ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 572 подписчиков, занимая 8 384 место в категории Технологии и приложения и 2 165 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 572 подписчиков.

Согласно последним данным от 23 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 0, а за последние 24 часа — -2, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 25.89%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 15.48% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 026 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 408 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 9.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 24 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 572
Подписчики
-224 часа
-37 дней
Нет данных30 день
Архив постов
የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት በቅርቡ ሙሉ በሙሉ እንደጠናቀቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለፁ ….///…. የኢትዮጵያ የአንድነት ተምሳሌት የሆነውና ብዙ ውጣ ውረድ የታየበት የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት በቅርቡ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ በቅርቡ አገልግሎት እንደሚጀመር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር  ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) አስታወቁ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ በሚቀጥሉት 6 ወራት የግንባታውን ቀሪ ሥራዎች በማጠናቀቅ የፕሮጀክቱን ፍፃሜ ለኢትዮጵያ ህዝብ እናበስራለን ብለዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የአፍሪካ ኩራት ከመሆኑም ባሻገር መቻልን ያሳየንበት፣ በውስጣችን ያለውን ውድቀት ያረምንበት እና 74 ቢሊዮን ሜትር ኩዩብ ውሃ ይዘን ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል የምናመርትበት ሀብት ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡ እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለፃ የህዳሴ ግድብ አፍሪካውያን የፋይናንስና ዲፕሎማሲያዊ ጫና ቢደረግባቸው እንኳ የራሳቸውን ሀብት በገዛ ዜጎቻቸው አልምተው መቀየር እንደሚችሉ በተግባር የሚያሳይ ነው፡፡ የህዳሴ ግድብን በተመለከተ ከታችኛው የተፋሰሱ ሀገራት ጋር ስላለው ዲፕሎማሲ የተጠየቁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ማምረት እንጂ ማንኛውንም ሀገር የመጉዳት ፍላጎት የላትም ብለዋል፡፡ ስለሆነም ግድቡ ግብፅን ጨምሮ በታችኛው የተፋሰሱ ሀገራት ምንም ዓይነት ጉዳት እንደማያመጣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልፀዋል፡፡ ከግብፅ ጋር በተደረጉ ተደጋጋሚ ውይይቶች የህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት በአስዋን ግድብ ምንም ዓይነት ተጽዕኖ እንደሌለው ተናግረዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም ኢትዮጵያ ከግብፅ ጋር ለውይይት፣ ለድርድር እና  በትብብር አብሮ ለመስራት ሁል ጊዜም በሯ ክፍት መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 11 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

በአዋሽ 7 ኪሎ አካባቢ የተፈፀመው ስርቆት ለምስራቅ ከተሞች ኃይል መቋረጥ ምክንያት ሆኗል .......///...... በአፋር ክልል አዋሽ 7 ኪሎ ከተማ አቅራቢያ በ3 የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ  የብረት ምሰሶዎች ላይ ሥርቆት መፈፀሙን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ 2 ሪጅን አስታወቀ። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ዘበርጋ እንደገለፁት ከለሊቱ 6:05 አካባቢ ከቆቃ ወደ ሁርሶ በተዘረጋው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በተፈፀመው ሥርቆት ድሬዳዋ፣ ሐረር እና ጅግጅጋን ጨምሮ በምስራቅ ኢትዮጵያ በሚገኙ ከተሞች ኃይል ተቋርጧል። የምስራቅ ረጅን 1 ዳይሬክተር አቶ ወርዲ መሀመድ በበኩላቸው ኃይል ለተቋረጠባቸው አካባቢዎች በሌላ አማራጭ ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሰራ ነው። በተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ ሥርቆቱ በከተማ አቅራቢያ መፈፀሙ የችግሩን አሳሳቢነት የሚያሳይ በመሆኑ የፀጥታና የመስተዳድር አካላት ድርጊቱን ለመከላከል ትኩረት እንዲሰጡት ጠይቀዋል። ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች በተቻለ ፍጥነት በሌላ አማራጭ ኃይል እንዲያገኙ እየተደረገ ቢሆንም በጊዜያዊነት በቂ ኃይል ላይኖር ስለሚችል ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚዎች አጠቃቀማቸውን እንዲያስተካክሉ አሳስበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 11 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

ማዕከሉ በጣቢያው ያሉ ችግሮችን በመለየት የመፍትሔ ኃሳብ ለማቅረብ እየሰራ ነው .......///....... በጊቤ ሦስት የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የተቋቋመው የጥናት፣ ምርምርና ሥልጠና ማዕከል በጣቢያው ያሉ ችግሮችን በመለየት የመፍትሔ ሀሳቦችን ለማቅረብ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ። በጣቢያው የኮሙዩኒኬሽን ኢንጅነርና የማዕከሉ አስተባባሪ አቶ ይስሃቅ ወልደየስ እንዳስታወቁት የማመንጫ ጣቢያው የሚያጋጥሙትን ችግሮች በጥናት ላይ ተመስርቶ ለመፍታት ከሦስት ዓመታት በፊት ማዕከሉን አቋቁሟል። ማዕከሉ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ጥናትና ምርምሮችን በመስራት የጣቢያውን የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎችን ለማቀለጠፍ የሚያግዙ ዘመናዊ አሰራሮችን ለመተግበር ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ማዕከሉ ለጣቢያው የኮሙዩኒኬሽን ሥርዓትና የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፎች ድጋፍ እያደረገ መሆኑን  ተናግረዋል። የወረቀት ሥራዎችን በዘመናዊ የአሠራር ሥርዓት ለመተካት በጣቢያው ኔትወርክ የሚሰራ "ጊቤ ፕላስ" የተሰኘ መተግበሪያ በልጽጎ ወደ ሥራ መግባቱን ገልጸዋል። እንደ አቶ ይስሐቅ ገለፃ መተግበሪያው የእያንዳንዱን የማሽን ታሪክ፣ የንብረት አያያዝ፣ የሰው ኃይሉንና የሚጠቀምባቸውን መሣሪያዎች ኮምፒውተራይዝድ በማድረግ በቀላሉ ታሪካቸውን ለማወቅ የሚያስችል ነው። መተግበሪያው በወረቀት የነበሩ አሰራሮችን በማዘመን ችግሮችን የቀረፈ ቢሆንም አገልግሎቱን ከዚህ የተሻለ ለማድረግ መተግበሪያውን ለማሻሻል ዕቅድ ተይዞ በመስራት ላይ መሆኑንም ጠቁመዋል። ማዕከሉ በተለይም በጣቢያው የኮሙዩኒኬሽንና የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ የአሰራር ሥርዓቶች ላይ የሚያስፈልጉ ሥልጠናዎችን በመለየት እንደሚሰጥም ጠቁመዋል። የጥናት፣ ምርምርና ሥልጠና ማዕከላት  በማመንጫ ጣቢያዎች ያሉ ችግሮችን በመቅረፍ በኩል ሚናቸው ከፍተኛ መሆኑን የተናገሩት አቶ ይስሃቅ ይኼን ከግምት በማስገባት በተቋሙ መዋቅር ተፈጥሮለት በሰው ኃይልና በግብዓት የሚደራጅበት መንገድ መታሰብ አለበት ብለዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 10 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

ሪጅኑ የፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል የተጠቃሚዎች ስልጠና እየሰጠ ነው ………//………... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ማዕከላዊ ሪጅን 3 ሥር ለሚገኙ የማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመር የጥገና እና ኦፕሬሽን ባለሙያዎች የሳፕ ፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል የተጠቃሚዎች ስልጠና መሰጠት ተጀመረ። የሳፕ ትግበራ ኮሚቴ አባልና አሰልጣኝ የሆኑት አቶ ወልዳይ ገ/ትንሳኤ እንደገለጹት ሥልጠናው በሪጅኑ የማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ማስተላለፊያ መስመሮች የአሰራር ሥርዓት ለማዘመን፣ ጠንካራ የሀብት ቁጥጥር ሥርዓት ለመዘርጋት፣ ወጭ ለመቀነስ እና ሥራን ለማቀላጠፍ አስተዋፅኦው ከፍ ያለ ነው። የፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል የማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ንብረቶች የሚመዘግብ ከመሆኑም ባሻገር የጥገና ሥራዎችን በዕቅድ ላይ ተመስርቶ ለማከናወን ፋይዳው የጎላ መሆኑን አስረድተዋል። እንደ አቶ ወልዳይ ገለፃ የሞጁሉ መተግበር የጥገና መረጃዎችን በመሰብሰብና በመተንተን የተሻለ ውሳኔ አሰጣጥ እና ትንበያ እንዲኖር ከማስቻሉም በተጨማሪ  የጥገና ሂደቱን  ሙሉ ለሙሉ በማዘመንና በማቀላጠፍ በኩል ጉልህ ሚና ይጫወታል። ሥልጠናው የማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ማስተላለፊያ መስመሮችን ንብረቶች አያያዝና አጠቃቀም ለመከታተልና አስተማማኝነታቸውን ለማረጋገጥ ያስችላል፡፡ በሪጅኑ መደበኛ የፍተሻ እና የጥገና ሥራዎችን  ለመከታተልና የቁጥጥር ሥርዓቱን ለማዘመን እንዲሁም  የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስ እንደሚረዳ አቶ ወልዳይ አብራርተዋል። ሥልጠናው በጥገና አሰራር ሥርዓት፣ በመለዋወጫ ዕቃዎች አቅርቦት፣ አስተዳደር እና ተያያዥ ርዕሰ ጉዳዮች የሚያተኩር ሲሆን በሪጀኑ በሚተዳደሩ 20 ማከፋፋያ ጣቢያዎች ውስጥ  ለሚገኙ  ለጥገና  እና ለኦፕሬሽን ባለሙያዎች በአንድ  ወር ቆይታዎች በአራት ዙር እንደሚሰጥ አመልክተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 9 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

የተቋሙ ሴት ሠራተኞች ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን በልዩ ልዩ ዝግጅቶች አከበሩ …………///……….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሴት ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች በዓለም ለ114ኛ በሀገር አቀፍ ደግሞ ለ49ኛ ጊዜ « ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ» በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን በልዩ ልዩ ዝግጅቶች አክብረዋል፡፡ በመርሀግብሩ ላይ የተገኙት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደተናገሩት ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ሲከበር ሴቶች በሁሉም ዘርፍ አቅማቸውን በማጎልበት ውጤታማ እንዲሆኑ የተጀመረውን ጥረት በማስቀጠል ሊሆን ይገባል፡፡ የሥራ ቦታዎችን  ከጾታ መድልዖ የጸዱ፣ አካታች እና አሳታፊ እንዲሆኑ በሚደረገው ጥረትም የተቋሙ ሴት ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች ሚናቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። በተቋሙ  የሴቶች እና ማህበራዊ መመሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ በበኩላቸው ሴቶች  የሚያገኙትን ዕድል ሳያባክኑ አሟጠው  በአግባቡ ሊጠቀሙበት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በርካታ የድጋፍ እርምጃዎችን ያመቻቻ ቢሆንም ዕድሉን ከመጠቀም አንጻር ውስንነቶች መኖራቸውን ጠቁመዋል፡፡ ስለሆነም ተቋሙ ለሴት ሠራተኞች ያስቀመጣቸውን የድጋፍ እርምጃዎች በአግባቡ በመጠቀም የሚጠበቅባቸውን ተቋማዊና ሀገራዊ አስተዋጽኦ ማበርከት አንዳለባቸውም ገልፀዋል፡፡ በበዓሉ ላይ በጡት እና በማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና  እና  ሥነ ግጥም ቀርቧል፡፡ በተመሳሳይ በዓሉ በተቋሙ በአዳማ 1 እና 2፣ በቆቃ፣ በአዋሽ 2 እና 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እንዲሁም በደሴና በማዕከላዊ ሪጅን 2 በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሯል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 8 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

photo content

በምዕራብ ሪጅን ኃይል ተቋርጦባቸው የነበሩ አካባቢዎች ኃይል አግኝተዋል ....///... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ምዕራብ ሪጅን ኃይል ተቋርጦባቸው የነበሩ አካባቢዎች ኃይል ማግኘታቸውን የሪጅኑ የኦፕሬሽንና ጥገና ኃላፊ ገለጹ። ኃላፊው አቶ ታሪኩ ደጉ እንደገለጹት የጊዳ አያና ባለ132 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያን ከነቀምቴ ማከፋፈያ ጣቢያ ጋር በሚያገናኝው ትራንስፎርመር ላይ በደረሰ ችግር የተነሳ ከየካቲት 25 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በአምስት ወረዳዎችና አንድ ከተማ አስተዳደር ኃይል ተቋርጦ ቆይቷል። ኃይል የተቋረጠባቸው ጊዳ፣ ገሊላ፣ ኤበቱ፣ ሀሮ ሊሙ፣ ኪረሙና ሀምሩ ወረዳዎች እንዲሁም ጉትን ከተማ አስተዳደር ናቸው። ችግሩ ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ የተጎዳውን የትራንስፎርመር ክፍል በመቀየር ወደ ሥራ ለማስገባት ጥረት ሲደረግ መቆየቱን የገለጹት አቶ ታሪኩ በዛሬው ዕለት የአራት ወረዳዎችንና አንድ አተማ አስተዳደር ኃይል እንዲያገኙ መደረጋቸውን ተናግረዋል። ቀሪ ኃይል ያላገኙ አካባቢዎች በአጭር ጊዜ ኃይል እንዲያገኙ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። በአደጋው በተከሰተው የኃይል መቋረጥ በትዕግስት ለጠበቁ ነዋሪዎችም ምስጋና አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 8 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

ተቋማዊ አሰራሮች ሕግን የተከተሉ እንዲሆን መስራት ይገባል ….....///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ውስጥ እየተተገበሩ ያሉ አሰራሮች ሕጋዊ ሂደትን ተከትለው መከናወናቸውን ማረጋገጥ እንደሚገባ በተቋሙ የኮርፖሬት ገቨርናንስና ኮምፕሊያንስ ሥራ አስፈጻሚ አሳሰቡ። ሥራ አስፈጻሚው አቶ ዱጉማ ነዳ ከተቋሙ የሕግ አገልግሎት መምሪያ ሠራተኞች እና የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አካሂደዋል። ውይይቱ ዓላማ በተቋሙ እየተከናወኑ ያሉ ተቋማዊ የለውጥ ሥራዎች ከመደገፍ ባለፈ የተቋሙን የፋይናንስ አቅም በእጅጉ እየተፈታተኑ ባሉት የታወር ስርቆትና የካሳ ክፍያ ጉዳዮች ዙሪያ መምሪያው በምን አግባብ እየሰራ ነው የሚለውን አይቶ ቀጣይ አቅጣጫ ማስቀመጥ ያለመ መሆኑን ሥራ አስፈጻሚው ተናግረዋል፡፡ ለውይይት መነሻ እንዲሆን አምስት አባላት ያሉት የጥናት ኮሚቴ በማቋቋም በመምሪያው እና በስሩ ባሉ ክፍሎች እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችና የመፍትሔ ሀሳቦች ለማመላከት የሚያስችል የዳሰሳ ጥናት መሰራቱን ተናግረዋል። መምሪያው ቅንጅታዊ አሰራርንና ሙያዊ ብቃትን በማሳደግና አሰራሮች ሕግን የተከተሉ መሆናቸውን በመቆጣጠር ተቋሙን በመጠበቅና በመከላከል በኩል ሚናውን ሊወጣ እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡ ተቋሙ በሀገር ደረጃ የሚሰራቸውን ትልልቅ ፕሮጀክቶች ከብክነት በፀዳ መልኩ በውጤታማነት ለመፈፀም የመምሪያው ሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡ በሕግ አገልግሎት መምሪያና በሥሩ በሚገኙ የሥራ ክፍሎችን የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመለየት እና የመፍትሔ ሀሳቦችን  ለማመላከት የተሰራው የዳሰሳ ጥናትም ለውይይቱ ተሳታፊዎች ቀርቧል፡፡ በመምሪያው ውስጥ ከሠራተኛ አቅም ግንባታ፣ ከአገልግሎት አሰጣጥ፣ ከመፈጸም አቅምና ከግብዓት አቅርቦት ጋር ያሉ ችግሮች እንዲሁም ከሌሎች የተቋሙ የሥራ ክፍሎች ጋር ያለውን ግንኙነት በተመለከተ በጥናቱ ተዳሷል። የውይይቱ ተሳታፊዎችም ጥናቱ ራሳቸውን እንዲያዩና በሥራ ክፍሎች መካከል እርስ በእርስ የመማማር ዕድልን እንደሚፈጥር ተናግረዋል። መምሪያው ተቋሙን የሚመጥን ሥራ ለመስራት ያስችለው ዘንድ ሊፈቱና ሊታዩ ይገባሉ ያሏቸውን ሀሳቦችና አስተያየቶች አንስተው መሰል ጥናቶችና ወይይቶች በየጊዜው የሚደረጉበት አሠራር እንዲዘረጋም ጠይቀዋል፡፡ የሕግ አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ መስከረም በቀለ በበኩላቸው ከተሳታፊዎች የተነሱ እንዲሁም በጥናቱ የተለዩ ችግሮችን እንደ ግብዓት በመውሰድ በተቋማዊ ለውጡ የሕግ ክፍል ሊኖረው የሚችለውን ሚና እንዲወጣ ይደረጋል ብለዋል፡፡ ከታወር ስርቆትና ከካሳ ክፍያ ጋር ያሉ ችግሮችን በዘላቂነት መፍታት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ከሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች፣ ከፍትህና አስተዳደር አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራም አብራርተዋል፡፡ የባለሙያዎችን አቅም በማሳደግ በፍርድ ቤት ባሉ ጉዳዮች ዙሪያም መረጃና ማስረጃ በማጠናከር የተቋሙን ጥቅም ለማስጠበቅና ለመከላከል የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የጠቆሙት ዳይሬክተሯ ተቋማዊ አሰራሮችን በመፈተሸ በሕግ እንዲደገፉ ብሎም ግልፅነትና ተጠያቂነት እንዲሰፍን መምሪያው በትኩረት እንደሚሰራም ተናግረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 6 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

ጣቢያው የጥገና ሥራዎቹን ቢያሳካም ኃይል የማምረት አፈፃፀሙ ከዕቅዱ ያነሰ ነበር …….///……. የአዳማ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ2017 ግማሽ በጀት ዓመት በቅድመ መከላከል፣ በትንበያ እና የገጠሙ ችግሮችን በማስተካከል ከዕቅዱ በላይ ቢያከናውንም ኃይል በማምረት ረገድ የያዘውን ዕቅድ ማሳካት እንዳልቻለ አስታወቀ፡፡ የጣቢያ ኃላፊው አቶ መለሰ ሲሎ እንደገለፁት ጣቢያው በግማሽ ዓመቱ በቅድመ መከላከል፣ በትንበያ እና የገጠሙ ችግሮችን በማስተካከል 141 ጥገናዎች ለማከናወን አቅዶ 150 ጥገናዎችን በማከናወን የ106 ነጥብ 21 በመቶ አፈፃፀም አስመዝግቧል፡፡ በንፋስ ተርባይኖችና በስዊችያርድ 152 የፍተሻ ሥራዎችን ለማከናወን የያዘውን ዕቅድ ሙሉ በሙሉ ማሳካቱን ኃላፊው አስረድተዋል፡፡ ይሁንና በመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ለማምረት ካቀደው 249 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ውስጥ ማምረት የቻለው 184 ነጥብ 26 ጊጋ ዋት ሠዓት ብቻ መሆኑን ነው ያስረዱት፡፡ እንደ ኃላፊው ገለጻ የኃይል ማምረት አፈፃፀሙ ከዕቅዱ አንፃር ዝቅ ያለ ቢሆንም የንፋስ ተርባይኖች የሚቆሙበትን ጊዜ በመቀነስ እና አስተማማኝ የጥገና ሥራዎችን በመስራት በተለዋዋጭ የንፋስ ሁኔታዎች ውስጥ ያልተቋረጠ ኃይል ማምረት ተችሏል፡፡ የጣቢያው የጥገና ባለሙያዎች ቴክኖሎጂን በቀላሉ መላመዳቸውና የሥራ ተነሳሽነታቸው ከፍ ያለ መሆኑ ለበጥገና ሥራ ለተመዘገበው ውጤት አስተዋጽኦ አበርክቷል ብለዋል፡፡ የተቋም ሀብት ዕቅድ ሶፍትዌር ወይም ERP፣ የሳፕ ጥገና ሞጁልና የኃይል አስተዳደር ሥርዓቶች እና ሌሎች የለውጥ መሳሪያዎች በጣቢያው መተግበራቸው ለጣቢያው የኦፕሬሽን ሥራዎች ጉልህ ድርሻ እንደነበራቸው ገልፀዋል፡፡ ኃላፊው እንደተናገሩት የጥገና ሥራዎች በዕቅድ መተግበራቸው የሥራ ጊዜን ውጤታማ በማድረግ እና የመሳሪያዎችን የህይወት ዘመን በማራዘም በጣቢያው የተሻለ አፈፃፀም እንዲኖር አስችሏል፡፡   💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 5 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

ማከፋፈያ ጣቢያው ለአግልግሎት ዝግጁ ተደርጓል .......///…..... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የበቆጂ ባለ 230/33 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ለደንበኞች አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን የፕሮጀክቱ ሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡ ሥራ አሰኪያጁ አቶ እንዳልካቸው ጃምቦ እንደገለጹት በማከፋፈፈያ ጣቢው የፍተሻ እና የሙከራ ሥራዎች ላለፉት ሦስት ወራት ሲከናወኑ ቆይተዋል። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያውን ከመልካ ዋከና ወደ ቆቃ ከሚሄደው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር ጋር በማገናኘት የፍተሻና የሙከራ ሥራዎች ሙሉ በሙሉ መጠናቀቃቸውን ተናግረዋል፡፡ የፍተሻና የሙከራ ሥራው መጠናቀቁን ተከትሎ አስር ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ለደንበኞች አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ መደረጋቸውን አስታውቀዋል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያው ለበቆጂና እና በ120 ኪሎ ሜትር ዙሪያ መለስ ውስጥ ለሚገኙ ከተሞች እና ወረዳዎች አስተማማኝ የኃይል ለማቅረብና የኢንቨስትመንት ፍሰት ለማፋጠን እንደሚያግዝ ጠቁመዋል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ በተቋሙ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ ላለፉት አስራ ዘጠኝ ወራት ሲከናወን ቆይቷል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3