en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 695 subscribers, ranking 8 036 in the Technologies & Applications category and 2 171 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 695 subscribers.

According to the latest data from 03 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 143 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 27.84%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.00% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 369 views. Within the first day, a publication typically gains 2 511 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 04 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 695
Subscribers
-124 hours
+47 days
+14330 days
Posts Archive
ፆታ ተኮር ጥቃትን መከላከል የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት ሊሆን ይገባል ……////……. ፆታ ተኮር ጥቃትን መከላከል የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት ሊሆን እንደሚገባ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሴቶች ሕፃናትና ወጣቶች ጉዳይ መምሪያ አስታወቀ፡፡ መምሪያው ከሪጅኖች፣ ከኃይል ማመንጫዎች  እና ከዋናው መስሪያ ቤት ለተውጣጡ ሠራተኞች በሥርዓተ ፆታ እና ልማት እንዲሁም በፆታ ተኮር ጥቃት ላይ ያተኮረ ሥልጠና በተቋሙ መሰብሰቢያ አዳራሽ ሰጥቷል። ሥልጠናውን በንግግር ያስጀመሩት የሴቶች ሕፃናትና ወጣቶች ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ እንደገለፁት ፆታ ተኮር ጥቃቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚፈፀሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ናቸው፡፡ የሴቶችን መብት ለማስከበር በርካታ የህግና የፖሊሲ ማዕቀፎች በሥራ ላይ እንደዋሉ የጠቆሙት ዳይሬክተሯ ይሁን እንጂ ከጊዜ ወደ ጊዜ በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ፆታዊ ጥቃቶችን በሚፈለገው ደረጃ ማስቆም እንዳልተቻለ ተናግረዋል፡፡ የሥልጠናው ተሳታፊዎች በአካባቢያቸውና በሥራ ቦታቸው ላይ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ በመገንዘብ ፆታ ተኮር ጥቃቶችን እንዲከላከሉና የግንዛቤ ፈጠራ ሥራዎችን እንዲያከናውኑ ዕድል ይሰጣል ብለዋል፡፡ ሥልጠናው ፆታ ተኮር ጥቃት የሚደርስባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የህግ፣ የሥነ-ልቦና እና ጤና ነክ ድጋፎችን እንዲያገኙ የማመቻቸት ሥራ እንዲሰሩ እንደሚያግዛቸውም ነው ያብራሩት፡፡ እንደ ዳይሬክተሯ ገለፃ የሥልጠናው ተሳታፊዎች ሥርዓተ ፆታ ከልማት ጋር ያለውን ትስስርና የሚያመጣውን ሁለተናዊ ዕድገት በመረዳት የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የግንዛቤ ፈጠራ ሥራዎችን ይሰራሉ፡፡ በተቋሙ የካሳ ጉዳዮች አስተዳደር ሥራ አስኪያጅ አቶ ደረጄ አጥናፌ በሥልጠናው ላይ እንደገለፁት ጥቃት ሰዎች ሰው በመሆናቸው ብቻ የተጎናፀፏቸውን እና በተለያዩ ዓለም አቀፍ ሰነዶች እውቅና የተሰጣቸውን ሰብዓዊ መብቶች የሚጥስ ድርጊት ነው፡፡ ፆታ ተኮር ጥቃት በሰዎች ላይ አካላዊ፣ ወሲባዊ እና ሥነ-ልቦናዊ ችግሮችን የሚያስከትል ፆታን መሰረት አድርጎ የሚፈፀም የኃይል ድርጊት መሆኑንም ነው የገለፁት፡፡ እንደ አቶ ደረጄ ገለፃ ያልተፈለገ እርግዝና፣ የአባላዘር በሽታ፣  የቤተሰብ ግጭት፣ አካላዊ እና ሥነ ልቦናዊ ጉዳቶች እንዲሁም ሞት የፆታ ተኮር ጥቃት ውጤቶች ናቸው፡፡ መንግሥትም ሆነ ተቋማት ፆታ ተኮር ጥቃቶች ላይ የተደነገጉ ህጎችን ወደ ተግባር በመቀየር ውጤታማ ሥራ መስራት እንደሚጠብቅባቸው አፅዕኖት ሰጥተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 15 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቱ ኃይል ማመንጨት ጀመረ .........///........ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በሦስት ተርባይኖች ኃይል ማመንጨት ጀምሯል። የፕርጀክቱን የግንባታ ሂደት እና የኃይል ማመንጨት የመጀመር ሥራ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰመሪታ ሰዋሰው፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ፣ የደንማርክ አምባሳደር ሚስተር ሱነ ክሩግስትረፕ፣ የአውሮፓ ህብረት እና ፕሮጀክቱን ፋይናንስ የሚያደረገው የዳኒሽ ባንክ ተወካዮች ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ላይ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰመሪታ ሰዋሰው እንደተናገሩት ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን ለማሳደግ እና የኃይል ስብጥርን ለማመጣጠን ትኩረት ሰጥታ እየሰራች ነው። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትም ኢትዮጵያ የኃይል ስብጥር ላይ ትኩረት ለማድረጓ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ የአውሮፓ ህብረትና የደንማርክ መንግስትም በኃይል ልማት ዘርፉ ላይ እያደረጉት ካለው ድጋፍ ባለፈ ለሌሎች መሠረተ ልማቶች ድጋፍ በማድረግ ለሀገሪቱ እድገት የበኩላቸውን እየተወጡ ይገኛሉ ነው ያሉት። የትብብር ሥራው ታዳሽ ኃይል ወደ ግሪድ በማስገባት የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለማሳደግ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት ተወካይ ሚስተር ቪንሰንት ቪያዉድ በበኩላቸው አሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ኢትዮጵያ ለታዳሽ ኃይል ልማት ለሰጠችው ትኩረት አመላካች መሆኑን ገልፀዋል። በቀጣይ ኢትዮጵያ በኃይል ልማት ዘርፉ ለምታከናውናቸው ሥራዎች ህብረቱ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በኢትዮጵያ የደንማርክ አምባሰደር ሚስተር ሱነ ክሩግስትረፕ እንደተናገሩት የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በኢትዮጵያና በደንማርክ መካከል ያለውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግረዋል ብለዋል፡፡ ሀገራቸው በንፋስ ኃይል ማመንጫ ያላትን ተሞክሮ ለኢትዮጵያ ብሎም ለአፍሪካ እያካፈለች እንደምትገኝ ገልፀው የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ላይ ያደረገችው ድጋፍም ለዚሁ ማሳያ መሆኑን ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማምጣት የኃይል መሠረተ ልማት ቁልፍ መሳሪያ እንደሆነ  በመገንዘብ የደንማርክ መንግስት  ለፕሮጀክቱ ካደረገው የመዋዕለ ነዋይ ድጋፍ በተጨማሪ የግንባታ ሥራውን በቅርበት ሲከታተል እንደነበር አስታውሰዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት በሀገሪቱ ያለውን የኃይል ተደራሽነት ለማስፋፋት በርካታ ፕሮጀክቶች እየተገነቡ ይገኛሉ። የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ማመንጨት እንዲጀምር የአውሮፓ ህብረትና የደንማርክ መንግስት ላደረጉት ድጋፍም ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ ጉብኝቱ ለፕሮጀክቱ ድጋፍ ያደረጉ አካላት ፕሮጀክቱ የደረሰበትን የግንባታ እና የመጀመሪያውን ኃይል የማመንጨት ሂደት በማየት ለቀሪ ሥራዎች አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ያለመ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡ ጉብኝቱ በቀጣይ በአካባቢው ለመገንባት ለታሰበው ተመሳሳይ ፕሮጀክት ድጋፍ የሚያደርጉበትን ዕድል እንደሚፈጥርም ዋና ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል፡፡ በዕለቱ ፕሮጀክቱ ስለደረሰበት ሂደትና ስለተከናወኑ ዋና ዋና ሥራዎች እንዲሁም በግንባታ ሂደት እያጋጠሙ ስላሉ ችግሮች በፕሮጀክቱ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ገለፃ ተደርጓል። ፕሮጀክቱ ከሚኖሩት 29 ተርባይኖች መካከል ዛሬ ሦስቱ ኃይል ማመንጨት የጀመሩ ሲሆን በቀጣይም ሌሎቹ ተርባይኖች ኃይል ወደማመንጨት ሥራ እንደሚገቡ ይጠበቃል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስና ትክክለኛ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 14 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

photo content
+9

የዋና መሥሪያ ቤት ህንፃ ግንባታ ዓለም አቀፍ ጨረታ ወጣ .......///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአዲስ አበባ ሜክሲኮ አካባቢ ለሚያስገነባው ባለ 66 ወለል ዘመናዊ የዋና መሥሪያ ቤት ሕንፃ ዓለም አቀፍ  ጨረታ አውጥቷል። አጠቃላይ ግንባታው በ20 ሺህ 792 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የሚያርፍ ሲሆን ሲጠናቀቅ 208 ሺህ 724 ካሬ ሜትር የሆነ አጠቃላይ የወለል ስፋት እና 345 ነጥብ 5 ሜትር ከፍታ ይኖረዋል። በአዲስ አበባ የፋይናንስ ማዕከል ተብሎ በተለየው በሜክሲኮ የሚገነባው ይህ ግዙፍ ሕንፃ ዲዛይኑ በተቋሙ እና በአማካሪ ድርጅት በኩል የተዘጋጀ ሲሆን አሸናፊው ተቋራጭ ግንባታውን ብቻ የሚያከናውንበት የውል ዓይነት ነው። የወጣው ጨረታ የግንባታውን የስራ ዝርዝር እና ግንባታውን ለማከናወን ተቋራጮች ሊያሟሉት የሚገባውን የፋይናንስና የቴክኒክ መስፈርት በዝርዝር የሚያመለክት ነው። በዚህ መሰረት ተጫራቾች ያለፉትን አምስት ዓመታት የኦዲት ሪፖርታቸውን እንዲሁም በአማካይ ቢያንስ 230 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ዓመታዊ ገቢ ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸው የጨረታ ሰነዱ ያመለክታል። ከቴክኒክ አንፃር ደግሞ ቢያንስ ለ10 ዓመታት በግንባታ ላይ ልምድ ያላቸውና እያንዳንዳቸው ቢያንስ 370 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ዋጋ ያላቸው ሦስት ፕሮጀክቶችን በተሳካ ሁኔታ ያጠናቀቁ መሆን ይኖርባቸዋል። የንድፍ እና የግንባታ ክትትል አማካሪ በመሆን ዳር አል-ሃንዳሳ ነው። የግንባታውን ወጪ በተለያዩ የፋይናንስ አማራጮች ለመሸፈን ተቋሙ አማራጮችን እያየ  ሲሆን የጨረታው ሂደት እንደተጠናቀቀ አጠቃላይ የግንባታው ዋጋ የሚገለጽ ይሆናል። በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፆች  ስለግንባታው ወጪና ሌሎች መረጃዎች የወጡት መረጃዎች በተቋሙ በኩል ያልወጡና የተሳሳቱ እንደሆኑ ለመግለጽ እንወዳለን። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስና ትክክለኛ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 13 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

“እንደ ሀገር ያለን ብቸኛ አማራጭ ለተጨማሪ ስኬት መትጋት ነው” ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) …///… ኢትዮጵያ እንደ ሀገር እና ህዝብ ያላት ብቸኛ አማራጭ የተገኙ ስኬቶችን በማፅናት ለተጨማሪ ድል መትጋት መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ 1፣ 2 እና 3 ሪጅኖች እና የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ሠራተኞች "የመሐሉ ዘመን" በሚል መሪ ሀሳብ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ውይይት አካሂደዋል። በመድረኩ "የመሐሉ ዘመን" ወጥመዶች እና የመሻገር ሂደቶችን የሚዳስስ ሰነድ በኮሚሽነር ዘለቀ የቀረበ ሲሆን በኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት በኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ዘርፎች የተመዘገቡ ስኬቶች፣ የድህረ ለውጡ መሰናክሎች፣ የዓለምአቀፉ የኃይል አሰላለፍ እንዲሁም በመንግስት የተወሰዱ እርምጃዎች እና የታዩ ክፍተቶችን ዳሰዋል፡፡ ስኬት ቀጣይነት ባለዉ ትጋት የማይታጀብ ከሆነ ውድቀት አይቀሬ ነው ያሉት ኮሚሽነሩ ጊዜያዊ ስኬት ብቻውን ለሀገራዊ ድል ዋስትና ሆኖ ሊቆይ እንደማይችል ገልፀው የመሐሉ ዘመን የተሟላ ስኬት ላይ ያልደረስንበት መሆኑ መታወቅ አለበት ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ በለውጥ ሂደት በርካታ ተፈጥሯዊ እና ሰው ሠራሽ ፈተናዎችን መሻገሯን የጠቀሱት ኮሚሽነሩ ድርቅ፣ ጎርፍ፣ የበረሃ አንበጣ፣ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ እንዲሁም የእርስ በርስ ግጭትና መፈናቀል ለውጡን የፈተኑ ጉዳዮች መሆናቸውን ለአብነት አንስተዋል። የሕዝብ ጥያቄዎችን በመመለስ፣ የትርክት ለውጥ በማምጣት፣ አካታች ፖለቲካዊ አጀረጃጀት እና ኢኮኖሚያዊ ሪፎርም በመተግበር ስኬት ማስመዝገብ መቻሉን ገልፀዋል። ለውጥ የአንድ ተቋም ወይም ግለሰብ ብቻ እንዳልሆነ የጠቀሱት ኮሚሽነር ዘለቀ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኃይል ልማት ዘርፉ እያከናወናቸው የሚገኙትን የለውጥ ሥራዎች ቀጣይነት ባለው መልኩ በማሳለጥ የኤሌክትሪክ አቅርቦቱን ለማሻሻል መስራት እንደሚገባው ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፋይናንስና ኃብት አስተዳደር ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ በበኩላቸዉ 55 በመቶ የደረሰውን የኤሌክትሪክ አቅርቦት ሽፋን ለማሳደግ ለኢትዮጵያ ተጨማሪ ህዳሴ እንደሚያስፈልጋት ገልፀዋል፡፡ እንደ አቶ ደመረ ገለፃ በኃይል አቅርቦት ዘርፍ ከተሰማሩ ሌሎች ተቋማት ጋር በመተባበር እና በመደጋገፍ ለላቀ ስኬት መስራት ለነገ የማይባል ጉዳይ ነው፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ በኢትዮጵያ ኢንሸስትመንት ሆልዲንግ የኢነርጂ ዘርፍ ዳይሬክተር ጌትነት መላክ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፋይናንስና ኃብት አስተዳደር ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ፣ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝን ጨምሮ ከአዲስ አበባ ሪጅኖቹ እና ከብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል የተውጣጡ ሠራተኞች እና አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡ ከዚህ በፊት ከዋና መስሪያ ቤት ሠራተኞች ጋር ተመሳሳይ ውይይት መካሄዱ የሚታወስ ነው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ኑሀ/ፍጌ ግንቦት 13 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

በተቋሙ ለሁለተኛ ጊዜ እየተካሄደ ያለዉ "የመሀሉ ዘመን" ሀገራዊ መድረክ መካሄድ  ጀመረ ........///........ በመዲናዋ የሚገኙ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ማዕከላዊ  ሪጂን 1፣ 2፣ 3 መምሪያዎች እና የብሄራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል የሚገኙ አመራሮችና ሠራተኞች "የመሀሉ ዘመን" በሚል መሪ ሀሳብ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ዉይይት ማካሄድ ጀምረዋል። ሀገራዊ መድረኩ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፋይናንስና ኃብት አስተዳደር ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ የተከፈተ ሲሆን "የመሐሉ  ዘመን" በሚል ርዕስ ስለ ለውጥ ወጥመዶች እና የመሻገር ሂደቶችን የሚዳስሰው ሰነድ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) ለውይይት ቀርቧዋል። በውይይት መድረኩ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፋይናንስና ኃብት አስተዳደር ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ፣ የኢትዮጵያ ኢንሸስትመንት ሆልዲንግ የኢነርጂ ዘርፍ ዳይሬክተር ጌትነት መላክ (ዶ/ር)፣ የዋና ስራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝን ጨምሮ ከመምሪያዎቹ እና ከብሃራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል የተውጣጡ ሠራተኞች እና አመራሮች ተገኝተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 13 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

ያለፉት ሰባት ዓመታት በርካታ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ስኬቶች የተመዘገቡበት ነው -  ተስፋሁን ጎበዛይ ….....///……... በኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት በርካታ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ስኬቶች መመዝገባቸውን  የኢፌዲሪ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ ገለፁ። ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች "መሀሉ ዘመን" በሚል መሪ ሀሳብ በመንግስት የተዘጋጀውን የመወያያ ሰነድ ያቀረቡት ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ እንደገለፁት መሀሉ ዘመን የኢትዮጵያን መነሻ፣ አሁን የደረሰችበትን ሁኔታ እና ቀጣይ መዳረሻ የሚያመላክት የሽግግር ዘመን ነው ብለዋል። ከትላንት ውድቀቶቻችንና ከዛሬ ስኬቶቻችን ተምረን ነገን የተሻለ ለማድረግ እንደ ሀገር ጠንክረን  መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል። ኢትዮጵያ በለውጥ ሂደት በርካታ ተፈጥሯዊ እና ሰው ሠራሽ ፈተናዎችን መሻገሯን የጠቀሱት ሚኒስትር ዴኤታው ድርቅ፣ ጎርፍ፣ የበረሃ አንበጣና የኮቪድ-19 ወረርሽኝ እንዲሁም የእርስ በርስ ግጭትና መፈናቀል ለውጡን የፈተኑ ጉዳዮች መሆናቸውን ለአብነት አንስተዋል። በለውጡ ዋዜማና በለውጡ ወቅት ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን እንዲሁም ስኬቶችን አብራርተው በዓለም ሀገራት የኃይል አሰላለፍ ውስጥ የኢትዮጵያ አቅም እንዴት እንዳደገና ምን ውጤት እንደመጣም ገልፀዋል። ያለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታት በርካታ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ስኬቶች የታዩበትና መዋቅራዊ ለውጥ የተደረገበት  መሆኑንም አስረድተዋል። በአሁኑ ወቅት የሕዝቡ የለውጥ ፍላጎት፣ የአመራሩ ቁርጠኝነት እና ብስለት የተሞላበት ውሳኔ ለውጡን ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገራቸውን ተናግረዋል። የሕዝብ ጥያቄዎችን በመመለስ፣ የትርክት ለውጥ በማምጣት፣ አካታች ፖለቲካዊ አጀረጃጀት እና ኢኮኖሚያዊ ሪፎርም በመተግበር ስኬት ማስመዝገብ መቻሉንም ነው የገለፁት። እንደ አቶ ተስፋሁን ገለፃ የተሳካ የህግ ማስከበር ዘመቻ፣ የፕሪቶሪያ ሥምምነት እና የህዳሴ ግድብ እያደገ ለመጣው የኢትዮጵያ አቅም አወንታዊ ሚና ተጫውተዋል። የህዳሴ ግድብ ግንባታ የማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ መድረሱ ለኢትዮጵያ የለውጥ ጉዞ ብርሃን የፈነጠቀና  በቀጣናው ሀገራት ላይም ያላትን የኃይል ሚዛን ያስጠበቀ መሆኑን ገልፀዋል። ተቋሙ በኃይል ልማት ዘርፉ ላይ እያከናወናቸው የሚገኙትን የለውጥ ሥራዎች ቀጣይነት ባለው መልኩ በማሳለጥ የኤሌክትሪክ አቅርቦቱን ለማሻሻል መስራት እንደሚገባው ጠቅሰዋል። በቀረበው ሰነድ ላይ የውይይቱ ተሳታፊዎች ጥያቄዎችና አስተያየቶችን ያነሱ ሲሆን የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተውባቸዋል። የባህር በር ጥያቄው ተቋሙ በኃይል ልማት ዘርፉ ለሚያከናውናቸው ፕሮጀክቶች የሚያገለግሉ ግብዓቶች በወቅቱ ወደ ሳይት እንዲደርሱ በማድረግ በአፈፃፀማቸው ላይ አወንታዊ አስተዋፅዖ እንደሚኖረው ኢንጂነር አሸብር ጠቅሰዋል። በኦፕሬሽን እና ግንባታ ሥራዎች ላይ ውጤታማ ለመሆን እንደ ተቋም ያለውን አቅምና ግብ ታሳቢ ያደረገ ዕቅድ በማዘጋጀት ወደ ተግባር መግባት እንደሚያስፈልግ አፅዕኖት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡ የተቋሙ አመራር እና ሠራተኛ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ንቁ ተሳታፊ በመሆን የህዝብ መሰረታዊ ጥያቄ የሆነውን የኤሌክትሪክ አቅርቦት ለመመለስ መስራት እንደሚገባ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አሳስበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥጌ/ግአ/ሙጉ/ሞመ ግንቦት 11 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

የተቋሙ ሠራተኞች "የመሀል ዘመን" ወጥመድ እና መሻገር በሚል መሪ ሀሳብ ላይ እየተወያዩ ነው ........///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች "የመሀል ዘመን" በሚል መሪ ሀሳብ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ዉይይት ማድረግ ጀምረዋል። የለውጥ ወጥመዶች እና የመሻገር ሂደቶች  ላይ ባተኮረው የዉይይት መድረክ ላይ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ በመንግስት የተዘጋጀውን የመወያያ ርዕሰ ጉዳይ አቅርበዋል። በውይይት መድረኩ ላይ የኢትዮጵያ ኢንሸስትመንት ሆልዲንግ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር)፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ አክሊሉ ታደሰ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ፣  የኢትዮጵያ ኢንሸስትመንት ሆልዲንግ የኢነርጂ ዘርፍ ዳይሬክተር ጌትነት መላክ(ዶ/ር) ጨምሮ ከስምንት መቶ በላይ የዋና መስሪያ ቤት ሰራተኞች በመሳተፍ ላይ ናቸው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሞመ ግንቦት 11 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

#News Update በጣቢያው ከሚተከሉት ሁለት ትራንስፎርመሮች መካከል የአንደኛው ሥራ ተጠናቋል ………///……… በወልቂጤ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እየተከናወነ የሚገኘው የትራንስፎርመር ቅየራ ሥራ በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ የማዕከላዊ 3 ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ታደሰ ገብሬ እንዳስታወቁት በማከፋፈያ ጣቢያው ከሚተከሉት ሁለት ትራንስፎርመሮች መካከል 7 ነጥብ 5 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለው አንደኛው ትራንስፎርመር ትናንት ምሽት ኃይል መስጠት ጀምሯል፡፡  ትራንስፎርመር ቅየራው በመጠናቀቁ በ33 ኪሎ ቮልት የአገና፣ ወሸርቤ እና ዋዩ  እንዲሁም ዳልጌ ከተሞች የኤሌክትሪክ ኃይል ማግኘት መጀመራቸውን ገልፀዋል። በጣቢያው የቴክኒክ ችግር የገጠመውንና ለወሊሶ፣ ቱሉቦሎና በዙሪያቸው ለሚገኙ ከተሞች አገልግሎት ሲሰጥ የቆየውን ትራንስፎርመር ከቦታው በማንሳት 63 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለው ሌላኛውን  ትራንስፎርመር የማስቀመጥ ሥራ መሰራቱንም ነው የገለፁት። በአሁኑ ወቅት ትራንፎርመሩን የመገጣጠም ሥራ እየተሰራ እንደሚገኝ የገለፁት አቶ ታደሰ በቀጣይ ቀናት ቀሪ ሥራዎችን በማከናወን የፍተሻና ሙከራ ሥራ እንደተጠናቀቀ ኃይል መስጠት ይጀምራል ብለዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በጣቢያው እየተከናወነ በሚገኘው የትራንስፎርመር ቅየራ ሥራ የወሊሶ ከተማን የኤሌክትሪክ አቅርቦት በእጥፍ ያሳድጋል። ሪጅኑ የትራንስፎርመር ቅየራ ሥራውን ከስምንት እስከ አስር ቀናት አጠናቆ ለህብረተሰቡ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ርብርብ እያደረገ እንደሚገኝም አቶ ታደሰ ተናግረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሙጉ/ሞመ ግንቦት 10 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

መስተዳድሮቹ ለማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ መፋጠን የበኩላቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል .........///......... የደቡብ ወሎ ዞን ዞንና የደሴ ከተማ መስተዳድሮች በደሴ ከተማ እየተገነባ የሚገኘው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ በተያዘለት መርሐ ግብር እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ አረጋገጡ። የዞኑ ዋና አስተዳደሪ፣ የደሴ ከተማ ከንቲባና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነ የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ በተያዘለት መርሐ ግብር ለማጠናቀቅ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት አድርገዋል። በውይይቱ ላይ አቶ ውድነህ እንደገለፁት ግንባታው የሚያስፈልጉ እንደ አሸዋ፣ ድንጋይና ጠጠር ያሉ ግብዐቶች የግንባታ የስራ በቅርበት የሚገኙበትን ሁኔታ በመቻቸት መስተዳድሮቹ ድጋፍ ሊያደርጉ ይገባል። በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች እየተፈፀመ ያለውን ስርቆት ለመከላከል የመስተዳድር አካላት ትኩረት እንዲሰጡ ጠይቀዋል። በውይይቱ ላይ የደሴ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሳሙኤል ሞላልኝ እንደገለፁት በከተማው ለረጅም ዘመን አገልግሎት ሲሰጥ የነበረው ባለ 66 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ በከተማዋ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት በበቂ ሁኔታ ማስተናገድ ባለመቻሉ የኃይል መቆራረጥና የፈረቃ አገልግሎት እንዲሰጥ ምክንያት ሆኗል። ችግሩ እንዲፈታና በየጊዜው እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለመመለስ የማከፋፈያ ጣቢያ እንዲገነባ ለመንግስት ጥያቄ ሲቀርብ እንደነበር ያነሱት ከንቲባው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለጥያቄው ምላሽ በመስጠቱ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በመሆኑም በግንባታ ላይ የሚገኘው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ መጠናቀቅ የከተማው ህዝብ በጉጉት የሚጠብቀው ፕሮጀክት ነው ብለዋል። ከንቲባው እንደገለፁት የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ እስከሚሆን ድረስ የግንባታው ተቋራጭ ለሚጠቀማቸው የነዳጅ፣ ድንጋይ፣ አሸዋና ጠጠር የመሳሰሉ ግብዓቶችን ቅድሚያ ማግኘት የሚችሉበትን ዕድል ይመቻቻል። ፕሮጀክቱ በተያዘለት መርሐ ግብር እንዲጠናቀቅ የከተማ አስተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዓሊ መኮንን በበኩላቸው በዞኑ ውስጥ የሚገነቡ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ እንዲጠናቀቁ እና መሰረተ ልማቶቹ ስርቆት እንዳይፈፀምባቸው ዞኑ ጥብቅ ክትትል እንደሚያደርግ አስታውቀዋል። ስርቆት የሚፈፅሙ አካላት በህግ እንዲጠየቁና የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች በነዋሪዎች እንዲጠበቁ እንደሚደርጉ ተናግረዋል። በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ ሀሳብ የሰጡት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነ መስተዳድሮቹ ተቋሙ ለሚያቀርባቸው ጥያቄዎች ድጋፍ ለማድረግ ያሳዩትን ዝግጁነት አድንቀዋል። በደሴ ከተማ እየተገነባ ያለው የማከፋፈያ ጣቢያ ለከተማው ብቻ ሳይሆን በቅርብ ርቀት ለሚገኙ የዞኑ አካባቢዎች በቂ ኃይል የሚሰጥ በመሆኑ ተቋሙ በዞኑ ሲቀርቡ ለነበሩ የኃይል ፍላጎት ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ እየመለሰ መሆኑን የሚያሳይ ነው ብለዋል።  💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ፍጌ/ሞመ ግንቦት 9 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

ሪጅኑ በበጀት ዓመቱ የታቀዱ ሥራዎችን በዕቅዱ መሰረት ለማከናወን እየሰራሁ ነው አለ ……..///…… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ አንድ ሪጅን በ2017 በጀት ዓመት የያዛቸውን መደበኛ የኦፕሬሽን እና ጥገና ሥራዎች እንዲሁም ጣቢያዎችን የማዘመን እና ሌሎች መደበኛ ተግባራት በዕቅዱ መሰረት ለማከናወን እየሰራ መሆኑን የሪጅኑ ዳይሬክተር አስታወቁ። ዳይሬክተሩ አቶ ወርዲ መሐመድ እንዳስታወቁት በዘጠኝ ወራት ውስጥ ያልተከናወኑ ሥራዎችን በቀሪ ጊዜያት በማጠናቀቅ የበጀት ዓመቱን ዕቅድ ለማሳካት ሪጅኑ የመቶ ቀን ዕቅድ አውጥቶ ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል። በመቶ ቀን ዕቅድ ከተያዙት ተግባራት መካከል በሀረር፣ ሁርሶ እና አዲጋላ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ በጋዝ የሚሰራ የመቆጣጠሪያ ቅየራ እንዲሁም በድሬዳዋ ቁጥር አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ የመቆጣጠሪያ ክፍል ዕድሳት እና ከሁርሶ ድሬዳዋ ቁጥር 3 ባለ 132 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር የኮንዳክተር ቅየራ ሥራዎች ዋንኛዎቹ መሆናቸውን ገልጸዋል። በማከፋፈያ ጣቢያዎች አገልግሎት ላይ የማይውሉ ንብረቶችን በመለየት የጣቢያዎችን ንጽህና መጠበቅ እና ለሥራ ምቹ የማድረግ ሥራዎችም የዕቅዱ አካል መሆናቸውን አክለዋል። እስከ በጀት ዓመቱ ማጠናቀቂያ ድረስ የተያዙትን ሥራዎች ብቅዱ መሰረት እንዲከናወን ከማድረግ ጎን ለጎን በቀጣይ በጀት ዓመት የሚከናወኑ ዋና ዋና ሥራዎችን ዕቅድ እየተዘጋጀ መሆኑንም ገልጸዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et አወ/ሞመ ግንቦት 8 ቀን 2017 ዓ.ም