en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 695 subscribers, ranking 8 036 in the Technologies & Applications category and 2 171 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 695 subscribers.

According to the latest data from 03 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 143 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 27.84%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.00% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 369 views. Within the first day, a publication typically gains 2 511 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 04 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 695
Subscribers
-124 hours
+47 days
+14330 days
Posts Archive
ሪጅኑ በበጀት ዓመቱ የታቀዱ ሥራዎችን በዕቅዱ መሰረት ለማከናወን እየሰራሁ ነው አለ ……..///…… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ አንድ ሪጅን በ2017 በጀት ዓመት የያዛቸውን መደበኛ የኦፕሬሽን እና ጥገና ሥራዎች እንዲሁም ጣቢያዎችን የማዘመን እና ሌሎች መደበኛ ተግባራት በዕቅዱ መሰረት ለማከናወን እየሰራ መሆኑን የሪጅኑ ዳይሬክተር አስታወቁ። ዳይሬክተሩ አቶ ወርዲ መሐመድ እንዳስታወቁት በዘጠኝ ወራት ውስጥ ያልተከናወኑ ሥራዎችን በቀሪ ጊዜያት በማጠናቀቅ የበጀት ዓመቱን ዕቅድ ለማሳካት ሪጅኑ የመቶ ቀን ዕቅድ አውጥቶ ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል። በመቶ ቀን ዕቅድ ከተያዙት ተግባራት መካከል በሀረር፣ ሁርሶ እና አዲጋላ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ በጋዝ የሚሰራ የመቆጣጠሪያ ቅየራ እንዲሁም በድሬዳዋ ቁጥር አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ የመቆጣጠሪያ ክፍል ዕድሳት እና ከሁርሶ ድሬዳዋ ቁጥር 3 ባለ 132 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር የኮንዳክተር ቅየራ ሥራዎች ዋንኛዎቹ መሆናቸውን ገልጸዋል። በማከፋፈያ ጣቢያዎች አገልግሎት ላይ የማይውሉ ንብረቶችን በመለየት የጣቢያዎችን ንጽህና መጠበቅ እና ለሥራ ምቹ የማድረግ ሥራዎችም የዕቅዱ አካል መሆናቸውን አክለዋል። እስከ በጀት ዓመቱ ማጠናቀቂያ ድረስ የተያዙትን ሥራዎች ብቅዱ መሰረት እንዲከናወን ከማድረግ ጎን ለጎን በቀጣይ በጀት ዓመት የሚከናወኑ ዋና ዋና ሥራዎችን ዕቅድ እየተዘጋጀ መሆኑንም ገልጸዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et አወ/ሞመ ግንቦት 8 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

የትራንፎርመር ጥገና ሥራውን እስከ ነገ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው ……….///………. በድሬዳዋ ቁጥር 3 ባለ 230/132/33/15 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ አጋጥሞ የነበረውን የትራንስፎርመር ብልሽት እስከ ነገ አጠናቆ ወደ ሥራ ለማስገባት እየተሠራ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ አበበው አበራ እንዳስታወቁት በቮልቴጅ አለመመጣጠን ምክንያት በጣቢያው የሚገኙ ሁለት ባለ 63 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮች ላይ ብልሽት አጋጥሞ ነበር። ጣቢያው ከቆቃ - ሁርሶ በ230 ኪሎ ቮልት ጥምር መስመር እና ከቆቃ - አዋሽ በ230 ኪሎ ቮልት ነጠላ መስመር እንዲሁም ከሁርሶ በ132 ኪሎ ቮልት ኃይል በመቀበል ለድሬዳዋ ከተማ፣ለድሬደዋ ቁጥር አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ እና በዙሪያው ለሚገኙ ኢንዱስትሪዎች እንዲሁም በ132 ኪሎ ቮልት ወደ ሀረር እና አካባቢው ኃይል እንደሚሰጥ ገልጸዋል። ይሁን እንጂ ትራንፎርመሮቹ በመበላሸታቸው ጣቢያው በ230 ኪሎ ቮልት ያገኝ የነበረው ኃይል ስለተቋረጠ በኃይል አቅርቦቱ ላይ ጫና ማሳደሩን ኃላፊው ገልጸዋል። እንደ ኃላፊው ገለጻ መጠነኛ ጉዳት የገጠመውን አንድ ትራንስፎርመር በአስቸኳይ ጠግኖ ወደ አገልግሎት እንዲመለስ ለማድረግ ከሪጅኑና ከዋና መስሪያ ቤት የተውጣጡ ባለሙያዎች እየሰሩ ነው። የጣቢያው የኦፕሬሽንና ጥገና ክፍል ኃላፊ አቶ ከድር አብደላ በበኩላቸው ትራንስፎርመሩ ተጠግኖ ወደ አገልግሎት ሲገባ ድሬደዋ ከተማ እና በዙሪያው ያሉ ኢንዱስትሪዎች፣ ሀረር እና አካባቢው ኃይል የሚያገኙበትን አማራጭ እንደሚያሰፋ ተናግረዋል። ሥራ አስኪያጁ እንዳሉት ጥገናው እስከ ነገ ተጠናቆ ወደ ሥራ ሲጀምር በጣቢያው ላይ የነበረውን ጫና በከፍተኛ ደረጃ ያቃልላል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et አወ/ሞመ ግንቦት 8 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

የመቆጣጠሪያ ክፍሉ ዕድሳት እየተደረገለት ነው ....///..... በምሥራቅ 1 ሪጅን በመቶ ቀን ዕቅድ ከተያዙት ሥራዎች መካከል አንዱ የሆነው የድሬዳዋ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያ የመቆጣጠሪያ ክፍል ዕድሳት እየተደረገለት መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ ገለጹ። ኃላፊው አቶ ሚካኤል አልዬ እንደገለጹት የመቆጣጠሪያ ክፍሉ ጣሪያ በዕድሜ ብዛት የተነሳ በመሠነጣጠቁ ፍሳሽ ወደ መቆጣጠሪያዎች በማስረግ ጉዳት እንዳያደርስ ዕድሳት እየተከናወነለት ነው። ዕድሳቱ በዋናነት በመቆጣጠሪያ ክፍሉ ጣሪያ ላይ እየተከናወነ መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው ይህም የዝናብ ውሃ በማስገባት መቆጣጠሪያዎቹን እንዳይጎዳ እና በጣቢያው የኦፕሬሽን ሥራ ላይ ጫና እንዳያሳድር ያደርጋል ብለዋል። እንደ ኃላፊው ገለጻ  የመቆጣጠሪያ ክፍሉ የአርማታ ንጣፍ ሙሊት እና  የልሰና ሥራ ሲጠናቀቅ የውሃ መከላከያ ንጣፎችን ጨምሮ ሌሎች የማጠናቀቀያ ሥራዎች በጥቂት ቀናት ውስጥ ይጠናቀቃሉ። የድሬዳዋ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያ ከ1952 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን በተለያዩ ጊዜያት በተደረገለት የማስፋፊያ እና የአቅም ማሳደግ ሥራ እስከ 56 ሜጋ ዋት ኃይል የመጫን አቅም አለው። ጣቢያው በ15 ኪሎ ቮልት ባሉት ስድስት ወጪ መስመሮች ለድሬዳዋ ከተማ እና በዙሪያው ለሚገኙ ፋብሪካዎች እንዲሁም በ132 ኪሎ ቮልት ለናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ አስተማማኝ ኃይል እያቀረበ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ኑሀ/ሞመ ግንቦት 7 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

የፕሮጀክቱን የሲቪል ሥራ አፈፃፀም 17 ከመቶ ለማድረስ እየተሰራ ነው ……….///………. የደሴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የፕሮጀክት የሲቪል ሥራ አፈፃፀምን እስከ በጀት ዓመቱ መጨረሻ 17 ከመቶ ለማድረስ እየተሰራ መሆኑን የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነ  የተመራ ቡድን የፕሮጀክቱን ግንባታ ሲጎበኝ ሥራ አስኪያጁ አብዱ ኪያር እንደተናገሩት በ1 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ግንባታው የተጀመረው የማከፋፈያ ጣቢያ የፕሮጀክት አፈፃፀም 12 በመቶ ደርሷል፡፡ ፕሮጀክቱ ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ ሳይቱን ለግንባታ ዝግጁ በማድረግ የመሬት ቆረጣና የአፈር ማንሳት፣ የአፈር መንሸተት መከላከያ ግንብ ግንባታ፣ የመኖሪያ ቤት መሠረት ግንባታ እና ኮለን የማቆምና ሥራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡ 63 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፎርመሮችን በቦታቸው የማስቀመጥ ሥራ መጠናቀቁን የሳይት ሥራ አስኪያጁ አስረድተዋል። የተቋሙ የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነ በበኩላቸው የማከፋፈያ ጣቢያው መገንባት በደሴና አካባቢዋ አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ እንደሚያስችል ገልፀዋል። ይህም ተቋሙ በሁሉም አካባቢዎች እያደረገ ያለውን የልማት ተደራሽነትን የሚያሳይ ነው ብለዋል። ግንባታው የሚገነባበት ቦታ ጥቁር አፈር በመሆኑ ተጨማሪ የመሬት ቆረጣና አፈር የማንሳት ሥራ ማስፈለጉን የተናገሩት ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ሥራው ቀድሞ ከታሰበው ውጭ ያጋጠመ በመሆኑ የተወሰነ መጓተት ማስከተሉን ጠቁመዋል፡፡ ሥራውን በተያዘለት ዕቅድ መሠረት ማጠናቀቅ የሚያስችሉ ሥራዎችን በቀሪ ጊዜያት ውስጥ ጠዋትና ማታ መስራት እንዳለባቸው አቅጣጫን አስቀምጠዋል። በጉብኝቱ ላይ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚውን ጨምሮ የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት መምሪያ ዳይሬክተር ሰለሞን ኃይለጊዮርጊስ፣ የኢንጂነሪንግ ሱፐርቪዥንና ኮንትራት አስተዳደር መምሪያ ዳይሬክተር ግርማ ዘለቀ፣ በዘርፉ የግዥና ፋይናንስ መምሪያ ተወካይ ዳይሬክተር ሙሉቀን ዮሴፍ ተገኝተዋል፡፡ የደሴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የግንባታ ወጪ ሙሉ ለሙሉ በተቋሙ የሚሸፈን ሲሆን የግንባታ ሥራውን የተቋሙ የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት መምሪያ የአማካሪነትና የቁጥጥር ስራዎችን ደግሞ የተቋሙ የኢንጂነሪንግ ሱፐርቪዥንና ኮንትራት አስተዳደር መምሪያ በጋራ ይሰሩታል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ኑሀ/ሞመ ግንቦት 6 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

በጣቢያው ሲከናወን የቆየዉ የመቆጣጠሪያዎች ቅየራ ተጠናቀቀ …….///………. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምስራቅ 2 ሪጂን ሥር በሚገኘው የሠመራ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሲከናወን የቆየው የመቆጣጠሪያ ወይም ስዊችጊር ቅየራ መጠናቀቁን የመምሪያው ዳይሬክተር አስታውቁ፡፡ ዳይሬክተሩ አቶ ሐሰን ሙሓመድ እንደገለፁት በተቋሙ በራስ አቅም የማከፋፈያ ጣቢያውን የመቆጣጠሪያ ክፍል የማሻሻልና የማዘመን ሥራዎች በመስራት የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝነት ለመጨመር ተችሏል፡፡ በማከፋፈያ ጣቢያው ለረጅም ጊዜ ያገለገለውን በአየር የሚሰራ መቆጣጠሪያ በጋዝ ወደሚሰራ መቆጣጠሪያ መቀየር መቻሉ የጣቢያውን የኦፕሬሽን አቅም በማሳደግ አስተማማኝ እና የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያስችል ጠቅሰዋል። የተቀየሩት መቆጣጠሪያዎች ቀደም ሲል የሚያጋጥመውን የኃይል መቆራረጥን ለማስወገድ እና የቁጥጥር ሥርዓቱን ለማዘመን እንደሚያስችል አስረድተዋል፡፡ በ2003 ዓ.ም ተገንብቶ ለአፋር ክልል በዋነኝነት ኃይል እያቀረበ የሚገኘው የሰመራ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ከኮምቦልቻ በ230 ኪሎ ቮልት የተቀበለውን ኃይል ወደ አፍዴራና ዲቾቶ ማከፋፈያ ጣቢያዎች በማስተላለፍ ከ80 በመቶ በላይ የሆነውን የአፋር ክልል ተደራሽ ያደርጋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ኑሀ/ሞመ ግንቦት 5 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

የማከፋፈያ ጣቢያውን መቆጣጣሪያዎች የማዘመን ሥራ እየተከናወነ ነው …….///…….. በሁርሶ ባለ 230/33/15 ኪሎ ቮልት ማከፋፊያ ጣቢያ አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩ መቆጣጠሪያዎችን በዘመናዊ መቆጣጠሪያዎች በመቀየር ጣቢያውን የማዘመን ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ  ተወካይ ገለፁ። ተወካዩ  አቶ  ናትናኤል ምንተስኖት እንደገለጹት ማከፋፈያ ጣቢያው ላይ የነበሩ መቆጣጠሪያዎች ለብዙ ዓመት ያገለገሉ ከመሆናቸው ባሻገር ዘመኑን የዋጁ አልነበሩም። ይህም የማስተላለፊያ መስመሮቹ ከጣቢያው እየራቁ ሲሄዱ እና በመስመሮቹ ላይ ችግሮች ሲፈጠሩ በቀላሉ ቮልቴጅ እንዲዋዥቅ በማድረግ የኤሌክትሪክ መቆራረጥን ያስከትሉ እንደነበር ተወካዩ ገልጸዋል። አሁን የተቀየሩት በጋዝ የሚሰሩት የጂ አይ ኤስ መቆጣጠሪያዎች በጣቢያው እና በመስመሮቹ ላይ ችግሮች ሲከሰቱ ቀድመው በማሳወቅ መቆጣጠሪያው በራሱ ችግሩን እንዲለይና እርምጃ እንዲወስድ በማድረግ በጣቢያው እና በመሳሪያዎቹ ላይ ችግር እንዳይከሰት እንደሚያደርጉ አስረድተዋል። በጣቢያው የሚከናወነው የመቆጣጠሪያ መሳሪዎች ቅየራ ሥራ የተጠናቀቀ ሲሆን ቀሪ የኮሙዩኒኬሽን እና ሌሎች መሳሪያዎችን በመግጠም ከስካዳ ስርዓቱ ጋር ለማገናኘት እየተሠራ መሆኑን አስረድተዋል። ጣቢያው 125 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፎርመሮች እና 50 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያለው አንድ ትራንስፎርመር ያለው ሲሆን እስከ 180 ሜጋ ዋት ኃይል የመጫን አቅም አለው። እንደ ተወካዩ ገለጻ ማከፋፈያ ጣቢያው ከቆቃ እና ከአይሻ ሁለት በ230 ኪሎ ቮልት ጥምር መስመር ኃይል ተቀብሎ  ለድሬዳዋ ፣  ሀረር፣  ጅግጅጋ ለአዲጋላ እና ጅቡቲ በአጠቃላይ ለምስራቁ የሀገራችን ክፍል ዋንኛ የኃይል ምንጭ በመሆን እያገለገለ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 5 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

በጣቢያው የሚከናወነው የትራንስፎርመር ቅየራ የኃይል አቅርቦቱን ያሳድጋል ………///……… በወልቂጤ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እየተከናወነ የሚገኘው የትራንስፎርመር ቅየራ ሥራ የኤሌክትሪክ አቅርቦቱን እንደሚያሳድገው የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ አቶ ሙጀረብ የኑስ እንደገለፁት 63 እና 7 ነጥብ 3 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፎርመሮች ተጓጉዘው ትናንት ማከፋፈያ ጣቢያው ላይ ደርሰዋል፡፡ ትራንስፎርመሮቹ የቴክኒክ ችግር የገጠመውን ባለ 40 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለውን ትራንስፎርመር በመተካት በፍጥነት ኤሌክትሪክ ለህብረተሰቡ ለማቅረብ ዝግጁ እየተደረጉ እንደሚገኙም ተናግረዋል፡፡ የትራንስፎርመሩ ኃይል የመሸከም አቅም ከ40 ወደ 70 ነጥብ 3 ሜጋ ቮልት አምፒር ከፍ ማለቱ ከጣቢያው ኃይል ሲያገኙ ለነበሩ አካባቢዎች አስተማማኝ ኤሌክትሪክ ለማቅረብ እንደሚረዳ የገለፁት አቶ ሙጀረብ ይህም አካባቢዎቹ ለኢንቨስመንት ተመራጭ እንዲሆኑ ድርሻው የጎላ እንደሚሆን አብራርተዋል፡፡ በማከፋፈያ ጣቢያው ትራንስፎርመሮቹን ለማስቀመጥ የሚያስችሉ የመሰረት ግንባታ፣ ከትራንስፎርመሮቹ ጋር የሚገናኙ ሽቦዎች ዝርጋታ፣ የብሬከር እና ሌሎች ተያያዥ ሥራዎች መጠናቀቃቸውንም ነው የገለፁት፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የትራንስፎርመር ቅየራ ሥራውን በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ ህብረተሰቡ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኝ እየተሰራ ነው፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው ከግልገል ጊቤ 1 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ በባለ 230 ኪሎ ቮልት ኃይል ተቀብሎ ለሰበታ፣ ለሆሳዕናና ለወሊሶ ማከፋፈያ ጣቢያዎች እንዲሁም ለጉራጌ ዞንና አካባቢው ማህበረሰብ ኃይል ያቀርባል። ከዚህ በተጨማሪም ጣቢያው ለሊፍ የተፈጥሮ ውሃና ለዘቢደር ቢራ ፋብሪካዎች  እንዲሁም ለወልቂጤ ዩኒቨርስቲ ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

ኃይል ሳይቋረጥ የኮንዳክተር ቅየራ ሥራ እየተከናወነ ነው …..….//…….. በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ተከስቶ በነበረው የፀጥታ ችግር ሳቢያ ጉዳት የደረሰበትን የለገጣፎ- ኮምቦልቻ- አላማጣ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ ሁለተኛ ሰርኪዩት መስመር ኃይል ሳይቋረጥ በአዲስ ኮንዳክተር የመቀየር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የለገጣፎ- ኮምቦልቻ- አላማጣ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ሁለተኛ ሰርኪዩት ሆት ላይን የኮንዳክተር ዝርጋታ ፕሮጀክት የሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮሐንስ ነጋ እንዳስታወቁት ኮንዳክተሩን የመቀየር ሥራው ከ86 ነጥብ 8 በመቶ በላይ ተከናውኗል። የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታው ከ2013 ዓ.ም በፊት ተጠናቆ ለፍተሻና ሙከራ ሥራ ዝግጁ እንደነበር ያስታወሱት ሥራ አስኪያጁ በወቅቱ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በነበረው ጦርነት ምክንያት መስመሩ መጎዳቱን ገልፀዋል፡፡ እንደ አቶ ዮሐንስ ገለፃ ፕሮጀክቱ በጦርነቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸውን መስመሮች በመለየትና በአዲስ ኮንዳክተር በመቀየር ለህብረተሰቡ ያልተቆራረጠ ኃይል ለማቅረብ እየሰራ ነው፡፡ ፕሮጀክቱ በሁለት ምዕራፍ ተከፍሎ እየተከናወነ እንደሚገኝ የጠቀሱት አቶ ዮሐንስ የመጀመሪያው ምዕራፍ ከለገጣፎ- ኮምቦልቻ 61 ኪሎ ሜትር እንዲሁም ሁለተኛው ምዕራፍ ከኮምቦልቻ- አላማጣ 114 ኪሎ ሜትር እንደሚሸፍን ተናግረዋል፡፡ የመጀመሪያው ምዕራፍ የለገጣፎ- ኮምቦልቻ የኃይል ማሰተላለፊያ መስመር የኮንዳክተር ቅየራ ሥራ መጠናቀቁን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ ይህም ከመስመሩ ኃይል ለሚያገኙ አካባቢዎችና ለለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ አስተማማኝ እሌክትሪክ ለማቅረብ ማስቻሉን ጠቅሰዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የሁለተኛው ምዕራፍ የኮምቦልቻ- አላማጣ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የኮንዳክተር ቅየራ ሥራ የአንደኛው ሰርኪዩት መስመር ኃይል ሳይቋረጥ እየተከናወነ እንደሚገኝም ነው የገለፁት፡፡ ይህም በኮምቦልቻና አጎራባች ከተሞች በኤሌክትሪክ መቋረጥ ሳቢያ ሊፈጠር የሚችለውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ለማስቀረት የጎላ አስተዋፅኦ ማበርከቱን ጠቁመዋል፡፡ የመስመር ዝርጋታውን ኃይል ሳይቋረጥ ማከናወን መቻሉ ለተቋሙ ትልቅ እምርታ መሆኑን ያብራሩት አቶ ዮሐንስ ሥራው በተቋሙ የራስ ኃይል መምሪያ ሠራተኞች አቅም እንዲከናወን መወሰኑ የዕውቀትና ልምድ ሽግግር እንዲኖር በር የከፈተ መሆኑንም ነው የጠቆሙት፡፡ የለገጣፎ- ኮምቦልቻ- አላማጣ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ሁለተኛ ሰርኪዩት ሆት ላይን የኮንዳክተር ዝርጋታ ፕሮጀክትን ለማጠናቀቅ ከ86 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ተያዘ ሲሆን የፋይናንስ ወጪውም ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚሸፈም ነው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

የኮንዳክተር ቅየራው 83 በመቶ ተጠናቋል .....///..... ከሁርሶ - ድሬዳዋ ቁጥር 3  ማከፋፈያ ጣቢያ የተዘረጋውን ባለ 132 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር የመቀየር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና ማስተባበሪያ ቢሮ ቁጥር ሁለት ሥራ አስኪያጅ አቶ ፀሐይነህ አበበ እንደገለጹት የኮንዳክተር ቅየራው  23 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍን እና በ84 የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ የሚከናወን ነው።  መስመሩ ከ28 ዓመት በላይ ያገለገለና የኮንዳክተሩ ዓይነትና መጠን አሁን ካሉት የኮንዳክተር ገመዶች ያነሰ በመሆኑ ለኤሌክትሪክ መቆራረጥ ምክንያት እንደነበር ሥራ አስኪያጁ አብራርተዋል። የቅየራ ሥራው በዓይነትና በመጠን ከፍ ያለ አቅም ያለው እና የኃይል ጭነትን መሸከም የሚችል ኮንዳክተር በመተካት በአካባቢው አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የኮንዳክተር ቅየራው ሲጠናቀቅ የኃይል መቆራረጥን ከማስቀረቱ በተጨማሪ በሌሎች መስመሮች ላይ እክል ቢያጋጥም በአካባቢው ኃይል እንዳይቋረጥ ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግ አስረድተዋል። አሁን ላይ ኮንዳክተሩን የመቀየር ሥራው በ70 ታወሮች ላይ የተከናወነ ሲሆን አጠቃላይ አፈጻጸሙም 83 በመቶ መድረሱን ገልጸዋል። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለጻ በቀሪ 14 ታወሮች ላይ የቅየራ ሥራውን  በአጭር ቀናት በማጠናቀቅ መስመሩን አገልግሎት ለማስጀመር በትጋት እየተሠራ ነው። ሥራው የሚከናወነው በራስ አቅም መሆኑ  የዕውቀት ሽግግር ከማድረጉ በተጨማሪ የፕሮጀክት አስተዳደር አፈጻጸምን በማሻሻል ሥራዎችን በተቀመጠላቸው ጊዜና ጥራት ለማከናወን ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 3 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ለወልቂጤ ማከፋፈያ ጣቢያ ተቀያሪ ትራንስፎርመር እየተጓጓዘ ነው ………///……… የቴክኒክ ችግር ለገጠመው የወልቂጤ ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ከአዲስ አበባ ተቀያሪ ትራንስፎርመር እየተጓጓዘ ነው። 230/66/33/15 የሆነው ትራንስፎርመር ዛሬ ማምሻውን ደቡብ ምዕራበ ሸዋ ዞን ወሊሶ ከተማ ደርሷል። በማከፋፈያ ጣቢያው ትራንስፎርመሩን ለማስቀመጥ የሚያስችል የመሰረት ግንባታ፣ ከትራንስፎርመሩ ጋር የሚገናኙ ሽቦዎች ዝርጋታ እና ሌሎች ተያያዥ ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። ትራንስፎርመሩ ችግር የገጠመውን ባለ 230/66/15 በመተካት ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች ኃይል በፍጥነት እንዲያገኙ  ያስችላል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ትራንስፎርመሩ ሲጓጓዝ መንገድ በማስከፈት ከፍተኛ ድጋፍ ላደረጉት የፌደራል ፖሊስ፣ የሸገር ከተማ ፖሊስ እና የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ፖሊስ መምሪያ ምስጋናውን ያቀርባል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 2 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5