሎት ይሰጥ የነበረው ይህ መስመር፣ በእርጅና ምክንያት ያጋጥመውን ችግር መቅረፍ የሚያስችል የማሻሻያ ሥራ እየተከናወነለት ነው። እንደ አቶ ደረጀ ገለፃ የማሻሻያ ሥራው አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ የፋብሪካዎችን ምርታማነት ለማሳደግ ያግዛል። አጠቃላይ ርዝመቱ 80 ኪሎ ሜትር እና 242 የታወር ብዛቶች ያሉት የገፈርሳ-ሙገር ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል መስመር የማሻሻያ ሥራ በሦስት ምዕራፎች ተከፍሎ የሚከናወን መሆኑንና ከዚህ ውስጥ 70 ኪሎ ሜትር ያህሉን ማጠናቀቅ እንደተቻለ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 14 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ማህበሩ የኢንዱስትሪ ሠላም እንዲፈጠር ከተቋሙ የሥራ አመራር ጋር በትብብር ይሰራል ‎....///.... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረታዊ የሠራተኛ ማህበር የኢንዱስትሪ ሠላም እንዲፈጠር ከተቋሙ የሥራ አመራር ጋር በትብብር እንደሚሰራ ገለጸ። ‎ ‎ማህበሩ ባካሄደው 11ኛ መደበኛ የምክር ቤት ስብሰባው በቀጣይ አምስት ዓመታት ማህበሩን የሚመሩ ስምንት የሥራ አስፈጻሚ አባላትን መርጧል። ‎ ‎በተጨማሪም በዋና ፀኃፊው አቶ ኃይሉ ወልዴና በሒሳብ ሹሙ አቶ ወርቅነህ ንጉሴ የቀረበውን የማህበሩን የ2018 በጀት ዓመት የኦፕሬሽንና የፋይናስ ዕቅድ ተወያይቶ አጽድቋል። ‎ ‎የማህበሩ ፕሬዝዳንት አቶ ዳንኤል ገብረ ሚካኤል እንደገለጹት ማህበሩ በቀጣይ አምስት ዓመታት የሠራተኞችን ተጠቃሚነትና ደህንነት ማረጋገጥ በሚያስችሉ ሥራዎች ላይ ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል። ‎ ‎የኢንዱስትሪ ሠላም እንዲረጋገጥ፣ የዓመታዊ ጭማሪና የማትጊያ አበልን ጨምሮ የተጠኑ ጥቅማ ጥቅሞች በሙሉ ተፈጻሚ እንዲሆኑ ከተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተቀራርቦ እንደሚሰራ ገልጸዋል። ‎  ‎ሠራተኞች በባንክ የብድር ስርዓት ቤትና መኪና መግዛት እንዲችሉ ከተለያዩ የፋይናንስ ተቋሞች ጋር በቅርበት እየተሰራ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ዳንኤል የሁለትዮሽ ስምምነቶችን በማጠናከር የሠራተኞችን ሕይወት የሚለውጡ ሥራዎችን እንደሚሰሩ ተናግረዋል። ‎ ‎ማህበሩ አንጋፉ በመሆኑ የነበሩ ችግሮችን በማረም፣ ጥንካሬዎችን በማጎልበትና አዳዲስ ዕይታዎችን በመጨመር ቀጣይነት ያለው ውጤት ለማስመዝገብ አዲሱ ሥራ አስፈጻሚ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። ምክር ቤቱ የማህበሩ አመራር የነበሩትንና የጡረታ ጊዜያቸው የደረሰውን አቶ ጌትነት መኮንን በክብር ሸኝቶ ስብሰባውን አጠናቋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 13 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

‎ማህበሩ ባለፉት አምስት ዓመታት አበረታች ተግባራትን አከናውኗል፤ ‎.....///..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረታዊ የሠራተኞች ማህበር ባለፉት አምስት ዓመታት የተቋሙንና የሠራተኞችን ጥቅም የሚያረጋግጡ አበረታች ተግባራትን ማከናወኑ ተገለጸ። ‎ የማህበሩ ሊቀመንበር አቶ ዳንኤል ኃይለሚካኤል ‎ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን በማህበሩ 5ኛ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ አቅርበዋል። ‎ ‎በተቋሙ ሥራ አመራር ቦርድ፣ በከፍተኛ ሥራ አመራር እና  በተለያዩ ውሳኔ በሚፈልጉ ኮሚቴዎች ላይ በመሳተፍ የሠራተኛውን መብትና ጥቅም፣ የሙያ ደህንነትና ጤንነት እንዲሁም የሥራ ዋስትና ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት መከናወናቸውን በሪፖርቱ ላይ አመልክተዋል። ‎ ‎የአባላትን ቁጥር በማሳደግ፣ ወጭ በመቀነስ እና ባንኮችን በማወዳደር በጊዜ ገደብ ተቀማጭ በማድረግ የማህበሩን ገንዘብ በ2012 በጀት ዓመት ከነበረበት 6 ሚሊዮን ብር ወደ 22 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር ማሳደግ መቻሉንም ገልጸዋል። ‎ ‎የፀጥታ ችግር ባለባቸው ቦታዎች የሚሰሩ ሠራተኞችን ከተቋሙና ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ጋር በመነጋገር የሥራ ላይ ደህንነታቸውን ለማስጠበቅ ሲሰራ መቆየቱንም ሊቀመንበሩ አብራርተዋል። ‎ ‎የሴት ሠራተኞችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከኢንዱስትሪ ፌዴሬሽን እና ከተቋሙ ጋር በመተባበር የማህበሩ የሴቶች ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደ ሥራ መግባቱንም ጠቁመዋል። ‎ ‎በተቋሙ ዋና መ/ቤት የሚገኘው የሠራተኛ ክበብ በውጭ አገልግሎት ሰጭ ድርጅቶች ሲመራ ከዋጋ እና ጥራት ጋር በተያያዘ በሠራተኞች ቅሬታዎች ሲነሱ እንደነበር ያስታወሱት አቶ ዳንኤል የሌሎች ተቋማትን ተሞክሮ በመውሰድ ክበቡ በሠራተኛ ማህበሩ ባለቤትነት በቦርድ እንዲመራ መደረጉን ተናግረዋል። ‎ ‎በቀጣይም በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች፣ በሪጅኖች እንዲሁም በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ አገልግሎቱን ተደራሽ ለማድረግ ከተቋሙ የሥራ አመራር ጋር በትብብር እየተሰራ ነው ብለዋል። ‎ ‎በዕለቱ የፋይናንስና የኦዲት ሪፖርት እንዲሁም የማህበሩ የተሻሻለ መተዳደሪያ ደንብ በማህበሩ ሒሳብ ሹም አቶ ወርቅነህ ንጉሴ እና በኦዲት ኮሚቴ ሰብሳቢው አቶ ተሾመ በላይ ቀርቧል። የማህበሩ ሥራ የአንድ ጊዜ ጉዳይ (event) ሳይሆን ቀጣይነት ያለው አቅም የሚፈልግ በመሆኑ፣ አደረጃጀቱ በመስፋቱ፣ የአባላት እና የፋይናንስ አቅሙ እያደገ በመምጣቱ  መተዳደሪያ ደንቡን ለማሻሻል ምክንያት መሆኑም ተገልጿል። ማህበሩ ባከናወናቸው ተግባራት በሀገር አቀፍ ደረጃ ካሉ ከ200 በላይ ማህበራት ከተመረጡትና የወርቅ ተሸላሚ ከሆኑ ሁለት ማህበራት አንዱ መሆን መቻሉን የሥራ አስፈጻሚ አባላቱ ገልጸዋል። ‎በቀረቡት ሪፖርቶች እና በተሻሻለው መተዳደሪያ ደንብ ላይ የጉባዔው አባላት የተለያዩ አስተያየቶችንና ጥያቄዎችን በማንሳት ውይይት አድርገዋል። ‎ማህበሩ በቀጣይ የታቀዱ ሥራዎችን ለመፈፀም ያሉትን ስትራቴጂካዊ የትኩረት መስኮች እና መልካም አጋጣሚዎችን እንደግብዓት በመያዝ የሠራተኛውን ሁሉን አቀፍ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መስራት እንዳለበት ጉባዔተኛው አሳስቧል። ‎ ጉባኤው የፋይናንስና የኦዲት ሪፖርቶችንና የተሻሻለውን የመተዳደሪያ ደንብ በማፅደቅ እንዲሁም የተጓደሉ የኦዲት አባላትን በመምረጥ ተጠናቋል። የማህበሩ 11ኛ መደበኛ የምክር ቤት ስብሰባ በዛሬው ዕለት የሚካሄድ ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 13 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8