ru
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 15 560 подписчиков, занимая 8 357 место в категории Технологии и приложения и 2 160 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 15 560 подписчиков.

Согласно последним данным от 26 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 27, а за последние 24 часа — -7, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 26.05%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 16.01% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 053 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 491 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 8.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
EEP Communication

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 27 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Технологии и приложения.

15 560
Подписчики
-724 часа
+147 дней
+2730 день
Архив постов
photo content
+3

ተቋሙ በኤሌክትሮ መካኒካል ዘርፍ ያሰለጠናቸውን 44 ቴክኒሺያኖች አስመረቀ …….///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለአራት ወራት በኤሌክትሮ መካኒካል የትምህርት ዘርፍ ያሰለጠናቸውን 44 ቴክኒሺያኖች በዛሬው ዕለት አስመርቋል። የተቋሙን ዋና ሥራ አስፈፃሚ በመወከል በምረቃ ሥነ- ሥርዓቱ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን እንደተናገሩት ተቋሙን በአህጉርና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና አስተማማኝ የኃይል አቅራቢ ለማድረግ የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ የተቋሙን ርዕይ ለማሳካት የሥልጠና ማዕከሉን ውጤታማ የሚያደርግ የአጭር፣ የመካከለኛና የረጅም ጊዜ ስትራቴጅ ተነድፎ እየተሰራ እንደሆነ አንስተዋል፡፡ በዕውቀት፣ በክህሎት እና በአመለካከት የዳበረ ሠራተኛ ለመፍጠር የማሰልጠኛ ማዕከሉን በአሰራር፣ በግብዓት እና በአደረጃጀት የማዘመን ሥራ ተጠናክሮ እንደሚከናወን አቶ ሞገስ አረጋግጠዋል፡፡ በተቋሙ የሰው ሀብት ልማት መምሪያ ዳይሬክተር ወንድወሰን ካሳ (ዶ/ር) በበኩላቸው የኤሌክትሮ መካኒካል ሥልጠናው ሠልጣኞች ወደ ሥራ ዓለም ከመግባታቸው በፊት ስለ ተቋሙና ስለሚያከናውኑት ሥራ በቂ ግንዛቤ የሚያስይዝ ነው ብለዋል፡፡ በሥልጠናው ይዘትና አሰጣጥ ላይ ማሻሻያዎችን በማድረግ ከሠልጣኞች የአመለካከት ለውጥ ጋር የተያያዙ ባህሪያዊ ሥልጠናዎች መካተታቸውንም አመልክተዋል፡፡ በሥልጠናው ላይ ከታዳጊ ክልሎች እንዲሁም በተለያየ ምክንያት የሰው ኃይል ካልተሟሉባቸው የሥራ አካባቢዎች በልዩ ሁኔታ ሠልጣኞች እንዲመለመሉ መደረጉንም አንስተዋል፡፡ በተቋሙ የሠው ኃይል ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ አቶ ተማም አፍደል በበኩላቸው ተቋሙ የሶስት ዓመት ግሪድ ስትራቴጅ በመቅረጽ ወደ ተግባር መግባቱን በማስታወስ ዕቅዱን ለማሳካት የዛሬ ተመራቂዎች ድርሻቸው የጎላ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ተመራቂዎቹ በኦፕሬሽን ዘርፎች ላይ የሚስተዋለውን የሰው ኃይል ፍላጎት ክፍተት ለማሟላት ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወቱም ጠቁመዋል፡፡ በተቋሙ የስልጠናና ልማት ማዕከል ሥራ አስኪያጅ አቶ ደምስ ሰይፉ የሥልጠና ማዕከሉ ተቋሙ እንደ አዲስ ከተቋቋመበት ከ2008 ዓ.ም ጀምሮ 800 የሚሆኑ ሠልጣኞችን በዘርፉ በማሰልጠን በኦፕሬሽን የሥራ ዘርፎች ላይ እንዲሳተፉ ማድረጉን አስታውቀዋል፡፡ በተያዘው በጀት ዓመት ማዕከሉ 39 ወንድና 5 ሴት ሠልጣኖችን በኤሌክትሮ ሜካኒካል የትምህርት ዘርፍ ማስመረቁን ተናግረዋል፡፡ ለምረቃ ከበቁት ሰልጣኞች መካከል አስሩ ከአርብቶ አደር አካባቢ የመጡ መሆናቸውን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ ይህንንም ታሳቢ በማድረግ የማደሪያ ቦታ፣ የኪስ ገንዘብ፣ የትራንስፖርትና የውሃ አቅርቦት እንደተመቻችላቸው ተናግረዋል፡፡ እንደ አቶ ደምስ ገለፃ ተመራቂዎቹ በስልጠና ቆይታቸው ከሥራው ጋር ግንኙነት ያላቸው ኮርሶችን በንድፈ ሃሳብና በተግባር በተደገፈ መልኩ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና ልምድ ባላቸው የተቋሙ ሠራተኞች ወስደዋል፡፡ በማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እና የተቋሙ መሠረታዊ የሠራተኛ ማህበር ፀሐፊ አቶ ኃይሉ ወልዴ በፕሮግራሙ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ተመራቂዎቹ ተቋሙ የነደፈውን ስትራቴጅ ለማሳካት ከፍተኛ አደራ እንደተጣለባቸው ተገንዝበው ለተቋሙ ምርታማነት የበኩላቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡ ተመራቂዎቹ በሚሰማሩበት የሥራ መስክ የሚሰጣቸውን ኃላፊነት ሙያዊ ስነ-ምግባርን በተላበሰና የሙያ ደህንነትን ባከበረ መልኩ በትጋትና በቅንነት ተቋሙን እንደሚያገለግሉ ቃል ገብተዋል። በዕለቱም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተመራቂዎች እና ለመምህራን የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 30 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

photo content
+9

ፕሮጀክቱን በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ……//…..… በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ሞጆ ከተማ አቅራቢያ በመገንባት ላይ የሚገኘው የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ግንባታን በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ቴዎድሮስ ጋሻው እንደገለጹት ለገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ኃይል ለማቅረብ የሚገነባው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የጀነሬተር እና የመቆጣጠሪያ ክፍሎች ግንባታ እየተከናወነ ነው። የኦፕሬተሮች መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ተጠናቆ የማጠናቀቂያ ሥራዎችን መጀመራቸውን  ተናግረዋል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያውን የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ለማስቀመጥ የሚያግዙ 250 የሚሆኑ የመሠረት ቁፋሮ ሥራዎች ተጠናቆ የኮንክሪት ሙሌት ስራ እየተከናወነ መሆኑንም ገልፀዋል። የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎቹ በተያዘው ዕቅድ መሠረት ሳይት ከደረሱ ፕሮጀክቱን እስከመጭው ሐምሌ 30 ድረስ ሙሉ ለሙሉ ለማጠናቀቅ ታቅዶ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ የፕሮጀክቱ ሳይት መሀንዲስ አቶ ቢኒያም ግርማ በበኩላቸው የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኃይል አቅርቦት ፕሮጀክት በታቀደለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች እተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። ገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በተለያዩ ምዕራፎች የሚቀርብ 575 ሜጋ ቮልት አምፔር ኃይል እንደሚፈልግ የተናገሩት አቶ ቢኒያም በመገንባት ላይ የሚገኘው የማከፋፈያ ጣቢያ በመጀመሪያው ምዕራፍ 252 ሜጋ ቮልት አምፔር ኃይል ለማቅረብ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል። የኤሌክትሮ ሜካኒካል ግንባታውን ለመጀመር የሚያስችሉ ዕቃዎች የዲዛይን ሥራ ተጠናቆ በፍብረካ ሂደት ላይ ይገኛል  ያሉት አቶ ቢኒያም የማከፋፈያ ጣቢያው የሲቪል ግንባታ 37 በመቶ፣  አጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም ደግሞ 26 በመቶ መድረሱን ገልፀዋል። የፕሮጀክቱ ተቆጣጣሪ መሀንዲስ አቶ ለሜሣ ረጋሣ በበኩላቸው የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኃይል አቅርቦት ኘሮጀክት የሲቪል ስራ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ እና የጥራት ደረጃ እየተከናወነ ነው ብለዋል። የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የማከፋፈያ ጣቢያ በተቋሙ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ እየተገነቡ ካሉ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ መሆኑን የጠቀሱት የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ሰሎሞን ኃ/ጊዮርጊስ ለሌሎች ፕሮጀክቶች ማሳያ በሚሆን መልኩ እየተገነባና ክትትል እየተደረገበት ስለመሆኑም ተናግረዋል። እንደዚህ ዓይነት ፕሮጀክቶችን በተቋሙ በራስ ኃይል እንዲከናወኑ የተቋሙ የሥራ አመራር እና ቦርድ ለሰጠው ዕድልና ኃላፊነትም ምስጋና አቅርበዋል። ፕሮጀክቱ በገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ባለስልጣን በሚሸፈን ከ840 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል መምሪያ እየተገነባ ይገኛል። ፕሮጀክቱ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ እንዲሁም 2‌ ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የኃይል ማስተላለፍያ መስመር ግንባታን ያካተተ ነው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     መስከረም 30 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

ፕሮጀክቱን በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ……//…..… በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ሞጆ ከተማ አቅራቢያ በመገንባት ላይ የሚገኘው የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ግንባታን በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ቴዎድሮስ ጋሻው እንደገለጹት ለገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ኃይል ለማቅረብ የሚገነባው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የጀነሬተር እና የመቆጣጠሪያ ክፍሎች ግንባታ እየተከናወነ ነው። የኦፕሬተሮች መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ተጠናቆ የማጠናቀቂያ ሥራዎችን መጀመራቸውን  ተናግረዋል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያውን የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ለማስቀመጥ የሚያግዙ 250 የሚሆኑ የመሠረት ቁፋሮ ሥራዎች ተጠናቆ የኮንክሪት ሙሌት ስራ እየተከናወነ መሆኑንም ገልፀዋል። የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎቹ በተያዘው ዕቅድ መሠረት ሳይት ከደረሱ ፕሮጀክቱን እስከመጭው ሐምሌ 30 ድረስ ሙሉ ለሙሉ ለማጠናቀቅ ታቅዶ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ የፕሮጀክቱ ሳይት መሀንዲስ አቶ ቢኒያም ግርማ በበኩላቸው የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኃይል አቅርቦት ፕሮጀክት በታቀደለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች እተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። ገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በተለያዩ ምዕራፎች የሚቀርብ 575 ሜጋ ቮልት አምፔር ኃይል እንደሚፈልግ የተናገሩት አቶ ቢኒያም በመገንባት ላይ የሚገኘው የማከፋፈያ ጣቢያ በመጀመሪያው ምዕራፍ 252 ሜጋ ቮልት አምፔር ኃይል ለማቅረብ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል። የኤሌክትሮ ሜካኒካል ግንባታውን ለመጀመር የሚያስችሉ ዕቃዎች የዲዛይን ሥራ ተጠናቆ በፍብረካ ሂደት ላይ ይገኛል  ያሉት አቶ ቢኒያም የማከፋፈያ ጣቢያው የሲቪል ግንባታ 37 በመቶ፣  አጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም ደግሞ 26 በመቶ መድረሱን ገልፀዋል። የፕሮጀክቱ ተቆጣጣሪ መሀንዲስ አቶ ለሜሣ ረጋሣ በበኩላቸው የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኃይል አቅርቦት ኘሮጀክት የሲቪል ስራ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ እና የጥራት ደረጃ እየተከናወነ ነው ብለዋል። የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የማከፋፈያ ጣቢያ በተቋሙ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ እየተገነቡ ካሉ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ መሆኑን የጠቀሱት የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ሰሎሞን ኃ/ጊዮርጊስ ለሌሎች ፕሮጀክቶች ማሳያ በሚሆን መልኩ እየተገነባና ክትትል እየተደረገበት ስለመሆኑም ተናግረዋል። እንደዚህ ዓይነት ፕሮጀክቶችን በተቋሙ በራስ ኃይል እንዲከናወኑ የተቋሙ የሥራ አመራር እና ቦርድ ለሰጠው ዕድልና ኃላፊነትም ምስጋና አቅርበዋል። ፕሮጀክቱ በገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ባለስልጣን በሚሸፈን ከ840 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል መምሪያ እየተገነባ ይገኛል። ፕሮጀክቱ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ እንዲሁም 2‌ ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የኃይል ማስተላለፍያ መስመር ግንባታን ያካተተ ነው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     መስከረም 30 ቀን 2017 ዓ.ም

የማከፋፈያ ጣቢያው የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ማስቀመጫ የኮንክሪት ሙሌት እየተከናወነ ነው …....///....... የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ማስቀመጫ መሰረት የኮንክሪት ሙሌት እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሰሎሞን ኃ/ጊዮርጊስ እንደተናገሩት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ኮንትራት ወስዶ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ በሞጆ ከተማ ዙሪያ እየገነባ ይገኛል። የጣቢያውን የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ማስቀመጫ የኮንክሪት ሙሊት ሥራ በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ ለኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራው ዝግጁ ለማድረግ ከመከላክያ ግንባታ ግብዓቶች ማምረቻ ድርጅት ጋር ስምምነት በመፈጸም የኮንክሪት ሙሌት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል። ስምምነቱ 1 ሺ ሜትር ኪዩብ ኮንክሪት የማቅረብና የሁለት ወራት ርዝማኔ እንዳለው የጠቆሙት አቶ ሰለሞን የአንድ መቶ ሃምሳ ሜትር ኪዩብ የኮንክሪት ሙሊት ሥራው መጠናቀቁንም ተናግረዋል። ቀሪውን የኮንክሪት ሙሊት ሥራ በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እንደሚደረግ ገልጸዋል። የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ ጋሻው በበኩላቸው 250 የሚሆኑ የማከፋፈያ ጣቢያው የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ማስቀመጫ የመሠረት ቁፋሮ ሥራ በአጭር ጊዜ በማከናወን የ132 ፓዶች የኮንክሪት ሙሌት መጠናቀቁን አብራርተዋል። የቀሪ ፓዶችና የአራት ትራንስፎርመሮች ማስቀመጫ መሠረት የኮንክሪት ሙሌት ሥራዎች በቀጣይ ቀናት እንደሚከናወን ተናግረዋል። የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች በምርት ሂደት ላይ እንደሚገኙ የተናገሩት ኃላፊው የኮንክሪት ሙሌት ሥራውን በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ ዕቃዎቹ ሳይት እንደደረሱ የተከላ ሥራ እንደሚጀመር ጠቁመዋል። የመከላከያ ግንባታ ግብዓቶች ማምረቻ ድርጅት የፍሬሽ ኮንክሪት ምርት ቴክኒክ ባለሙያ አቶ ሄኖክ ሻሜሮ በበኩላቸው ድርጅቱ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር ስምምነት በመፈጸም ሲ - 30 የተሰኘ ጥራቱን የጠበቀ የኮንክሪት ዓይነት እያቀረበ መሆኑን ተናግረዋል። ተቋማቱ በትብብር መስራታቸው ሥራው ጥራቱን በጠበቀ መልኩ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ እንደሚያግዝ የጠቆሙት ባለሙያው በቀጣይም ድርጅታቸው ከተቋሙ ጋር በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ በሞጆ ከተማ አቅራቢያ እየተገነባ የሚገኘው የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የማከፋፍያ ጣቢያ ፕሮጀክት 190 ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ ዕድል ፈጥሯል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 29 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

photo content
+9

በማከፋፈያ ጣቢያዎች የተተከሉት የኢነርጂ ሜትሮች የኃይል አቅርቦቱን በአንድ ማዕከል ለመቆጣጠር ያግዛሉ …….//…. የኢትየጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የተከላቸው የኢነርጂ ሜትሮች የኃይል አቅርቦቱን በአንድ ማዕከል ለመቆጣጠር የሚያግዙ መሆናቸውን የኃይል ማስተላለፊያዎችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የዲጂታላይዜሽንና አቅም ማሳደግ ፕሮጀክት-2 ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሃይማኖት ተፈራ እንደገለፁት ተቋሙ የኃይል ሽያጭ ሥርዓቱን የሚከታተልባቸው የኢነርጂ ሜትሮች በሁሉም ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ተክለዋል፡፡ ተቋሙ የኢነርጂ ሜትሮችን በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ከመትከሉ በፊት ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኃይል ሽያጩን ያከናውን የነበረው በ40/60 የቀመር ስሌት ከአጠቃላይ ገቢ ላይ 60 በመቶውን ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰጥበት አሰራር እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ በዚህም ተቋማቱ ከኃይል ሽያጭ ማግኘት የሚገባቸውን ትክክለኛ ገቢ ለማወቅ የማይችሉበት አሰራር ይከተሉ እንደነበረ ነው ሥራ አስኪያጇ የገለፁት፡፡ ወ/ሮ ሃይማኖት አክለውም አሰራሩ ለኃይል ብክነት ከመጋለጡም ባሻገር በተቋሙና በከፍተኛ የኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች መካከል አለመግባባትና አለመተማመኖችን ፈጥሮ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት 1 ሺህ 472 የኢነርጂ ሜትሮች በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ መተከላቸውንና በዚህም ከከፍተኛ የኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ጋር መግባባትና መተማመን መፈጠሩን ጠቁመዋል፡፡ የኢነርጂ ሜትሮቹ ከማከፋፈያ ጣቢያዎቹ ለደንበኞች የቀረበውን ኃይል በማረጋገጥ ተቋሙ በአግባቡ ገቢውን እንዲሰበስብ አስችለዋል ያሉት ሥራ አስኪያጇ የኃይል ብክነትን በመቀነስ በኩልም ጉልህ ሚና መጫወታቸውን ተናግረዋል፡፡ ቀደም ሲል የኢነርጂ ሜትሮችን የተከላና የፍተሻ ሥራ ያከናወነው ሲመንስ ሊሚትድ የተባለ ኩባንያ መሆኑን ያወሱት ወ/ሮ ሃይማኖት ኩባንያው ባልደረሰባቸው የሰሜን እና ምዕራብ ሪጅኖች ላይ የራስ አቅምን በማጎልበት የተከላና ፍተሻ ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ የኢነርጂ ሜትሮች የሳይበር ደህንነት ቅድመ ሁኔታዎችን እንዲያሟሉ ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በትብብር መሰራቱን ገልፀው በመሳሪያዎቹ የሳይበር ጥቃትን ለመከላከል የሚያስችል የክትትል ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 29 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

የመስክ ምልከታው በጣቢያዎቹ ላይ ለሚስተዋሉ ችግሮች መፍትሔ ለመስጠት ያግዛል ….///…. በሰሜን ሪጅን በሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች የተካሄደው የመስክ ምልከታ በጣቢያዎቹ የሚስተዋሉ ችግሮችን በተደራጀ መልኩ መፍትሔ ለመስጠት እንደሚያስችል በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ገለፀ። በዘርፉ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ የሥራ ኃላፊዎች በሪጅኑ ከሚገኙ 9 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ውስጥ በመቐለ፣ አቢ ዓዲ፣ አድዋ፣ አክሱም፣ አዲግራት እና ውቅሮ ጣቢያዎች ላይ የመስክ ምልከታ አካሂደዋል፡፡ በመስክ ምልከታው ወቅት የመንገድ፣ የመኖሪያ ቤት፣ የውሃ አቅርቦት፣ የትራንስፎርመር ብልሽት፣ የብሬከር እጥረትና ብልሽት፣ የጣቢያዎች አቅም ማነስና የመሳሰሉ ችግሮች መኖራቸውን ማረጋገጥ እንደተቻለ በዘርፉ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ ገልጸዋል፡፡ የመስክ ምልከታው ችግሮች መኖራቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ በሪጅኑ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚገኙ የመለዋወጫ ዕቃዎችን ከአንዱ ወደ አንዱ በማዘዋወር መፍትሔ የሚሰጥበት ግብዓት መገኘቱንም ጠቁመዋል፡፡ በመስክ ምልከታው የታዩና በሪጅኑ የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ወደ መፍትሔ እንደሚገባም ነው አቶ ጋሻው ያስረዱት፡፡ እንደ አቶ ጋሻው ገለፃ በጣቢያዎቹ የተካሄደው የመስክ ምልከታ ከኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎች እንዲሁም ከሌሎች አስተዳደራዊ ጉዳዮች ጋር ተያይዘው በሪጅኑ ለሚነሱ ጥያቄዎች ተገቢውን መፍትሔ ለመስጠትና የሠራተኞቹን የሥራ ተነሳሽነት ለማሳደግ ያግዛል፡፡ በመምሪያው የማከፋፈያ ጣቢያዎች ማስተባበሪያ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘውዱ አስማረ በበኩላቸው የመስክ ምልከታው ጣቢያዎቹ የኦፕሬሽን ሥራዎችን የሚያካሂዱበትን ሁኔታ ለመገምገምና ለሥራዎች ማነቆ የሆኑ ችግሮችን ለይቶ መፍትሔ ለመስጠት ያለመ ነው፡፡ በጣቢያዎቹ ላይ የተለያዩ ችግሮች መኖራቸውን እንደተመለከቱ የተናገሩት አቶ ዘወዱ ከተለዩ ችግሮች አብዛኛዎቹ በሪጅኑ አቅምና በዘርፉ የሚፈቱ መሆናቸውንም አመልክተዋል፡፡ በሰሜን ሪጅን የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ክፍለ ተስፋይ ምልከታው ሪጂኑ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች በማረጋገጥ መፍትሔ ለመስጠት እና ተቀራርቦ የመስራት ሁኔታውን ለማጠናከር እንደሚያግዝ ገልፀው ተቋሙ በሪጅኑ ለሚስተዋሉ ችግሮች አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጥ ጠይቀዋል፡፡ በየጊዜው የሚያጋጥሙ ችግሮችን በወቅቱ ለመፍታት የመስክ ምልከታው ተጠናክሮ እንዲቀጥልም አሳስበዋል፡፡ የሥራ ኃላፊዎቹ በሪጅኑ ከሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች በተጨማሪ የመሶቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን የኦፕሬሽን ሥራ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 28 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

ዘርፉ ከደቡብ ምዕራብ ሪጅን የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ጋር ውይይት ማካሄድ ጀመረ ……....///………. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ከደቡብ ምዕራብ ሪጅን የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ጋር በሪጅኑ እየተከናወኑ ስላሉ ሥራዎች እና ተግዳሮቶች ዙሪያ በጅማ ከተማ ውይይት ማካሄድ ጀምሯል፡፡ መስከረም 27 እና 28 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ውይይት ላይ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ የሥራ ኃፊዎች፣ በሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና የሥራ ኃፊዎችና ሠራተኞች ይሳተፋሉ ተብሏል፡፡ በመምሪያው የማከፋፈያ ጣቢያዎች ማስተባበሪያ ሁለት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘውዱ አስማረ እንደተናገሩት ውይይቱ በሪጅኑ እየተከናወኑ የሚገኙ ሥራዎችን በመገምገም ጠንካራ ጎኖቹን ለማስቀጠል እና ለችግሮቹ የመፍትሔ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ ነው። ውይይቱ በሪጅኑ በሚገኙ የማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በሚከናወኑ ሥራዎች ላይ ዘርፉ በዕቅድ ላይ የተመዘረተ ድጋፍና ክትትል የሚያደርግበትን አግባብ ለመዘርጋት እንደሚያግዝም ጠቁመዋል፡፡ አቶ ዘውዱ እንዳሉት ውይይቱ ከኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎች ጋር የተያያዙ ችግሮች በሪጅኑ እና በዘርፉ በጋራ የሚቀረፉበትን አሰራር ከመዘርጋት ባለፈ የሪጅኑ ሠራተኞቹ ያሉባቸውን ችግሮች በመረዳት ለችግሮቹ የመፍትሔ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ይረዳል፡፡ ውይይቱ ከኃይል ማስተላለፊያ መስመር የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ጋር ዛሬ ከሰዓት የተጀመረ ሲሆን በነገው ዕለት ደግሞ ከማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽንና ጥገና የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ጋር የሚካሄድ ይሆናል፡፡ ከመስከረም 20 እስከ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ከሰሜን ሪጅን የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ጋር ተመሳሳይ ውይይት መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን በቀጣዩ ሳምንት ደግሞ ከደቡብ 1 ሪጅን ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች ጋር ውይይቱን ለማካሄድ መርሃ ግብር ተይዟል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቁጥር ኢ.ኤ.ኃ/8.4/22/16 ነሐሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በሾፌር-1ኛ (ጡረተኛ) የስራ መደብ ለውጭ አመልካቾች ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም በወጣው ማስታወቂያ መሰረት ከዚህ በላይ ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ ጥቅምት 04 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ ብረታብረት ፊትለፊት ዋናው መ/ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ ስለሆነ በፈተናው ቦታ ላይ እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ ማሳሰቢያ፦ በፈተና ሰዓት የእጅ ስልካችሁን (ሞባይል) ይዞ መግባት ፈጽሞ የተከለከለ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ለአክሱም ማከፋፈያ ጣቢያ ተጨማሪ ትራንስፎርመር ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ ነው። ……....///………. በአክሱም ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተጨማሪ አንድ ትራንስፎርመር ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የማከፋፈያ ጣቢያዎች የሪጅኖች ማስተባበሪያ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘውዱ አስማረ እንዳስታወቁት በማከፋፈያ ጣቢያው ላይ 125 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያለው አንድ ተጨማሪ ትራንስፎርመር ለማስቀመጥ እየተሰራ ነው። ትራንስፎርመሩን ለመትከል በአሁኑ ወቅት የትራንስፎርመሩ የተለያዩ አክሰሰሪዎች ከተቀመጡበት የአድዋ ማከፋፈያ ጣቢያ እና ትራንስፎርመሩን ከተቀመጠበት የአክሱም ከተማ ወደ ማከፋፈያ ጣቢያው የማጓጓዝ ሥራ ዛሬ እንደሚጀመር አስታውቀዋል። እንደ አቶ ዘውዱ ገለፃ ትራንስፎርመሩ ሲቀመጥ ከመቀሌ- አድዋ- አክሱም እና ከተከዜ- አክሱም ያለውን መስመር በቀለበት ሥርዓት በማስተሳሰር የግሪድ ሲስተሙን ለማጠናከር ያግዛል ብለዋል። የሰሜን ሪጅን የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ክፍለ ተስፋይ በበኩላቸው የአክሱም ማከፋፈያ ጣቢያ ከአድዋ እና ከተከዜ በሁለት ገቢ መስመሮች ኃይል እያገኘ ይገኛል ብለዋል። የመቀሌ- አደዋ- አክሱም ባለ 132 እና የተከዜ -አክሱም ባለ 230 ኪሎ ቮልት መስመር በቀለበት ያልተያያዘ በመሆኑ በአንዱ መስመር ላይ ኃይል ከተቋረጠ ከአክሱም እና አድዋ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል የሚያገኙ አካባቢዎች ኃይል እንደሚቋረጥባቸው ተናግረዋል። ትራንስፎርመሩ የመቀሌ -አድዋ መስመር በተለያዩ ምክንያቶች ሲቋረጥ ለአድዋ ከአክሱም እንዲሁም የተከዜ - አክሱም መስመር ሲቆረጥ ለአክሱም በአድዋ መስመር ኃይል በማቅረብ ለአካባቢዎቹ አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ እንደሚያስችል አስረድተዋል። እንደ አቶ ክፍለ ገለፃ ትራንስፎርመሩ ሲተከል ከተከዜ በባለ 230 ኪሎ ቮልት የሚገባውን ኃይል ወደ 132 በመቀየር አድዋ ከመቀሌና ከአክሱም ማከፋፈያ ጣቢያዎች በሁለት መስመር ኃይል የሚያገኝበትን ዕድል ይፈጥራል። የማከፋፈያ ጣቢያው ሦስት ትራንስፎርመሮች እንዲኖሩት ተደርጎ ዲዛይን የተደረገ እንደነበር ያስታወሱ የሥራ ኃላፊዎቹ በአሁኑ ወቅት የሚተከለው ሁለተኛው ትራንስፎርመር የፕሮጀክቱ አካል የነበረና በተለያዩ ምክንያቶች ሳይተከል የቆየ እንደሆነም አስታውቀዋል። የአክሱም ማከፋፈያ ጣቢያ በአሁኑ ወቅት ከ18 እስከ 20 ሜጋ ዋት ኃይል በመጫን ላይ የሚገኝ ሲሆን ሦስተኛው ትራንስፎርመር ሲተከል የጣቢያውን አቅም በእጥፍ እንደሚያሳድገውም ተገልጿል። የአክሱም ማከፋፈያ ጣቢያ ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ባለው አንድ ትራንስፎርመር አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም