en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 676 subscribers, ranking 8 043 in the Technologies & Applications category and 2 176 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 676 subscribers.

According to the latest data from 06 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 111 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.35%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.94% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 974 views. Within the first day, a publication typically gains 2 500 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 07 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 676
Subscribers
-124 hours
-157 days
+11130 days
Posts Archive
በፕሪሚየር ሊጉ የሴቶች ቡድን ሲያሸንፍ ወንዶች ነጥብ ተጋርተዋል ………///………. በኢትዮጵያ የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ባህርዳር ከነማን አንድ ለባዶ ሲረታ በወንዶች ፕሪሚየር ሊግ ደግሞ ነጥብ ተጋርቶ ወጥቷል፡፡ የኢትዮ-ኤሌክትሪክ እንስቶች ሙሉ የጨዋታ የበላይነት ባሳዩበት የ5ኛ ሳምንት ጨዋታ ባህርዳር ከነማ መከላከል ላይ የተመሠረተ የአጨዋወት ስልት ተግባራዊ አድርጓል። በሁለተኛው አጋማሽ ተቀይራ ወደ ሜዳ የገባችው ሀና ሲሳይ በ90ኛው ደቂቃ ብቸኛዋን የማሸነፊያ ጎል ከመረብ ማሳረፍ ችላለች። የኢትዮ-ኤሌክትሪኳ ሃና ሲሳይ የጨዋታው ኮከብ በመሆን ተሸላሚ ሆናለች። ይህ በእንዲህ እንዳለ ትናንት ምሽት በድሬዳዋ ስቴዲየም በተከናወነው የኢትዮጵያ የወንዶች ፕሪሚየር ሊግ 8ኛ ሳምንት ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከመቻል ጋር አቻ ተለያይቷል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ናትናኤል ገ/ጊዮርጊስ በ57ኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ጎል አንድ ለባዶ ሲመራ ቢቆይም በ92ኛው ደቂቃ በተሰጠበት የፍፁም ቅጣት ምት ነጥብ ሊጋራ ችሏል። ሁለቱ ክለቦች በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ አንደኛ እና ሶስተኛ ደረጃ የሚገኙ በመሆናቸው ጠንካራ ፉክክር የታየበት ጨዋታ ያሳዩ ሲሆን መቻሎች መሀል ሜዳውን ተቆጣጥረው በመጫወት ጫና ለማድረግ ሲሞክሩ በአንፃሩ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ የመስመር ኳስ ለመጠቀም ጥረት አድርገዋል። ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ13 ነጥብ በሊጉ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። በመጪው ህዳር 19 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው 9ኛ ሳምንት የወንዶች ፕሪሚየር ሊግ መርሃግብር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከድሬዳዋ ከተማ ጋር ይጫወታል። ህዳር 20 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው 6ኛ ሳምንት የሴቶች የጨዋታ መርሃግብር ደግሞ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚገጥም ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 17 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

የተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች የቦሌ ለሚ የኃይል ማከፋፈያ  ጣቢያን ጎበኙ …...///.....… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ ኃላፊዎች የቦሌ ለሚ ባለ 230/33/15 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን ጎብኝተዋል። ጉብኝቱ የተካሔደው በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የተከናወነው የማስፋፊያ ግንባታ ሥራ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ተከትሎ ነው። በጉብኝቱ ወቅት ለሥራ ኃላፊዎቹ ገለፃ ያደረጉት በማዕከላዊ ሁለት ሪጅን የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮሐንስ ተስፋዬ እንዳስታወቁት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በአካባቢው በ15 ኪሎ ቮልት የኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር መጨመር ለማስፋፊያ ግንባታው ዋና ምክንያት ነው። የማስፋፊያ ሥራው የተለያዩ የሲቪልና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ግንባታዎችን ጨምሮ አንድ ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለው ትራንፎርመር የማስቀመጥ፣ የኃይል መቆጣጠሪያ ቤት ግንባታ፣ የጂ.አይ.ኤስ ስዊች ጊር ገጠማና በ230 ኪሎ ቮልት በኩል የቤይ ዕቃዎችን የመትከል እንዲሁም የፍተሻና የሙከራ ሥራዎችን እንደሚያጠቃልል ነው በጉብኝቱ ወቅት የገለፁት። አንድ ዓመት ከስድስት ወር በወሰደው የማስፋፊያ  ሥራ ስድስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች እንደተገነቡ የገለፁት ሥራ አስኪያጁ ይህም ለቦሌ አራብሳ፣ በሻሌና አካባቢው አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ እንደሚያስችል ተናግረዋል። የማዕከላዊ ሁለት ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ዘበርጋ እንደገለፁት በሪጅኑ አቅም በጣቢያው የተከናወነው የማስፋፊያ ሥራ እንደ ተቋም የመጀመሪያ ሊባል የሚችል ነው። በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው በተከናወነው የማስፋፊያ ግንባታ አዳዲስ መሐንዲሶች እና የቴክኒክ ባለሙያዎች የልምድና የዕውቀት ሽግግር እንዲያገኙ በር የከፈተ ነውም ብለዋል። የማስፋፊያ ሥራው 15 ሚሊየን ብር ወጪ እንደተደረገበት የገለፁት አቶ አለማየሁ ግንባታው በሪጅኑ አቅም በመከናወኑ ተቋሙን ከተጨማሪ ወጪ ማዳን መቻሉን ጠቅሰዋል። በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ በበኩላቸው የተከናወነው የማስፋፊያ ሥራ አዲስ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ከመገንባት ጋር እኩል ነው። በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የተከናወነው የማስፋፊያ ሥራ በአካባቢው ለረጅም ዓመታት ተገንብተው የኃይል አቅርቦት ሳያገኙ ለቆዩ የጋራ መኖሪያ ቤቶች እፎይታን የሚሰጥ እንደሆነም ነው የገለፁት። በጣቢያው ዝግጁ የተደረጉት አዳዲስ ወጪ መስመሮች ለህብረተሰቡ ኃይል መስጠት እንዲችሉ ለማድረግ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል የማሰራጫ መስመሮች ዝርጋታ መጀመሩንም ነው ያስታወቁት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 16 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

photo content

✅ የፈተና ውጤት ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር 4ኛ ነሀሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር የውጪ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታ
+1
የፈተና ውጤት ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር 4ኛ ነሀሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር የውጪ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁ ተወዳዳሪዎች መካከል ከተራ ቁጥር 1 እስከ 5 ያላችሁ በመንገድ ትራንስፖርት ህግና ደንብ በሚፈቅደው አግባብ መሰረት በተሰጠው የተግባር ፈተና የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ በመሆኑ ከህዳር 18 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ ብረታ ብረት ፊለፊት በሚገኘው በዋናው መ/ቤት የሰው ኃይል ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃ የታደሰ መንጃ ፈቃድ እና የስራ ልምድ ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ ቀረበው የቅጥር ሂደት እንድትፈጽሙ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 16 ቀን 2017 ዓ.ም

በጣቢያው ጥገናዎችን በራስ አቅም የማከናወን ልምምድ እያደገ መጥቷል …....///…….... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በግልገል ጊቤ 2 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ጥገናዎችን በራስ አቅም የማከናወን ልምምድ እያደገ መምጣቱን የጣቢያው የጥገና ክፍል ኃላፊ ገለጹ። ኃላፊው አቶ አሸናፊ ተስፉ እንደተናገሩት ከአሁን ቀደም በጣቢያው ከፍተኛ ውጪ ወጥቶባቸው በውጭ ሀገር ባለሙያዎች ብቻ ይከናወኑ የነበሩ የጥገና ሥራዎች በራስ አቅም እየተከናወኑ ነው። ጣቢያው በሙሉ አቅሙ ኃይል እንዲያመነጭ የሚያስችሉ ከቅድመ መከላከል ጀምሮ የትንበያ እና የሁኔታ አመላካች የጥገና ሥራዎች በራስ አቅም መከናወናቸውን ገልጸዋል። ለአብነትም የጣቢያው አራቱም ተርባይኖች ውሃን ለመቆጣጠር የሚያገለግለው ሹል ጫፍ ያለው የብረት አካል ወይም ኖዝሎች በመበላታቸው ምክንያት የአንድ ተርባይን የማመንጨት አቅም ከ105 ሜጋ ዋት ወደ 25 ሜጋ ዋት ቀንሶ እንደነበር ኃላፊው አስታውሰዋል፡፡ በኃይል ማመንጫ ጣቢያው ለረጅም ዓመታት አገልግሎት ላይ የዋሉ የተርባይን ፓዎር ኖዝሎች በራስ አቅም የጥገና ሰራዎችን በማከናወን ተርባይኖቹ በሙሉ አቅማቸው 105 ሜጋ ዋት እንዲያመነጩ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል። የተበሉ ካርበን ብረሾችን በአዲስ የመተካት፤ የስዊችያርድ፣ የመቆጣጠሪያ ክፍል እና የመሳሰሉት የሙቀት መጠን የመቆጣጠር እና የማቀዝቀዣ መሳሪያዎች እንዲሁም ሌሎች የጥገና ሥራዎች በራስ አቅም እንደሚከናወኑ ተናግረዋል። ይህም ጣቢያው በሙሉ አቅሙ ኃይል እንዲያመርት ከማስቻሉም በላይ ጊዜንና ወጭን በመቀነስ በኩል ሚናው ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል። የጥገና ሥራው በራስ አቅም መከናወኑ ተቆሙ ያሉትን ባለሙያዎች አቅም ሙሉ በሙሉ እንዲጠቀም እድል የፈጠረ መሆኑን የጠቆሙት አቶ አሸናፊ ሠራተኞች ሙያዊ አቅማቸውን እንዲያሳድጉና ትልልቅ የጥገና ሥራዎችን መስራት እንችላለን የሚል የራስ መተማመን እንዲኖራቸው አስችሏል ብለዋል። የጣቢያው የጥገና ባለሙያ መልካም ባወቀ በበኩሏ በጣቢያው ከተቀጠረች ሁለት ዓመት ቢሆናትም በራስ አቅም በተከናወኑ የሁለት ተርባይኖች ኖዝል ሥራ ላይ መሳተፏን ገልጻለች። ይህም እሷ እና ሌሎች አዳዲስ የጥገና ባለሙያዎቹ ተግባር ተኮር ዕውቀት ያገኙበትና ትልልቅ የጥገና ሥራዎችን በራስ አቅም መስራት እንደሚቻል ትምህርት የወሰዱበት መሆኑን ተናግራለች። በጣቢያው የኦፕሬሽን ክፍል ኃላፊ አቶ ሽመልስ አዱኛ እንደገለጸው በጣቢያው በራስ አቅም የተከናወኑ የጥገና ሥራዎች የኦፕሬሽን ሥራውን በማሳለጥ በኩል ጉልህ ሚና ተጫውተዋል። ቀደም ሲል በተርባይኖቹ ላይ ባጋጠመ ችግር ምክንያት የኦፕሬሽን ሥራዎችን ከአንድ ማዕከል ለመቆጣጠር አስቸጋሪ አድርጎት መቆየቱን ጠቁመዋል። በዚህም የኦፕሬሽን ባለሙያዎች በማንዋል ቁጥጥር ለማድረግ አስገድዷቸው እንደነበር አስታውሰዋል። በተርባይኖቹና በጣቢያው ማሽኖች ላይ በራስ አቅም የተከናወነው የጥገና ሥራ ጣቢያው በሙሉ አቅሙ ኃይል እንዲያመነጭ ከማድረጉም ባሻገር የኦፕሬሽን ሥራውን ከአንድ ማዕከል መቆጣጠር አስችሏል ብለዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 16 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ግንባታ ወጪን ተቋሙ በራሱ ገቢ እየሸፈነ ነው ……...///…..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን ከፕሮጀክቶች አፈፃፀም ጋር ተያይዞ የሚታዩበትን ውሱንነቶች ለመፍታት የሚያደርገውን ጥረት እንደሚያግዝ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር አስታወቀ፡፡ አስተዳደሩ የተቋሙን የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ከኃይል ሽያጭ፣ ከተቋማዊ የሪፎርም ሥራዎች፣ ከታሪፍ ማሻሻያ፣ ከፕሮጀክቶች አፈፃፀምና ከፋይናንስ እንዲሁም ከሥርዓተ ፆታ ስብጥር አንፃር ገምግሟል። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለፁት የተቋሙን ስምና አርማ ለመቀየር እና የካፒታል መጠኑን ለማሳደግ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር ያለውን የሥራ ግንኙነት ለማሻሻል የሚያስችሉ ደንቦች ተዘጋጅተው ወደሚመለከታቸው አካላት ተልኳል። መንግሥት የተቋሙን የሀገር ውስጥ ዕዳ በከፊል መሰረዙን እና ቀሪ 1 ነጥብ 6 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ብድር ዕዳን ለመክፈል የሚያስችል ታሪፍ እንዲኖር እየተሰራ በመሆኑ የገንዘብ ሚኒስቴር እና የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር አስፈላጊውን እገዛ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል። እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ የኮይሻ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታን ባለበት ፍጥነት ለማስቀጠል ከኃይል ሽያጭ ገቢ ላይ በየወሩ 5 ሚሊየን ዮሮ እየተከፈለ ይገኛል። በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ እንደተናገሩት በበጀት ዓመቱ ለታንዛኒያ ሊቀርብ የታሰበው የኃይል ሽያጭ በታቀደው ጊዜ ባለመጀመሩ የውጭ የኃይል ሽያጭ አፈፃፀም ቀንሷል። በኬንያ እና ታንዛኒያ መካከል ያለው ሥምምነት በቅርቡ እልባት ስለሚያገኝ የኃይል ማስተላለፊያ ኮሪደሩ እስከ ደቡብ አፍሪካ ድረስ ኤሌክትሪክ ለማስተላለፍ አመቺ እንደሆነም ነው የገለፁት። በተቋሙ የኢንጂነሪንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ውድነህ የማነ በበኩላቸው በበጀት ዓመቱ የፕሮጀክቶችን የግንባታ አፈፃፀም ለማሻሻል ታቅዶ እየተሰራ ቢሆንም ከፀጥታና መሰል ችግሮች ጋር በተያያዘ ተግዳሮቶች ማጋጠማቸውን ጠቅሰዋል። እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ከመሰረተ ልማት ስርቆትና ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዘው ለሚነሱ ችግሮች ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች እገዛ ማድረግ አለባቸው። በተቋሙ የፋይናንስ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ እንዳሉት ደግሞ ተቋሙ ከኃይል ሽያጭ ገቢ በርካታ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶችን እየገነባ ይገኛል። ተቋሙ አጠቃላይ ሀብቱ 719 ቢሊየን ብር እንዲደርስ መንግሥት፣ ገንዘብ ሚኒስቴር፣ የሥራ አመራር ቦርዱ እና አስተዳደሩ ያደረጉት ድጋፍ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው ለተደረገው እገዛም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በተቋሙ የንብረት አስተዳደር ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ስመኝ አያሌው በበኩላቸው በ2016 በጀት ዓመት የሸገር ከተማ አስተዳደር በውስጡ ለሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ዓመታዊ የይዞታ ግብር የጠየቀው ከፍተኛ የገንዘብ መጠን እልባት እንዲያገኝ ጉዳዩ ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት መድረሱን ተናግረዋል። በተቋሙ የሰው ኃይል አስተዳደር ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አታላይ አበበ በበኩላቸው በተቋሙ ከሥርዓተ ፆታ ስብጥር እና የማሰልጠኛ ማዕከላትን ከማስፋፋት ጋር በተያያዘ በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ ነው። በግምገማው ላይ የማጠቃለያ ሃሳብ የሰጡት የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ተወካይ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዝናቡ ይርጋ እንደገለፁት በየሩብ ዓመቱ የሚደረገው ግምገማ የተቋሙን ውጤታማነት ለማሻሻል ያግዛል። ተቋሙ በ2017 የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ከኃይል ሽያጭ ያልተሰበሰቡ ገቢዎችን በመሰብሰብና አማራጭ የገቢ ማግኛ አማራጮችን በማስፋት አቅሙን ማጠናከር እንዳለበት አሳስበዋል። ከፕሮጀክቶች አፈፃፀም ጋር ተያይዘው የሚነሱ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት አስተዳደሩ ድጋፍ እንደሚያደርግም ነው ማረጋገጫ የሰጡት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 14 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

የፈተና የውጤት ማስታወቂያ ነሐሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በሹፌር-3ኛ ጂ1 የስራ መደብ በቋሚነት ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎ
+1
የፈተና የውጤት ማስታወቂያ ነሐሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በሹፌር-3ኛ ጂ1 የስራ መደብ በቋሚነት ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል ከተ.ቁ 1 እስከ 6 ያላችሁ በመንገድ ትራንስፖርት ህግና ደንብ በሚፈቅደው አግባብ መሰረት በተሰጠው የተግባር ፈተና የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ በመሆኑ ከህዳር 16 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 5 (አምስት) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ በዋናው መ/ቤት ኮተቤ ብረታብረት በሚገኘው የሰራተኛ ምደባ ቢሮ የትምህርት ማስረጃችሁን እና የስራ ልምድ ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ፎርም እንድትሞሉ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 14 ቀን 2017 ዓ.ም

ባለፉት ሦስት ወራት ተቋሙ ከሀገር ውስጥ የኃይል ሽያጭ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር አግኝቷል ........///....... የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ገምግሟል። የተቋሙን የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት አፈፃፀም ያቀረቡት በተቋሙ የዕቅድ ዝግጅት፣ ክትትልና ትንተና መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ልደት ዘሪሁን እንደገለፁት ለመደበኛና ለካፒታል ፕሮጀክቶች ማስፈፀሚያ 110 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ፀድቆ ወደ ሥራ ተገብቷል። ባለፉት ሦስት ወራት ተቋሙ ከሀገር ውስጥ የኃይል ሽያጭ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር እንዲሁም ለውጭ ሀገር እና ለዳታ ማይኒንግ ከቀረበ ኃይል 59 ነጥብ 42 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ማግኘቱን ነው የጠቀሱት። እንደ ወ/ሮ ልደት ገለፃ የተለያዩ ንብረቶችን በማስወገድና ተቋሙ የማይጠቀሞባቸውን ቤቶች በማከራየት በሩብ ዓመቱ ከ33 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል። በ2017 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ከኃይል ሽያጭ ያገኘው ገቢ ከዕቅዱ አንፃር የ13 በመቶ ብልጫ እንዳለው የጠቀሱት ወ/ሮ ልደት የተመዘገበው የኃይል ሽያጭ ከባለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ36 በመቶ ጭማሪ እንዳሳየም ነው የገለፁት። በበጀት ዓመቱ ከ7 ሺህ 200 ሜጋ ዋት በላይ የማመንጨት አቅም ያላቸው የአምስት ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን ዳይሬክተሯ ጠቁመዋል። ተቋሙ በሩብ ዓመቱ 6 ሺህ 501 ጊጋ ዋት ሰዓት በማመንጨት ከዕቅዱ 17 ነጥብ 8 በመቶ ብልጫ ያለው ኃይል ማምረቱን አመልክተዋል። ከሰው ኃይል አቅም ግንባታ አንፃር ከ2 ሺህ ለሚልቁ የተቋሙ ሠራተኞች ሙያዊ እና የአመራር ክህሎት ስልጠና መሰጠቱንም ነው ያስታወቁት። በሩብ ዓመቱ የለገጣፎ- ኮምቦልቻ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ሁለተኛ የመስመር ዝርጋታን በተቋሙ የራስ ኃይል የግንባታ መምሪያ እንዲከናወን በመደረጉ ከ2 ነጥብ 1 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር በላይ ወጪ ማዳን መቻሉን ዳይሬክተሯ ተናግረዋል። ባለፉት ሦስት ወራት ብቻ በ15፣ 33፣ 45 እና 66 ኪሎ ቮልት መስመሮች ላይ በተፈጠረ የቴክኒክ ችግር  ከ12 ሺህ 500 ጊዜያት በላይ የኃይል መቋረጥ ማጋጠሙን ነው ወ/ሮ ልደት የተናገሩት። በመጀመሪያው ሩብ ዓመት ለተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች እና ለተቋሙ የመሰረታዊ ሠራተኛ ማህበር የሰራተኞች ክበብ የሚውል 258 ሚሊየን ብር ወጪ በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነቱን መወጣቱን ጠቁመዋል። በመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር የማዕድንና ኢነርጂ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሀገሬ ውሒብ እንደገለፁት  የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሀገር ኢኮኖሚ አስተዋጽኦ እያደረገ ያለ ተቋም ነው። በመጀመሪያው ሩብ ዓመት የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ማደጉን፣ የታሪፍ ማሻሻያ ተግባራዊ መደረጉን እና የኃይል ሽያጭ ዕድገት ማሳየቱን እንዲሁም የተቋሙ የ2016 በጀት ዓመት ሒሳብ ተዘግቶ ለኦዲት መሰጠቱን በጥንካሬ አንስተዋል። የፕሮጀክቶች አፈፃፀም ከጊዜና ከበጀት አንፃር ትኩረት እንዲደረግበት፣ የውጭ ሀገር ብድር ክፍያ እና የውጭ ሀገር የኃይል ሽያጭ የገቢ አሰባሰብ ላይ የታዩ ክፍተቶች እንዲስተካከሉ ወ/ሮ ሀገሬ አሳስበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 13 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

የፈተና ውጤት ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአድሚንስትሬሽን ኦፊሰር 1ኛ እና በፋይናንስ አድሚንስትሬሽን ኦፊሰር 1ኛ የስራ መደቦች በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታህሳስ 12 ቀን 2015 ዓ.ም ሰራ
+2
የፈተና ውጤት ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአድሚንስትሬሽን ኦፊሰር 1ኛ እና በፋይናንስ አድሚንስትሬሽን ኦፊሰር 1ኛ የስራ መደቦች በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታህሳስ 12 ቀን 2015 ዓ.ም ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁ ተወዳዳሪዎች መካከል በአድሚንስትሬሸን ኦፊሰር 1ኛ ከተራ ቁጥር 1 እስከ 3 እና በፋይናንስ አድሚንስትሬሽን ኦፊሰር 1ኛ ከተራ ቁጥር 1 እስከ 4 ስማችሁ የተገለጸው ከህዳር 16 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ በሚገኘው በዋናው መ/ቤት የሰው ኃይል ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ሂደት እንድትፈጽሙ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 13 ቀን 2017 ዓ.ም

ለጥገና ሥራ ሲባል የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት እሁድ ህዳር 15 ቀን 2017 ዓ.ም በቃሊቲ 2 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ፤ በቡታጅራ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና በገፈርሳ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመሮች ላይ የጥገና ሥራ ይከናወናል፡፡ በተጨማሪም የለገጣፎ -ኮምቦልቻ 2ኛ መስመርን ኢነርጃይዝ የማድረግ ሥራ ይሠራል፡፡ ስለሆነም በተጠቀሰው ዕለት በቃሊቲ 2 የማከፋፈያ ጣቢያ በሚከናወነው የጥገና ሥራ በሃና ማርያም፣ በብሔረ ፅጌ፣ በአዲስ ጎማ ፋብሪካ፣ በሳሪስ፣ በቦሌ ቡልቡላ፣ በአዋሽ ቆዳ ፋብሪካ፣ በአዲስ ሰፈር፣ በኦሳካ ብረታብረት ፋብሪካ አካባቢ ከጠዋቱ 12፡00 እስከ ቀኑ 7፡00 ሰዓት ድረስ፤ እንዲሁም በቡታጅራ የማከፋፈያ ጣቢያ በሚከናወነው ጥገና በቡታጅራ፣ በወራቤ፣ በቡኢ እና በዙሪያው ባሉ አካባቢዎች ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 9፡00 ሰዓት ድረስ ኃይል ተቋርጦ ይቆያል፡፡ በገፈርሳ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በሚከናወነው የጥገና ሥራ ደግሞ ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 9፡00 ሰዓት ድረስ በፊቼ ከተማና አካባቢው ኤሌክትሪክ ተቋርጦ የሚቆይ ይሆናል፡፡ በተመሳሳይ ዕለት እሁድ ህዳር 15 ቀን 2017 ዓ.ም የለገጣፎ -ኮምቦልቻ 2ኛ መስመርን ኢነርጃይዝ የማድረግ ሥራ ስለሚከናወን ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት እስከ ጠዋት 1፡00 ሰዓት ድረስ በደብረብርሃን ከተማ፣ በሲኖ ብረታ ብረት ፋብሪካ እና በለሚ ሲሚንቶ ፋብሪካ ኤሌክትሪክ ተቋርጦ የሚቆይ በመሆኑ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ ከወዲሁ ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳስባለን፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 13 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ጣቢያዎቹ ከ72 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል አምርተዋል ......///...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአዋሽ ሁለትና ሦስት የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች በ2017 የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ከ72 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል ማምረታቸውን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለጹ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ጌታቸው አበበ እንደተናገሩት በሩብ ዓመቱ በአዋሽ ሁለት 24 ነጥብ 6 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማምረት ታቅዶ 17 ነጥብ 65 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል በማምረት የዕቅዱን 71 ነጥብ 73 በመቶ ማሳካት ተችሏል፡፡ በአዋሽ ሦስት ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ደግሞ 56 ነጥብ 32 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማምረት ታቅዶ 55 ነጥብ 25 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል በማምረት የ98 ነጥብ 11 በመቶ አፈጻጸም ተመዝግቧል፡፡ የአዋሽ ሁለት አፈጻጸሙ ዝቅ ሊል የቻለው ዓመታዊ ጥገና በሚከናወንበት ጊዜ በተርባይን ቤሪንግ ቫይብሬሽን ላይ የተከናወነው ጥገና ከታቀደው በላይ ጊዜ በመውሰዱ እና የክረምቱ የውሃ መጠን በማነሱ እንደሆነ ጠቁመዋል። የመጀመሪያው ሩብ ዓመት አፈጻጸም ከዕቅዱ ዝቅ ያለ ቢሆንም በአዋሽ ሦስት ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የተመረተው ኃይል ግን ካለፈው ሁለት በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከነበረው የኃይል ምርት የ 6 በመቶ ብልጫ ያለው ነው ብለዋል። ጣቢያዎቹ ከዕድሚያቸው አኳያ የመልሶ ግንባታ ሥራ የሚያስፈልጋቸው መሆኑን የተናገሩት አቶ ጌታቸው የታቀደውን ኃይል ለማማረት የሚያስችሉ የጥገና ሥራዎችን በማከናወን ውጤታማ ሥራ መሰራቱን ገልጸዋል። የአዋሽ ሁለት እና ሦስት የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እያንዳንዳቸው 32 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም አላቸው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 13 ቀን 2017 ዓ.ም