fa
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

رفتن به کانال در Telegram

EEP Communication

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام EEP Communication

کانال EEP Communication (@eepcommuication) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 553 مشترک است و جایگاه 8 395 را در دسته فناوری و برنامه‌ها و رتبه 2 164 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 553 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 22 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 5 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 1 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 25.99% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.38% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 4 043 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 393 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 9 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
EEP Communication

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 23 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته فناوری و برنامه‌ها تبدیل کرده‌اند.

15 553
مشترکین
+124 ساعت
+47 روز
+530 روز
آرشیو پست ها
photo content
+9

‎መርሀ ግብሩ ተቋሙ የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ለመሆን የያዘውን ዕቅድ ለማሳካት ሚናው የጎላ ነው - ኢንጅነር አሸብር ባልቻን ‎....///...... ‎የአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ7ኛ ጊዜ "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በአንድ ጀንበር በ294 ሺ ሄክታር መሬት ላይ 700 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል መርሀ ግብር በዛሬው ዕለት እየተከናወነ ይገኛል። ‎ ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻን ጨምሮ የተቋሙ የሥራ መሪዎች፣ የማዕከላዊ ሁለት ሪጅንና የጣቢያው ሠራተኞች በሞጆ ቁጥር ሁለት ማከፋፈያ ጣቢያ የችግኝ ተከላ አከናውነዋል። ‎ ‎በመርሀ ግብሩ ላይ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻ እንደገለጹት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች ባለፉት ጊዜያት በተካሄዱ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብሮች በንቃት ሲሳተፉ ቆይተዋል፡፡ ‎ ‎በየዓመቱ የሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ተቋሙ አረንጓዴ እና ጽዱ ኢትዮጵያን በመፍጠር የታዳሽ ኃይል አማራጮችን በመጠቀም የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት እና በማስተላለፍ የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ለመሆን የያዘውን ዕቅድ ለማሳካት ጉልህ አበርክቶ እንዳለው ገልጸዋል። ‎ ‎የኃይል ማመንጫ ግድቦችን ከደለል በመከላከል የግድቦችን ደህንነት ለማስጠበቅ እንደሚያስችል የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈጻሚው ወቅቱን የጠበቀ ዝናብ እንዲኖር በማድረግ አስተማማኝ ኃይል ለማመንጨት የሚረዳ ነው። ‎ ‎ተቋሙ በማመንጫና ማከፋፈያ ጣቢያዎች በአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብሩ ትኩረት ሰጥቶ እየተከላቸው የሚገኙ ችግኞች ለምግብነት የሚውሉ መሆኑንም አንስተዋል። ‎ ‎በመሆኑም በአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብሩ ላይ ሁሉም ሠራተኛ በንቃት በመሳተፍ ለሀገራዊ ጥሪው በጎ ምላሽ እንዲሰጥ አሳስበዋል። ‎ ‎የችግኝ ተከላው ላይ የተሳተፉ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች በበኩላቸው የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራሙ ጽዱና አረንጓዴ አካባቢን በመፍጠር የምግብ ዋስትናዋን ያረጋገጠች ሀገር ለትውልድ ለማስተላለፍ ከፍተኛ ሚና አለው ብለዋል። ‎ ‎መርኃ ግብሩ የተራቆቱ አካባቢዎችን በደን ለመሸፈንና በምግብ ራስን ለመቻል ጉልህ ሚና ያለው መሆኑን በመረዳት ችግኞቹን ከመትከል ባለፈ በመንከባከብም ሁሉም ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ ገልጸዋል። ‎ ‎በተመሳሳይ የተቋሙ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ከሞጆ ቁጥር ሁለት ማከፋፈያ ጣቢያ በተጨማሪ በቦሌ ለሚ፣ በቢሾፍቱ ቁጥር ሦስት እና በሁሉም የኃይል ማመንጫ እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የአረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 24 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

በመትከል ማንሰራራት ....///..... ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ አንድ ሪጅን የሥራ መሪዎች እና ሠራተኞች በለገጣፎ እና አያት ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ከ500 በላይ አገር በቀል ችግኞች
+9
በመትከል ማንሰራራት ....///..... ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ አንድ ሪጅን የሥራ መሪዎች እና ሠራተኞች በለገጣፎ እና አያት ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ከ500 በላይ አገር በቀል ችግኞችን ተክለዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 11 ቀን 2017 ዓ.ም

የተቋሙ የሥራ መሪዎች በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ ተሳተፉ ......///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ መሪዎች"በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር 7 መቶ ሚሊየን ችግኞችን ለመትከል እየተካሄደ ባለው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ ተሳትፈዋል። የተቋሙ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ባለፉት ዓመታት በተከናውኑ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብሮች ላይ በንቃት ሲሳተፉ የቆዩ ሲሆን በዛሬው ዕለትም በተለያዩ የተቋሙ ሥራ ቦታዎች ላይ አሻራቸውን አሳርፈዋል። በቢሾፍቱ ቁጥር 3 ማከፋፈያ ጣቢያ በተካሄደው የችግኝ ተካላ ላይ የተሳተፉት በተቋሙ የኢትዮ ፓወር አካዳሚ ዳይሬክተር ወንድወሰን ካሳ (ዶ/ር) እንደገለፁት የተቋሙ አመራርና ሠራተኞች ንቅናቄው ከተጀመረ ጊዜ ጀምሮ ባለፉት ዓመታት በተለያዩ አካባቢዎች ችግኞችን በመትከል ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን ሲወጡ ቆይተዋል። በዛሬው ዕለት በተቋሙ የተካሄደው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር እንደ ሀገር የተያዘውን ዕቅድ ከማሳካት ባለፈ ተቋሙ ከአረንጓዴ ኢኮኖሚ ስትራቴጂ የተቀዳ  የታዳሽ ኃይል አማራጮችን ለመጠቀም  እየሰራ ላለው ሥራ አጋዥ ስለመሆኑም ጠቁመዋል። የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች በመርሃ ግብሩ ላይ መሳተፋቸው ለሠራተኛው አርአያ ይሆናል ያሉት ዳይሬክተሩ የተቋሙ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች በታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ላይ እንዳደረጉት ርብርብ ሁሉ በአረንጓዴ አሻራ ላይ የመሪነት ሚና በመያዝ ማስቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል። በተቋሙ የጀኔሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ የቴክኒካል ድጋፍ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ዮናስ ተስፋዬ በበኩላቸው የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብሩ በሀገሪቱ የሚገኙ የኃይል ማመንጫ ግድቦችን ከጎርፍና ከደለል በመከላከል ለረጅም ዓመት እንዲያገለግሉ ያደርጋል ብለዋል። ከዚህ በተጨማሪም የአካባቢ ስነ- ምህዳርን በማመዛዘን ወደ ግድቦች በቂ የውሃ ፍሰት እንድኖር በማድረግ ማመንጫ ጣቢያዎች የሚጠበቅባቸውን የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያመርቱ ለማድረግ ሚናው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል። በተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን እንደተናገሩት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ የውሃ አካላት እንዲያገግሙ በማድረግ ግድቦች የውሃ እጥረት እንዳይገጥማቸው ያግዛል። ከዚህ በፊት እንደ ሀገር የተከናወኑ የችግኝ  ተከላ ሥራዎች በግድቦች የውሀ አያያዝ ላይ ለውጥ ማምጣቱን በማስታወስ ይህም የተቋሙ ማመንጨት አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ እንዲሄድ አስችሏል ብለዋል። እንደ አቶ ሞገስ ገለፃ የአረንጓዴ አሻራው ሥነ ምህዳርን በመጠበቅ የተቋሙን የሥራ ቦታዎች ለኑሮ ምቹ  ከማድረግ ባለፈ የምግብ ዋስትናዋን በማረጋገጥ በኩል የራሱን አስተዋፅዖ እያበረከተ ይገኛል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተሳተፉት የሴቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ እና የፀረ ሙስናና ሥነ ምግባር መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ደረጀ አጥናፌ በሀገራዊ ንቅናቄው ላይ መሳተፋቸው እንዳስደሰታቸው ገልፀው መርሃ ግብሩ ለቀጣይ ትውልድ ፅዱና አረንጓዴ ኢትዮጵያን ለማስተላለፍ ይረዳል ብለዋል። የቢሾፍቱ ቁጥር 3 ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሲሳይ አይቸው በበኩላቸው በጣቢያው ከዚህ በፊት ምንም አይነት ችግኝ እንዳልነበረ አንስተዋል። ከዚህ በፊት በተከናወኑ ተመሳሳይ መርሃ ግብሮች ከ1ሺህ በላይ ችግኞችን በመትከል የግቢውን የአየር ንብረት መቀየር የተቻለ ሲሆን በዛሬው ዕለትም ለምግብነት የሚውሉ ችግኞች መተከላቸውን ገልፀዋል። መርሀ ግብሩ ለተቋሙ የሚኖረውን ሚና በመረዳት ሠራተኛውና አመራሩ ለስኬቱ የድርሻውን እንዲወጣ እና ችግኞቹን ከመትከል ባለፈ በመንከባከብ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መሰራት እንዳለበት የሥራ ኃላፊዎቹ አሳስበዋል።  በዕለቱ በዋና መስሪያ ቤቱ የሚገኙ ከፍተኛ የሥራ መሪዎች በሞጆ፣ ቦሌ ለሚና ቢሾፍቱ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ካከሄዱት የችግኝ ተከላ ሥራ በተጨማሪ በኃይል ማመንጫዎች፣ በሌሎች ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና በሪጅን ቢሮዎች እየተከናወነ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 24 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

የችግኝ ተከላ እየተካሄደ ነው .......///........ በዛሬው ዕለት በመትከል ማንሰራራት በሚል መሪ ቃል በሃገር አቀፍ ደረጃ ለ7ኛ ጊዜ የችግኝ ተከላ መርሃግብር እየተካሄደ ይገኛል። በቦሌ ለሚ
+1
የችግኝ ተከላ እየተካሄደ ነው .......///........ በዛሬው ዕለት በመትከል ማንሰራራት በሚል መሪ ቃል በሃገር አቀፍ ደረጃ ለ7ኛ ጊዜ የችግኝ ተከላ መርሃግብር እየተካሄደ ይገኛል። በቦሌ ለሚ ቁጥር ሁለት ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በተካሄደው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግ እና ኮንትራክሽን ዘርፍ ም/ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነን ጨምሮ የዘርፍ ስራ አስፈፃሚዎች እና ዳይሬክተሮች በመርሃ ግብሩ ላይ ተሳትፈዋል። በአንድ ጀንበር 700 ሚሊዮን የችግኝ ተከላ መርሃግብር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ዛሬ ጠዋት በጅማ ከተማ በአባ ጅፋር ቤተ መንግስት በይፋ አስጀምረውታል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 24 ቀን 2017 ዓ.ም

በመትከል ማንሰራራት! .....///...... የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር በአገር አቀፍ ደረጃ ለ7ኛ ጊዜ "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በአንድ ጀንበር 700 ሚሊዮን ችግኝ የመትከል መርሀ ግብር በዛሬው ዕለት እየተካሄደ ይገኛል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ መሪዎች በሦስት ቦታ ማለትም በቦሌ ለሚ፣ በቢሾፍቱ ቁጥር ሦስት እና በሞጆ ቁጥር ሁለት ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ አሻራቸውን የሚያኖሩ ይሆናል። በተመሳሳይ በኃይል ማመንጫ እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች እንዲሁም በፕሮጀክቶች የሚገኙ የተቋሙ ሠራተኞችም በየአካባቢያቸው ችግኞችን በመትከል የሀገራዊ መርሀ ግብሩ ተሳታፊ ይሆናሉ። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 24 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

ማከፋፈያ ጣቢያው ተጨማሪ ደንበኞችን የማስተናገድ አቅም አለው .....///..... የራይቱ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ከደንበኞች የሚቀርቡ የኃይል ጥያቄዎችን የመመለስ አቅም እንዳለው የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ይድነቃቸው ሙሉጌታ አስታወቁ፡፡ የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ እንደገለፁት ጣቢያው 63 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለው አንድ ትራንስፎርመር፣ ሦስት ሻንት ሪያክተር እንዲሁም አራት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች አሉት፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው ከመልካ ዋከና ማመንጫ ጣቢያ ኃይል ተቀብሎ በባለ 230 ኪሎ ቮልት ለጎዴ ማከፋፈያ ጣቢያ እንዲሁም በባለ 33 ኪሎ ቮልት ለምስራቅ ባሌ ዞን እና ለሶማሌ ክልል የተወሰኑ አካባቢዎች ኃይል እንደሚያቀርብ ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡ በአካባቢው የኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር አነስተኛ በመሆኑ ማከፋፈያ ጣቢያው መጫን ከሚችለው 50 ሜጋ ዋት ውስጥ ጥቅም ላይ እየዋለ ያለው 25 በመቶ እንደማይደርስ ነው አቶ ይድነቃቸው የተናገሩት። ማከፋፈያ ጣቢያው ተጨማሪ የኃይል ፍላጎት የማስተናገድ አቅም እንዳለው የገለፁት ሥራ አስኪያጁ በአካባቢው ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋት በቂ እና ያልተቆራረጠ ኃይል ለማቅረብ ጣቢያው ዝግጁ መሆኑንም አረጋግጠዋል፡፡ በማከፋፈያ ጣቢያው የኦፕሬሽን ሠራተኛ የሆኑት አቶ ሽታው ኑርልኝ በበኩላቸው ጣቢያው በምስራቅ ባሌ ዞን ስር ለሚገኙት ለጊኒር ከተማና አካባቢው፣ ለራይቱና ዳዌ ሰረር ወረዳዎችና በስራቸው ለሚገኙ የገጠር ቀበሌዎች እንዲሁም ለሶማሌ ክልል የተወሰኑ ቦታዎች ኃይል እያቀረበ ይገኛል፡፡ በጣቢያው ያሉት አራት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች እስከ 25 ሜጋ ዋት የመሸከም አቅም ቢኖራቸውም አገልግሎት እየሰጡ በሚገኙት ሦስት ወጭ መስመሮች እየቀረበ ያለው ኃይል ግን 3 ነጥብ 34 ሜጋ ዋት ብቻ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ጣቢያው ተጨማሪ ደንበኞችን የማስተናገድ አቅም እንዳለው በመረዳት የሚመለከተው አካል በአካባቢው ኢንቨስትመንትን በመሳብ የኃይል ተጠቃሚዎችን ቁጥር ማሳደግ እንደሚጠበቅበትም አስገንዝበዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የራይቱ የደንበኞች አገልግሎት መስጫ ማዕከል ሥራ አስኪያጅ አቶ ደበበ ዳዲ እንደገለፁት የራይቱ ማከፋፈያ ጣቢያ ያለውን አቅም ለመጠቀም የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡ በዚህም የኃይል ተጠቃሚ ደንበኞችን ለመሳብ ከመስተዳደር አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ስለመሆኑም አስታውቀዋል፡፡ የራይቱ ማከፋፈያ ጣቢያ ለሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ለከተሞች መስፋፋት፣ ለመሰረተ ልማቶች መስፋፋት እና ለማህበረሰቡ የአኗኗር ዘይቤ መሻሻል ከፍተኛ ሚና እየተወጣ ይገኛል፡፡ በምስራቅ ባሌ ዞን የሚገኘው ይህ ማከፋፈያ ጣቢያ ከ2007 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 11 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

ሪጅኑ በበጀት ዓመቱ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ስኬታማ ሥራዎችን አከናዉኗል …///… በሪጂኑ ባሉ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች የተቀናጀ እና የተናበበ ሥራ በመሰራቱ በበጀት ዓመቱ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ማስቻሉን የሰሜን ምስራቅ ሪጅን ሁለት አስታወቀ፡፡ የሪጂኑ ዳይሬክተር አቶ ሐሰን ሙሃመድ እንደተናገሩት ለረጅም ዓመታት ሲያገለግሉ የቆዩ መስመሮችን ወደ ጂ.አይ.ኤስ. ዘመናዊ የመቆጣጠሪያ ስርዓት መቀየር፣ የሲቪል እና የኤሌክትሮ መካኒካል፣ የፍተሻና ጥገና ስራዎች እንዲሁም የመስሪያ ቁሶችን የማሟላት ስራዎች ተከናውነዋል፡፡ በተጨማሪም በመረጃ አያያዝና ኦፕሬሽን ዙሪያ ለሠራተኞች የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች እንዲሁም የመሠረተ ልማት ስርቆትን ለመከላከል ከክልሉ የፀጥታ አካላት ጋር የወይይት መድረኮችን ማካሄድ በበጀት ዓመቱ ታቅደው ሙሉ ለሙሉ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት ናቸው፡፡ ይህም በሪጅኑ የተቀናጀና የተናበበ የአሰራር ስርዓት ከመፍጠሩም በተጨማሪ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲቀርብ አስችሏል፡፡ በየጊዜው እያደገ የመጣው የኃይል ፍላጎት ለማሟላት በቀጣይ 2018 በጀት ዓመት የሰመራ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን አቅም የማሳደግ ሥራ እንደሚከናወን የጠቆሙት አቶ ሐሰን ሪጅኑ እያንዳንዳቸው 230 ኪሎ ቮልት መጠን ያላቸውን  የሰመራ፣ ዲቼቶ እና አፍዴራ ማከፋፈያ ጣቢያዎችን እና ከ436 ኪሎ ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸውን የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች እንዲሁም 988 የብረት ምሰሶዎችን ያስተዳድራል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 21 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ጣቢያው በአማካኝ 220 ሜጋ ዋት ኃይል ያቀርባል ….///…. ለተለያዩ ደንበኞች በቀን በአማካኝ እስከ 220 ሜጋ ዋት የሚደርስ ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ የለገጣፎ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ አስታወቀ። የጣቢያው ኃላፊ አቶ ታምራት ፎጊ እንደተናገሩት ጣቢያው በቀን ከሚያቀርበው 220 ሜጋ ዋት ውስጥ 216 ነጥብ ስምንት ያህሉን በአካባቢው ለሚገኙ የንግድ ተቋማትና ነዋሪዎች በማቅረብ ላይ ይገኛል። ቀሪው ሦስት ነጥብ ሁለቱን ሜጋ ዋት ደግሞ በአቅራቢያው ለሚገኘው ኤም ኤን ኤስ የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ በየቀኑ እያቀረበ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። ጣቢያው ሰባት ባለ 230 ኪሎ ቮልት ገቢ መስመሮች እንዲሁም ወደ ደብረብርሃን እና አያት ጣፎ የሚወጡ ሁለት ባለ 132 ኪ.ቮ ከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን ጨምሮ ሃያ ሁለት የተለያዩ ኪ.ቮ መጠን ያላቸው ወጪ መስመሮች ያሉት መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል፡፡ የጣቢያውን አቅም ይበልጥ ለማጎልበት አንድ ተጨማሪ ባለ 125 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመር ለመትከል የሲቪል ስራ እየተከናወነ ይገኛል። ጣቢያው በአጠቃላይ ስድስት ትራንስፎርመሮችን በመጠቀም 24 ሰዓት አገልግሎት በመስጠት ላይ ነው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 18 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

የሀገሪቱን የልማት ዕቅድ ለማሳካት የፕሮጀክቶች አፈፃፀም ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ይገባል ….///…. የኢትዮጵያን የ2018 በጀት ዓመት የልማት ዕቅድ ከግብ ለማድረስ የፕሮጀክቶች አፈፃፀም ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል  አስታወቀ፡፡ የተቋሙ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች በሀገራዊ የ2018 በጀት ዓመት የልማት ዕቅድ ላይ ውይይት አካሂደዋል። የበጀት ዓመቱን ሀገራዊ የልማት ዕቅድ ያቀረቡት በተቋሙ የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነ እንደገለፁት ዕቅዱ ዓለም አቀፋዊ፣ አህገራዊና ቀጣናዊ የኢኮኖሚ አዝማሚያዎችን እና የሀገሪቱን የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምን መነሻ በማድረግ የተዘጋጀ ነው። በውይይቱ ላይ በማክሮ ኢኮኖሚ፣ በመሠረተ ልማት ግንባታ፣ በማህበራዊ ልማትና የህዝብ አገልግሎት፣ በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ፣ በሠላም፣ በፍትህ፣ በውጭ ግንኙነት እና ዲፕሎማሲ ዘርፎች ላይ ለማከናወን የተያዙ ሀገራዊ ዕቅዶችን በዝርዝር አቅርበዋል። በዚህም በበጀት ዓመቱ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመቀነስ እና ሀገር በቀል ኢኮኖሚ ተኪ ምርቶች ላይ ትኩረት በማድረግ ኢኮኖሚው ላይ ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት እንደሚሰራ ገልፀዋል። ኢንጂነር ውድነህ እንደጠቀሱት በበጀት ዓመቱ የአምራች ኢንዱስትሪዎችንና የቱሪዝም ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋት፣ የወጭ ንግድን ለማሳደግ፣ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ሥራ ስምሪትን በማስፋፋት ለዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር፣ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን አስተዳደርና አፈፃፀም ለማሻሻል፣ የኤሌክትሪክ ኃይል ብክነት ቅነሳ እና የገቢ ግብር አሰባሰብ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል፡፡ በበጀት ዓመቱ በገበያ ላይ የተመሰረተ የወለድ ምጣኔ ሥርዓት በመተግበር፣ የግብርና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በማሳደግ እንዲሁም የገበያ መሰረተ ልማቶችን በማስፋፋት የዋጋ ግሽበትን ወደ ነጠላ አሃዝ ለማውረድ መታቀዱንም አስታውቀዋል፡፡ የወጭ ንግድን ለማሳደግ የኢነርጂ ዘርፉ የራሱ አበርክቶት እንደሚኖረውና በዚህም በተያዘው በጀት ዓመት ከኃይል ሽያጭ 426 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት መታቀዱን ጠቁመዋል፡፡ ኢትዮጵያ በቀጣናውና በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላትን ተሰሚነት ለማሳደግ እና ሉዓላዊ ጥቅሟን ለማስጠበቅ እንደምትሰራ ገልፀው ከተለያዩ ሀገራት ጋር እያደረገች ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል  ትስስርም በዲፕሎማሲ ሥራዎች ላይ አወንታዊ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው አመልክተዋል፡፡ በዕለቱ ከዋጋ ግሽበትና የኑሮ ውድነት፣ ብሔራዊ መግባባትን ከመፍጠር፣ ከመሰረተ ልማት ግንባታ ፍትሃዊነት፣ ከግብርና ግብዓት አቅርቦት፣ ከሰላምና ፀጥታ፣ ከኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት፣ ከፕሮጀክት አፈፃፀም፣ ከመንግሥት ሠራተኛ የገቢ ግብር አተገባበር፣ ከፍትህ ሥርዓት እና ከመኖሪያ ቤት አቅርቦት ጋር የተያያዙ አስተያየቶችና ጥያቄዎች ከተሳታፊዎቹ ቀርበዋል፡፡ ለተነሱ አስተያየቶችና ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደተናገሩት ውይይቱ ሠራተኛውን የዕቅዱ ባለቤት በማድረግ ወደ ውጤት ለመቀየር ያስችላል፡፡ የፕሮጀክቶችን አፈፃፀም ለማሻሻል ውስጣዊ ችግሮችን በመፍታት በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባ ያነሱት አቶ ሙላት የመኖሪያ ቤት አቅርቦት ችግሮችን ለመፍታት መንግሥት የግል አልሚዎችን በማሳተፍ እየሰራ ስለመሆኑም አስረድተዋል፡፡ በተቋሙ የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነ በበኩላቸው በመንግሥት ለተያዙ ዕቅዶች የሚያስፈልገውን የኤሌክትሪክ ኃይል በአግባቡ ለማቅረብ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ትልቅ እፎይታን እንደሚሰጥ ተናግረዋል፡፡ የግል ባለሃብቱ በኃይል ልማት ዘርፉ ላይ እንዲሳተፍ የሚያደርግ አሰራር መዘርጋቱ የኤሌክትሪክ አቅርቦቱን ለማሳደግ እንደሚረዳም ነው አቶ ውድነህ የተናገሩት፡፡ የኑሮ ውድነትን ለማቃለል መንግሥት ምርታማነትን ማሳደግ እና ዋጋ ማረጋጋት ላይ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራም አስታውቀዋል፡፡ በተቋሙ የኮርፖሬት ገቨርናንስና ኮምፕሊያንስ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደጉማ ነዳ እንደተናገሩት በበጀት ዓመቱ የሚከናወኑ ሥራዎችን በውስጥ የፋይናንስ አቅም ለመሸፈን የገቢ ግብርን በአግባቡ መሰብሰብ ያስገድዳል፡፡ እንደ ሀገር የተያዘውን የልማት ዕቅድ ለማሳካት በፕሮጀክቶች አስተዳደርና አፈፃፀም ላይ በዕውቀት ላይ የተመሰረተ ክትትልና ቁጥጥር በማድረግ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባም የሥራ ኃላፊዎቹ አሳስበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 17 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

በ2018 ሀገራዊ የልማት ዕቅድ ላይ ውይይት እየተካሄደ ነው ....///... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች በ2018 በጀት ዓመት ሀገራዊ የልማት ዕቅድ ላይ ውይይት እያካሄዱ ነው። በውይይቱ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻ እንደገለፁት ውይይቱ እንደሀገር በበጀት ዓመቱ ለማከናወን የታቀዱ ሥራዎችን እና ዕቅዱን ለማሳካት ከሰራተኛው የሚጠበቀውን ሚና ለማሳወቅ ያለመ ነው። ተቋሙ እንደ ሀገር የተያዙ ዕቅዶችን በማሳካት በኩል ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው በመረዳት ሁሉም የሥራ መሪና ሠራተኛ የተሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት እንደሚኖርበት ዋና ሥራ አስፈፃሚው አሳስበዋል። በአሁኑ ወቅት በበጀት ዓመቱ እንደ ሀገር በሁሉም ዘርፎች ለማከናወን የተያዘው ዝርዝር የዕቅድ ሰነድ እየቀረበ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 17 ቀን 2017 ዓ.ም