en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 676 subscribers, ranking 8 043 in the Technologies & Applications category and 2 176 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 676 subscribers.

According to the latest data from 06 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 111 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.35%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.94% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 974 views. Within the first day, a publication typically gains 2 500 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 07 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 676
Subscribers
-124 hours
-157 days
+11130 days
Posts Archive
ለጥገና ሥራ ሲባል የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት እሁድ ህዳር 15 ቀን 2017 ዓ.ም በቃሊቲ 2 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ፤ በቡታጅራ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና በገፈርሳ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመሮች ላይ የጥገና ሥራ ይከናወናል፡፡ በተጨማሪም የለገጣፎ -ኮምቦልቻ 2ኛ መስመርን ኢነርጃይዝ የማድረግ ሥራ ይሠራል፡፡ ስለሆነም በተጠቀሰው ዕለት በቃሊቲ 2 የማከፋፈያ ጣቢያ በሚከናወነው የጥገና ሥራ በሃና ማርያም፣ በብሔረ ፅጌ፣ በአዲስ ጎማ ፋብሪካ፣ በሳሪስ፣ በቦሌ ቡልቡላ፣ በአዋሽ ቆዳ ፋብሪካ፣ በአዲስ ሰፈር፣ በኦሳካ ብረታብረት ፋብሪካ አካባቢ ከጠዋቱ 12፡00 እስከ ቀኑ 7፡00 ሰዓት ድረስ፤ እንዲሁም በቡታጅራ የማከፋፈያ ጣቢያ በሚከናወነው ጥገና በቡታጅራ፣ በወራቤ፣ በቡኢ እና በዙሪያው ባሉ አካባቢዎች ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 9፡00 ሰዓት ድረስ ኃይል ተቋርጦ ይቆያል፡፡ በገፈርሳ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በሚከናወነው የጥገና ሥራ ደግሞ ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 9፡00 ሰዓት ድረስ በፊቼ ከተማና አካባቢው ኤሌክትሪክ ተቋርጦ የሚቆይ ይሆናል፡፡ በተመሳሳይ ዕለት እሁድ ህዳር 15 ቀን 2017 ዓ.ም የለገጣፎ -ኮምቦልቻ 2ኛ መስመርን ኢነርጃይዝ የማድረግ ሥራ ስለሚከናወን ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት እስከ ጠዋት 1፡00 ሰዓት ድረስ በደብረብርሃን ከተማ፣ በሲኖ ብረታ ብረት ፋብሪካ እና በለሚ ሲሚንቶ ፋብሪካ ኤሌክትሪክ ተቋርጦ የሚቆይ በመሆኑ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ ከወዲሁ ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳስባለን፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 13 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ጣቢያዎቹ ከ72 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል አምርተዋል ......///...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአዋሽ ሁለትና ሦስት የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች በ2017 የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ከ72 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል ማምረታቸውን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለጹ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ጌታቸው አበበ እንደተናገሩት በሩብ ዓመቱ በአዋሽ ሁለት 24 ነጥብ 6 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማምረት ታቅዶ 17 ነጥብ 65 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል በማምረት የዕቅዱን 71 ነጥብ 73 በመቶ ማሳካት ተችሏል፡፡ በአዋሽ ሦስት ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ደግሞ 56 ነጥብ 32 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማምረት ታቅዶ 55 ነጥብ 25 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል በማምረት የ98 ነጥብ 11 በመቶ አፈጻጸም ተመዝግቧል፡፡ የአዋሽ ሁለት አፈጻጸሙ ዝቅ ሊል የቻለው ዓመታዊ ጥገና በሚከናወንበት ጊዜ በተርባይን ቤሪንግ ቫይብሬሽን ላይ የተከናወነው ጥገና ከታቀደው በላይ ጊዜ በመውሰዱ እና የክረምቱ የውሃ መጠን በማነሱ እንደሆነ ጠቁመዋል። የመጀመሪያው ሩብ ዓመት አፈጻጸም ከዕቅዱ ዝቅ ያለ ቢሆንም በአዋሽ ሦስት ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የተመረተው ኃይል ግን ካለፈው ሁለት በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከነበረው የኃይል ምርት የ 6 በመቶ ብልጫ ያለው ነው ብለዋል። ጣቢያዎቹ ከዕድሚያቸው አኳያ የመልሶ ግንባታ ሥራ የሚያስፈልጋቸው መሆኑን የተናገሩት አቶ ጌታቸው የታቀደውን ኃይል ለማማረት የሚያስችሉ የጥገና ሥራዎችን በማከናወን ውጤታማ ሥራ መሰራቱን ገልጸዋል። የአዋሽ ሁለት እና ሦስት የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እያንዳንዳቸው 32 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም አላቸው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 13 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

ችግሮችን በምክክር በመፍታት ምርታማነትን ማሳደግ ይገባል .........///......... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሥራ ላይ ሊከሰቱ የሚችሉ ችግሮችን በምክክር ለመፍታት የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ። ከተቋሙ የተለያዩ የሥራ ክፍሎች ለተውጣጡ የሥራ መሪዎች እና ሠራተኞች የተሰጠውን ሥልጠና በንግግር የከፈቱት በተቋሙ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ፍስሃ ጌታቸው እንደገለፁት ለሚፈጠሩ ችግሮች ወቅታዊ መፍትሔ ለመስጠት ምክክር የማይተካ ሚና ይኖረዋል። የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናው ጤናማ የሆነ ምክክር በማድረግ ተቋሙን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሻገር እንደሚያስችልም ጠቁመዋል። "የኢንዱስትሪ ማህበረሰብ ምክክር ለምርታማነት" በሚል ርዕስ ሥልጠናውን የሠጡት በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የማህበራዊ ምክክር ባለሙያ አቶ ጌታቸው ታምሩ እንደተናገሩት  ሥልጠናው በቀጣይ በተቋሙ የሚካሄዱ ምክክሮች ውጤታማ እንዲሆኑ በግብዓትነት ያግዛል። ምክክሩ አሰሪውና ሠራተኛው በተቋሙ ያሉ ችግሮችን በመፍታት ምርታማነትን ማዕከል ያደረገ የኢንዱስትሪ ግንኙነት እንዲፈጠር ያስችላል ብለዋል። እንደ ባለሙያው ገለፃ በምክክር ሂደቱ ላይ አሰሪ፣ ሠራተኛ እና መንግስት የሁለትዮሽና የሦሰትዮሽ ውይይቶችን በማድረግ መሳተፍ እንደሚጠበቅባቸው ጠቅሰዋል። የምክክር ሂደቱ "ከክርክር ወደ ምክክር፣ ከምክክር ደግሞ ወደ ምርታማነት" ለመሸጋገር ሚናው የጎላ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ምክክሩ የተቋም ምርታማነትና ተወዳዳሪነትን  ለማሳደግ፣ ማህበራዊ ፍትህን ለማረጋገጥ፣ የሥራ ባህል ለውጥ ለማምጣት፣ የአሰሪና ሠራተኛን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እና ምቹ የሥራ ከባቢ ለመፍጠር እንዲሁም የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመለየትና መፍትሔዎቻቸውን ለማመላከት እንደሚያግዝ አስረድተዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመረጃና ዕውቀት አስተዳደር ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ጌታቸው ከበደ እና የተቋሙ መሠረታዊ ሠራተኞች ማህበር ፀሐፊ አቶ ኃይሉ ወልዴ በበኩላቸው ምክክሩ ሠራተኛው ለተቋሙ ምርታማነት ማነቆ የሆኑ ጉዳዮችን በውይይት በመለየት ለችግሮቹ የመፍትሔ አማራጮቹን ለማስቀመጥ ይረዳል ብለዋል። በሥልጠናው ላይ የተሳተፉ ሠራተኞቸ እና የሥራ መሪዎች በየሥራ ክፍላቸው የሚካሄዱ ምክክሮችን በበላይነት እንደሚመሩ አስታውቀው ምክክሩ ውጤታማ እንዲሆንም ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። በዕለቱ በምክክር ሂደቱና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ከተሳታፊዎች ለተነሱ አስተያየቶችና ጥያቄዎች ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በመጡ ባለሙያዎች ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል። የተቋማትን ምርታማነት ለማሳደግ "የኢንዱስትሪ ማህበረሰብ ምክክር ለምርታማነት" የሚል ስትራቴጅ ተቀርጾ እየተሰራ ሲሆን ምክክሩም ህዳር 16 ቀን 2017 ዓ. ም እንደሚጀምር ለማወቅ ተችሏል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 12 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ ➡️ Link 1 ➡️ Link 2 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌ
የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ ➡️ Link 1 ➡️ Link 2 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 12 ቀን 2017 ዓ.ም

የማመንጫ ጣቢያውን ደህንነት ለመጠበቅ ሁሉም ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል ......///...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመልካ ዋከና የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን ደህንነት ለመጠበቅ ሁሉም ኃላፊነቱን እንዲወጣ የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ጥሪ አቀረቡ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ቴዎድሮስ በቀለ እንደገለጹት ከወሰን አለመከበር እና ከስርቆት ጋር ተያይዞ የማመንጫ ጣቢያው ደህንነት አደጋ ላይ ወድቋል። የጣቢያው ውሃው የሚተኛበት ቦታ ወይም ከሰዎች እና እንስሳት ንክኪ ነጻ እንዲሆን የተከለለውን አካባቢ በማለፍ የግድቡ ውሃ በሚቀንስበት በበጋ ወራት የእርሻ ሥራ መበራከቱ የግድቡን ደህንነት አደጋ ላይ እየጣለ መምጣቱን ገልጸዋል። ይህም ጣቢያው በደለል እንዲሞላ ከማድረጉም በላይ የግብርና ተረፈ ምረቱ ወደ ጣቢያው እየገባ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ቴዎድሮስ እንቅስቃሴው ውሃ ወደ ጣቢያው እንዳያልፍ እያደረገ ነው ብለዋል። እንደ አቶ ቴዎድሮስ ገለፃ የግብርና ተረፈ ምርቱና ገለባው ወደ ጣቢያው የማቀዝቀዣ ማሽኖች በመግባት እንዳይሰሩ ከማድረግ ባለፈ የሚፈጠረው ሙቀት ዕቃዎቹን እስከ ማቅለጥ መድረሱን ተናግረዋል። በዚህ የተነሳ ጣቢያው ሙሉ በሙሉ ከሦስት ቀን በላይ እንዲቆም ማድረጉን እና የኦፕሬሽን ሥራ ላይ እንቅፋት መፍጠሩን ገልጸዋል። ከዚህም ሌላ ከኃይል ማመንጫ ቤቱ እስከ ውሃ መቀበያው ወይም ኢንቴክ ያለው የመሬት ውስጥ መስመር እና ስዊች ያርዱንና ማመንጫ ቤቱን የሚያገናኙ መስመሮች ላይ የሚፈጸመው ስርቆትም ለጣቢያው ፈተና መሆናቸውን ተናግረዋል። የአካባቢው አባገዳ የሆኑት ሐጂ እንድሪስ ሐጂ ጉራሪ በበኩላቸው ማመንጫ ጣቢያው ለአካባቢው ማህበረሰብ የልማት መሰረት መሆኑን ገልጸዋል። የማመንጫ ጣቢያው መኖር ከተሞች እንዲስፋፉ፣ የመብራትና ውሃ አቅርቦት እንዲኖር፣ በአቅራቢያቸው ትምህርት ቤት እንዲከፈት በማድረግ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው አንስተዋል። በመሆኑም የማመንጫ ጣቢያውን ወሰን አልፎ ከማረስ እና ከስርቆት ጋር ተያይዞ እየተፈጠሩ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት ከህብረተሰቡ ጋር ውይይት እየተደረገ መሆኑን አባ ገዳ ሐጂ እንድሪስ ገልጸዋል። ከሚመለከታቸው የመስተዳድር አካላት እና ከማህበረሰቡ ጋር በመሆን የማመንጫ ጣቢያው ደህንነት ላይ ስጋት የደቀኑ ችግሮችን ለመፍታት መስራታቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 12 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ሁለተኛው ምዕራፍ የሳፕ ቴክኖሎጂ በይፋ መተግበር ጀመረ ………///……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን የተቋም ሀብት ዕቅድ ሥርዓት - ERP የሚያዘምነው የሳፕ ቴክኖጂ ሁለተኛ ምዕራፍ በተጠናቀቁ አስራ አንድ ሞጁሎች ዛሬ በይፋ መተግበር ጀምሯል፡፡ የተጠናቀቁን የአሰራር ሞጁሎች በይፋ ሥራ ያስጀመሩት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ ተቋሙን ከቴክኖሎጂ ጋር በማስተሳሰር ወደተሻለ ዲጂታል አሰራር ለማሸጋገር እተሰራ ነው፡፡ በመጀመሪያው ምዕራፍ የሳፕ ትግበራ ወቅት የታዩ ክፍተቶችን መሙላት እና ለአሰራር ምቹ ያልሆኑትን ማስተካከል በቀጣም በትኩረት እርምት መውሰድ እንደሚገባ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አሳስበዋል፡፡ የተቋሙ የሞደርናዜሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ገነቱ ደሳለኝ እንደተናገሩት ሁለተኛው ምዕራፍ ከፋይናንስ፣ ከንብረት አስተዳደር፣ ከቅጥርና ሰው ሀብት አስተዳደር ጋር ተያይዞ ከሚኖሩት 22 ሞጁሎች ውስጥ ሙሉ በሙሉ ተጠናቀው ወደ ተግባር የሚገቡት 11 ሞጆሎች ናቸው፡፡ ቀሪዎቹ 11 ሞጁሎች ጥቃቅን ማስተካከያ ተደርጎላቸው በቅርቡ ወደ ትግበራ እንዲገቡ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አቶ ገነቱ ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኢንፎርሜሽን ቺፍ ኦፊሰር አቶ ጌትነት ታደሰን ጨምሮ ጉዳዩ የሚመለከታቸው የሥራ ኃፊዎች ስለ ሞጁሎች ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የሥራ ኃለፊዎች ገለጻ አድርገዋል፡፡ ሞጁሎቹ ሙሉ በሙሉ ሲተገበሩ ጠንካራ የሀብት ቁጥጥር ስርዓት ለመዘርጋት፣ የተቋሙን ወጭ ለመቀነስና ሥራን ለማቀላጠፍ እና መረጃዎችን ለማጥራት እንዲሁም በተቋሙ የሚሰጡ አገልግሎቶችንና አሰራሮችን ለማዘመን ቁልፍ ሚና ይጫወታሉ፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 11 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

የሚከናወኑት የአካባቢያዊና ማህበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ ጥናቶች የፕሮጀክቶችን ተቀባይነት ከፍ ያደርጋል ……….///………… የኃይል መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ከመተግበራቸው በፊት የሚከናወኑ የአካባቢያዊና ማህበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ ጥናቶች በፕሮጀክቶች ትግበራ ወቅት የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመቅረፍ እያገዘ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአካባቢያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ ገለፀ፡፡ የቢሮው ተወካይ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋቀሳ ተሰማ እንደገለጹት ፕሮጀክቶች የሚገኙበትን አካባቢና የአካባቢውን የማህበረሰብ ደህንነት ለመጠበቅና ከለላ ለመስጠት ፕሮጀክቶች ከመተግበራቸው በፊት የአካባቢና ማህበረሰባዊ ተፅዕኖ ግምገማ ጥናቶች ይከናወናሉ፡፡ ጥናቶቹ በሀገሪቱ ያሉ የአካባቢያዊና ማህበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ አዋጅ፣ ደንብና መመሪያዎችን እንዲሁም የአበዳሪ ተቋማትን ፖሊሲና አሰራር መሰረት በማድረግ እንደሚከናወኑም ጠቅሰዋል፡፡ እንደ አቶ ዋቀሳ ገለፃ የአካባቢያዊና ማህበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ ጥናቶች ከፕሮጀክት ትግበራ ጋር ተያይዞ በአካባቢውና በማህብረሰቡ ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን ለማስወገድ ከፍተኛ ሚና ይኖራቸዋል፡፡ ጥናቶቹ በፕሮጀክት ትግበራ ጊዜ ሊከሰቱ ለሚችሉ ችግሮቹ እንደ ጉዳት ዓይነት እና መጠን በዕቅድ ላይ የተመሰረተ የመፍትሔ እርምጃዎችን ለመውሰድ ያግዛል ብለዋል። እየተከናወኑ ያሉ ጥናቶች ማህበረሰቡ በፕሮጀክቶች ዕቅድና አተገባበር ላይ እምነት እንዲኖረው በማድረግ የፕሮጀክቶችን ተቀባይነት እና አፈፃፀምን ከማሳደጉም ባለፈ በቀጣይ ለሚታቀዱ ሥራዎች በግብዓትነት እያገዘ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡ የጥናት ሥራው ውጤታማ እንዲሆን በየደረጃው ያሉ የመንግስት አካላትን እና ፕሮጀክቶች በሚካሄዱባቸው አካባቢ የሚገኙ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ በቅንጅት እንደሚከናወን ተወካዩ አመልክተዋል፡፡ በጥናቱ የተገኙ ውጤቶች በአግባቡ ተግባራዊ እንዲደረጉ ፕሮጀክቱን ለሚተገብረው ቢሮ ሰነዱ እንደሚሰጥና ቢሯቸውም በአፈጻጸሙ ላይ ክትትል እንደሚያደረግ አስታውቀዋል፡፡ በተያዘው በጀት ዓመት የ19 የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች እና 11 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ጥናት ለማከናወን መታቀዱን አቶ ዋቀሳ ጠቁመዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 11 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ቡድኑ ወደ አሸናፊነት ተመልሷል ..........///........ የኢትዮ-ኤሌክትሪክ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን የሀምበርቾ አቻውን አንድ ለባዶ አሸንፏል። ዛሬ ከቀኑ 9 ሰዓት በአዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ስቴዲየም በተከናወነው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ማህሌት ምትኩ በ30ኛው ደቂቃ የኢትዮ-ኤሌክትሪክን ብቸኛ ጎል አስቆጥራለች። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ፍፁም የጨዋታ የበላይነት ባሳየበት በዚህ ጨዋታ የአማካኝ ቦታ ተጫዋችዋ ዙፋን ደፈርሻ የጨዋታው ኮከብ በመሆን ሽልማት ተበርክቶላታል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ5ኛ ሳምንት መርሃግብር ከባህርዳር ከነማ ጋር በመጪው ህዳር 16 ቀን 2017 ዓ.ም  ጨዋታውን የሚያከናውን ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 10 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

ሰባት የመንግሥት ተቋማት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መስሪያ ቤትን ጎበኙ ........///....... በገንዘብ ሚኒስቴር እና በመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ስር የሚገኙ ከሰባት ተቋማት የተውጣጡ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መስሪያ ቤትን ጎበኙ። በጉብኝቱ ወቅት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያሉትን ሀብቶች ወደ ልማት በመቀየር ለሠራተኞቹ ምቹ የሥራ አካባቢ መፍጠር ችሏል። ተቋሙ በምስራቅ አፍሪካ ትልቁ የኃይል አስተላላፊ ለመባል በቅቷል ያሉት ዋና ሥራ አስፈፃሚው በቀጣይም ፍኖተ ካርታ በማዘጋጀት በአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ለመሆን እየሰራ ይገኛል ብለዋል። እንደ ኢንጂነር አሸብር ገለፃ ተቋሙ በራሱ አቅም በጎረቤት ሀገራት በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ዙሪያ የማማከር እና የመገንባት ዕቅድ ይዞ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። በሀገሪቱ እያደገ የመጣውን የኃይል ማመንጨት አቅም ታሳቢ ያደረገ ዘመናዊ የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ግንባታ እየተከናወነ እንደሆነም ነው የገለፁት። ተቋሙ ከስያሜ ጀምሮ በርካታ ተግዳሮቶች እየገጠሙት እንደሚገኙ የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈፃሚው ከካሳ ክፍያ እና ከኃይል መሰረተ ልማት ስርቆት ጋር ያሉትን ችግሮች ለመቅረፍ የሚመለከታቸው ሁሉ እገዛ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ ለጎብኚዎች ስለ ተቋሙ ወቅታዊ አቋም ገለፃ አድርገዋል። አቶ አንዱዓለም በገለፃው ላይ እንደተናገሩት ባለፉት ስድስት ዓመታት የሀገሪቱ የኢነርጂ ምርት በአማካይ የ8 በመቶ  እንዲሁም የተቋሙ ዓመታዊ ገቢ በ34 በመቶ  ዕድገት አሳይቷል። በቀጣይ ዓመታት 825 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው ስድስት የንፋስ እንዲሁም 775 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው አምስት የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ለመገንባት ዕቅድ መያዙን አቶ አንዱዓለም ገልፀዋል። እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ በቀጣይ ሦስት ዓመታት 1 ሺህ 038 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና 27 አዳዲስ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን በመገንባት በ60 ኪሎሜትር ርቀት የኃይል አቅርቦት ተደራሽነትን ወደ 91 በመቶ ለማሳደግ ይሰራል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቀጣዮቹ ዓመታት የአፍሪካ የኃይል የልህቀት ማዕከል ለመገንባት ማቀዱንም ነው የጠቀሱት። የገንዘብ ሚኒስትር ልዩ አማካሪና የጉብኝቱ አስተባባሪ አቶ ሐጂ ኢብሳ በበኩላቸው  የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሠራተኛው ምቹ የሥራ ቦታ ለመፍጠር ያከናወናቸው ሥራዎች የሚደነቁ በመሆናቸው ሌሎች ተቋማት ከዚህ ልምድ መውሰድ እንደሚገባቸው ተናግረዋል። ተቋሙ እያከናወናቸው ስለሚገኙ ሥራዎችና በስትራቴጂክ ዕቅዶቹ ዙሪያ ስለተደረገላቸው ገለፃም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በጉብኝቱ ላይ ከገንዘብ ሚኒስቴር፣ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ኮርፖሬሽን፣ ከኢትዮጵያ ፖስታ ድርጅት፣ ከመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር፣ ከኢትዮ-ኢንጂነሪንግ ግሩፕና ከኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን እንዲሁም ከኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት የተውጣጡ ከ400 በላይ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ተሳትፈዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 10 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

photo content
+9

ሠራተኛው በሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ላይ ግልፅ ግንዛቤ በመጨበጥ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ ቀረበ ……...///…….. የመንግስትን ፖሊስ የሚያስፈጽሙ ሠራተኞች በመላው ሀገሪቱ በሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ላይ ግልፅ ግንዛቤ በመጨበጥ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሳሰቡ፡፡ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ኢንጂነር አሸበር አሸበር ባልቻ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ባካሄዱት ውይይት ማጠቃለያ ላይ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት በኮቪድ፣ በዓለም የኢኮኖሚ ቀውስ፣ በእርስ በእርስ ግጭት እና በመሳሰሉት ችግሮች ውስጥ ሆና ዕድገት አስመዝግባለች፡፡ የተመበዘገበው ዕድገት ትሩፋቶቸና የመጣው ለውጥ ሀገራችን የገጠማትን ተግዳሮቶች አልፋ መሄድ እንደምትችል ከማሳየት ባለፈ ለውጡ በተቋሙ በግልጽ የሚታይ እንደሆነም አስረድተዋል፡፡ የተቋሙ ሠራተኞች ከጨለምተኛ አመለካከት ወጥተው ትክክለኛ መረጃ በመያዝ ለአላስፈላጊ ነጣለ ትርክት ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከለውጡ በፊት ምን ደረጃ ላይ እንደነበር የሚዘጋ አይደለም ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው ከለውጡ በኋላ በምን ያህል መስዋትነት እና ቁርጠኛ አመራር አሁን ላለበት ደረጃ መብቃቱ ተጨባጭ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ይሁንና ተቋሙ በፕሮጀክቶች አፈጻጸም እና መዘግየት የሚያጋጥሙትን ከፍተቶች ለማስወገድ የሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች በትኩረት እንዲሰሩ አቅጣጫ መቀመጡን ገልፀዋል፡፡ ስለሆነም ሠራተኞች የሚመለከቷቸውን የብልሹ አሰራር ክፍተቶች የሚያሳዩ ማስረጃዎችን በመያዝ ድርጊቱን እንዲዋጉ ኢንጂነር አሸብር ጠይቀዋል፡፡ በውይይቱ ከሠራተኞች የተነሱትን የተለያዩ ጥያቄዎች ዋና ሥራ አስፈጻሚው እና ሌሎች የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች ምላሽ ሰጥተውባቸዋል ፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች ካካሄዱት ውይይት ጎን ለጎን የደም ልገሳ አካሂደዋል፡፡ የደም ልገሳ መርሃግብሩ በተለያዩ ምክንያቶች ደም ለሚያስፈልጋቸው የህብረተሰብ ክፍሎች እንዲውል ታስቦ የተዘጋጀ ነው፡፡ መርሃ ግብሩን አስመልክቶ ንግር ያደረጉት በደምና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት የትምህርት እና የቅስቀሳ ባለሙያ ሲስተር አሰጋሽ ጎሳ እንደተናገሩት ደም በፋብሪካ የማይመረት በመሆኑ በደም አጦት ማንም ሰው ህይወቱን ሊያጣ አይገባም፡፡ ሠራተኛው የወገን ደራሽነቱን ደም በመለገስ በተግባር ማሳየት እንደሚገባው የተናገሩት ባለሙያዋ ደም በለገስ ከኮሌትሮል፣ ከደም ውስጥ የብረት መጠን ክምችት፣ ከካንሰርና ከሌሎች በሽታዎች የመታደግ የጤና ጠቀሜታዎች እንዳሉት አስረድተዋል፡፡ ደም የሚሞት እና የሚያረጅ እንዲሁም የሚተካ በመሆኑ በሚተካ ደም የማይተካ የሰው ህይወት ልናድንበት ይገባል ብለዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 09 ቀን 2017 ዓ.ም