en
Feedback
ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

Open in Telegram

ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።

Show more
638
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-1130 days
Posts Archive
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ እንኳን #ለሰሞነ_ሕማማት_ለመጀመርያ_ቀን #ለአንጾሖተ_ቤተ_መቅደስ (ለቤተ መቅደስ መንጻት) እና መርገመ በለስ በሰላም አደረሰን።                ❤ #ዕለተ_ሰኑይ_ሰኞ። ❤ ይህ ዕለት አንጾሖተ ቤተ መቅደስ የቤተ መቅደስ መንጻት እና መርገመ በለስ የተፈጸመበት ዕለት ነው፡፡ ማር.11-11፣ ማቴ.21-18-22 ሉቃ.13-6-9፡፡ ❤ ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ "ወመሰለ ሎሙ ወይቤሎሙ አሐዱ ብእሲ በለሰ ቦቱ ውስተ አጸደ ወይኑ ወየሐውር ይንሣእ ፍሬሃ ወኢይረክብ ...፤ ይህንም ምሳሌ አለ ለአንድ ሰው በወይኑ አትክልት የተተከለች በለስ ነበረችው ፍሬም ሊፈልግባት ወጥቶ ምንም አላገኘም"። ሉቃ13፥6 በማለት በበለስ ስለተመሰለ የሰው ልጅ ሕይወት በማሰብ እንዲመለስ ንስሐ እንዲገባ በሕይወትም እንዲኖር እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ማሳሰቡን ያጠይቃል፡፡ ❤ ንስሐ አልገባም አልመለስም ያለም በለሷ እንደጠወለገችና እንደተቆረጠች ሁሉ ፍሬ ባለማፍራታቸው እንደሚቆረጡ እንዲሁም ወደ እሳት እንደሚጣሉ መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ያስረዳል፡፡ ❤ በለስ የተባለች ቤተ እስራኤል ፍሬ የተባለ ደግሞ ሃይማኖትና ምግባርን ነው፡፡ ሁላችን ቤተ እስራኤላውያን ፍሬ ሃይማኖት ወምግባር አስተባብረን ይዘን መገኘት ይገባናል፡፡ ❤ ፍሬ አልባ እንዳንሆን ጌታ ሲመጣም እንዳናፍር የመጽሐፉን ቃል ልንጠብቅና ልንፈጽም ይገባናል፡፡ በዚህ የሕማማት የመጀመሪያ ቀን ዕለተ ሰኑይ የምናስበው የምንዘክረው የሰው ልጅ ሕይወት በከንቱ በቸልተኝነት እንዳይደክም እንዳይጠወለግ እንዳይደርቅ ወደ እሳትም እንዳይጣል ማድረግ ይገባናል፡፡ ❤ እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ፃዕማ ወድካም አመ ከመዮም ያብጽኀነ ያብጽዕክሙ እግዚአብሔር በፍስሃ ወበ ሰላም አሜን። ❤ መልካም የሰሞነ ሕማማት የጾምና የስግደት ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ እንኳን #ለሰሞነ_ሕማማት_ለመጀመርያ_ቀን #ለአንጾሖተ_ቤተ_መቅደስ (ለቤተ መቅደስ መንጻት) እና መርገመ በለስ በሰላም አደረሰን።                ❤ #ዕለተ_ሰኑይ_ሰኞ። ❤ ይህ ዕለት አንጾሖተ ቤተ መቅደስ የቤተ መቅደስ መንጻት እና መርገመ በለስ የተፈጸመበት ዕለት ነው፡፡ ማር.11-11፣ ማቴ.21-18-22 ሉቃ.13-6-9፡፡ ❤ ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ "ወመሰለ ሎሙ ወይቤሎሙ አሐዱ ብእሲ በለሰ ቦቱ ውስተ አጸደ ወይኑ ወየሐውር ይንሣእ ፍሬሃ ወኢይረክብ ...፤ ይህንም ምሳሌ አለ ለአንድ ሰው በወይኑ አትክልት የተተከለች በለስ ነበረችው ፍሬም ሊፈልግባት ወጥቶ ምንም አላገኘም"። ሉቃ13፥6 በማለት በበለስ ስለተመሰለ የሰው ልጅ ሕይወት በማሰብ እንዲመለስ ንስሐ እንዲገባ በሕይወትም እንዲኖር እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ማሳሰቡን ያጠይቃል፡፡ ❤ ንስሐ አልገባም አልመለስም ያለም በለሷ እንደጠወለገችና እንደተቆረጠች ሁሉ ፍሬ ባለማፍራታቸው እንደሚቆረጡ እንዲሁም ወደ እሳት እንደሚጣሉ መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ያስረዳል፡፡ ❤ በለስ የተባለች ቤተ እስራኤል ፍሬ የተባለ ደግሞ ሃይማኖትና ምግባርን ነው፡፡ ሁላችን ቤተ እስራኤላውያን ፍሬ ሃይማኖት ወምግባር አስተባብረን ይዘን መገኘት ይገባናል፡፡ ❤ ፍሬ አልባ እንዳንሆን ጌታ ሲመጣም እንዳናፍር የመጽሐፉን ቃል ልንጠብቅና ልንፈጽም ይገባናል፡፡ በዚህ የሕማማት የመጀመሪያ ቀን ዕለተ ሰኑይ የምናስበው የምንዘክረው የሰው ልጅ ሕይወት በከንቱ በቸልተኝነት እንዳይደክም እንዳይጠወለግ እንዳይደርቅ ወደ እሳትም እንዳይጣል ማድረግ ይገባናል፡፡ ❤ እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ፃዕማ ወድካም አመ ከመዮም ያብጽኀነ ያብጽዕክሙ እግዚአብሔር በፍስሃ ወበ ሰላም አሜን። ❤ መልካም የሰሞነ ሕማማት የጾምና የስግደት ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።                   @Teamihokidusan

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #መጋቢት ፳፰ (28) ቀን። ❤ እንኳን #ለጻድቁ_ለታላቁ_ንጉሥ የክርስቶስ መስቀል ላገኘችው ለንግሥት ለቅድስት ዕሌኒ ልጅ #ለቅዱስ_ቈስጠንጢኖስ ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓልና #ለአርእስተ_አበው_ለቅዱሳን_ለአብርሃም፣ #ለይስሐቅና_ለያዕቆብ ለበዓላቸው መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰ።                                                      ✝ ✝ ✝ ❤ #ታላቁ_ንጉሥ_ቅዱስ_ቈስጠንጢኖስ፦ የዚህ ቅዱስ የአባቱ ስም ቊንስጣ የእናቱም ስም ቅድስት ዕሌኒ ነው። ቊንስጣም በራንጥያ ለሚባል አገር ንጉሥ ነው። መክስምያኖስም በሮሜ በአንጾኪያ በግብጽ ላይ ነግሦ ነበር። ❤ ይህም ቊንስጣ አረማዊ ነበር፤ ግን በጎ ሥራ ያለው እውነትን የሚወድ በልቡናውም ይቅርታና ርኅራኄን የተመላ ክፉት የሌለበት ነበር። ወደ ሮሐ ከተማ በሔደ ጊዜ ቅድስት ዕሌኒን አይቶ ሚስት ልትሆነው አገባት እርሷም ክርስቲያናዊት ናት። ንጉሥ ቈስጠንጢኖስንም ፀንሳ ወለደችው ስሙንም ቈስጠንጢኖስ ብላ ጠራችው ይህም ዝንጉርጒር ማለት ነው። ❤ ከዚህም በኋላ ንጉሥ ቊንስጣ ዕሌኒን በዚያም ትቷት ወደ በራጥያ ከተማ ተመለሰ። እርሷም ልጇን እያሳደገች በዚያው ኖረች የክርስትናን ትምህርት አስተማረችው ይቅርታንና ርኅራኄን በክርስቲያን ወገኖች ላይ እንዲያደርግ በልቡናው ትዘራበት ነበር። እርሷ ክርስቲያን ስትሆን የክርስትና ጥምቀትን ታጠምቀው ዘንድ አልደፈረችም መንፈሳዊ ዕውቀትን ሁሉ ለማስተማር አሳደገችው ዳግመኛም ለመንግሥት ልጆች የሚገባውንም ሁሉ። ❤ ከዚያም በኋላ ወደ አባቱ ሰደደችው አባቱም በአየው ጊዜ ደስ ተሰኘበት ዕውቀትን የተመላ ሁኖ አግኝቶታልና በበታቹም መስፍን አድርጎ ሹሞ በመንግሥቱ ሥራ ላይ ሁሉ ሥልጣን ሰጠው። ❤ ከሁለት ዓመትም በኋላ አባቱ ዐረፈ ቈስጠንጢኖስም መንግሥቱን ሁሉ ተረከበ የቀና ፍርድንም የሚፈርድ ሆነ ከእርሱ በፊት የነበሩ ነገሥታት የጫኑባቸውን ጽኑ አገዛዝ ከሰዎች ላይ አስወገደ። አሕዛብም ሁሉ ታዘዙለት ወደዱትም የአገዛዙ ቅንነትና የፍርዱ ትክክለኛነት በአገሮች ሁሉ እስቲሰማ ተገዙለት። ❤ የሮሜ ሰዎች ታላላቆች መልክትን ወደርሱ ላኩ ከከሀዲ መክስምያኖስ ጽኑ አገዛዝ እንዲያድናቸው እየለመኑ እርሱ አሠቃይቷቸው ነበርና። መልእክታቸውንም በአነበበ ጊዜ ስለ ደረሰባቸው መከራ እጅግ አዘነ ያድናቸውም ዘንድ ምን እንደሚያደርግ በዐደባባይ ተቀምጦ እያሰበ ሲያዝን እንሆ ከቀኑ በስድስት ሰዓት በቀትር ጊዜ ኅብሩ እንደ ከዋክብት የሆነ መስቀል ታየው በላዩም በዮናኒ ቋንቋ "ኒኮስጣጣን" የሚል ጽሑፍ አለ ትርጓሜውም በዚህ ጠላትህን ድል ታደርጋለህ ማለት ነው። የመስቀሉም ብሔር የፀሐይን ብርሃን ሲሸፍነው በአየ ጊዜ አደነቀ። በላዩ ስለተጻፈውም አስቦ ለጭፍሮቹ አለቆችና ለመንግሥቱ ታላላቅ ባለሥልጣኖች አሳያቸው። እርሱም ቢሆኑ ይህ መስቀል ስለምን እንደተገለጠ አላወቁም። ❤ በዚያችም ሌሊት የእግዚአብሔር መልአክ ለቈስጠንጢኖስ በራእይ ተገልጦ እንዲህ አለው "በቀኑ እኩሌታ በቀትር በአየኸው በዚያ መስቀል አምሳል ላንተ ምልክት አድርግ በርሱም ጠላትህን ድል ታደርጋለህ" አለው። ከእንቅልፉም በነቃ ጊዜ ልቡ ጸና የወርቅ መስቀልም አሠርቶ በነገሠበት ዘውድ ላይ አደረገው መኳንንቱንና ወታደሮቹን ጭፍሮቹን ሁሉ መስቀል ሠርተው በጦር መሣሪያቸው ላይ ያደርጉ ዘንድ አዘዛቸው እርሱም እንዳዘዛቸው አደረጉ። ❤ ይህም የሆነው በበራንጥያ በነገሠ በሰባተኛ ዓመት ነው። የሮሜን ሰዎች ከሥቃያቸው ሊያድናቸው ሥራዊቱን ሰብስቦ ተነሥቶ ወጣ። መክስምያኖስም ሰምቶ በታላቅ ወንዝ ላይም ታላቅ ድልድይ ሠርቶ ወደ ቈስጠንጢኖስም ተሻግሮ ከእርሱ ጋር ተዋጋ። የመስቀሉም ምልክት ቀድሞ በታየ ጊዜ የመክስምያኖስ ሠራዊት ድል ይሆኑ ነበር የቈስጠንጢኖስ ሠራዊት ከመክስምያኖስ ሠራዊት ብዙ ሰው ገደሉ። የቀሩትም ሸሽተው ሲሔዱ ከመክስምያኖስ ጋር ሊሻገሩትና ወደ ወሜ ሊገቡ ድልድይ ላይ ወጡ ድልድዩም ፈርሶ ፈርዖን ከሠራዊቱ ጋራ እንደ ሠጠመ እንዲሁ መክስምያኖስ ከሠራዊቱ  ጋራ ሠጠመ። ❤ ቈስጠንጢኖስም ወደ ሮሜ ከተማ ሲገባ የሮሜ ሰዎች ከካህናት ጋራ መብራቶች ይዘው በዕንቊ የተሸለሙ አክሊሎችን ደፍተው እምቢልታ እየነፋ ተቀበሉት የተማሩ ሊቃውንትም የከበረ መስቀልን ሲያመሰግኑት የአገራችን መዳኛ ይሉት ነበር ለከበረ መስቀልም ሰባት ቀን በዓል አደረጉ። ❤ ቈስጠንጢኖስም ዳግመኛ በሮሜ ነገሠ ከሀዲዎች የሆኑ መክስምያኖስና ዲዮቅልጥያኖስ ስለ ክብር ባለቤት ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሃይማኖት ያሠሩሯቸውን እሥረኞች ሁሉንም ፈታቸው ደግሞ የጣዖታት ቤቶች ይዘጉ አብያተ ክርስቲያናት ይከፈቱ ብሎ ዓዋጅ አስነገረ። ዳግመኛም ክርስቲያኖችን እንዲያከብሯቸው እንዲ እንዳያዋርዷቸው የጣዖታቱንም ገንዘብና ምድራቸውን በአረማውያን ላይ እንዲሾሙ አደረገ። ዳግመኛም አባቶቻችን ሐዋርያት እንዘዙ ማንም ሰው በሰሙነ ሕማማት ሥራ እንዳይሠራ አዘዘ። ❤ በነገሠ በዐሥራ አንድ ዓመት በሮሜ ሊቀ ጳጳሳት በሶል ጴጥሮስ እጅ የክርስትና ጥምቀትን ተጠመቀ። ሠራዊቱም ሁሉ ይህም የከበረ መስቀል ከተገለጠለት በኋላ በአራት ዓመት ነው። ❤ ከዚህ በኋላም በእርሱ ርዳታና ድል ያገኘበትን የሚያድን ስለ ሆነ ስለ ጌታችን መስቀል ትመረም ዘንድ እናቱ ቅድስት ዕሌኒን ወደ ኢየሩሳሌም ላካት። እርሷም ዓመፀኞች አይሁድ ቀብረው ከደፈኑት ቦታ አወጣችው። ❤ በዘመኑ ሃይማኖታቸው የቀና የሦስት መቶ ዐሥራ ስምንት ጳጳሳት የአንድነት ስብሰባ በኒቅያ ስለ አርዮስ ተደረገ። ለክርስቲያኖች መመሪያ በበጎ አሠራር ክርስቲያናዊት ሥርዓት ተሠራች። ❤ ከዚህም በኋላ በበራንጥያ ታላቅ ከተማ ሊሠራ አሰበ እንደ አሰበውም ታላቅ ከተማ ሠርቶ በስሙ ቊስጥንጥንያ ብሎ ጠራት። በውስጧም አምላክን በወለደች በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ስም በአግያና በሶፍያም ታላቅ ቤተ ክርስቲያን ሠራ መንፈሳዊ በሆነ በመልካም ጌጥ ሁሉ አስጌጣት በውስጥዋ ከሐዋርያት የብዙዎቹን ዓፅም ከሰማዕታትና ከቅዱሳን ጻድቃን ሥጋቸውን ስለሚሰበስብ። ❤ የክብር ባለቤት ጌታችንን ደስ አሰኝቶ መልካም ተጋድሎውን ከፈጸመ በኋላ በኒቆምድያ ከተማ ጥቂት ታሞ መጋቢት28 ዐረፈ።ገንዘውም በወርቅ ሣጥን አድርገው ተሸክመው ወደ ከቊስጥንጥንያ አደረሱት የጳጳሳት አለቆችና ካህናቱ ከሁሉ ሕዝብ ጋር ወጥተው ተቀበሉት በብዙ ጸሎት በመዘመርና በማኅሌት በምስጋና ወደ ከበሩ ሐዋርያት ቤተ መቅደስ አስገብተው በክብር አኖሩት። የቅዱስ ቈስጠንጢኖስም በረከቱ ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት28 ስንክሳር።

                                                        ✝ ✝ ✝  ❤ #ዑደት_ሲጀመር_የቤተ_መቅደስ_ምስባክ፦ "ብሩክ ዘይመጽእ በስመ እግዚአብሔር። ባረክናክሙ እመቤተ እግዚአብሔር። እግዚእ አስተርአየ ለነ"። መዝ 117፥26-27። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 19፥1-11።                             ✝ ✝ ✝  ❤ #የምዕራብ_በኩል_ምስባክ፦ "ተፈሣሕኩ እስመ ይቤሉኒ ቤተ እግዚአብሔር ነሐውር። ወቆማ እገሪነ ውስተ አዕፃድኪ። ኢየሩሳሌምሰ ሕንፅት ከመ ሀገር"። መዝ 121፥1-2። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 21፥1-17።                            ✝ ✝ ✝  ❤ #የደቡብ_በኩል_ምስባክ፦ "እምአፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሐተ። በእንተ ጸላኢ። ከመ ትንሥቶ ለጸላኢ ወለገፋዒ"። መዝ 8፥2-3። የሚነበበው ወንጌል ማር 11፥1-11።                            ✝ ✝ ✝  ❤ #የምሥራቅ_በኩል_ምስባክ፦ "እምሥራቀ ፀሐይ እስከ ዓረብ። ወእምጽዮን ስነ ስብሐቲሁ። እግዚአብሔርሰ ገሃደ ይመጽእ"። መዝ 49፥1-2። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 19፥28-48።                            ✝ ✝ ✝  ❤ #የሰሜን_በኩል_ምስባክ፦ "ትሴብሖ ኢየሩሳሌም ለእግዚአብሔር። ወሰብሒዮ ለአምላክኪ ጽዮን። እስመ አፅንዐ መናሥግተ ኆኃትኪ"። መዝ 147፥1-2። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 12፥12-19። መልካም የሆሳዕና በዓልና የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ እንኳን #ለክብር_ባለቤት_ለጌታችን_ለአምላካችን_ለመድኃኒታችን_ለኢየሱስ_ክርስቶስ ከዘጠኙ ዐበይት በዓል አንዱ ለሆነው፤ ለዐቢይ ጾም ስምንተኛ ሳምንት #ለሆሣዕና በዓል እግዚአብሔር በሰላምና በጤና አደረሰን።                            ✝ ✝ ✝  ❤ #የዚህ_ሳምንት_የሆሣዕና_መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ በ፭ "ወእንዘ ሰሙን በዓለ ፋሲካ ቀርቡ አርዲኢሁ ለአምላከ ጽድቅ ኀበ #ደብረ_ዘይት_ሙራደ_ዐቀብ_ሀገረ_እግዚአብሔር ወተቀበልዎ ሕዝብ ብዙኀን አዕሩግ ወሕፃናት ነሢኦሙ አዕፁቀ በቀልት #እንዘ_ይብሉ_ሆሣዕና_በአርያም ተፅዒኖ ዲበ ዕዋል ቦአ ሀገረ ኢየሩሳሌም በትፍሥሕት ወበሐሤት ይሁቦሙ ኀይለ ወሥልጣነ። ትርጉም፦ "በፋሲካ ሰሞን የጽድቅ አምላክ ደቀ መዛሙርት #የእግዚአብሔር_ሀገር_ወደምትኾን_ወደ_ደብረ_ዘይት አቅራቢያ ቀረቡ፤ ብዙ ሕዝብ፣ ብዙ አዛውንትና ሕፃናት የዘንባባ ዝንጣፊ ይዘው #ሆሣዕና_በአርያም_እያሉ ተቀበሉት፤ ኀይልን ይሰጣቸው ዘንድ በአህያ ውርንጫ ተቀምጦ በፍጹም ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ገባ። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በጾመ_ድጓው_ላይ።                              ✝ ✝ ✝  ❤ #ሆሣዕና፦ ማለት የዕብራይስጥ ቃል ነው፤ "ሆሻአና" ሲባል ትርጒሙም "አቤቱ አሁን አድን" ማለት ነው። የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ኢየሩሳሌም ከተማ ገብቶ ቤተ መቅሱን በአህያ ግልገል ተቀምጦ በመዞር ሆሣዕና እያሉ እንዲያመሰግኑት አድርጓል። ይህም ስርሱ እየአንዳንዳቸው በዘመናቸው ነቢያት የተናገሩት ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ነው። ❤ ያዕቆብ በክርስቶስ ስለ ተመሰለው ስለ ልጁ "ይሁዳ አህያውን ዘይት ዕንጨት ላይ ያሥራል ውርንጫውንም በወይን አረገ" አለ። ዘካርያስም "ጽዮን ልጅ አትፍሪ እነሆ ንጉሥሽ በአህያ ግልገል ተቀምጦ ይመጣል" አለ። ❤ ኢሳይያስ "ንጉሥሽ ጻድቅ የዋህ የሆነ ይመጣል ዋጋውም ከእርሱ ጋራ ነው ሥራውም በፊቱ የተገለጠ ነው በአህያ ግልገልም ላይ ይቀመጣል" አለ። ❤ አብርሃምም የሰሌን ዝንጣፊ ይዞ መሠውያውን በዞረ ጊዜ "ይችን ዕለት ተድላ ደስታ የሚደረግባት የእግዚአብሔር በዓል" ብሎ ጠራት። ❤ ዳዊትም "ከሕፃናትና ከልጆች አንደበት ምስጋናን አዘጋጀህ" አለ። ሰሎሞንም "የሕፃናት አንደበታቸው የተቃናች ሆነች" አለ። ሁለተኛም "ልጆችና ሽማግሌዎች በኢየሩሳሌም ይጫወታሉ ምርጒዛቸውም መትከያዎችሽን አስፍተሽ ድንኳኖችሽን ዘርጊ" ያለም አለ። ❤ ይህንንም የትንቢት ነገር ለመፈጸም በከረ ወንጌል እንተጻፈ ጌታ በአህያዋና በውርንጭላዋ ላይ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ገባ። ወደ ኢየሩሳሌም ሊገባ በቀረበ ጊዜ የደብረ ዘይት አጠገብ ከምትሆን ቤተ ፋጌ ደረሰ ደብረ ዘይት ወደሚባል ቢታንያም በደረሰ ጊዜ ከደቀ መዛመቱን ሁለቱን ላከ። "ወደ ፊታችሁ ወዳለ አገር ሒዱ በገባችሁም ጊዜ ሰው ያልተቀመጠበት አህያ ግልገል ታገኛላችሁ ፈትታችሁ አምጡልኝ። ለምን ትፈቱታላችሁ የሚል ሰው ቢኖር ጌታው ይሻዋል" በሉ። የተላኩትም በሔዱ ጊዜ እንደነገራቸው አገኙ። የአህያውም ግልገል ፈቱ ጌቶቹም "ለምን ትፈቱታላችሁ" አሏቸው። "ጌታው ይሻዋል" አሉ። ወደ ጌታ ኢየሱስም ይዘውት ሔዱ ልብሳቸውንም በአህያው ግልገል ላይ ጐዘጐዙ ጌታችንም አስቀመጡት። ቅጠል ቆርጠው በመንገድ ላይ የጐዘጐዙ ብዙዎች ናቸው። ልብሳቸውንም በመንገድ ላይ ያነጠፋ አሉ። በፊትም በኋላ ይሔዱ የነበሩት በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ የተባረከ መድኃኒት ነው ብለው አሰምተው ተናገሩ። በእግዚአብሔር ስም የምትመጣ የአባታችን ዳዊት መንግሥትም የተባረከች ናት። ❤ ጌታ ኢየሱስም ወደ ኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ ገባ ሕዝቡም ሁሉ አዩት በመሸም ጊዜ ከዐሥራ ሁለቱ ደቀመዛሙርት ጋር ወደ ቢታንያ ወጣ። በነጋውም ከቢታንያ በወጣ ጊዜ ተራበ። በሩቅም ቅጠል ያላትን በለስ አየ። በርሷ ፍሬ ያገኝ እንደሆነ ሊያይ ሔደ ወደርሷም በደረሰ ጊዜ ከቅጠል ብቻ በቀር ያገኘው የለም የበለስ ወራት አልነበረምና "ዘላለም ካንቺ ፍሬ የሚበላ አይኑር" አላት። ደቀ መዛሙርቱም ሰሙ። ❤ ወደ ኢየሩሳሌም ደርሶ ወደ ቤተ መቅደስ ገባ በምኵራቡም ግቢ የሚገበያዩትን ያስወጣ ጀመረ የለዋጮችንም ሰደቃቸውን ገለበጠ ርግብ የሚሸጡትንም ወንበራቸውን። ወደ ምኵራብ ለንግድ ገንዘብ ይዘው እንዳይገቡ ከለከለ። "ቤተ ለአሕዛብ ሁሉ የጸሎት ቤት ይሁን የሚል መጽሐፍ ያለ አይደለምን እናንተ ግን የሌቦችና የወንበዴዎች ዋሻ አደራጋችሁት" ብሎ አስተማራቸው። ❤ ቅዱስ ዮሐንስም እንዲህ አለ "አልዓዛርን ከሙታን ለይቶ ካስነሣው በኋላ። በነጋውም እሑድ ለበዓል የመጡ ሰዎች ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ኢየሩሳሌም እንዲመጣ በሰሙ ጊዜ። የሰሌን ዛፍ ዝንጣፊ ይዘው ከኢየሩሳሌም ፈጥነው ወጡ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ከአርያም የተገኘ መድኃኒት የእስራኤል ንጉሥ የተባረከ ነው" እያሉ እየጮኹ ተቀበሉት። ❤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የአህያ ግልገል አገኘ።ተቀመጠበትም እንደ ተጻፈ እንዲ ሲል። "የጽዮን ልጅ አትፍሪ እንሆ ንጉሥሽ በአህያ ግልገል ተቀምጦ ይመጣል"። አስቀድሞ ግን ደቀ መዛሙርቱ ይህን ነገር አላወቁም ነበር ጌታ ሳይሰቀል። ጌታ በተሰቀለ ጊዜ ይህ የተጻፈ ስለ እርሱ እንደሆነ ያን ጊዜ አወቁት እንጂ እንዲህም አደረጉለት። ❤ አልዓዛር አልዓዛር ብሎ ከሙታን ለይቶ እንዳስነሣው ባስነሣው ጊዜ ከእርሱ ጋር የነበሩ ሰዎች መሰከሩለት። ስለዚህም ሕዝቡ አመኑበት። ያደረገውን ተአምራት ሰምተወልና የሕፃናቱንም ምስጋና ደግሞ አልዓዛርን ማስነሣቱን። የካህናቱ አለቆችና ፈሪሳውያን ግን እርስ በርሳቸው "የምታገኙት ረብሕ ጥቅም እንደሌለ አታውቁምን እንሆ ሰው ሁሉ አመነበት" አሉ። ❤ ቅዱሳን ማቴዎስና ማርቆስ የሰሌንን ነገር አላወሱም ሌሎች ከእንጨቶች ቅጠሎችን እየቆረጡ በመንገድ ውስጥ ጐዘጐዙ አሉ እንጂ። ❤ ቅዱስ ሉቃስም ቅጠልን ወይም ሰሌንን አላወሳም ሲሒዱ ልብሳቸውን በመንገድ ላይ ይጐዘጒዙ ነበር አለ እንጂ። ❤ ቅዱስ ዮሐንስ ግን ለብቻው "ከኢየሩሳሌም ከሰሌን ዛፍ ላይ ዘንባባ ቆርጠው ያዙ" አለ። ሰሌንም በኢየሩሳሌም አልነበረም ጌታችን ሕፃን ሁኖ ሳለ ወደ ግብጽ በወረደ ጊዜ ከእናቱ ቡርክት ቅድስት ከሆነች ከእመቤታችን ድንግል ማርያም ጋር እስሙናይን ከሚባል አገር ደረሱ ከዚያም ሰሌን አገኙ። ጌታችንም ከሥርዋ ተነቅላ ሒዳ በደብረ ዘይት ላይ እንድትተከል አዘዛት ያንጊዜ ወደ አየር ወጥታ በረረች ሒዳም በዚያ በደብረ ዘይት ተተከለች ከእርስዋም ወስደው የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ተቀበሉት። ❤ ጌታችንም የሆሣዕናን ዑደት በአሳየ ጊዜ የአይሁድ ወገን ቅናት ይዟቸው በሚገድሉት ገንዘብ ምክንያት ፈለጉ። ለእርሱም ምስጋና ይሁን በእኛ ላይም ይቅርታው ቸርነቱ ይደረግልን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት 22 ስንክሳር።                                                      ✝ ✝ ✝  ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "እምአፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሐተ። በእንተ ጸላኢ። ከመ ትንሥቶ ለጸላኢ ወለገፋዒ"። መዝ 8፥2። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 9፥11-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 4፥1-12 እና የሐዋ ሥራ 28፥11-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 12፥1-11 ወይም ዮሐ 5፥11-31። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ባስልዮስ ወንድሜ የቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘኑሲስ ቅዳሴ ነው።

❤ ነፍሱ ወደ ሰማይ መላእክት ሲያሳርጓት ሰይጣናት እየተከተሉ "መቃሪ ሆይ አሸነፍከን አሸነፍከን" እያሉ ሲጮኹ አባ መቃርስ "እስከ ዛሬ ገና ነኝ በጌታዬ በቀኙ ልቁም በግራው አላወኩምና" ብሎ በትሕትና መለሰላቸው፡፡ ወደ ገነትም ሲገባ "መቃሪ ሆይ አሸነፍከን ብለው በታላቅ ድምፅ ጮኹ" እርሱም "የክብር ባለቤት ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ይመስገን ስሙም ይባረክ ከእጃችሁ ያዳነኝ" አላቸው ፡፡ ከአባታችን ከአባ መቃርስ ረድኤትና በረከት ያሳትፈን፡፡ በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፡- የመጋቢት27 ስንክሳር እና ታላቁ ቅዱስ መቃርዮስ የተጋድሎ ሕይወቱና ትምህርቱ።                                 ✝ ✝ ✝ ❤ #አቡነ_ጊዮርጊስ_ዘጣና፦ ሀገራቸው ጣና ዘጌ ነው። በዋሻ ውስጥ አርባ ዘመን ሙሉ ዘግተው ሲኖሩ መና ከሰማይ እየወረደላቸው ውሃም በዋሻ ውስጥ ፈልቆላቸው ይኖሩ ነበር። አንድ ቀን መልአክ መጥቶ ምን ቢጋደሉ የጌታችንን ስጋውን በልተው ደሙን ካልጠጡ እንደማይድኑ ነገራቸው። በመልአኩም ትዕዛዝ መሰረት ከዋሻው ወጥተው ሊቆርቡ ቤተ ክርስቲያን ገቡ በቅዳሴም ላይ ሳሉ አንድ ድንቅ ምስጢር ተመለከቱ ይህም በጸሎተ ሐሙስ ዕለት ካህኑ "ሀበነ" ሲል ጌታችን በዕለተ አርብ እንተ ተሰቀለ ሆኖ ደሙ ሲፈስ የካህኑ እጅ በደም ተነክሮ በመንበሩ ቆሞ ቢያዩት በድንጋጤ ሳይቀሳቀሱ አርባ ዓመት ተኝተዋል ይህም በሰው አቆጣጠር በጌታችን ዘንድ ግን ምን ያይህል ጊዜ እንደ ሆነ እራሱ ባለቤቱ ያውቀዋል። በመጨረሻም ጻድቁ በዐረፉ ጊዜ መቃብራቸውን አራዊት ቆፍረውላቸው መነኮሳቱ ገንዘው ቀብረዋቸዋል። ታቦታቸው በጣና ይገኝል። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳንና ቅዱሳን በዓላት።

ሠራ፡፡ በውስጥዋም ሆኖ ያለማቋረጥ በጾም በጸሎት በስግደትም በመትጋት ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለ፡፡ ሰይጣናትም ተገልጠው የሚመጡበትና በቀንም በሌሊትም በግላጭ የሚዋጉት ሆኑ በጾምና በጸሎት ሲጋደል ሰይጣናት እየተዋጉት ዕረፈትን ስለ አላገኘ ከሶስት ዓመት በኋላ በልቡ አሰበ "በአለም ውስጥ ሳለሁ የቅዱስ አባ እንጦንዮስን ዜና ሰምቻለሁ የምንኩስናን ሥርዓት ያስተምረኝና ይመራኝ ዘንድ ተነሥቼ ወደርሱ ልሂድ የረከሱ ሰይጣናት የመከሩትን ምክራቸውን እገለብጥ ዘንድ እርሱ ዕውቀትንና ማስተዋልን ይሰጠኛልና" አለ ፡፡ ❤ ቅዱስ መቃርዮስም ተነስቶ ከጸለየ በኋላ ወደ ቅዱስ እንጦንዮስ ጉዞ ጀመረ ከቅዱሱ አረጋዊ ከእንጦንስ ጋር በተገናኘ ጊዜ በታላቅ ፍሰሐ ተቀበለው፡፡ ቅዱስ መቃርስ ልጅ በአባቱ ፊት እንደሚሆን ሀሳቡን ሁሉ ገለጠለት፤ ምንም ነገር አልደበቀውም፡፡ ቅዱስ እንጦንዮስም የቅዱስ መቃርስን ራሱን ሳመው፤ እንዲህም አለው "ልጄ መቃርስ ሆይ እንደ ስምህ ትርጓሜ ብፁዕ ትባል ዘንድ አለህ፤ እግዚአብሔር አምላኬ የአንተን ግብር ከብዙ ዘመን አስቀድሞ ገልጦልኛልና ወደ እኔ እንደምትመጣ ነግሮኝ ነበር፡፡ ስለዚህም ወደ እኔ መምጣትህን ስጠብቅ ኖርሁ፤ ስለ ደህንነትህም የማስብ ሆንሁ" አለው፡፡ ቅዱስ አረጋዊ እንጦንስ በብዙ ነገር እየተናገረ ለምንኩስና ግብር እንደሚገባ መከረው አጽናናው፤ የሰይጣናትን ጾርም እንዴት እንደ ሆነ ገልጦ አስረዳው፤ እርሱ በክፉ ህሊና በስውርና በገሃድ እስከ ሞት ድረስ አጽንተው እንደሚዋጉት ነገረው፡፡ "ቢታገሉህም እስከ ሞት ድረስ ፈጽሞ የምትታገስ ሁን" አለው፡፡ ቅዱስ መቃርስ ከእርሱ ጋር ይኖር ዘንድ ለመነው እርሱ ግን አልፈቀደለትም፤ እንዲህ አለው "ከእኛ እያንዳንዱ እግዚአብሔር በወሰነለት ቦታ በትዕግሥትና በአርምሞ ይኑር" አለው፡፡ ቅዱስ መቃርስ እንጦንስ በነበረበት ጊዜ የምንኩስናን የአኗኗር ሥርዓት ተማረ፡፡ ከዚያም በኋላ ወደ በዓቱ ተመለሰ፡፡ ለአባ ሰራጰዮን እንዲህ አለው "በቅዱስ እንጦንስ ዘንድ በነበርኩበት ጊዜ ሁሉ ሌሊት ፈጽሞ ተኝቶ አይቼው አላውቅም ትዕግሥቱና ገድሉ ሁሉ የሚደንቅ ነበር" አለው፡፡ አባ መቃርስም በምንኩስና ሥርዓት ተጠምዶ እየተጋደለ ብዙ ቀን ኖረ ያ ኪሩብም በግልጽ ይጎበኘው ነበር። ❤ ቅዱስ መቃርስ በሌሊትም በጸሎት ጊዜ ቁሞ ሳለ ጌታችን ጆሮውን ከፍቶለት ሰይጣናትን ሲማከሩ ሰማቸው እንዲህም አሉ "ይህን ሰው በዚህ በረሀ እንዲኖር ብንተወው የብዙ ብዙ ወገኖችን ይመራቸዋል፡፡ እነርሱም በዚህ በረሀ ውስጥ ነዋሪዎች ሆነው የሰማያውያን አገር ያደርጉታል፡፡ እነርሱ ለዘለዓለም ጸንቶ በሚኖር ሕይወት ይተማመናሉና፡፡እኛንም በሚቀጣ ጸሎታቸው ቀጥተው አሰቃይተው ያሳድዱናልና ከዚህ ቦታ ልናሳድደው እስኪ እንችል እንደሆነ ኑ ዛሬ በእርሱ ላይ እንሰብሰብ” ሲሉ ሰማቸው፡፡ አባ መቃርስም ይህን በሰማ ጊዜ ልቡ ጸና በሰይጣናት ላይም ተበረታታ የሰይጣናት ምክራቸውን እስከሚሰማ ጆሮውን የከፈተለት እግዚአብሔርን አመሰገነ፡፡ ድካማቸውንም አወቀ፡፡ ❤ ከዚህ በኋላ ይዋጉት ዘንድ ሰይጣናት በእርሱ ላይ ተሰበሰቡ በደጁም እሳትን እያነደዱ ከእሳቱ እያነሱ ወደ በዓቱ ይጨምሩ ጀመር፡፡ ያቺ እሳት ግን በጸሎቱ የምትጠፋ ሆነች፡፡ እንስሳዊ በሆነ ሥራ በፈቲው ጦር ተዋጉት በዚህም ታገሰ፡፡ ትካዜን፣ ዓለማዊ ክብር መውደድን፣ ትዕቢትን፣ መመካትን፣ ታካችነትን፣ ስድብን፣ ሃይማኖት ማጣትን፣ ከእግዚአብሔር ዘንድ ተስፋ መቁረጥን በልቡ አሳደሩበት፡፡ ከዚህም ሁሉ በሚበዛ ተዋጉት የከበረ አባ እንጦንዮስ እንደነገረው ከሰይጣናቱ ፈተና በኋላ ዳግመኛ ወደ አባት እንጦንዮስ ተነሥቶ ሄደ ፡፡ ❤ ወደ ቅዱስ አባት በቀረበ ጊዜ በምድር ላይ ሰገደለት በፍጥነትም ቀና አድርጎ ሳመው ፊቱ እንደ በሽተኛ ፊት ተለውጦ አይቶታልና ይኸውም ሰይጣናት አብዝተው ስለተዋጉት ነው፡፡ ከዚያም ጸሎት አድርገው በአንድነት ተቀመጡ አባት እንጦንዮስ ደስታ በተመላ ቃል "ልጄ መቃርስ በደኀና አለህን" አለው ቅዱስ መቃሪስ "እነሆ ከእኔ የሆነውን ሁሉ እግዚአብሔር ቀድሞ ገልጦለሃል" ብሎ መለሰለት፡፡ እርሱም ያን ጊዜ አስተማረው አጽናናውም እንዲህም ብሎ መከረው "መንፈሳዊ ጥበብን ለሚሹ ለብዙ ወገኖች መምህራን እንድንሆን ይቺውም ምንኩስና ናት ከጠላታችን በላያችን የሚመጣብንን መከራ ሁሉ ልንታገስ ለእኛ የሚገባ ነው ልጄ መቃርስ ሆይ ውሀ ለመቅዳት ስትሄድ እግዚአብሔር የነገረህን ያንን አስብ" አለው ፡፡ ❤ ቅዱስ መቃርስም ሰምቶ እጅግ አደነቀ፡፡ የተሰወሩ ሥራዎቹ ለከበረ አባት ለእንጦንዮስ የተገለጡለት እንደሆኑ አወቀ፡፡ በእርሱ ዘንድም እየተማረና በረከትንም እየተቀበለ ብዙ ቀኖች ኖረ፡፡ ከዚያም የከበረች አስኬማን ያለብሰው ዘንድ ፈለገ አባ እንጦንዮስም በላዩ ጸለየ እርሷን አስኬማይቱን አለበሰው በትሩን ሰጠውና ዐረፈ ስለዚህም የከበረ እንጦንዮስ አባት ተባለ፡፡ ❤ የከበረ አባ መቃርስም ወደ ቦታው ተመልሶ በአስቄጥስ ገዳም ተቀመጠ ዜናውም በአራቱ ማእዘን ተሰማ እግዚአብሔርም በእጆቹ አስደናቂዎች ተአምራትን አደረገ ከተአምራቱ አንዱ ይህ ነው፡፡ በአገረ አውሲም ትንሣኤ ሙታንን አላምንም የሚል ባሕታዊ ተነስቶ ነበርና አባ መቃርስ ሄዶ ቢያስተምረው "የሞተ ሰው ከመቃብር ካላስነሳህ እኔ አላምንም" ብሎ መለሰለት፤ ያን ጊዜ አባ መቃርስ ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጸልዮ አንድ ሙት አስነሥቷል፤ በዚህ ጊዜ ያ የሳተው ባሕታዊና ያሳታቸው ሁሉ ተመልሰዋል፡፡ ያን ከሞት ያነሣውን ሰው የክርስትና ጥምቀትን አጥምቆ ልብሰ ምንኩስናን ካለበሰው በኋላ ሰባት ዓመት ኑሮ ተመልሶ አርፏል፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ የከበረ አባ መቃርስ ተመልሶ ከእርሱ አስቀድሞ በዚያ በረሀ ውስጥ ሰው እንዳለ ያይ ዘንድ ወደ በረሀው ውስጥ ዘልቆ ገባ ዕራቁታቸውን የሆኑ ሁለት ሰዎችን አይቶ ፈራ የሰይጣን ምትኃት መስሎታልና "እልቦት ቦሪቦን" ብሎ ጸለየ ይህም "አቡነ ዘበሰማያት" ማለት ነው እነርሱም "በስሙ ጠርተው መቃሪ ሆይ አትፍራ" አሉት እርሱም በበረሀ የሚኖሩ ቅዱሳን እንደሆኑ አውቆ ወደ እርሳቸው ቀርቦ እጅ ነሳቸው፡፡ እነርሱም በዓለም ስላሉ ሰዎች ስለ ሥራቸውም ጠየቁት እርሱም "በቸርነቱ እግዚአብሔር በሁሉም ላይ አለ" ብሎ መለሰላቸው፡፡ እርሱም ደግሞ "የክረምት ቅዝቃዜ ይቀዘቅዛቸው እንደሆነ የበጋውም ትኩሳት ያላልባቸው እንደሆነ" ጠየቃቸው፡፡ እነርሱም "በዚህ በረሀ እግዚአብሔር አርባ ዓመት ጠብቆናል የክረምት ቅዝቃዜ ሳይቀዘቅዘን የበጋ ትኩሳት ሳያላልበን ኖርን" ብለው መለሱለት ደግሞ "እንደ እናንተ መሆን እንዴት እችላለሁ" አላቸው፡፡ እነርሱም "ወደ በዓትህ ተመልሰህ ስለ ኃጢአትህ አልቅስ አንተም እንደእኛ ትሆናለህ" አሉት ፡፡ ከእነርሱም በረከትን ተቀብሎ ወደቦታው ተመለሰ፡፡ ❤ ወደ አስቄጥስ ገዳም ተመለሰ ከእርሱ ዘንድ መነኰሳት በበዙ ጊዜ ጉድጓድ ቆፍረው መታጠቢያ ሰሩለት፡፡ ሊታጠብ በወረደ ጊዜ ሊገድሉት ሰይጣናት በላዩ አፈረሱበት፡፡ መነኰሳቱም መጥተው አወጡት፡፡ በመጨረሻም እግዚአብሔር ከዚህ ዓለም መከራ ሊያሳርፈው በወደደ ጊዜ ሁልጊዜ የሚጎበኘውን ኪሩብን ወደእርሱ ላለ፡፡ አርሱም "እኔ ወደ አንተ መጥቼ እወስድሀለሁና ተዘጋጅ” አለው፡፡ ከዚያ በኋላ አባ እንጦንስና የቅዱሳንን አንድነት ማኀበር ሰማያውያን የሆኑ የመላእክትም ሠራዊት ተገለጡለትና በመዓዛ ገነት በይባቤ መላአክት ነፍሱን መጋቢት 27 ቀን 397ዓ.ም በ97 ዓመቱ በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ፡፡

"ወደ ቤትህ ሂድ፤ ሚስትህንም ባወቅኻት ጊዜ ትፀንሳለች፤ ወንድ ልጅንም ትወልድልሃለች ፡፡እርሱም ለአንተና ለሚስትህ ደስታ የሚሆንና ብዙ መንፈሳውያን ልጆችን የሚወልድ እጅግ የታወቀ ታላቅ መንፈሳዊ አባት ይሆናል፤ በዚህም የተነሣ ስሙ በዓለም ሁሉ ይነገራል፡፡ ብዙዎችን ሰዎች እንደመላእክት ሆነው እግዚአብሔርን ያገለግሉት ዘንድ ወደ እርሱ ያመጣቸዋል፡፡ እነርሱም በሕይወታቸው ፍጹም ሰማያውያን መላእክትን ይመስላሉ" አለው፡፡ ❤ አረጋዊው ካህን አብርሃም ከራዕዩ በነቃ ጊዜ ሚስቱ ሣራ እርሱን እያስታመመች አብራው ነበረችና ያየውን ነገር ሁሉ ነገራት፡፡ በነጋም ጊዜ ከበሽታው ድኖ ወደ ቤታቸው በደስታ ተመለሱ፡፡ ከዚያም በኋላ መልአኩ እንደተናገረው ሣራ ፀነሰች፡፡ መቃርዮስ በግብጽ ሃገር መኑፍ በሚባል አውራጃ ጁቢር በሚባል ቦታ በ300 ዓ.ም ተወለደ፤ የስሙ ትርጓሜም ብፁዕ ማለት ነው፡፡ እርሱም በእግዚአብሔር ጸጋ የተሞላና የተወደደ ልጅ ሆነ፡፡ ❤ መቃርዮስም ባደገ ጊዜ የእግዚአብሔር ጸጋ ስላደረበት ለወላጆቹ ይታዘዝና ያገለግል፣ በወላጆቹ ትዕዛዝ ምጽዋትንም በየቀኑ ይመጸውት ስለነበር በጣም ይደሰቱ ነበር፡፡ ወላጆቹን በሁሉም ነገር እያገዛቸው በማንኛውም መንገድ እግዚአብሔርን ያገለግል ነበር፡፡ በዚህ ሁኔታ በጥሩ ሥነ ምግባር ቀስ በቀስ እያደገና እየጠነከረ በመምጣት ወላጆቹን ከበፊቱ በበለጠ ሁኔታ ይንከባከባቸው ነበር፡፡ እግዚአብሔርም አብዝቶ ባረካቸው፤ ከብቶቻቸውና እርሻቸው በሚያስደንቅ ሁኔታ እየበዛ ቤታቸው በተትረፈረፈ ሀብት ተሞላ፡፡ ❤ ወጣቱ መቃርዮስ በመንፈሳዊ ሕይወቱ አርአያ በመሆን በሰዎች ዘንድ በጣም የሚወደድ ሆነ፡፡ የእግዚአብሔር ጸጋ በላዩ እንዳለበት በግልጽ እስኪታወቅ ድረስ ፊቱ ያበራ ነበር፡፡ የአገሩ ካህናት ይህን በተመለከቱ ጊዜ ወደ ጳጳሱ ወሰዱትና አናጉንስጢስ እንዲሆን አደረጉት፡፡ እናትና አባቱ ግን በዚህ ደስተኛ አልነበሩም ነገር ግን "የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሁን" አሉ እድሜው ከፍ አያለ ሲመጣ እናትና አባቱ ሊያጋቡትም አሰቡ እርሱ ግን አይሻም ነበር፡፡ ፈቃዳቸውን ይፈጽም ዘንድ ግድ ብለው አጋቡት፡፡ ወደ ሙሽራይቱም በገባ ጊዜ ራሱን እንደታመመ ሰው አደረገ እንዲህም ሁኖ ብዙ ቀን ኖረ፡፡ አባቱን "ተወኝ ወደ ገዳም ልሒድ ከበሽታዬ ጥቂት ጤና ባገኝ" አለው፡፡ እግዚአብሔር ወደ ሚወደው ሥራ ይመራው ዘንድ ሁል ጊዜ በጾምና በጸሎት ሁኖ ይለምነው ነበር፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ ወደ አስቄጥስ በረሀ ሄደ፡፡ ከበረሀውም በገባ ጊዜ ራእይን አየ፡፡ ስድስት ክንፍ ያለው ኪሩብ እጅና እግሩን ይዞ ወደ ተራራ ላይ እንደሚያወጣውና የአስቄጥንስን በረሀ ምሥራቋን ምዕራቧን የዚያችን በረሀ አራት ማዕዘንዋን አሳይቶ "እነሆ ይቺን በረሀ መላዋን ላንተና ለልጆችህ ርስት አድርጎ እግዚአብሔር ሰጥቶሃል" አለው፡፡ ከሦስት ቀን በኋላ መቃርዮስ ባየው ራእይ እየተገረመ ከአስቄጥስ በረሃ ወደ ቤቱ በተመለሰ ጊዜ ያቺ ሚስት ትሆነው ዘንድ ብለው ያመጡለት ብላቴና በጽኑ ታማ አገኛት፡፡ ጥቂት ቆይታም ወዲያው በድንግልናዋ እንዳለች በሰላም ዐረፈች፡፡ የክብር ባለቤት እግዚአብሔርንም አመሰገነው፡፡ እርሱም "መቃርዮስ ሆይ ከእንግዲህ ወዲህ ለነፍስህ ድኀነት በሚሆን ትጋት በመትጋት መንፈሳዊ ፍሬን ለማፍራት ታጠቅ አንተም እንዲህ ትወሰዳለህና" እያለ ራሱን ይገስጽ ጀመር፡፡ ❤ ከጥቂት ቀኖችም በኋላ እናት አባቱ ዐረፉ፡፡ የተውለትንም ገንዘብ በሙሉ ለድሆችና ለጦም አዳሪዎች ሰጠ፡፡ የሳሱይር ሰዎች ግን ዕውነተኛነቱንና ቅድስናውን አይተው ቅስና አሾሙት፡፡ ከከተማውም ውጭ ቤት ሰሩለት፡፡ ሥጋውንና ደሙን ይቀበሉ ዘንድ ወደርሱ ይሄዱ ነበር ፡፡ በዚያች አገርም አንዲት ድንግል ብላቴና ነበረች፡፡ ከአንድ ጐልማሳ ጋርም አመንዝራ ፀነሰች፡፡ ጐልማሳውም "አባትሽ ድንግልናሽን ማን አጠፋው ብሎ ሲጠይቅሽ መቃርስ የሚባለው ባሕታዊ ቄስ እርሱ ስለ ደፈረኝ ነው በይው" ብሎ መከራት ጽንሷም በታወቀ ጊዜ አባቷ "ይህን አሳፋሪ ሥራ በአንቺ ላይ የሰራብሽ ማነው ብሎ ጠየቃት" እርሷም "በአንዲት ቀን መቃርስ ወደሚባለው ቄስ ሄጄ ሳለሁ በኃይል ይዞኝ ከእኔ ጋር ተኛ ስለዚህ ከእርሱ ፀነስኩ" ብላ መለሰችለት፡፡ ወላጆቿና ቤተሰቦቿም በሰሙ ጊዜ እጅግ ተቆጡ ከብዙ ሰዎችም ጋራ ወደ ቅዱስ መቃርስ ሄደው ይዘው ከበዓቱ አወጡት እርሱ ግን ምን እንደሆነ አላወቀም ለመሞት እስኪቃረብም አጽንተው ደበደቡት እርሱም "ኃጢአቴ ምንድናት እናንተ ያለ ርኀራሄ ትደበድቡኛላችሁና" እያለ ይጠይቃቸው ነበር ፡፡ ከዚህ በኋላ በፍሕም የጠቆሩ ገሎችን በአንገቱ ላይ በገመድ አንጠልጥለው ወዲያና ወዲህ እየጎተቱ የልጃችንን ድንግልና ያጠፋ ይህ ነው እያሉ እንደ እብድ በላዩ ይጮኩ ጀመር፡፡ ❤ በዚያን ጊዜ መላእክት ከሩቅ አገር መጡና በሚታወቁ ደጋግ ምዕመናን ሰዎች አንጻር ተገልጠው እነዚያ ክፉ ሰዎች ከሚያደርሱበት ድብደባና ነቀፋ የተነሣ ሊሞት እንደቀረበ ባዩት ጊዜ የሚያሰቃዩትን ሰዎች "ይህ ተጋዳይ ምን አደረገ" አሏቸው፡፡ እነርሱም በልጃቸው ላይ የኃፍረትን ሥራ እንደ ሰራ አድርገው መልሰው ነገሩአቸው ፡፡ እነዚያ መላእክትም "ይህ ነገር ሐሰት ነው እኛ ይህን ሰው ከታናሽነቱ ጀምሮ እስከዚች ቀን እናውቀዋለን እርሱ የተመረጠ ጻድቅ ሰው ነውና" አሏቸው፡፡ የታሰረበትን ፈትተው ከላዩ ገሎችን ጣሉ፤ ከድካሙም አበረቱት፡፡ የልጅቷ አባት ግን "ፈጽሞ አይሆንም፤ እስክትወልድ ድረስ ቀለቧን እንደሚችልና ከወለደች በኋላም ለልጁ ማሳደጊያ ገንዘብ እንደሚሰጥ ዋስ ካላቀረበ በስተቀር አንለቀውም" አለ፡፡ እጅ ሥራውን የሚሸጥለት አንድ ሰው መጣ ለልጅቷም በየጊዜው ምግቧን ሊሰጣት ዋስ ሆነው ከዚያ በኋላ አሰናብተው ወደ በዓቱ ተመልሶ ገባ ከዚያች ቀን ጀምሮ ራሱን ለራሱ "መቃርስ ሆይ እነሆ እንግዲህ ባለ ሚስትና ባል ልጅ ሆነሃልና ሌሊትና ቀን መሥራት ይገባሃ" እያለ ያቺ ሴት ሴት ልጅ የምትወልድበት ጊዜ እስኪደርስ ድረስ ቅርጫቶችን እየሠራ ለዚያ ወዳጅ ለሆነውና ለሚገለግለው ወንድም ይሰጠውና ያም ሰው ለዚያች ሐሰተኛ ልጅ እየሰጠ ኖረ፡፡ ❤ ያቺ ሴት ልጅ የምትወልድበትም ቀን ሲደርስ እጅግ አስጨነቃት በታላቅ ስቃይም ውስጥ አራት ቀኖች፣ ያህል ኖረች ለሞትም ተቃረበች እናቷም "ከአንቺ የሆነው ምንድነው የተሠራ ሥራ አለና ንገሪኝ" አለቻት፡፡ እርሷም "በእግዚአብሔር አገልጋይ ላይ ዋሽቻለሁና ያመነዘርኩት ከዕገሌ ጐልማሳ ጋር ሲሆን በእውነት ሞት ይገባኛል" አለቻት ፡፡ አባትና እናቷም በሰሙ ጊዜ ደንግጠው እጅግ አዘኑ የአገሩ ሰዎችም ሁሉም ተሰበሰቡ በእርሱ ላይ የሠሩትን በደል ይቅር ይላቸው ዘንድ ወደ ቅዱስ መቃርስ ሄደው ለመኑት ያን ጊዜ በበረሃ ያየውን ራእይ አስታወሰ ይቅር አላቸው ቀድሶም ሥጋውንና ደሙን አቀበላቸው ፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ ክንፉ ስድስት የሆነ ኪሩብ ደግሞ ተገለጠለት ትርጓሜው የልብ ሚዛን ወደተባለ ወደ አስቄጥስ ገዳም እጁን ይዞ መርቶ አደረሰው ቅዱስ መቃርስ ያንን ኪሩብ "ጌታዬ ሆይ በውስጡ የምኖርበትን ቦታ ወስንልኝ" አለው፡፡ ያ ኪሩብም "አልወስንልህም የእግዚአብሔርንም ትእዛዝ አትተላለፍ እነሆ ይህ ገዳም ሁለመናው ላንተ ተሰጥቷልና ወደ ፈለግህበት ሂደህ ተቀመጥ" ብሎ መለሰለት፡፡ ቅዱስ መቃርስም የቅዱሳን ሮማውያን ወንድማማቾዎችና የመኪሲሞስና የዱማቴዎስ ቦታ ወደ ሆነው ከውስጠኛው በረሀ ገብቶ ኖረ፡፡ እነርሱ ወደ እርሱ በመጡ ጊዜ ከእርሱ አቅራቢያ ኑረዋልና ከዕረፍታቸው በኋላ ግን ሂዶ በዚያ ቦታ እንዲኖር የእግዚአብሔር መልአክ አዘዘው፡፡ የከበረ አባት መቃርስም ታናሽ በዓት

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤              ❤ #መጋቢት ፳፯ (27) ቀን። ❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ንጉሥ_ለቅዱስ_ዐፄ_ገላውዴዎስ አንገቱን በመሰየፍስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል፣ በገዳም ለሚፈጸም ተጋድሎ ፋና ለሆነ ለአስቄጥስ ገዳም ለሚኖሩ መነኰሳት ሁሉ አባት ለሆኑ ለከበሩ አባት #ለታላቁ_አባ_መቃርስ ለዕረፍታቸው በዓል፣ #ለአቡነ_ጊዮርጊስ_ዘጣና ለመታሰቢያ በዓላቸው እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን፡፡                                ✝ ✝ ✝ ❤ #ንጉሥ_ቅዱስ_ዐፄ_ገላውዴዎስ፦ ይህ ቅዱስ በተግሣጽ በምክር በፈሪሀ እግዚአብሔር አደገ አባቱ ንጉሥ ልብነ ድንግል ሃይማኖቱ የቀና ነበርና በዘመኑም የእስላም ወገን የሆነ ስሙ ግራኝ የሚባል ተነሥቶ አብያተ ክርስቲያናትን አጠፋ። ከንጉሥ ልብነ ድንግል ጋር ጦርነት ገጠመ ንጉሡም ወግቶ መመለስ ቢሳነው አርበኞች ሠራዊትን እስከሚሰበስብ ከእርሱ ሸሸ በስደትም እያለ በድንገት ታሞ ሞተ። ❤ ይህም ዐመፀኛ የኢትዮጵያን አገሮች እያጠፋ ዐሥራ አምስት ዓመት ያህል ኖረ። ከኢትዮጵያም ሕዝቦች በመመካትም ማርኮ ከቀናች ሃይማኖት አውጥቶ የእርሱ ሃይማኖት ተከታዮች አደረጋቸው በመመካትም እንዲህ አለ "አገሮችን ሁሉ ግዛቶቼ ስለአደረግኋቸው ከእንግዲህ የሚቃወመኝ የለም"። ❤ ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር ይህን ቅዱስ ገላውዴዎስን አስነሣ ከግራኝ ታላላቅ መኳንቶቹ ጋር ጦርነት ገጠማቸው ድልም አድርጎ አሳደዳቸው። ግራኝም በሰማ ጊዜ ተቆጣ ከቱርክ አርበኞች ጋርና ከአእላፍ ፈረሰኞች ጋር መጥቶ ንጉሡም ገጠመው ጌታችንም ግራኝን በንጉሥ ገላውዴዎስ እጅ ጣለው ገደለውም። ግራኝን በመፍራት የተበተኑ ሁሉ ከተማረኩበትም ሁሉ ተመለሱ የፈረሱ አብያተ ክርስቲያናትም ተመልሰው ታነፁ የክቡር ባለቤት የሆነ የክርስቶስ ሃይማኖት ተቃናች። ❤ ከዚህም በኋላ ከእስላሞች ወገን አንዱ ከብዙ አርበኞች ሠራዊት ጋር መጣ በመድኃኒታችን ስቅለት በዓል ከጥቂት ሰዎች ጋራ ተቀምጦ ሳለ በድንገት ንጉሡን ተገናኘው ሰዎቹም "የጦር መኰንኖች እስቲሰበሰቡ ፈቀቅ እንበል" አሉት። እርሱ ግን የክርስቲያኖችን መማረክና የአብያተ ክርስቲያናትን አላይም ብሎ እምቢ" አለ እንዲህም እያለ ወደ ውጊያው መካከል ገብቶ በርትቶ ሲዋጋ የኋላ ኋላ እስላሞች ሁሉም ከበቡት ተረባረቡበት ነፍሱንም በጐራዴም ጨፈጨፋት በብዙ ጦሮችም ወጉት ከፈረሱም ጣሉት የከበረች አንገቱንም ቆረጡት ነፍሱንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ። በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት 27 ስንክሳር።                             ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለአባ_መቃሪ ዘእግዚአብሔር ነባሪ፤ መምህረ ሕግ ምስለ መላእክት ዘውግ"። ትርጉም፦ ከመላእክት ጋር የሚወጋገን የሕግ መምህር፤ የእግዚአብሔር አገልጋይ ለኾነ #ለአባ_መቃሪ_ሰላምታ_ይገባል።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #ታላቁ_አባ_መቃርስ_መቃርዮስ_መቃሪ፣ መቃራ፦ ይህም የከበረ አባት በግብጽ ደቡብ መኑፍ ከሚባል አውራጃ ሳሱይር ከሚባል መንደር ከሚኖሩ ከተወደዱ ደጋግ ክርስቲያኖች የተገኘ ታላቅ አባት ነው፡፡ ወላጆቹ በደጋጎቹ በቀደሙት በአብርሃምና በሣራ ስም የአባቱ ስም አብርሃም የእናቱ ስም ሣራ ተብለው ይጠሩ ነበር፡፡ አባቱም በፈሪሃ እግዚአብሔር ሆኖ ንጽሕናውን ቅድስናውን ጠብቆ ሁል ጊዜ ቤተ ክርስቲያንን በትጋት በማገልገል ጸንቶ የሚኖር ካህን ነበር፡፡ እናቱም እንደ ኤልሳቤጥና እንደ ሣራ በእግዚአብሔር ትእዛዝ ጸንታ የምትኖር ነበረች፡፡ ❤ እግዚአብሔርም በላያቸው በረከቱን አሳድሮ በሥራቸው ሁሉ ከፍ ከፍ አደረጋቸው፡፡ እነርሱም ለድሆች የሚመጸውቱ ለሰው ሁሉ የሚራሩ ነበሩ፡፡ የመጀመሪያ ልጃቸው ሴት ነበረች ባደገች ጊዜም እግዚአብሔር ጎበኛትና ዐረፈች፡፡ ይህ ደግ ካህን አብርሃም እግዚአብሔርን የሚወድ ነበር፡፡ ቅድስት የሆነች ሣራ ንጽሕናን የምትወድ ነበረችና ልጃቸው ከሞተች በኋላ ባልና ሚስቱ በመመካከር ተወስነው አልጋ ለይተው በጾም፣ በጸሎት፣ ምጽዋትን በመስጠትና በሽተኞችን በመንከባከብ በታላቅ ትሩፋት መኖር ጀመሩ፡፡ በዚህ የተቀደሰ ሕይወታቸውም ሰው ሁሉ በጣም ይወዳቸው ነበር፡፡ ነገር ግን የመልካም ነገር ጠላት የሆነው ዲያብሎስ በእንዲህ ዓይነት ሕይወት እየኖሩ ማየት አላስቻለውም፡፡ በመሆኑም እንደ ልማዱ በቅናት ተነሣባቸውና የእርሱ ማደሪያ በሆኑ ክፉ ሰዎች አማካኝነት በእነርሱ ላይ ከባድ ፈተና አመጣባቸው፡፡ በመጨረሻም ሀብታቸው ሁሉ ጠፍቶ በድህነት መኖር ጀመሩ፡፡ ቅድስት የሆነች የዚህ የተቀደሰ ካህን አብርሃም ሚስት ሣራ የሆነውን ነገር ሁሉ ባየች ጊዜ በፍርሃት ሆና ነፍሳቸውን ለማዳን ዘመዶቻቸውንና አገራቸውን ለቅቀው መሄድ እንዳለባቸው ለባሏ ነገረችው፡፡ ነገር ግን የመቃርዮስ አባት አብርሃም ስለ ተከሰተው ነገር ሁሉ በጣም ተጨነቀና "በእኔ ላይ የሆነው ይህ ነገር ምንድን ነው" አለ፡፡ በመሸም ጊዜ ተኝቶ እያለ አረጋዊው አባት አበ ብዙኃን አብርሃም የሚያንጸባርቅና የሚያበራ ልብስ እንደ ተጎናጸፈ በህልም ታየው እርሱም ወደ መቃርዮስ አባት አብርሃም ተጠጋና እንዲህ አለው፦ "አይዞህ አትፍራ እኔ ያዕቆብን የወለደው የይስሐቅ አባት አብርሃም ነኝ፤ ስለዚህ የምነግርህን አድምጠኝ፤ የሚስትህን ቃል ከመስማት ወደ ኋላ አትበል፡፡ ይህን ቦታ ትለቅ ዘንድ እግዚአብሔር ፈቅዷልና በጁቢር ተቀመጥ፤ ጌታ እግዚአብሔር አልተውህም እባርክሃለሁ ይላልና፡፡ እኔ እግዚአብሔር እንደ ነገረኝ አገሬን በመተው በከነዓን ምድር ተቀመጥኩ፡፡ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ "ወንድ ልጅን እሰጥሃለሁ፣ ስሙም በትውልድ የታወቀ ይሆናል፣ እኔ በማሳየው ቦታ ያገለግሉኝ ዘንድ ብዙ የመንፈስ ልጆችን ይወልዳል" አረጋዊው ካህን ይህን በሰማ ጊዜ በታላቅ ሁኔታ አደነቀ፣ ነገር ግን ነገሮቹ አሳማኝ ስለ ነበር ተደሰተ፡፡ ❤ ጠዋትም በሆነ ጊዜ ሚስቱን ጠራትና ያየውንና የሰማውን ሁሉንም ነገር ነገራት ወዲያውም እግዚአብሔር ያዘዛቸውን ነገር ለማድረግ ሁለቱም ተስማሙ ከዚያም በምሥጢር ለጊዜው የሚያስፈልጋቸውን ጥቂት ነገር ብቻ በመያዝ የቀራቸውን ንብረትና አገራቸውን በመተው በህልም እንደ ታዘዙት ወደ ጁባር ሄደው ተቀመጡ፡፡ በጁባር በሚኖሩበት ጊዜም የበለጠ የእግዚአብሔርን ሕግ በመጠበቅ መኖር የዘወትር ሕይወታቸው ነበር፡፡ የዚያች ከተማ ካህንም የአረጋዊው ካህን የአብርሃምን ምግባሩን በተመለከተ ጊዜ በቤተ ክርስቲያን ከእነርሱ ጋር እንዲያገለግል ጠየቀው ፡፡ እርሱ ግን አልተስማማም፤ ምክንያቱም ከሌላ ቦታ የመጣ ካህን እንዲሁ ማገልገል አይችልም ነበርና፡፡ አብርሃም በዚያ ቦታ ጥቂት እንደቆየ ራሱን በማረጋጋት መሬት በመያዝ ቀድሞ ይሠራ እንደነበር እርሻ ማረስ ጀመረ፡፡ ❤ እንዲያ እየኖረ እያለም በድንገት ታመመ፤ በዚያን ጊዜ ወደ ቤተክርስቲያን ውሰዱኝ አላቸው ፡፡ በዚያም ይድን ዘንድ ከቤተ ክርስቲያኑ ግቢ መሬቱ ላይ በእምነት ተኛ፡፡ ሌሊትም በሆነ ጊዜ በሕማሙ ምክንያት እንቅልፍ አልወስደው ብሎ ነበርና በድንገት ቀና ሲል የእግዚአብሔር መልአክ ከፊቱ ለፊቱ በመቅደሱ ቆሞ ተመለከተ፡፡ መልአኩም "ተነስና ወደዚህ ና" በማለት ሦስት ጊዜ በመደጋገም ጠራው። ነገር ግን ለመልአኩ "ጌታዬ ከሕመሜ የተነሣ እውነት እልሃለሁ መነሣት አልችልም፣ እባክህ እለምንሃለሁ" አለው፡፡ መልአኩም ወደ እርሱ ተጠግቶ ዳሰሰውና "እግዚአብሔር እንድትድን አዝዟልና ተነስ ቁም" አለው፡፡ አብርሃም ወዲያው ተነስቶ ቆመ፤ መልአኩም

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤           ❤ #መጋቢት ፳፯ (27) ቀን። ❤ እንኳን #ለጌታችን_ለአምላካችንና_ለመድኀኒታችን፤ #ለፈጣሪያችንና_ለአዳኛችን_መድኃኔዓለም ለጥንተ ስቅለት መታሰቢያ ዓመታዊ በዓል፣ ከአዳም ቀድሞ ገነት ለገባው #ለቅዱስ_ጥጦስ (ፈያታይ ዘየማን) ገነት ለገባበት፣ ጌታችን ለገነዙት ቅዱሳን ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ለመታሰቢያ በዓላቸው እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                                                    ✝ ✝ ✝ ❤ በዚችም ቀን የክቡር ባለቤት #ጌታችን_መድኃኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ ስለ ዓለም ድኅነት በሥጋ ተሰቀለ። ❤ ፈጣሪዋ በዕንጨት መስቀል ላይ ተዘርግቶ ተሰቅሎ በአየችው ጊዜ ፀሐይ ጨለመች እርሱም ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም የነሣትን ለባዊት ነባቢት የሆነች ነፍሱን ከሥጋው ለያት ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በሥጋ ምውት ሲሆን በመለኮት ሕያው ነው እንዳለ ነፍሱ ከመለኮት ሳትለይ ከሥጋ ተለየች በዚያ ጊዜ ሥጋ ከመለኮት ሳይለይ በዕንጨት መስቀል ላይ ተሰቅሎ ነበር። እንዲሁም ነፍስ ከመለኮት ጋራ አንድ ሁና እሥረኞች ነፍሳትን ትፈታቸው ዘንድ ወደሲኦል ወረደች። ❤ እርሱ ከሰማያት በላይ ከፍ ከፍ ያለ ልዑል ባሕርይ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ በጌትነቱ ዙፋን ተቀምጦ ያለ ለእርሱም ምስጋና ክብር ዘላለሙ የሆነ ራሱን ሠውቶ ያዳነን የመንግሥቱን ደጆች በፈሳሽ ደሙ የከፈተልን ለእርሱ ስግደት አምልኮት ይገባዋል ለዘላለሙ የመስቀሉም በረከት በላያችን ይደር አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት 27 ስንክሳር።                              ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለዮሴፍ_ወለኒቆዲሞስ እለ አምጽኡ አፈወ ከርቤ ወዐልወ ወበልብሰ ገርዜን ሐዲስ፤ #እለ_ገነዝዎ_ለክርስቶስ፤ እለ ገሰሱ ሥጋሁ ወእለ ሰዓሙ አፉሁ"። ትርጉም፦ ከርቤ፣ ሽቱ፣ የሽቱ ወገን የሚኾን ዋግራ አምጥተው ዐዲስ በኾነ በፍታ ክርስቶስን የገነዙት፤ ሥጋውን ዳስሰው አፋን የሳሙት ለኾኑ #ለዮሴፍና_ኒቆዲሞስ_ሰላምታ_ይገባል።                             ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለዮሳፍጥ_ዘውእቱ_ፈያታይ_ዘየማን ዘአርኀዋ ለአንቀጸ ገነት ሶበ ቀጸበቶ #ዕለተ_መድኃኒት"። ትርጉም፦ ያውም የድኅነት ዕለት በተጠቀሰችው ጊዜ የገነት ደጃፍን የከፋታት #ፈያታይ_ዘየማን_ነው፤ ለርሱ #ለዮሳፍጥ_በረኸኛ_ለጥጦስ_ሰላምታ_ይገባል። #ሊቁ_አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ_በተአምኆ_ቅዱሳን_ላይ።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ተንሥኡ ላዕሌየ ሰማዕተ ዐመፃ። ወዘኢየአምር ነበቡ ላዕሌየ። ፈደዩኒ እኪተ ህየንተ ሠናይት"። መዝ34፥11-12። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ23፥1-17።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "እግዚአብሔርሰ ንጉሥ ውእቱ እምቅድመ ዓለም። ወገብረ መድኃኒተ በማእከለ ምድር። አንተ አጽናዕካ ለባሕር በኃይልከ"። መዝ 73፥12-13። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 12፥1-16፣ 1ኛ ጴጥ 3፥15-20 እና የሐዋ ሥራ 10፥30-40። የሚነበበው ወንጌል ማቴ27፥1-55። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ነው። መልካም የመድኃኔ ዓለም የጥንት ስቅለቱ በዓልና የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤        ❤ #መጋቢት ፳፮ (26) ቀን። ❤ እንኳን #ለክብር_ባለቤት_ለጌታችን_ለአምላካችን #ለመድኃኒታችን_ለኢየሱስ_ክርስቶስ ደቀ የመዛሙርቱን እግር ላጠበበትና፣ #የሐዲስ_ኪዳንን_የቊርባን_ሥርዓት_ለመሰረተበት (ለጥንት ጸሎተ ሐሙስ)ና ለከበረችና ለተመሰገነች ለድንግሊቱ ከዘጠኛ ዓመቷ ጀምሮ ስትጋደል ለኖረች፤ ዐቢይ ጾም ምን ሳትባለ ትጾም ለነበረች #ለቅድስት_ኢዮጰራቅስያ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰበው፦ #ከቅድስት_ኢዮጰራቅስያ_ጓደኛ (ከመጋቢዋ)ና #ከእመ_ምኔቷ ከዕረፍታቸው መታሰቢያና #ከቅዱስ_ፍርፍርዮስ ከመታሰቢያው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ በዚች ዕለት #የክብር_ባለቤት_ጌታችን_የደቀ_መዛሙርቱን_እግር_አጠበ እንዲህም አላቸው "እናንተም ለባልንጀሮቻችሁ እንዲሁ አድርጉ"።                            ✝ ✝ ✝ ❤ ደግሞ #የሐዲስ_ኪዳንን_የቊርባን_ሥርዓት አሳያቸው። አሁንም በዚች ዕለት የክብር ባለቤት ጌታችንን ለአይሁድ ይሁዳ አሳልፎ ሰጠው። ነቢያት ትንቢት እንደተናገሩ የሽያጩን ዋጋ ሠላሳ ብር ተቀበለ። ይቅርታው ቸርነቱ ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ጋር ለዘላለሙ ይኑር አሜን።                                                           ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅድስት_ኢዮጰራቅስያ፦ ይችም የተቀደሰች ብላቴና የንጉሥ አኖሬዎስ ዘመዱ ለሆነ በሮሜ ከተማ ከቤተ መንግሥት የአንድ ታላቅ መኰንን ልጅ ናት። የሚሞትበትም ቀን በደረሰ ጊዜ እርሷን ልጁን ለንጉሥ አኖሬዎስ ይጠብቃት ዘንድ አደራ ሰጠው። አባቷም ካረፈ በኋላ ለአንድ ታላቅ መኰንን ልጅ ንጉሥ አኖሬዎስ አጫት። ❤ በዚያም ወራት እናቷ የመሬቷን ግብር ልትቀበል ባሏ የተወላትን የአትክልት ቦታዎቿም ያፈሩትን ይችንም ቅድስት ብላቴናዋን ከእርሷ ጋር ወሰደቻት። ዕድሜዋ ዘጠኝ ዓመት ሁኖ ሳለ አስከትላት ወደ ግብጽ ሔደች። ❤ ወደ ግብጽ አገርም በደረሱ ጊዜ ሥራቸውን እስከሚፈጽሙ በአንድ የደናግል ገዳም ውስጥ ኖሩ። በዚያ ገዳም ውስጥ የሚኖሩ ደናግል ለገድል የተጸመዱ ናቸው። የሥጋ መብልን፣ ቅባትም ቢሆን ጣፋጭ ፍሬዎችንም ምንም ምን አይበሉም፣ ወይንም ቢሆን ከቶ አይቀምሱም ያለ ምንጣፍም በምድር ላይ ይተኛሉ። ኢዮጰራቅስያም በዚያ ገዳም ውስጥ መኖርን ወደደች ገዳሙን ከምታገለግል መጋቢዋ ጋር ተፋቅራለችና። መጋቢዋም "አንቺ ከዚህ ገዳም ወጥተሽ ተመልሰሽ እጮኛሽን ላትፈልጊ ቃል ግቢልኝ" አለቻት ኢዮጰራቅስያም በዚህ ነገር ቃል ገባችላት። ❤ እናቷ ሥራዋን በፈጸመች ጊዜ ወደ አገርዋ ልትመለስ ወደደች ልጅዋ ግን "እኔ የዚህን ኃላፊውን ዓለም ሙሽርነት ስለማልሻ ራሴን ለክብር ባለቤት ለጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰማያዊ ሙሽራ ሰጥቻለሁ" ብላ ከእርሷ ጋር መመለስን አይሆንም አለች። ብላቴናዋ ከእርሷ ጋር እንደማትመለስ በተረዳች ጊዜ ገንዘቧን ለድኆችና ለጦም አዳሪዎች መጽውታ ከልጅዋ ጋር በዚያ ገዳም ብዙ ዘመን ኑራ ከዚያ በኋላ ዐረፈችና በዚያው ቀበሯት። ❤ ንጉሥ አኖሬዎስም የኢዮጰራቅስያ እናቷ እንደሞተች ሰምቶ ለአጫት ያጋባት ዘንድ ኢዮጰራቅስያን እንዲያመጧት መልእክተኞችን ላከ። ቅድስቲቱም "ንጉሥ ሆይ ዕወቅ የክብር ባለቤት ለሆነ ለሰማያዊ ሙሽራ ለጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ እኔ ራሴን ሰጥቻለሁና" ብላ ወደ ንጉሥ ላከች። ንጉሥ አኖሬዎስም መልእክቷን በሰማ ጊዜ አደነቀ ስለርሷም አለቀሰ እርሷ በዕድሜዋ ታናሽ ብላቴና ናትና። ❤ ይህቺ የከበረች ኢዮጰራቅስያ ግን ታላቅ ተጋድሎን ታጋደለች ለመንፈሳዊ ሥራ እጅግ የተጠመደች ሆነች በየሁለት ቀን ሁለት ሁለት ቀን እያከፈለች መጾም ከዚያም በሦስት ቀን ሦስት ሦስት ቀን ትጾም ጀመር ከዚያም በየሰባት ቀን ሰባት ሰባት ቀን የምትጾም ሆነች። በተለየች በከበረች አርባ ጾም ምንም ምን የምትበላ አልሆነችም። ❤ ሰይጣንም በእርሷ ላይ ቀንቶ አስጨናቂ በሆነ አመታት እግርዋን መታት ብዙ ቀኖችም በሕማም ኖረች ከዚያም እግዚአብሔር ራርቶላት ከደዌዋ አዳናት በሽተኞችንም ታድናቸው ዘንድ በሽተኞችን የምትፈስበትን ሀብት ሰጣት። ❤ ለእመ ምኔቷና ለእኅቶቿ ደናግል በመታዘዝ ታገለግላቸው ነበር በእኅቶች ደናግል ሁሉ ዘንድ የተወደደች ናት። ❤ በአንዲት ዕለትም እመ ምኔቷ አክሊላትንና አዳራሾችን እንደ አዘጋጁ ራእይን አየች እርሷም እያደነቀች "ከልጆቼ ለማን ይሆን ይህ የሚገባት" ስትል "እሊህ አክሊላትና አዳራሾች የተዘጋጁላት ለልጅሽ ለኢዮጰራቅስያ ነው እርሷም ወዲህ ትመጣለች" አሏት። ይህንንም ራእይ ለደናግሎች ነገራቻቸው እግዚአብሔርም በዚህ ዓለም መከራ ሊያሳርፋት እስከ ወደደበት ቀን ለኢዮጰራቅስያ እንዳይነግሯት አዘዘቻቸው። ❤ ከዚህ በኋላ በሆድ ዝማ ሕማም ጥቂት ታመመች ሁሉም ደናግል ከእመ ምኔቷ ጋር ወደ እርሷ ተሰበሰቡ ያቺ ቃል ኪዳን ያስገባቻት የምትወዳት መጋቢዋም መጣች። በእግዚአብሔርም ዘንድእንድታስባቸው ለመኑዋት እርሷም በጸሎታቸው እንዲያስቧት ለመነቻቸው ከዚያም መጋቢት 26 ቀን ዐረፈች። የተቀደሰችና የተባረከች እርሷን እኅታቸውን አጥተዋታልና ደናግሉ እጅግ አዝነው አለቀሱ። ❤ ከዚህም በኋላ የምትወዳት የገዳሙ መጋቢ የነበረችው ዐረፈች። ከእርስዋም በኋላ እመ ምኔቷ ጥቂት ቀን ታመመች ደናግሎቹንም ሰብስባ "በላያችሁ የምትሾሙትን እመ ምኔት ምረጡ ስለ እኔ ኢዮጰራቅስያ ለምናለችና እኔ ወደ ጌታዬ ኢየሱስ እሔዳለሁ አሁን ግን ደጁን በላዬ ዘግታችሁ ሒዱ" አለቻቸው እነርሱም እንዘዘቻቸው አደረጉ። በማግሥቱም ማለድ ብለው ሲደርሱ ዐርፋ አገኟት። የእሊህም የከበሩ እናቶች በረከታቸው ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት 26 ስንክሳር።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ተሐፅበኒ እምበረድ እጸዓዱ (ወእጻዓዱ)። ታሰምዐኒ ትፍሥሕተ ወኃሤት። ወይትፌሥሑ አዕፅምተ ጻድቃን"። መዝ 50፥7-8። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ 11፥20-30፣ 1ኛ ዮሐ 3፥18-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 4፥24-31። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 26፥14-31። የሚቀደሰው ቅዳሴ ቅዳሴ እግዚእነ ወይም የቅዱስ ኤጲፋንዮስ ቅዳሴ ነው። ❤ ወይም                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ንፍሑ ቀርነ በዕለተ ሠርቅ"። በእምርተ ዕለተ በዓልነ። እስመ ሥርዓቱ ለእስራኤል ውእቱ"። መዝ 80፥3-4። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 8፥1፥ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 1፥11-13 እና የሐዋ ሥራ 8፥26-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 12፥1-12። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ባስልዮስ ወንድም የቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘኑሲስ ቅዳሴ ነው። መልካም የጾም ጊዜና በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤           ❤ #መጋቢት ፳፭ (25) ቀን። ❤ እንኳን #ከሰባ_ሁለቱ_አርድእት ለአንዱ ጌታችንም በአገረ ናይን የመበለቲቱን ልጅ በአስነሣው ጊዜ አይቶ ከአይሁድነት #በኢየሱስ_ክርስቶስ_አምኖ ለተከተለው ለከበረና ለተመሰገነ #ለሐዋርያ_ለቅዱስ_አንሲፎሮስ ለዕረፍት በዓልና #ለዘመነ_ሐጋይ(በጋ) መውጫ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                           ✝ ✝ ✝ ❤ #ሐዋርያ_ቅዱስ_አንሲፎሮስ፦ ይህም ከእስራኤል ልጆች ከብንያም ነገድ ነው። ወላጆቹም የኦሪትን ሕግ የሚጠብቁ ናቸው። እርሱም ሥራዎቹን በአየ ጊዜ ትምህርቶቹንም በሰማ ጊዜ ጌታችንን ተከተለው። ❤ ድንቅ የሆኑ ተአምራቶችን እየተመለከተ ጥቂት ቀን ተቀመጠ ጌታችንም በአገረ ናይን የመበለቲቱን ልጅ በአስነሣው ጊዜ ከዚያ ነበር። ይህን አይቶ ወዲያውኑ አመነ ሌላ ምልክት አልሻም ብልጭ ብልጭ ሲል የነበረ የአይሁድ የሕግ ፋናን ትቶ ወደ እውነተኛ ፀሐይ ወደ ጌታ ኢየሱስ ቀርቦ ደመ መዝሙሩ ሆነው እንጂ። ❤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከዐረገ በኋላ በጽዮን አዳራሽ አጽናኝ መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜ ከሐዋርያት ጋራ የመንፈስ ቅዱሳን ጸጋ ተቀብሎ የሐዋርያትንም በመከተል በብዙ አገሮች አስተማረ። ❤ ሐዋርያትም በአገረ አቴና ኤጲስቆጶስ አድርገው ሾሙት በውስጥዋም ወንጌልን በመስበክ ብዙዎችን አሳመነ የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቃቸው በትምህርቱና በምክሩ ዕውቀት እንዲያድርባቸው አደረጋቸው በትምህርቱም ከደዌ ሥጋ ከደዌ ነፍስ ፈወሳቸው። ❤ ተጋድሎውንም በፈጸመ ጊዜ መጋቢት25 በሰላም ዐረፈ። በድል አድራጊነትም የክብር አክሊል ተቀበለ። መላ ዘመኑ ሰባ ዓመት ነው። በአይሁድ ሕግ ሃያ ዘጠኝ ዓመት በክርስትና ሕግ አርባ አንድ ዓመት ኖረ። ❤ እንሆ የከበረ ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስም በመልእክቶቹ አስታውሶታል ሰላምታም አቅርቦለታል። ከሐዋርያ ቅዱስ አንሲፎሮስ በጸሎቱ የምትገኝ በረከቱ ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት25 ስንክሳር።                            ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለአንሲፎሮስ_እግዚአብሔር_ዘጸውዖ። ምስለ ሐዋርያት በጽዮን መንፈስ ቅዱስ ይቅብዖ። ለወልደ መበለት ምውት በሀገረ ናይን ጊዜ አንሥኦ። መንክሮ ነጺሮ ወትምህርተ ቃሉ ሰሚዖ። #ለወልደ_ማርያም አብደረ ከመ ይኩን ረድኦ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የመጋቢት_25።                           ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ወኢይትቃወመከ መንበረ ዓመፃ። ዘይፋጥር ፃማ ዲበ ትእዛዝ። ወይንዕዋ ለነፍስ ጻድቅ።" መዝ 93፥14-15። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 4፥14-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 5፥5-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 19፥21-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 4፥2-12። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ባስልዮስ ወንድም የቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ። መልካም የጾም ጊዜና በዓል። በሁላችንም ይሁንልን።

ያለ እኔን እንቢ ማለቱ ነው፡፡ የላከኝ አባቴንም እንቢ ማለቱ ነው፡፡ ይህን ሥልጣን ቀድሞ ለሐዋርያት ሰጥቻቸው ነበር፡፡ ከሐዋርያትም ሹመትን የተቀበለ ጳጳሱ ትሾምና ትሽር፣ ትተክልና ትነቅል ዘንድ ሥልጣንን ሰጠህ፡፡ ይህንንም ያደረኩልህ የጳጳሱን ቃል በመናቅ አይደለም፡፡ የፍቅሬን ጽናት ባንተ እገልጽ ዘንድ ነው እንጂ፡፡ ሐዋርያት ወዳልደረሱበት ሕዝብ በመምህርነት እልክህ ዘንድ በሚካኤል ቃል አዲስ ስም አወጣሁልህ፡፡ አንተም በማናቸውም ሥራ ከእነርሱ አታንስም፣ ሐዲስ ሐዋርያ አድርጌሃለሁና፡፡ ሰውን ሁሉ በእኔ ስም እያስተማርክ ታሳምን ዘንድ፣ ሚካኤልም ባሰብከው ሥራ ሁሉ ረዳት ይሁንህ፣ ሁል ጊዜ ካንተ አይለይም፤ በምትሄድበትም ጎዳና ሁሉ እርሱ መሪ ይሁንህ፤ እኔም ባለ ዘመንህ ሁሉ አልለይህም" ካላቸው በኋላ ሰላምታ ሰጥቷቸው ዐረገ፡፡ ❤ ብፁዕ አባታችንም እጅ ነሥተው ለእኔ ለኀጥኡ የማይገባኝ ሲሆን ይህን ሁሉ ጸጋ የጠኸኝ ስምህ በሰማይ በምድር የተመሰገነ ይሁን" አሉ፡፡ ከዚያች ቀን ጀምሮ ሀብተ ኃይልን የተመሉ ሆኑ፡፡ ወደቤታቸው ተመልሰው ያላቸውን ሀብት ንብረት ሁሉ ለቤተ ክርስቲያን፣ ለድኆችና ለጦም አዳሪዎች ሰጥተው ጨረሱ፡፡ ከዚያም "አቤቱ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! የመንግሥተ ሰማያትን በር ትከፍትልኝ ዘንድ እነሆ ቤቴን እንደተከፈተ ተውኩልህ" ብለው ቤታቸውን እንደተከፈተ ትተው ወንጌልን ለማስተማር ወጡ፡፡ ጻድቁ አባታችን በሀገራችን ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ ሕዝቡን ከኃጢአት ወደ ገቢረ ጽድቅ፣ ከክህደት ወደ ኃይማኖት ስለመለሱት በዚህም የተነሣ ለኢትዮጵያውያን ብርሃን ተብለዋል፡፡ ከአባታችን ከአቡነ ተክለሃይማኖት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን።