EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 560 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 357,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 160 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 560 名订阅者。
根据 26 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 27,过去 24 小时变化为 -7,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.05%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.01% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 053 次浏览,首日通常累积 2 491 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 8。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 27 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 560
订阅者
-724 小时
+147 天
+2730 天
帖子存档
15 550
ተቋሙ በኤሌክትሮ መካኒካል ዘርፍ ያሰለጠናቸውን 44 ቴክኒሺያኖች አስመረቀ
…….///…….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለአራት ወራት በኤሌክትሮ መካኒካል የትምህርት ዘርፍ ያሰለጠናቸውን 44 ቴክኒሺያኖች በዛሬው ዕለት አስመርቋል።
የተቋሙን ዋና ሥራ አስፈፃሚ በመወከል በምረቃ ሥነ- ሥርዓቱ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን እንደተናገሩት ተቋሙን በአህጉርና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና አስተማማኝ የኃይል አቅራቢ ለማድረግ የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡
የተቋሙን ርዕይ ለማሳካት የሥልጠና ማዕከሉን ውጤታማ የሚያደርግ የአጭር፣ የመካከለኛና የረጅም ጊዜ ስትራቴጅ ተነድፎ እየተሰራ እንደሆነ አንስተዋል፡፡
በዕውቀት፣ በክህሎት እና በአመለካከት የዳበረ ሠራተኛ ለመፍጠር የማሰልጠኛ ማዕከሉን በአሰራር፣ በግብዓት እና በአደረጃጀት የማዘመን ሥራ ተጠናክሮ እንደሚከናወን አቶ ሞገስ አረጋግጠዋል፡፡
በተቋሙ የሰው ሀብት ልማት መምሪያ ዳይሬክተር ወንድወሰን ካሳ (ዶ/ር) በበኩላቸው የኤሌክትሮ መካኒካል ሥልጠናው ሠልጣኞች ወደ ሥራ ዓለም ከመግባታቸው በፊት ስለ ተቋሙና ስለሚያከናውኑት ሥራ በቂ ግንዛቤ የሚያስይዝ ነው ብለዋል፡፡
በሥልጠናው ይዘትና አሰጣጥ ላይ ማሻሻያዎችን በማድረግ ከሠልጣኞች የአመለካከት ለውጥ ጋር የተያያዙ ባህሪያዊ ሥልጠናዎች መካተታቸውንም አመልክተዋል፡፡
በሥልጠናው ላይ ከታዳጊ ክልሎች እንዲሁም በተለያየ ምክንያት የሰው ኃይል ካልተሟሉባቸው የሥራ አካባቢዎች በልዩ ሁኔታ ሠልጣኞች እንዲመለመሉ መደረጉንም አንስተዋል፡፡
በተቋሙ የሠው ኃይል ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ አቶ ተማም አፍደል በበኩላቸው ተቋሙ የሶስት ዓመት ግሪድ ስትራቴጅ በመቅረጽ ወደ ተግባር መግባቱን በማስታወስ ዕቅዱን ለማሳካት የዛሬ ተመራቂዎች ድርሻቸው የጎላ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
ተመራቂዎቹ በኦፕሬሽን ዘርፎች ላይ የሚስተዋለውን የሰው ኃይል ፍላጎት ክፍተት ለማሟላት ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወቱም ጠቁመዋል፡፡
በተቋሙ የስልጠናና ልማት ማዕከል ሥራ አስኪያጅ አቶ ደምስ ሰይፉ የሥልጠና ማዕከሉ ተቋሙ እንደ አዲስ ከተቋቋመበት ከ2008 ዓ.ም ጀምሮ 800 የሚሆኑ ሠልጣኞችን በዘርፉ በማሰልጠን በኦፕሬሽን የሥራ ዘርፎች ላይ እንዲሳተፉ ማድረጉን አስታውቀዋል፡፡
በተያዘው በጀት ዓመት ማዕከሉ 39 ወንድና 5 ሴት ሠልጣኖችን በኤሌክትሮ ሜካኒካል የትምህርት ዘርፍ ማስመረቁን ተናግረዋል፡፡
ለምረቃ ከበቁት ሰልጣኞች መካከል አስሩ ከአርብቶ አደር አካባቢ የመጡ መሆናቸውን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ ይህንንም ታሳቢ በማድረግ የማደሪያ ቦታ፣ የኪስ ገንዘብ፣ የትራንስፖርትና የውሃ አቅርቦት እንደተመቻችላቸው ተናግረዋል፡፡
እንደ አቶ ደምስ ገለፃ ተመራቂዎቹ በስልጠና ቆይታቸው ከሥራው ጋር ግንኙነት ያላቸው ኮርሶችን በንድፈ ሃሳብና በተግባር በተደገፈ መልኩ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና ልምድ ባላቸው የተቋሙ ሠራተኞች ወስደዋል፡፡
በማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እና የተቋሙ መሠረታዊ የሠራተኛ ማህበር ፀሐፊ አቶ ኃይሉ ወልዴ በፕሮግራሙ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ተመራቂዎቹ ተቋሙ የነደፈውን ስትራቴጅ ለማሳካት ከፍተኛ አደራ እንደተጣለባቸው ተገንዝበው ለተቋሙ ምርታማነት የበኩላቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡
ተመራቂዎቹ በሚሰማሩበት የሥራ መስክ የሚሰጣቸውን ኃላፊነት ሙያዊ ስነ-ምግባርን በተላበሰና የሙያ ደህንነትን ባከበረ መልኩ በትጋትና በቅንነት ተቋሙን እንደሚያገለግሉ ቃል ገብተዋል።
በዕለቱም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተመራቂዎች እና ለመምህራን የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 30 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
ፕሮጀክቱን በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው
……//…..…
በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ሞጆ ከተማ አቅራቢያ በመገንባት ላይ የሚገኘው የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ግንባታን በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡
ሥራ አስኪያጁ አቶ ቴዎድሮስ ጋሻው እንደገለጹት ለገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ኃይል ለማቅረብ የሚገነባው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የጀነሬተር እና የመቆጣጠሪያ ክፍሎች ግንባታ እየተከናወነ ነው።
የኦፕሬተሮች መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ተጠናቆ የማጠናቀቂያ ሥራዎችን መጀመራቸውን ተናግረዋል፡፡
የማከፋፈያ ጣቢያውን የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ለማስቀመጥ የሚያግዙ 250 የሚሆኑ የመሠረት ቁፋሮ ሥራዎች ተጠናቆ የኮንክሪት ሙሌት ስራ እየተከናወነ መሆኑንም ገልፀዋል።
የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎቹ በተያዘው ዕቅድ መሠረት ሳይት ከደረሱ ፕሮጀክቱን እስከመጭው ሐምሌ 30 ድረስ ሙሉ ለሙሉ ለማጠናቀቅ ታቅዶ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
የፕሮጀክቱ ሳይት መሀንዲስ አቶ ቢኒያም ግርማ በበኩላቸው የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኃይል አቅርቦት ፕሮጀክት በታቀደለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች እተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በተለያዩ ምዕራፎች የሚቀርብ 575 ሜጋ ቮልት አምፔር ኃይል እንደሚፈልግ የተናገሩት አቶ ቢኒያም በመገንባት ላይ የሚገኘው የማከፋፈያ ጣቢያ በመጀመሪያው ምዕራፍ 252 ሜጋ ቮልት አምፔር ኃይል ለማቅረብ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል።
የኤሌክትሮ ሜካኒካል ግንባታውን ለመጀመር የሚያስችሉ ዕቃዎች የዲዛይን ሥራ ተጠናቆ በፍብረካ ሂደት ላይ ይገኛል ያሉት አቶ ቢኒያም የማከፋፈያ ጣቢያው የሲቪል ግንባታ 37 በመቶ፣ አጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም ደግሞ 26 በመቶ መድረሱን ገልፀዋል።
የፕሮጀክቱ ተቆጣጣሪ መሀንዲስ አቶ ለሜሣ ረጋሣ በበኩላቸው የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኃይል አቅርቦት ኘሮጀክት የሲቪል ስራ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ እና የጥራት ደረጃ እየተከናወነ ነው ብለዋል።
የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የማከፋፈያ ጣቢያ በተቋሙ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ እየተገነቡ ካሉ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ መሆኑን የጠቀሱት የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ሰሎሞን ኃ/ጊዮርጊስ ለሌሎች ፕሮጀክቶች ማሳያ በሚሆን መልኩ እየተገነባና ክትትል እየተደረገበት ስለመሆኑም ተናግረዋል።
እንደዚህ ዓይነት ፕሮጀክቶችን በተቋሙ በራስ ኃይል እንዲከናወኑ የተቋሙ የሥራ አመራር እና ቦርድ ለሰጠው ዕድልና ኃላፊነትም ምስጋና አቅርበዋል።
ፕሮጀክቱ በገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ባለስልጣን በሚሸፈን ከ840 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል መምሪያ እየተገነባ ይገኛል።
ፕሮጀክቱ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ እንዲሁም 2 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የኃይል ማስተላለፍያ መስመር ግንባታን ያካተተ ነው፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 30 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
ፕሮጀክቱን በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው
……//…..…
በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ሞጆ ከተማ አቅራቢያ በመገንባት ላይ የሚገኘው የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ግንባታን በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡
ሥራ አስኪያጁ አቶ ቴዎድሮስ ጋሻው እንደገለጹት ለገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ኃይል ለማቅረብ የሚገነባው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የጀነሬተር እና የመቆጣጠሪያ ክፍሎች ግንባታ እየተከናወነ ነው።
የኦፕሬተሮች መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ተጠናቆ የማጠናቀቂያ ሥራዎችን መጀመራቸውን ተናግረዋል፡፡
የማከፋፈያ ጣቢያውን የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ለማስቀመጥ የሚያግዙ 250 የሚሆኑ የመሠረት ቁፋሮ ሥራዎች ተጠናቆ የኮንክሪት ሙሌት ስራ እየተከናወነ መሆኑንም ገልፀዋል።
የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎቹ በተያዘው ዕቅድ መሠረት ሳይት ከደረሱ ፕሮጀክቱን እስከመጭው ሐምሌ 30 ድረስ ሙሉ ለሙሉ ለማጠናቀቅ ታቅዶ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
የፕሮጀክቱ ሳይት መሀንዲስ አቶ ቢኒያም ግርማ በበኩላቸው የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኃይል አቅርቦት ፕሮጀክት በታቀደለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች እተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በተለያዩ ምዕራፎች የሚቀርብ 575 ሜጋ ቮልት አምፔር ኃይል እንደሚፈልግ የተናገሩት አቶ ቢኒያም በመገንባት ላይ የሚገኘው የማከፋፈያ ጣቢያ በመጀመሪያው ምዕራፍ 252 ሜጋ ቮልት አምፔር ኃይል ለማቅረብ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል።
የኤሌክትሮ ሜካኒካል ግንባታውን ለመጀመር የሚያስችሉ ዕቃዎች የዲዛይን ሥራ ተጠናቆ በፍብረካ ሂደት ላይ ይገኛል ያሉት አቶ ቢኒያም የማከፋፈያ ጣቢያው የሲቪል ግንባታ 37 በመቶ፣ አጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም ደግሞ 26 በመቶ መድረሱን ገልፀዋል።
የፕሮጀክቱ ተቆጣጣሪ መሀንዲስ አቶ ለሜሣ ረጋሣ በበኩላቸው የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኃይል አቅርቦት ኘሮጀክት የሲቪል ስራ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ እና የጥራት ደረጃ እየተከናወነ ነው ብለዋል።
የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የማከፋፈያ ጣቢያ በተቋሙ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ እየተገነቡ ካሉ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ መሆኑን የጠቀሱት የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ሰሎሞን ኃ/ጊዮርጊስ ለሌሎች ፕሮጀክቶች ማሳያ በሚሆን መልኩ እየተገነባና ክትትል እየተደረገበት ስለመሆኑም ተናግረዋል።
እንደዚህ ዓይነት ፕሮጀክቶችን በተቋሙ በራስ ኃይል እንዲከናወኑ የተቋሙ የሥራ አመራር እና ቦርድ ለሰጠው ዕድልና ኃላፊነትም ምስጋና አቅርበዋል።
ፕሮጀክቱ በገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ባለስልጣን በሚሸፈን ከ840 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል መምሪያ እየተገነባ ይገኛል።
ፕሮጀክቱ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ እንዲሁም 2 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የኃይል ማስተላለፍያ መስመር ግንባታን ያካተተ ነው፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 30 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
የማከፋፈያ ጣቢያው የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ማስቀመጫ የኮንክሪት ሙሌት እየተከናወነ ነው
…....///.......
የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ማስቀመጫ መሰረት የኮንክሪት ሙሌት እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ አስታወቀ።
በዘርፉ የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሰሎሞን ኃ/ጊዮርጊስ እንደተናገሩት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ኮንትራት ወስዶ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ በሞጆ ከተማ ዙሪያ እየገነባ ይገኛል።
የጣቢያውን የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ማስቀመጫ የኮንክሪት ሙሊት ሥራ በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ ለኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራው ዝግጁ ለማድረግ ከመከላክያ ግንባታ ግብዓቶች ማምረቻ ድርጅት ጋር ስምምነት በመፈጸም የኮንክሪት ሙሌት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል።
ስምምነቱ 1 ሺ ሜትር ኪዩብ ኮንክሪት የማቅረብና የሁለት ወራት ርዝማኔ እንዳለው የጠቆሙት አቶ ሰለሞን የአንድ መቶ ሃምሳ ሜትር ኪዩብ የኮንክሪት ሙሊት ሥራው መጠናቀቁንም ተናግረዋል።
ቀሪውን የኮንክሪት ሙሊት ሥራ በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እንደሚደረግ ገልጸዋል።
የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ ጋሻው በበኩላቸው 250 የሚሆኑ የማከፋፈያ ጣቢያው የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ማስቀመጫ የመሠረት ቁፋሮ ሥራ በአጭር ጊዜ በማከናወን የ132 ፓዶች የኮንክሪት ሙሌት መጠናቀቁን አብራርተዋል።
የቀሪ ፓዶችና የአራት ትራንስፎርመሮች ማስቀመጫ መሠረት የኮንክሪት ሙሌት ሥራዎች በቀጣይ ቀናት እንደሚከናወን ተናግረዋል።
የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች በምርት ሂደት ላይ እንደሚገኙ የተናገሩት ኃላፊው የኮንክሪት ሙሌት ሥራውን በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ ዕቃዎቹ ሳይት እንደደረሱ የተከላ ሥራ እንደሚጀመር ጠቁመዋል።
የመከላከያ ግንባታ ግብዓቶች ማምረቻ ድርጅት የፍሬሽ ኮንክሪት ምርት ቴክኒክ ባለሙያ አቶ ሄኖክ ሻሜሮ በበኩላቸው ድርጅቱ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር ስምምነት በመፈጸም ሲ - 30 የተሰኘ ጥራቱን የጠበቀ የኮንክሪት ዓይነት እያቀረበ መሆኑን ተናግረዋል።
ተቋማቱ በትብብር መስራታቸው ሥራው ጥራቱን በጠበቀ መልኩ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ እንደሚያግዝ የጠቆሙት ባለሙያው በቀጣይም ድርጅታቸው ከተቋሙ ጋር በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡
በሞጆ ከተማ አቅራቢያ እየተገነባ የሚገኘው የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የማከፋፍያ ጣቢያ ፕሮጀክት 190 ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ ዕድል ፈጥሯል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ;
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 29 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
በማከፋፈያ ጣቢያዎች የተተከሉት የኢነርጂ ሜትሮች የኃይል አቅርቦቱን በአንድ ማዕከል ለመቆጣጠር ያግዛሉ
…….//….
የኢትየጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የተከላቸው የኢነርጂ ሜትሮች የኃይል አቅርቦቱን በአንድ ማዕከል ለመቆጣጠር የሚያግዙ መሆናቸውን የኃይል ማስተላለፊያዎችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና ዘርፍ አስታወቀ፡፡
በዘርፉ የዲጂታላይዜሽንና አቅም ማሳደግ ፕሮጀክት-2 ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሃይማኖት ተፈራ እንደገለፁት ተቋሙ የኃይል ሽያጭ ሥርዓቱን የሚከታተልባቸው የኢነርጂ ሜትሮች በሁሉም ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ተክለዋል፡፡
ተቋሙ የኢነርጂ ሜትሮችን በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ከመትከሉ በፊት ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኃይል ሽያጩን ያከናውን የነበረው በ40/60 የቀመር ስሌት ከአጠቃላይ ገቢ ላይ 60 በመቶውን ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰጥበት አሰራር እንደነበር አስታውሰዋል፡፡
በዚህም ተቋማቱ ከኃይል ሽያጭ ማግኘት የሚገባቸውን ትክክለኛ ገቢ ለማወቅ የማይችሉበት አሰራር ይከተሉ እንደነበረ ነው ሥራ አስኪያጇ የገለፁት፡፡
ወ/ሮ ሃይማኖት አክለውም አሰራሩ ለኃይል ብክነት ከመጋለጡም ባሻገር በተቋሙና በከፍተኛ የኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች መካከል አለመግባባትና አለመተማመኖችን ፈጥሮ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት 1 ሺህ 472 የኢነርጂ ሜትሮች በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ መተከላቸውንና በዚህም ከከፍተኛ የኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ጋር መግባባትና መተማመን መፈጠሩን ጠቁመዋል፡፡
የኢነርጂ ሜትሮቹ ከማከፋፈያ ጣቢያዎቹ ለደንበኞች የቀረበውን ኃይል በማረጋገጥ ተቋሙ በአግባቡ ገቢውን እንዲሰበስብ አስችለዋል ያሉት ሥራ አስኪያጇ የኃይል ብክነትን በመቀነስ በኩልም ጉልህ ሚና መጫወታቸውን ተናግረዋል፡፡
ቀደም ሲል የኢነርጂ ሜትሮችን የተከላና የፍተሻ ሥራ ያከናወነው ሲመንስ ሊሚትድ የተባለ ኩባንያ መሆኑን ያወሱት ወ/ሮ ሃይማኖት ኩባንያው ባልደረሰባቸው የሰሜን እና ምዕራብ ሪጅኖች ላይ የራስ አቅምን በማጎልበት የተከላና ፍተሻ ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰዋል፡፡
የኢነርጂ ሜትሮች የሳይበር ደህንነት ቅድመ ሁኔታዎችን እንዲያሟሉ ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በትብብር መሰራቱን ገልፀው በመሳሪያዎቹ የሳይበር ጥቃትን ለመከላከል የሚያስችል የክትትል ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ;
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 29 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
የመስክ ምልከታው በጣቢያዎቹ ላይ ለሚስተዋሉ ችግሮች መፍትሔ ለመስጠት ያግዛል
….///….
በሰሜን ሪጅን በሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች የተካሄደው የመስክ ምልከታ በጣቢያዎቹ የሚስተዋሉ ችግሮችን በተደራጀ መልኩ መፍትሔ ለመስጠት እንደሚያስችል በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ገለፀ።
በዘርፉ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ የሥራ ኃላፊዎች በሪጅኑ ከሚገኙ 9 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ውስጥ በመቐለ፣ አቢ ዓዲ፣ አድዋ፣ አክሱም፣ አዲግራት እና ውቅሮ ጣቢያዎች ላይ የመስክ ምልከታ አካሂደዋል፡፡
በመስክ ምልከታው ወቅት የመንገድ፣ የመኖሪያ ቤት፣ የውሃ አቅርቦት፣ የትራንስፎርመር ብልሽት፣ የብሬከር እጥረትና ብልሽት፣ የጣቢያዎች አቅም ማነስና የመሳሰሉ ችግሮች መኖራቸውን ማረጋገጥ እንደተቻለ በዘርፉ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ ገልጸዋል፡፡
የመስክ ምልከታው ችግሮች መኖራቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ በሪጅኑ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚገኙ የመለዋወጫ ዕቃዎችን ከአንዱ ወደ አንዱ በማዘዋወር መፍትሔ የሚሰጥበት ግብዓት መገኘቱንም ጠቁመዋል፡፡
በመስክ ምልከታው የታዩና በሪጅኑ የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ወደ መፍትሔ እንደሚገባም ነው አቶ ጋሻው ያስረዱት፡፡
እንደ አቶ ጋሻው ገለፃ በጣቢያዎቹ የተካሄደው የመስክ ምልከታ ከኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎች እንዲሁም ከሌሎች አስተዳደራዊ ጉዳዮች ጋር ተያይዘው በሪጅኑ ለሚነሱ ጥያቄዎች ተገቢውን መፍትሔ ለመስጠትና የሠራተኞቹን የሥራ ተነሳሽነት ለማሳደግ ያግዛል፡፡
በመምሪያው የማከፋፈያ ጣቢያዎች ማስተባበሪያ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘውዱ አስማረ በበኩላቸው የመስክ ምልከታው ጣቢያዎቹ የኦፕሬሽን ሥራዎችን የሚያካሂዱበትን ሁኔታ ለመገምገምና ለሥራዎች ማነቆ የሆኑ ችግሮችን ለይቶ መፍትሔ ለመስጠት ያለመ ነው፡፡
በጣቢያዎቹ ላይ የተለያዩ ችግሮች መኖራቸውን እንደተመለከቱ የተናገሩት አቶ ዘወዱ ከተለዩ ችግሮች አብዛኛዎቹ በሪጅኑ አቅምና በዘርፉ የሚፈቱ መሆናቸውንም አመልክተዋል፡፡
በሰሜን ሪጅን የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ክፍለ ተስፋይ ምልከታው ሪጂኑ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች በማረጋገጥ መፍትሔ ለመስጠት እና ተቀራርቦ የመስራት ሁኔታውን ለማጠናከር እንደሚያግዝ ገልፀው ተቋሙ በሪጅኑ ለሚስተዋሉ ችግሮች አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጥ ጠይቀዋል፡፡
በየጊዜው የሚያጋጥሙ ችግሮችን በወቅቱ ለመፍታት የመስክ ምልከታው ተጠናክሮ እንዲቀጥልም አሳስበዋል፡፡
የሥራ ኃላፊዎቹ በሪጅኑ ከሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች በተጨማሪ የመሶቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያን የኦፕሬሽን ሥራ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ;
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 28 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
ዘርፉ ከደቡብ ምዕራብ ሪጅን የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ጋር ውይይት ማካሄድ ጀመረ
……....///……….
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ከደቡብ ምዕራብ ሪጅን የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ጋር በሪጅኑ እየተከናወኑ ስላሉ ሥራዎች እና ተግዳሮቶች ዙሪያ በጅማ ከተማ ውይይት ማካሄድ ጀምሯል፡፡
መስከረም 27 እና 28 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ውይይት ላይ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ የሥራ ኃፊዎች፣ በሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና የሥራ ኃፊዎችና ሠራተኞች ይሳተፋሉ ተብሏል፡፡
በመምሪያው የማከፋፈያ ጣቢያዎች ማስተባበሪያ ሁለት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘውዱ አስማረ እንደተናገሩት ውይይቱ በሪጅኑ እየተከናወኑ የሚገኙ ሥራዎችን በመገምገም ጠንካራ ጎኖቹን ለማስቀጠል እና ለችግሮቹ የመፍትሔ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ ነው።
ውይይቱ በሪጅኑ በሚገኙ የማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በሚከናወኑ ሥራዎች ላይ ዘርፉ በዕቅድ ላይ የተመዘረተ ድጋፍና ክትትል የሚያደርግበትን አግባብ ለመዘርጋት እንደሚያግዝም ጠቁመዋል፡፡
አቶ ዘውዱ እንዳሉት ውይይቱ ከኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎች ጋር የተያያዙ ችግሮች በሪጅኑ እና በዘርፉ በጋራ የሚቀረፉበትን አሰራር ከመዘርጋት ባለፈ የሪጅኑ ሠራተኞቹ ያሉባቸውን ችግሮች በመረዳት ለችግሮቹ የመፍትሔ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ይረዳል፡፡
ውይይቱ ከኃይል ማስተላለፊያ መስመር የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ጋር ዛሬ ከሰዓት የተጀመረ ሲሆን በነገው ዕለት ደግሞ ከማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽንና ጥገና የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ጋር የሚካሄድ ይሆናል፡፡
ከመስከረም 20 እስከ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ከሰሜን ሪጅን የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ጋር ተመሳሳይ ውይይት መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን በቀጣዩ ሳምንት ደግሞ ከደቡብ 1 ሪጅን ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች ጋር ውይይቱን ለማካሄድ መርሃ ግብር ተይዟል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ;
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቁጥር ኢ.ኤ.ኃ/8.4/22/16 ነሐሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በሾፌር-1ኛ (ጡረተኛ) የስራ መደብ ለውጭ አመልካቾች ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡
ስለሆነም በወጣው ማስታወቂያ መሰረት ከዚህ በላይ ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ ጥቅምት 04 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ ብረታብረት ፊትለፊት ዋናው መ/ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ ስለሆነ በፈተናው ቦታ ላይ እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡
ማሳሰቢያ፦ በፈተና ሰዓት የእጅ ስልካችሁን (ሞባይል) ይዞ መግባት ፈጽሞ የተከለከለ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ;
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም
15 550
ለአክሱም ማከፋፈያ ጣቢያ ተጨማሪ ትራንስፎርመር ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ ነው።
……....///……….
በአክሱም ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተጨማሪ አንድ ትራንስፎርመር ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን በተቋሙ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ።
በዘርፉ የማከፋፈያ ጣቢያዎች የሪጅኖች ማስተባበሪያ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘውዱ አስማረ እንዳስታወቁት በማከፋፈያ ጣቢያው ላይ 125 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያለው አንድ ተጨማሪ ትራንስፎርመር ለማስቀመጥ እየተሰራ ነው።
ትራንስፎርመሩን ለመትከል በአሁኑ ወቅት የትራንስፎርመሩ የተለያዩ አክሰሰሪዎች ከተቀመጡበት የአድዋ ማከፋፈያ ጣቢያ እና ትራንስፎርመሩን ከተቀመጠበት የአክሱም ከተማ ወደ ማከፋፈያ ጣቢያው የማጓጓዝ ሥራ ዛሬ እንደሚጀመር አስታውቀዋል።
እንደ አቶ ዘውዱ ገለፃ ትራንስፎርመሩ ሲቀመጥ ከመቀሌ- አድዋ- አክሱም እና ከተከዜ- አክሱም ያለውን መስመር በቀለበት ሥርዓት በማስተሳሰር የግሪድ ሲስተሙን ለማጠናከር ያግዛል ብለዋል።
የሰሜን ሪጅን የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ክፍለ ተስፋይ በበኩላቸው የአክሱም ማከፋፈያ ጣቢያ ከአድዋ እና ከተከዜ በሁለት ገቢ መስመሮች ኃይል እያገኘ ይገኛል ብለዋል።
የመቀሌ- አደዋ- አክሱም ባለ 132 እና የተከዜ -አክሱም ባለ 230 ኪሎ ቮልት መስመር በቀለበት ያልተያያዘ በመሆኑ በአንዱ መስመር ላይ ኃይል ከተቋረጠ ከአክሱም እና አድዋ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል የሚያገኙ አካባቢዎች ኃይል እንደሚቋረጥባቸው ተናግረዋል።
ትራንስፎርመሩ የመቀሌ -አድዋ መስመር በተለያዩ ምክንያቶች ሲቋረጥ ለአድዋ ከአክሱም እንዲሁም የተከዜ - አክሱም መስመር ሲቆረጥ ለአክሱም በአድዋ መስመር ኃይል በማቅረብ ለአካባቢዎቹ አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ እንደሚያስችል አስረድተዋል።
እንደ አቶ ክፍለ ገለፃ ትራንስፎርመሩ ሲተከል ከተከዜ በባለ 230 ኪሎ ቮልት የሚገባውን ኃይል ወደ 132 በመቀየር አድዋ ከመቀሌና ከአክሱም ማከፋፈያ ጣቢያዎች በሁለት መስመር ኃይል የሚያገኝበትን ዕድል ይፈጥራል።
የማከፋፈያ ጣቢያው ሦስት ትራንስፎርመሮች እንዲኖሩት ተደርጎ ዲዛይን የተደረገ እንደነበር ያስታወሱ የሥራ ኃላፊዎቹ በአሁኑ ወቅት የሚተከለው ሁለተኛው ትራንስፎርመር የፕሮጀክቱ አካል የነበረና በተለያዩ ምክንያቶች ሳይተከል የቆየ እንደሆነም አስታውቀዋል።
የአክሱም ማከፋፈያ ጣቢያ በአሁኑ ወቅት ከ18 እስከ 20 ሜጋ ዋት ኃይል በመጫን ላይ የሚገኝ ሲሆን ሦስተኛው ትራንስፎርመር ሲተከል የጣቢያውን አቅም በእጥፍ እንደሚያሳድገውም ተገልጿል።
የአክሱም ማከፋፈያ ጣቢያ ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ባለው አንድ ትራንስፎርመር አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ;
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
