ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ
Open in Telegram
ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።
Show more638
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-1130 days
Posts Archive
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #መጋቢት ፳፬ (24) ቀን።
❤ እንኳን እንኳን ለታላቁ አባት ለሐዲስ ሐዋርያ ለኢትዮጵያ ብርሃኗ ለሆኑት #ለአቡነ_ተክለ_ሃይማኖት_ለፅንሰታቸው በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት (ፅንሰታቸው)፦ እግዚአብሔር አምላካችን ለኢትዮጵያ ሐዲስ ሐዋርያ አድርጎ የመረጣቸው ጻድቁ አባታችን ተክለ ሃይማኖት በሊቀ መላእክት በቅዱስ ሚካኤል አብሳሪነት ከአባታቸው ከካህኑ ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ከቅድስት እግዚእ ኀረያ መጋቢት 24 ቀን ተፀንሰው ታኅሣሥ 24 ቀን 1197 ዓ.ም ተወለዱ፡፡ ጻድቁ በተወለዱ በሦስተኛው ቀን ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው "አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ" ማለትም "አንዱ አብ ቅዱስ ነው አንዱ ወልድ ቅዱስ ነው አንዱ መንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ነው" በማለት የፈጠራቸውን አምላክ አመስግነውታል፡፡ ወላጆቻቸውም ስማቸውን ፍሥሐ ጽዮን አሏቸው፡፡ ይኸውም የጽዮን ተድላዋ ደስታዋ ማለት ነው፡፡ የወላጆቻቸው የቀድሞ ስማቸው ዘርዐ ዮሐንስና ሣራ ይባል ነበር፡፡
❤ ቅዱሳን አባቶቻችን እነ አቡነ ተክለ ሃይማኖትና እነ አቡነ ዜና ማርቆስ ሌሎቹም እነ አቡነ ሳሙኤል ዘወገግ፣ አቡነ ሕፃን ሞዐ፣ አቡነ አኖሪዮስ (ትልቁ)፣ አቡነ ገላውዲዮስ፣ አቡነ ማትያስ ዘፈጠጋርና አቡነ ቀውስጦስ ዘመሐግል የትውልዳቸው መሠረት ኢያሱ ለሌዋውያን ክፍል ትሆን ዘንድ ከለያት ከኢየሩሳሌም ነው፡፡ ስማቸውን የጠቀስኳቸው እነዚህ ቅዱሳን አባቶቻችን የወንድማማቾች ልጆች ሲሆኑ ከአዳም ጀምሮ 61ኛ ትውልድ ናቸው፡፡ ይኸውም እንዴት ነው ቢሉ ትውልዱ ከአዳም ጀምሮ በካህኑ አሮን በኩል የሆነውና የሌዋዊያን ሊቀ ካህን የነበረው የሳዶቅ ልጅ አዛርያስ በንጉሥ ሰሎሞን ዘመን ከታቦተ ጽዮንና ከብዙ ሌዋዊያን ካህናት ጋር ሊቀ ካህን ሆኖ ከኢየሩሳሌም ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ አክሱም ተቀምጦ ኖረ፡፡ የኦሪትንም ሕግ እየዞረ ለኢትዮጵያ ሰዎች አስተማረ:: ትውልዱም በአብርሃ ወአጽብሓና በአባ ሰላማ ዘመን እስከነበረው እንበረም የሚባለው ጻድቅ ድረስ ደረሰ፡፡ የእንበረምም ትውልድ ደገኛው ሕይወት ብነ በጽዮን ድረስ ደረሰ፡፡ ሕይወት ብነ በጽዮንም የደማስቆ ምድር ከሚሏት ከወለቃ ሀገር የመኰንን ልጅ የሆነችውን ወለተ ሳውልን አግብቶ አበይድላን ወለደ፡፡ አበ ይድላም በንጉሡ ድልዓዥን ዘመነ መንግሥት ለ150 ካህናት አለቃ ሆኖ በወለቃ ሀገር የክርስቶስን የወንጌል ሕግ እያስተማረ ብዙዎችን አጠመቀ፡፡ እስከ ሸዋ ምድር ድረስ እያስተማረ መጥቶ በሸዋ ምድር ተቀመጠ፡፡ ብዙ አብያተ ክርስቲያናትንም አሳነጸ፡፡ እጅግ አስደናቂ ተአምራትንም ያደርግ ነበር፡፡ "በሸዋ ጽላልሽ ተቀምጦ ሲያስተምርም በአንዲት ቀን እስከ ሁለት መቶ ሺህ ሕዝብ ያጠምቅ ነበር" በማለት ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ይመሰክርለታል፡፡
❤ አበይድላ በመጨረሻ በፈቃደ እግዚአብሔር ከሸዋ ጽላልሽ ምድረ ዞረሬ ሚስት አግቶ ሀበነ እግዚእን ወለደ፤ ሀበነ እግዚእም በኩረ ጽዮንን ወለደ፤ በኩረ ጽዮንም ሕዝበ ቀድስን ወለደ፤ እርሱም ነገደ እግዚእ የተባለ ነው፡፡ ሕዝበ ቀድስም ብርሃነ መስቀልን ወለደ፤ እርሱም ዐቃቢነ እግዚእ የተባለ ነው፡፡ ብርሃነ መስቀልም ሕይወት ብነን ወለደ፤ እርሱም ሴትን ወለደ፡፡ ሴትም ወረደ ምሕረትን ወለደ፡፡ ወረደ ምሕረትም ዘካርያስን ወለደ፡፡ ዘካርያስም የእነ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አባት የሆኑ 6 ወንድማማች ልጆችን ወለደ፡፡ እነርሱም እንድርያስ፣ አርከሌድስ፣ ዘርዐ አብርሃም፣ ዘርዐ ዮሐንስ ወይም ጸጋ ዘአብ፣ ቀሲስ ዮሐንስና ቀሲስ ዮናስ ናቸው:: እንድርያስም ሳሙኤል ዘወገግን ወለደ፤ አርከሌድስም ሕፃን ሞዐን ወለደ፤ ዘርዐ አብርሃምም ታላቁን አኖርዮስን ወለደ፤ ዘርዐ ዮሐንስ ወይም ጸጋ ዘአብም ተክለ ሃይማኖትን ወለደ፤ ቀሲስ ዮሐንስም ዜና ማርቆስን ወለደ፣ ቀሲስ ዮናስ ደግሞ የፈጠጋሩን ማትያስንና ገላውዲዮስን ወለዳቸው፡፡ ገላውዲዮስም የመሐግሉ ቀውስጦስን ወለደ፡፡ እነዚህ ደጋግ ቅዱሳን በእናታቸውም በኩል እንዲሁ በዝምድና የተሳሰሩ ናቸው፡፡ ማቴዎስ የተባለው ደገኛ ክርስቲያን የሸዋ ገዥ የነበረ ሲሆን አንድ ወንድ ልጅ መድኃኒነ እግዚእንና ሦስት ሴቶች ልጆችን ወለደ፡፡ ሶስቱ ሴቶች ልጆችም እምነ ጽዮን፣ ትቤ ጽዮንና ክርስቶስ ዘመዳ ይባላሉ፡፡ ሦስቱ እኅትማማቾችም ደጋጎቹን አባቶቻችንን ወለዱልን፡፡ እምነ ጽዮን የእነ ዜና ማርቆስን እናት ማርያም ዘመዳንና ወለደች፡፡ ትቤ ጽዮንም ሕፃን ሞዐን ወለደች፡፡ ክርስቶስ ዘመዳ ደግሞ ታላቁን አኖሬዎስን ወለደች፡፡ የፈጠጋሩ ገዥ መድኃኒነ እግዚእ ደግሞ የተክለ ሃይማኖትን እናት እግዚእ ኀረያን ወይም በሌላ ስሟ ሣራን ወለደ፡፡
❤ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከልጅነታቸው ጀምሮ በወላጅ አባታቸው በካህኑ ቅዱስ ጸጋ ዘአብ ግብረ ዲቁናን ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን ሲያጠኑ ቆይተው በ15 እና በ22 ዓመታቸው ከእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ ከአቡነ ቄርሎስ (ጌርሎስ) ዲቁናንና ቅስናን ተቀብለዋል፡፡ ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን ቅድስት ቤተክርስቲያንን በወጣትነት ዕድሜያቸው ያገለግሉ እንደነበር በዚህ ይታወቀል፡፡
❤ ከዕለታት በአንዱ ቀን አባታችን ከጓደኞቻቸው ጋር ለአደን ወደ ዱር ሄደው ሳለ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦ ታያቸው፡፡ ቅዱስ አባታችንም "እንደዚህ ባለ ገናንነት የማይህ ጌታዬ ማነህ?" ባሉት ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል "ዘወትር የምጠብቅህ ካንተ የማልለይ እናትህንና አባትህንም ስላንተ ከውኃ ስጥመትና ከምርኮ ያዳንኳቸው እኔ ሚካኤል ነኝ፡፡ ከእንግዲህ አውሬ አዳኝ አትሁን፤ ሰውን ወደ እግዚአብሔር ለመመለስ ሰውን በትምህርት የምታድን ሁን እንጂ፡፡ እነሆ እግዚአብሔር ጽኑዕ ሥልጣን ሰጥቶሃልና፤ ሙት ታስነሣለህ፤ ድውያንን ትፈውሳለህ፤ አጋንንትም አንተን በመፍራት ይሸሻሉ፡፡ ስምህ ፍሥሐ ጽዮን አይሁን፤ ተክለ ሃይማኖት ይሁን እንጂ፡፡ ትርጓሜውም ተክለ አብ፥ ተክለ ወልድ፥ ተክለ መንፈስ ቅዱስ ማለት ነው" አላቸው፡፡
❤ ቅዱስ ሚካኤል ይህን ሲነግራቸው ጌታችን በሥጋ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር እንደነበር ሆኖ መልከ መልካም ጎልማሳ መስሎ ታያቸው፡፡ ጌታችንም "ወዳጄ እንዴት ሰነበትክ? ቸር አለህን?" አላቸው፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖትም "ጌታዬ ሆይ አንተ ማነህ?" ብለው ሲጠይቁት ጌታችንም "እኔ የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ነኝ፤ በናትህ ማኅፀን ፈጥሬህ ያከበርኩህ እኔ ነኝ፡፡ በተወለድክ በሦስተኛው ቀን አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ብለህ ታመሰግነኝ ዘንድ የምስጋና ሀብት ያሳደርኩብህ እኔ ነኝ፡፡ በርሃብ ዘመን በቤት የሚያሻው ምግብ ሁሉ ቅቤው፣ የስንዴው ዱቄት በእናት በአባትህ ቤት ይመላ ዘንድ በእጅህ ሀብተ በረከት ያሳደርኩብህ እኔ ነኝ፡፡ ያንን ሰው አንተን በተጣላ ጊዜ በነፋስ አውታር የሰቀለኩት በመዓት ጨንገር የገረፍኩት እኔ ነኝ፡፡ ውኃ ጠምቶህ በለመንከኝ ጊዜ ከደረቅ መሬት የጣፈጠ ውኃ ያመነጨሁልህ እኔ ነኝ፡፡ ከልጅነትህ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ብዙ ተአምራት እያደረግሁ በአንተ እጅ የታመሙትን ያዳንኳቸው እኔ ነኝ፡፡ ወደፊትም አደርግልሃለሁ" አላቸው፡፡ ይህንን ብሎ በእጆቹ ባረካቸውና "ንሣእ መንፈስ ቅዱስ" ብሎ የሹመትን ሀብት አሳደረባቸው፡፡ ዳግመኛም "በምድር ያሰርከው በሰማይ የታሰረ ይሁን፤ በምድርም የፈታኸው በሰማይ የተፈታ ይሁን፤ አንተን የሰማ እኔን መስማቱ ነው፤ የላከኝ አባቴንም መስማቱ ነው፡፡ አንተን እንቢ
❤ እግዚአብሔር መልአኩን ወደ ዕንባቆም ላከው እርሱም በኢየሩሳሌም ውስጥ ለአጫጅዎች ምሳ ተሸክሞ ሲሔድ በራስ ጠጉሩ ተሸከመው። ወስዶም ዳንኤል በአለበት ጒድጓድ ውስጥ አኖረው ዳንኤልም ተመግቦ እግዚአብሔርን አመሰገነው በዕንባቆምም ቃል ተረጋጋ በዚያችም ሰዓት እግዚአብሔር የላከው መልአክ ወደ አገሩ ወደ ኢየሩሳሌም መልሶ አደረሰው።
❤ በሰባተኛዪቱ ቀንም ስለ ዳንኤል እያለቀሰ ንጉሡ ወደ ጒድጓዱ መጣ ዳንኤል ሙቶ አንበሶች የበሉት መስሎት ነበርና። ወደ ጒድጓዱም ሲመለከት ዳንኤልን አየው አንበሶችም እንደ ድመቶች እግሮቹን እየላሱ ከእግሮቹ በታች እጥፍጥፍ ብለው ተኝተው ነበር። ንጉሡም "እግሮቹን እስከሚልሱ እንደ ድመቶች አንበሶችን ያገረመለትና ያስገዛለት የዳንኤል አምላክ ታላቅ ነው ብሎ ከፍ ባለ ድምፅ ጮኸ"።
❤ በዚያን ጊዜ ዳንኤልን ከጒድጓድ እንዲያወጡት እነዚያንም የዳንኤልን ጠላቶች ይዘው ለአንበሶች ወደ ጒድጓድ እንዲጥሏቸው ንጉሥ አዘዘ ወዲያው እነዚያ አንበሶች በንጉሡ ፊት በሏቸው።
❤ ዳንኤልም የእስራኤል ልጆች ወደ ኢየሩሳሌም እስከ ሚመለሱበት ጊዜ በባቢሎን ኖረ እርሷም ሰባ ዘመን ናት ከዚያም በኋላ መጋቢት23 በሰላም በፍቅር ዐረፈ። ከቅዱስ ዳንኤል በጸሎቱ የምትገኝ በረቱ ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ በዚች ቀን በጌታችን ላይ ሊመክሩ የአይሁድ ማኅበር በቀያፋ ቤት ተሰበሰቡ። ይቅርታውና ቸርነቱ ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ይኑር አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት 23 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ዳንኤል እንተ ፈከረ በቃሉ። ሕልመ ንጉሥ ሥውረ እንዘ ትርጓሜ ያተሉ። ተዘኪሮሙ ረድኤተ ዘተውህበቶ እምላዕሉ። ሶበ በጸሎት አምላክ ዳንኤል ይብሉ። እምአፈ አናብስት ድኅኑ ሰማዕታት ኵሉ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የመጋቢት 23።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ ወበጽርሑሰ ኵሉ ይብል ስብሐት። እግዚአብሔር ያስተጋብዖ ለማየ አይኅ። ይነብር እግዚአብሔር ወይነግሥ ለዓለም"። መዝ 28፥9-10 ወይም መዝ 117፥25-26። የሚነበቡት መልዕታት 1ኛ ቆሮ 6፥14-18 ወይም ገላ 4፥12- 21፣ 3ኛ ዮሐ 1፥12-15 ወይም 1ኛ ዮሐ 5፥1-9 እና የሐዋ ሥራ 3፥22-26 22፥16-20 የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 19፥28-44 ወይም ማቴ 21፥1-14። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ። መልካም በዓልና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #መጋቢት ፳፫ (23) ቀን።
❤ እንኳን ከአራቱ ዐበይት ነቢያት ለአንዱ የዮናኪር ሴት ልጁ ለወለደችው #ለታላቁ_ነቢይ_ለቅዱስ_ዳንኤል ለዕረፍት በዓል መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #ነቢዩ_ቅዱስ_ዳንኤል፦ ናብከደ ነጾርም ኤየሩሳሌምን በወራራት ጊዜ አባታቸው ዮናኪር አናንያን አዛርያና ሚሳኤልን ሦስቱን ልጆቹን የልጁን ልጅ ዳንኤልንም ወሰዳቸው ከእርሳቸውም ጋር ከእስራኤል ልጆች ብዙ ሰዎች ተማረኩ። ይህም ዮናኪር የንጉሡ የኢዮአቄም ልጅ ነው።
❤ ኢሳይያስ ለሕዝቅያስ ንጉሥ ትንቢት እንደተናገረ የቤተ መንግሥቱንና የቤተ እግዚአብሔርን እቃ ሁሉ ናብከደጾር ወደ ባቢሎን ወደሰደ።
❤ ይህ ዳንኤል በእድሜው ታናሽ ነበር ፍጽም የሆነ ታላቅ ተጋድሎ ተጋደለ የእግዚአብሔር መንፈስ አድሮበት በባቢሎን አገር ትንቢት ሲናገር ኖረ።
❤ ምርኮ በሆነ በአራተኛው ዓመት ናቡከደነፆር የምታስፈራ ራእይ አየ ከእቅልፉም በነቃ ጊዜ ያች ህልም እረሳት በባቢሎን የሚኖሩትን ሁሉ ጥበበኞች ሰበሰባቸው ከርሳቸውም ያች ራእይ ትርጓሜዋን እንዲነግሩ ፈለገ እነርሱ ግን ያች ራእይ ትርጓሜዋን ሊያውቋት አልቻሉም የባቢሎንን ጥበበኞች ሁሉ እርሱንና ባልጀሮቹን ሠለስቱ ደቂቅን ይገድሏቸው ዘንድ ንጉሥ አዘዘ።
❤ ዳንኤልም ይህን ነገር ሰምቶ የዘበኞቹን አለቃ "ስለምን እዲህ ያለ ትዕዛዝ ከንጉሥ ዘንድ ታዘዘን" ብሎ ጠየቀው እርሱም "ንጉሥ ስላያት ራእይ ነው። የባቢሎንና የግብጽ ጠቢባን ሁሉ እርሷን ራእይ ትርጓሜዋን ሊነግሩት አልተቻላቸውምና" ብሎ መለሰለት ዳንኤልም የዘበኞቹን አለቃ "እኔ ለንጉሥ ህልሙን እንደምነግረውና ፍችው እንደምተረጉምለት ስለእኔ ንገረው እሊህንም ተዋቸው" አለ።
❤ ከዚህ በኋላ ዳንኤል ወደ እግዚአብሔር ጸለየ ባልጀሮቹ ሠለስቱ ደቂቅም ከእርሱ ጋር የንጉሡን ህልም ፍችዋንም ሊገልጥላቸው ዘንድ በአንድነት ማለዱ እግዚአብሔርም ገለጠላቸው ዳንኤልም ወደ ንጉሥ ገብቶ ህልሙንና ፍቺዋን ነገረው ከእርሱ በኋላ ስሚነሱ ነገሥታት ከእያንዳንዳቸው የሚሆነውን ገለጠለት የዳንኤልም ቃል ናቡከደነፆርን ደስ አሰኘው በፊቱ ሰገደ ብዙ እጅ መንሻ ሰጠው ታላቅ ክብርንም ሰጥቶ በባቢሎን ጠጢባን ሁሉ ላይ አለቃ አድርጎ ሾመው።
❤ ከዚህም በኋላ ናቡከደነፆር ሌላ ህልም አየ ያንንም ተረጎመለት እንዲህም ብሎ አስረዳው "ስለታበይክ እግዚአብሔር ከሰው መካከል አውጥቶ ከአራዊት ጋራ በዱር ሰባት ዓመት ያኖር ዘንድ አለው እንደ እንስሳ ሣር ትበላለህ ከሰባት ዓመትም በኋላ ወደ መንግሥትህ ይመልስሃል" በማለት ይህም ተፈጸመበት።
❤ ናቡከደነፆር ከሞተ በኋላ መልአክ በግድግዳ ላይ የጻፉቱን ለልጁ ለብልጣሶር ተረጐመለት በቤተ እግዚአብሔር እቃ በጠጣ ጊዜ ጽሑፍ የተቀጠረ የተመጠነ የተመዘነ እንደሆነ ትርጓሜውን ዙፋኑን መግሥቱን እግዚአብሔር ለሌላ የሰጠው መሆኑን ገለጠለት እዲህም አለው "ቢመዝንህ ጎደሎ ሁነህ አገኘህ መንግሥትህም ለፋርስ አሳልፎ ሰጠ" ትንቢቱም ተፈጸመች።
❤ እግዚአብሔርም እስከ ዓለም ፍጻሜ የሚነግሡቱን ነገሥታት በራእይ አሳየው የሐሳዊ መሲሕንም መገለጥ አሳየው።
❤ ከዚህ በኋላ እግዚአብሔርነቱን ክቡር ልዕልናውን ጌትነቱን አሳየው። የክብር ባለቤት ክርስቶስን ወደ ዓለም መምጣቱን ትንቢት ተናገረ ሱባኤዎችም ወሰነ እነዚያ ሱባኤዎችም በተፈጸሙ ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መጣ። ክርስቶስ ይመጣል ይገድሉታልም በኢየሩሳሌም መዳኞዋ ይሆናታል ብሎ ትንቢት እንደተናገረ የክብር ባለቤት ከሆነ ከጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ስቅለት በኋላ ኢየሩሳሌም እንደምትጠፋ ቤተ መቅደስ እንደሚፈርስ የተናገረው ትንቢት ሁሉ ተፈጸመ።
❤ በባቢሎን አገርም ቤል የሚባል ጣዖት ነበር ምግቡም ሁል ጊዜ ዐሥራ ሁለት ጫን በሚፈጅ ቻል፣ ዐሥራ ሁለት መስፈርያ ስንዴ፣ አርባ በግ፣ ሰባት ፊቀን የወይን ጠጅ እያወጣጡ ይሰጡተት ነበር። ንጉሡም ሁል ጊዜ ይሰግድለታል ቤል ጣዖትም ከንጉሡ ቤት የሚሰጡትን የሚበላና የሚጠጣ ይመስለው ነበር። ንጉሡም ዳንኤልን "ለቤል የማትሰግድ ለምድን ነው?" አለው ዳንኤልም ንጉሡን "እኔስ ሰማይንና ምድርን ለፈጠረ ፍጥረቱንም ሁሉ በሕያውነት ለሚያኖር አምላክ እንጂ የሰው እጅ ለሠራው ጣዖት አልሰግድም" አለው። ንጉሡም "ቤል ሕያው ያልሆነ ይመሰግሃልን? በየነጋታው እንዲበላ እንዲጠጣ አታይምን" አለው። ዳንኤልም በንጉሡ ሳቀበት "ንጉሥ ሆይ ይበላል ይጠጣል እያሉ አያታሉህ ይህ ውስጡ ጭቃ ላይ ናስ ነው ምንም ምን አይበላም አይጠጣም" አለው። ንጉሡም ተቆጣ የጣዖቱንም ካህናት ጠራቸው "እውነት ነውን ቤል አምላክ አይበላም አይጠጣም" አላቸው።"ሁል ጊዜ የምንሰጠውን በእውነት ይበላል ይጠጣል" አሉት።
❤ ከዚህም በኋላ በመሸ ጊዜ ከጣዖቱ ዘንድ መብሉንና መጠጡን ሁሉ ንጉሡ እየተመለከተ ካህናቱ አስቀምጠው ወጡ የጣዖቱ ካህናትም ከወጡ በኋላ ዳንኤል አመድ አምጡ ብሎ አዘዘ። አመጡለትም ንጉሡም ከእዛ ሆኖ እያየ ከጣዖቱ ቤት ውስጥ ነሰነሰው ንጉሡም በቁልፉ ከዳንኤል ጋራ በአንድነት ቈለፉት አተሙትም ወደ ማደሪያቸውም ሔዱ። የጣዖቱ ካህናት ግን ከምድር በታች ውስጥ ለውስጥ መግቢያ ቀዳዳ ነበራቸው ከሚስቶቻቸው ከልጆቻቸው ጋራ በሌሊት በዚያ ገብተው በሉ ጠጡ በመጡበትም ተመለሱ።
❤ በማግስቱም ንጉሡ መጥቶ የጣዖቱን ቤት ከፈተ ራሱ ከአኖረው መብሎች ምንም አላገኘም ንጉሡም "ቤል ሆይ ፈጣሪዬ ዳንኤልን ያሳፈርከው አንተ ገናና ነህ" ብሎ ጮኸ። ዳንኤልም ሳቀ ለንጉሡም ወንዶችና የሴቶችን የልጆችንም ፍለጋቸውን በአመድ ላይ አሳየው ንጉሡም የጣዖቱን ካህናት ይዞ መረመራቸው እነርሱም ውስጥ ለውስጥ ተሠውረው የሚገቡበትንና የሚወጡበትን ለንጉሥ አሳዩት። ያን ጊዜ ንጉሥ ተቆጥቶ የጣዖቱን ካህናት ከሚስቶቻቸውና ከልጆቻቸው ጋራ ገደላቸው ጣዖቱንም ለዳንኤል ሰጠው ዳንኤልም ሰበረው ምኵራቡንም አፈረሰ።
❤ ከዚህ በኋላ ደግሞ የባቢሎን ሰዎች የሚያመልኩትና የሚሰገዱለት ታላቅ ዘንዶ ነበር ንጉሡም ዳንኤልን "ይህንንስ አምላክ አይደለም ትለዋለህን እነሆ ሕያው ነው ይባላል ይጠጣል ናስ ነው ትለው ዘንድ አትችልምና ስገድለት እንጂ" አለው። ዳንኤልም ለንጉሡ እንዲህ ብሎ መለሰለት "እኔስ በሕያውነት ከሚኖር ከእግዚአብሔር በቀር ለሌላ አልሰግድም ግን ያለ ሰይፍና ያለ በትር ይህን ከይሲ እገድለው ዘንድ አሰናብተኝ" አለው። ንጉሥም "አሰናበትኩህ" አለው።
❤ ዳንኤልም ጠጉርና አደሮ ማር ወስዶ እንደ እንቁላልም አድበልብሎ በእሳት አጋለው በሞራም ጠቅልሎ ለከይሲው አጐለሰው በዋጠውም ጊዜ ሆዱ ተሰንጥቆ ሞተ ዳንኤልም "የባቢሎን ሰዎች ሆይ አምላካችሁን ተመልከቱ" አላቸው። የባቢሎን ሰዎች በሰሙ ጊዜ እጅግ ተቆጡ ወደ ንጉሡም ተሰብስበው "አይሁዳዊ ዳንኤል ነግሦአልን እነሆ ቤልን ሰበረው ካህናቶቹንም ገደላቸው። ከዚያም ደግሞ ዘንዶውን ገደለው አሁን እርሱን ዳንኤልን እንድንገድለው ካልሰጠህን አንተን ቤተ ሰብህን እንገድላለን" አሉት።
❤ ንጉሡንም እጅግ አስጨነቁት ጊዜ ስለ ዳንኤል አዘነ ግን ዳንኤልን ሰጣቸው እነርሱም ለአንበሶች ጒድጓድ ውስጥ ጣሉት በዚያም ሰባት ቀን ኖረ። ከረኀብ ጽናትም የተነሣ እንዲበሉት በሌላ ጊዜ የሚሰጧቸውን በእነዚያ ቀኖች ምንም ምን አልሰጧቸውም ነበር።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #መጋቢት ፳፫ (23) ቀን።
❤ እንኳን #ከአቡነ_ተክለ_ሃይማኖት በኋላ ለደብረ ሊባኖስ ሦስተኛ መምህር (እጨጌ) ለሆኑት #ለአቡነ_ፊሊጶስ_ፍልሰተ_ዐፅማቸው በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #አቡነ_ፊሊጶስ_ዘደብረ_ሊባኖስ፦ በተወለዱ በ15 ዓመታቸው በምናኔ ወደ ደብረ ሊባኖስ ገቡ፡፡ ከብዙ ጊዜ አገልግሎትም በኋላ በአቡነ ተክለሃይማኖት እጅ መንኩሰው ከእርሳቸውም ዕረፍት በኋላ ሦስተኛ አበምኔት ሆነው አገልግለዋል፡፡ በኢትዮጵያ ከተወለዱት የመጀመሪያ ፓትርያርክ ሆነዋል፡፡ አባታቸው ቅዱስ ተክለሃይማኖትም በመንፈቀ ኢትዮጵያ ጳጳስ ሆነው ነበር፡፡ በመጀመሪያ የአቡነ ፊሊጶስን የጽድቅ ሕይወትና ሹመታቸውን በተመለከተ በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ገድልና በራሳቸው በአቡነ ፊሊጶስ ገድል ላይ የተጻፈውን እንመልከት፡- "ክቡር አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ከዚህ ዓለም ተለይቶ የሚሄድበት ጊዜ ሲደርስ "ከአንተ በኋላ አንተን ተክቶ በዙፋንህ የሚቀመጥ ማነው?" አሉት፡፡ እርሱም "ብዙ ዘመን አይኖርም እንጂ ኤልሳዕ በእኔ ተተክቶ ይቀመጥ" አለ፡፡ ስለ ፊሊጶስ ግን አላነሳም፣ ኤልሳዕ ካረፈ በኋላ በእርሱ ተተክቶ አባት ይሆን ዘንድ ጌታችን የተሸለመ ፊሊጶስን እንደመረጠው ስም አጠራሩ ለልጅ ልጅ ዘመን እንደሚጸና ያውቅ ነበርና ስለዚህ "አልሳዕ በእኔ ተተክቶ አባት ይሁናችሁ" አለ፡፡ ክቡር አባታችንም በታላቅ ክብር ዐረፈ፡፡
❤ አንድ ቀን አንድ ዲያቆን ዐረፈና ሬሳውን ገንዘው አጠቡት፣ ይቀብሩትም ዘንድ አስክሬኑን ይዘው ሲሄዱ በአልጋ ላይ ሳለ አስክሬኑ ተንቀሳቀሰ፡፡ የተሸከሙትም ደንግጠው መሬት ላይ አስቀመጡትና ከመግነዙ ፈቱት፡፡ እርሱም ተነሥቶ ሦስት ጊዜ ተነፈሰ፡፡ ወንድሞችም "ምን እያልክ ነው?፣ ወዴትስ ነበርክ?" አሉት፡፡ ያ የከበረና የተመረጠ ዲያቆንም ‹ክቡር አባታችን ተክለሃይማኖት "ኤልሳዕ ወደኔ ይምጣ፣ ፊሊጶስ ስለ እኔ ተሹሞ በወንበሬ ይቀመጥ እርሱ ለብዙዎች አሕዛብ አባት ይሆናልና የክርስቶስንም መንጋ በጽድቅና በቅን ይጠብቃል" ብሎኛል› ብሎ ይህን ተናግሮ ተመልሶ ዐረፈ፡፡ ወንድሞችም ኤልሳዕ እንደልማዱ ጎኑን ሳያሳርፍ በወንበር ላይ እንደተደገፈ በሞት ማረፉን አላወቁም ነበር"፡፡
❤ ወደ ጻድቁ የልጅነት ገድላቸው እንመለስና አቡነ ፊሊጶስ በእግዚአብሔር ተመርጠው የመንፈስ ቅዱስም ማደሪያ ሆነዋልና ገና በሕፃንነታቸው በተወለዱባት ሰላሌ ክፍለ ሀገር ዝማ በምትባል ልዩ ቦታ ውስጥ ሰይጣን በጠንቋይ ላይ አድሮ በነደደ በእሳት ውስጥ በመግባትና የተለያዩ ተአምራትን በማድረግ በአካባቢው ራሱን ያስመልክ የነበረን ሰይጣን በእሳት ውስጥ እንዳለ በስመ ሥላሴ አማትበውበት አመድ አድርገውታል፡፡ በዚህ በአቡነ ፊሊጶስ ድንቅ ተአምር የጠንቋዩ ቤተሰቦችና የአካባቢው ሰዎችም አምነው ሊጠመቁ ችለዋል፡፡ ይህንንም ያደረገው ገና ሕፃን ሳለ ነው፡፡ መልአከ እግዚአብሔር ተገልጦለት የትውልድ መንደሩን ትቶ ወደ ግራርያ ሀገር ደብረ አስቦ ሄዶ ቅዱስ ተክለሃይማኖትን እንዲያገኝ በነገረው መሠረት አንድ ቀን ያህል ተጉዞ ተክለሃይማኖትን አገኛቸውና ባርከውት ከመነኰሳት ጋር እንዲያርፍ አደረጉት፡፡ ሦስት ዓመት እነርሱን በመልካም ሥራ ፍጹም ሆኖ ሲያገለግላቸው ከቆየ በኋላ "ሁሉም በአንድነት አሁን ልብሰ ምንኩስና ይገባዋል" አሉ፡፡ ቅዱስ አባታችን ተክለሃይማኖትም የምንኵስናን ሥራ የሚያሠራ ቅድስናን ሰጠው፡፡
❤ በሌላም ጊዜ ቅስናን ይቀበል ዘንድ ወደ ጳጳሱ ዘንድ ላኩት፡፡ አቡነ ፊሊጶስ በንጉሥ አምደ ፅዮን ዘመነ መንግሥት ሥጋቸው አልቆ አጥንታቸው እስኪቀር ድረስ ሲገረፉ ደማቸው እሳት ሆኖ ገራፊዎቻቸውን ያሳደደ ቅዱስና ጻዲቅ አባት ናቸው፡፡ ንጉሥ አምደ ጽዮን በክፉ ጠንቋዮች ምክር ተታሎ ‹‹ያልወለደችህን የአባትህን ሚስት ብታገባ መንግሥትህ ትፀናለች›› ብለው ክፉ ምክርን መክረውት የእንጀራ እናቱን አገባትና ንግሥት አደረጋት፡፡ አቡነ ፊሊጶስም ይህን ሲሰሙ ነቢዩ ኤልያስ ንጉሡ አክአብንና አልዛቤልን በድፍረት እንደገሠጻቸው እርሳቸውም በቀጥታ ሄደው ንጉሡን ዘልፈው ገሠጹት፡፡ ወደ ንጉሡም ከመሄዳቸውም በፊት በዚህ ምክንያት ሰማዕት እንደሚሆኑ አውቀውት ነበርና ልጆቻቸውን ተሰናብተውና የሚተካቸውን ሰው ነግረዋቸው ነው የሄዱት፡፡ ንጉሡ አምደ ጽዮንም አጥንታቸው እስኪቀር ድረስ አስገረፋቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቶቻቸውም መሬት ላይ እየተቆረሰ የወደቀውን ሥጋቸውን እያነሱ ለበረከት ወሰዱት፡፡ ደማቸውም እንደ እሳት ሆኖ ገራፊዎቻቸውን ያቃጥላቸው ነበር፡፡ 300 አንስራ ውኃ አምጥተው ከደሙ በወጣው እሳት ላይ ቢያፈሱትም የውኃው ብዛት እሳቱን ማጥፋት አልቻለም፡፡ ንጉሡም በፍርሃት ከዙፋኑ ላይ ወርዶ ሸሸ፡፡
❤ የንጉሡ ጭፍሮች ግን በጋለ ማረሻ ጀርባና ግንባራቸውን ደረታቸውንም ተኮሷቸው፡፡ ኃፍረታቸውንም እንዳይሸፍኑ እጆቻቸውን ወደ ኋላ አስረው ራቁታቸውንም በከተማው ሁሉ ሲያዞሯቸው ዋሉ፡፡ ማታም ንጉሡ "ታስረው ለኖሩ ኃይለኛ ውሾች ስጡት" ብሎ በማዘዝ ውሾቹ እንዲቦጫጭቋቸው ቢያደርጉም ውሾቹ ግን ከእግራቸው ስር ሰግደዋል፣ እርሳቸውም በእግራቸው ባረኳቸው፡፡ አማካሪዎቹም ንጉሡን ‹‹ከዚህ መነኩሴ ጋር ምን አጨቃጨቀህ በግዞት አርቀህ ስደደው ብለው" ብለው መክረውት "እስከ ቆርቆራ አገር አውጥታችሁ ወደ ትግሬ አገር ውሰዱት" ብሎ አዘዘ፡፡ እርሳቸውም ንጉሡን ከ3 ዓመት በኋላ ትሞታለህ ብለው ትንቢት ነገረውት በወታደሮች ተወሰዱ፡፡ በግርፋት ብዛት የተቆረሰ ሥጋቸው ድውያንን ይፈውስ ነበር፡፡
❤ ደማቸውም አስረው የሚወስዷቸውን የአንዱን ወታደር አንድ ስውር ዐይኑን ፈወሰለትና ወታደሮቹም አምነው ከእርሳቸው ጋር በዚያው ተሰደው መከራን ተቀብለዋል፡፡ እሳቸው በትግራይ ታላላቅ ተአምራትን እያደረጉ ሲያስተምሩ በትንቢታቸው መሠረትም ንጉሡ ከሦስት ዓመት በኋላ ሞተና ልጁ ነገሠ፡፡ ልጁም አባታችንን ከስደት መለሳቸውና ከተክለሃይማኖት መቃብር ደብረ አስቦ ገቡ፡፡ የነገሠውንም ልጅ አንድ ክፉ ሰው "ከአንድ በላይ ማግባት ትችላለህ፣ በገና ወቅትም ረቡዕና አርብን መጾም ተገቢ አይደለም" ብሎ ስለመከረው ጳጳሱን ወደ ሀገራቸው ግብፅ እንዲሰደዱ ሲያደርግ አቡነ ፊሊጶስን ደግሞ "ረቡዕና አርብን በጠዋት ካልቀደስክ" ብሎ ወደ ደራ ተሰደው እንዲሄዱ አደረገ፡፡ አባታችን በአጠቃላይ አምስት ጊዜ ተሰደው በትግራይ፣ በደራ፣ በዝዋይ ባሕረ ደሴት፣ በዳሞት ገማስቄ እና በወለቃ በስደት ቆይተዋል፡፡ ጳጳሱን አባ ሰላማን በአቃሊት ቅበረኝ ብለዋቸው በቃሬዛ አድርጎ ከጌርጌሳ ወደ አቃሊት ወሰዷቸው፤ እዚያም ሐምሌ 28 ቀን በሰላም ዐረፉ፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሰባት አክሊላት አቀዳጅቷቸዋል፡፡ዐፅማቸውም ከተቀበረ ከ140 ዓመት በኋላ በመጋቢት 23 ቀን ወደ ደብረ ሊባኖስ በክብር መጥቶ ዐርፏል፡፡ ከአቡነ ፊሊጶስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። ምንጭ፦ ከገድላት አንደበት።
❤ ከዚህም በኋላ ይህ መናፍቅ ቈስጠንጢኖስ ሞተ። ልጁ ሦስተኛው ቈስጠንጢኖስ ነገሠ ይህንንም አባት ከተሰደደበት ወደ መንበረ ጵጵስናው መለሰው አባቱ ያሳደዳቸው ኤጲስቆጶሳት ሁሉንም መለሳቸው። ይህም አባት የተረፈውን ዘመን በሰላምና በጸጥታ ኖረ።
❤ ታላቁ ቴዎዶስዮስም በነገሠ ጊዜ ስለ መቅዶንዮስ ስለ ሰባልዮስና ስለ አቡሊናርዮስ በቊስጥንጥንያ መቶ ሃምሳ ኤጲስቆጶሳትን አንድነት ጉባኤው ውሰጥ አንዱ እርሱ ነበር መናፍቃንም መመለስን እንቢ በአሉ ጊዜ ከወገኖቹ ጋር ረገማቸው አውግዞም ለያቸው።
❤ ሃይማኖትን ያቀኑ ሦስት መቶ ዐሥራ ስምንቱ በሠሩት በጸሎተ ሃይማኖት ላይ ለመንግሥቱም ፍጻሜ የለውም ከሚለው ቀጥሎ እንዲህ የሚል ጨመረ። "የባሕርይ ገዢ የሚሆን በሚያድን በመንፈስ ቅዱስ እናምናለን። ከአብ የተገኘ ከአብ ከወልድ ጋር እንስገድለት እናመሰግነውም በነቢያት አድሮ የተናገረ። ሐዋርያት ስብስበው አንድ በአደረጓት ከሁሉ በላይ በምትሆን ክብርት ንጽሕይት ጽንዕት ልዩ በምትሆን በአንዲት ቤተ ክርስቲያን እናምናለን። ኃጢአት በሚሠረይባቶ በአንዲት ጥምቀት እናምናለን። የሙታንንም መነሳት ተስፋ እናደርጋለን የሚመጣውንም የዘላለም ሕይወት"።
❤ ከዚህ በኋላ ይህ አባት በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶ ብዙ ድርሳናትንና ተግሣጻትን ደረሰ። ሁለተኛም ስለ ጸሎት ሃይማኖትና ስለ ትርጓሜው ሌላ በውስጡ ዐሥራ ስምንት ያህል ድርሳን ያለው መጽሐፍ ደረሰ። እርሱም ጥበብን እውቀትን ሁሉ የተመላ እጅግ የሚጠቅም ነው።
❤ በጵጵስናውም መንበር ሠላሳ ሦስት ዓመት ከኖረ በኋላ መጋቢት 22 ቀን በሰላም ዐረፈ። በአባ ቄርሎስ በጸሎቱ የምትገኝ በረከቱ ከእኛ ጋር በዘላለም ትኑር አሜን። ምንጭ፦የመጋቢት22 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለዕርገትከ ወለበዓትከ ማዕከላ። #ኢየሱስ_ክርስቶስ በተጽዕኖ ዕድግት ምስለ ዕዋላ። ኢየሩሳሌም አሜሃ ኢያእመረት መዋዕለ ሣህላ።ሀገርኒ ተሀውከት ኵላ። መኑ ውእቱ ኪያከ ብሂላ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የመጋቢት 22።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "እምአፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሐተ። በእንተ ጸላኢ። ከመ ትንሥቶ ለጸላኢ ወለገፋዒ"። መዝ 8፥2። የሚነበቡት መልዕክታት 1ቆሮ 4፥1-7፣ 2ኛ ዮሐ 1፥8-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 5፥1-17። የሚነበበው ማቴ 21፥1-18። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ቄርሎስ ወይም የቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ ቅዳሴ ነው። መልካም የጥንት ሆሳዕና በዐልና የጾም ወራት። በሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #መጋቢት ፳፪ (22) ቀን።
❤ እንኳን #ለክብር_ባለቤት_ለጌታችን_ለአምላካችን #ለመድኃኒታችን_ለኢየሱስ_ክርስቶስ ወደ ኢየሩሳሌም ከተማ ገብቶ ቤተ መቅደሱን በአህያ ግልገል ተቀምጦ በመዞር ሆሣዕና እያሉ እንዲያመሰግኑት ላደረገበት (ጥንት ሆሣዕና)ና ስለ መቅዶንዮስ ስለ ሰባልዮስና ስለ አቡሊናርዮስ በቊስጥንጥንያ መቶ ሃምሳ ኤጲስቆጶሳትን ከተሰበሰቡት አንድነት ጉባኤው ውሰጥ አንዱ ለሆነው #ለኢየሩሳሌም_ኤጲስቆጶስ_ለአባ_ቄርሎስ ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #ጥንት_ሆሳዕና፦ ይህም ስርሱ እየአንዳንዳቸው በዘመናቸው ነቢያት የተናገሩት ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ነው።
❤ ያዕቆብ በክርስቶስ ስለ ተመሰለው ስለ ልጁ "ይሁዳ አህያውን ዘይት ዕንጨት ላይ ያሥራል ውርንጫውንም በወይን አረገ" አለ። ዘካርያስም "ጽዮን ልጅ አትፍሪ እነሆ ንጉሥሽ በአህያ ግልገል ተቀምጦ ይመጣ" አለ።
❤ ኢሳይያስ "ንጉሥሽ ጻድቅ የዋህ የሆነ ይመጣል ዋጋውም ከእርሱ ጋራ ነው ሥራውም በፊቱ የተገለጠ ነው በአህያ ግልገልም ላይ ይቀመጣል" አለ።
❤ አብርሃምም የሰሌን ዝንጣፊ ይዞ መሠውያውን በዞረ ጊዜ "ይችን ዕለት ተድላ ደስታ የሚደረግባት የእግዚአብሔር በዓል" ብሎ ጠራት።
❤ ዳዊትም "ከሕፃናትና ከልጆች አንደበት ምስጋናን አዘጋጀህ" አለ። ሰሎሞንም "የሕፃናት አንደበታቸው የተቃናች ሆነች" አለ። ሁለተኛም "ልጆችና ሽማግሌዎች በኢየሩሳሌም ይጫወታሉ ምርጒዛቸውም መትከያዎችሽን አስፍተሽ ድንኳኖችሽን ዘርጊ" ያለም አለ።
❤ ይህንንም የትንቢት ነገር ለመፈጸም በከረ ወንጌል እንተጻፈ ጌታ በአህያዋና በውርንጭላዋ ላይ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ገባ። ወደ ኢየሩሳሌም ሊገባ በቀረበ ጊዜ የደብረ ዘይት አጠገብ ከምትሆን ቤተ ፋጌ ደረሰ ደብረ ዘይት ወደሚባል ቢታንያም በደረሰ ጊዜ ከደቀ መዛመቱን ሁለቱን ላከ። "ወደ ፊታችሁ ወዳለ አገር ሒዱ በገባችሁም ጊዜ ሰው ያልተቀመጠበት አህያ ግልገል ታገኛላችሁ ፈትታችሁ አምጡልኝ። ለምን ትፈቱታላችሁ የሚል ሰው ቢኖር ጌታው ይሻዋል" በሉ። የተላኩትም በሔዱ ጊዜ እንደነገራቸው አገኙ። የአህያውም ግልገል ፈቱ ጌቶቹም "ለምን ትፈቱታላችሁ" አሏቸው። "ጌታው ይሻዋል" አሉ። ወደ ጌታ ኢየሱስም ይዘውት ሔዱ ልብሳቸውንም በአህያው ግልገል ላይ ጐዘጐዙ ጌታችንም አስቀመጡት። ቅጠል ቆርጠው በመንገድ ላይ የጐዘጐዙ ብዙዎች ናቸው። ልብሳቸውንም በመንገድ ላይ ያነጠፋ አሉ። በፊትም በኋላ ይሔዱ የነበሩት "በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ የተባረከ መድኃኒት ነው" ብለው አሰምተው ተናገሩ። "በእግዚአብሔር ስም የምትመጣ የአባታችን ዳዊት መንግሥትም የተባረከች ናት"።
❤ ጌታ ኢየሱስም ወደ ኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ ገባ ሕዝቡም ሁሉ አዩት በመሸም ጊዜ ከዐሥራ ሁለቱ ደቀመዛሙርት ጋር ወደ ቢታንያ ወጣ። በነጋውም ከቢታንያ በወጣ ጊዜ ተራበ። በሩቅም ቅጠል ያላትን በለስ አየ። በርሷ ፍሬ ያገኝ እንደሆነ ሊያይ ሔደ ወደርሷም በደረሰ ጊዜ ከቅጠል ብቻ በቀር ያገኘው የለም የበለስ ወራት አልነበረምና "ዘላለም ካንቺ ፍሬ የሚበላ አይኑር" አላት። ደቀ መዛሙርቱም ሰሙ።
❤ ወደ ኢየሩሳሌም ደርሶ ወደ ቤተ መቅደስ ገባ በምኵራቡም ግቢ የሚገበያዩትን ያስወጣ ጀመረ የለዋጮችንም ሰደቃቸውን ገለበጠ ርግብ የሚሸጡትንም ወንበራቸውን። ወደ ምኵራብ ለንግድ ገንዘብ ይዘው እንዳይገቡ ከለከለ።
"ቤተ ለአሕዛብ ሁሉ የጸሎት ቤት ይሁን የሚል ጽሐፍ ያለ አይደለምን እናንተ ግን የሌቦችና የወንበዴዎች ዋሻ አደራጋችሁት" ብሎ አስተማራቸው።
❤ ቅዱስ ዮሐንስም እንዲህ አለ "አልዓዛርን ከሙታን ለይቶ ካስነሣው በኋላ። በነጋውም እሑድ ለበዓል የመጡ ሰዎች ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ኢየሩሳሌም እንዲመጣ በሰሙ ጊዜ። የሰሌን ዛፍ ዝንጣፊ ይዘው ከኢየሩሳሌም ፈጥነው ወጡ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ከአርያም የተገኘ መድኃኒት የእስራኤል ንጉሥ የተባረከ ነው" እያሉ እየጮኹ ተቀበሉት።
❤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የአህያ ግልገል አገኘ። ተቀመጠበትም እንደ ተጻፈ እንዲ ሲል። "የጽዮን ልጅ አትፍሪ እንሆ ንጉሥሽ በአህያ ግልገል ተቀምጦ ይመጣል"። አስቀድሞ ግን ደቀ መዛሙርቱ ይህን ነገር አላወቁም ነበር ጌታ ሳይሰቀል። ጌታ በተሰቀለ ጊዜ ይህ የተጻፈ ስለ እርሱ እንደሆነ ያን ጊዜ አወቁት እንጂ እንዲህም አደረጉለት።
❤ አልዓዛር አልዓዛር ብሎ ከሙታን ለይቶ እንዳስነሣው ባስነሣው ጊዜ ከእርሱ ጋር የነበሩ ሰዎች መሰከሩለት። ስለዚህም ሕዝቡ አመኑበት። ያደረገውን ተአምራት ሰምተወልና የሕፃናቱንም ምስጋና ደግሞ አልዓዛርን ማስነሣቱን። የካህናቱ አለቆችና ፈሪሳውያን ግን እርስ በርሳቸው "የምታገኙት ረብሕ ጥቅም እንደሌለ አታውቁምን እንሆ ሰው ሁሉ አመነበት" አሉ።
❤ ቅዱሳን ማቴዎስና ማርቆስ የሰሌንን ነገር አላወሱም ሌሎች ከእንጨቶች ቅጠሎችን እየቆረጡ በመንገድ ውስጥ ጐዘጐዙ አሉ እንጂ።
❤ ቅዱስ ሉቃስም ቅጠልን ወይም ሰሌንን አላወሳም ሲሒዱ ልብሳቸውን በመንገድ ላይ ይጐዘጒዙ ነበር አለ እንጂ።
❤ ቅዱስ ዮሐንስ ግን ለብቻው "ከኢየሩሳሌም ከሰሌን ዛፍ ላይ ዘንባባ ቆርጠው ያዙ" አለ። ሰሌንም በኢየሩሳሌም አልነበረም ጌታችን ሕፃን ሁኖ ሳለ ወደ ግብጽ በወረደ ጊዜ ከእናቱ ቡርክት ቅድስት ከሆነች ከእመቤታችን ድንግል ማርያም ጋር እስሙናይን ከሚባል አገር ደረሱ ከዚያም ሰሌን አገኙ። ጌታችንም ከሥርዋ ተነቅላ ሒዳ በደብረ ዘይት ላይ እንድትተከል አዘዛት ያንጊዜ ወደ አየር ወጥታ በረረች ሒዳም በዚያ በደብረ ዘይት ተተከለች ከእርስዋም ወስደው የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ተቀበሉት።
❤ ጌታችንም የሆሣዕናን ዑደት በአሳየ ጊዜ የአይሁድ ወገን ቅናት ይዟቸው በሚገድሉት ገንዘብ ምክንያት ፈለጉ። ለእርሱም ምስጋና ይሁን በእኛ ላይም ይቅርታው ቸርነቱ ይደረግልን ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ቄርሎስ፦ ይህም አባት የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት በመማር ያደገና እጅግም አዋቂ ምሁር ነበር። ከእርሱ በፊት የነበረ ኤጲስቆጶስ አባ በኪኪሶስ በዐረፈ ጊዜ ይህን አባት መርጠው ለኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ አድርገው ሾሙት። በተሾመም ጊዜ ከመነናውያንና ከአርዮሳውያን ተኲላዎች በመልካም አጠባበቅ ሕዝቡን ጠበቀ።
❤ የኤጲስቆጶሳት ጉባኤ በሰርድቄ በተሰበሰበ ጊዜ ይህ አባት ከዚያ ደርሶ አርዮሳውያንን ተከራክራቸው ምላሽ አሳጥቶም አውግዞ አሳደዳቸው አካክዮስንም ከቂሣርያ አገር ስብከቱ መንበር አሳደደው። አካክዮስም ወደ ታናሹ አርዮስዊ ወደ ሆነው ቆስጠንጢኖስ ሒዶ ከማኅበሩ ስለ ደረሰበት ውግዘትና ስደት ይልቁንም ከዚህ አባት ቄርሎስ የደረሰበትን ሁሉ በመናገር ከሰሰው። ስለዚህም አርዮሳዊ ንጉሥ ይህን አባት ከኢየሩሳሌም አሳደደው ሌሎችንም ብዙዎች ኤጲስቆጶሳትን ከአገረ ስብከቱ መንበራቸው አሳደዳቸው።
❤ ይህም አባት ቄርሎስ ወደ ተርሴስ ከተማ ሒዶ ከአገሩ ኤጲስቆጶስ ከስልዋኖስ ጋራ ተገናኘ። እርሱም ተራዳው ጥቂት ቀኖችም ከእርሱ ዘንድ አስቀመጠ። በሉክያኖስ ስብሰባ በሆነ ጊዜም ይህ አባት ከተሰበሰቡት ውስጥ አንዱ እርሱ ነው አካክዮስም ደግመው አወገዙት ረገሙትም ዳግመኛ ወደ ንጉሥ ሒዶ በዚህ በቅዱስ ቄርሎስ ነገር ሰራበት ንጉሡም ወታደሮች ልኮ ከዚያም ካለበት አሳደደው።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #መጋቢት ፳፩ (21) ቀን።
❤ እንኳን #የክብር_ባለቤት_ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ ከሙታን ለይቶ ወደ አስነሣው ወደ አልዓዛር ቤት ከደቀ መዛሙርቱ ጋራ ለሔደበት፣ አምላክ ለወለደች #ለእመቤታች_ለቅድስት_ድንግል_ማርያም ለወራዊ በዓሏ መታሰቢያና ለማቱሳላ ልጅ #ለቅዱስ_ላሜህ ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓሉ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡት፦ ለከበሩ ሰማዕታት #ከቅዱሳን_ቴዎድሮስና_ከጢሞቴዎስ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ በዚችም ዕለት የክብር ባለቤት #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ ከሙታን ለይቶ ወደ አስነሣው ወደ አልዓዛር ቤት ከቀደ መዛሙርቱ ጋራ ሔደ በዚያም ምሳ አዘጋጁለት ማርታም ምግብ በማቅረብ ታገለግላቸው ነበር። ሁለተኛዋ ማርያም ግን እግሮቹን ሽቱ እየቀባች በጸጒሩዋ ታሸው ነበር።
❤ ጌታችንም አመሰገናት "እርሷ ለመቀበሪያዬ ጠብቃዋለች" በማለት ስለ ቅርብ ሞቱ አመለከተ። ዳግመኛም "ድኆች ሁል ጊዜ ከእንተ ጋራ ይኖራሉ እኔ ግን ከእናንተ ጋራ አልኖርም" አለ በዚህም ተሰቅሎ የሚሞትበት ጊዜ ቅርብ መሆን ያመለክታል ለርሱም ክብር ከሃሊነት ገንዘቡ ስለሆነ ምስጋና ይገባዋል ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ በዚችም ቀን አልዓዛርን ሊገሉት የካህናት አለቆች ተማከሩ ገናና ስለሆነች ምልክት በእርሱ ምክንያት ብዙዎች በጌታችን የሚያምኑ ሁነዋልና። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #የማቱሳላ_ልጅ_ቅዱስ_ላሜህ፦ እርሱም አንድ መቶ ሰማንያ ሁለት ዓመት ኑሮ ኖኅን ወለደው ከወለደውም በኋላ አምስት መቶ ስልሳ አምስት ዓመት ኖረ። በድምሩ ሰባት መቶ አርባ ሰባት ዓመት ኖረ። እግዚአብሔርንም አገልግሎት በሰላም ዐረፈ። የማቱሳላ ልጅ የቅዱስ ላሜህ የፈጣሪው በረከት ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ይኑር አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት 21 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ሚጥ ገጸከ እምኃጢአትየ። ወደምስስ ሊተ ኵሎ አበሳየ። ልበ ንጹሕ ፍጥር ሊተ እግዚኦ"። መዝ 50፥9-10። የማሚነበበው ወንጌል ዮሐ 12፥1-12።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወትቀውም ንግሥት በየማንከ። በአልባሰ ወርቅ ዑጽፍት ወኊብርት። ስምዒ ወለትየ ወርእዪ ወአጽምዒ ዕዝነኪ"። መዝ 44፥9-10። የሚነበቡት ወንጌል ኤፌ 2፥13-ፍ.ም፣ 2ኛ ዮሐ 1፥1-8 እና የሐዋ ሥራ 7፥40-51። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ1፥20-39። የሚቀደሰው ቅዳሴ ቅዳሴ እግዚእነ ወይም የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የጾም ጊዜና በዓል። በሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #መጋቢት ፳፩ (21) ቀን።
❤ እንኳን ለታላቁ አባት የአባታችን #የአቡነ_የተክለ_ሃይማኖት ገዳም "ደብረ ሊባኖስ" በስማቸው ለተሰየመላቸው፤ ከዐለት ላይ ውኃ እያፈለቁ ድውያንን ለሚፈውሱት ለታምረኛው አባት፤ #ለአባ_ሊባኖስ (ዘመጣዕ) ዓለምን ፍጹም በመናቅ ለመነኑበት ነው ለመታሰቢያ ቀን እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ሊባኖስ_ዘመጣዕ፦ እርሳቸውም የአባታችን የተክለ ሃይማኖት ገዳም "ደብረ ሊባኖስ" በስማቸው የተሰየመላቸው ናቸው፡፡ አባ ሊባኖስ አባታቸው አብርሃም እናታቸው ንግሥት ይባላሉ፡፡ እነርሱም በወርቅና በብር እጅግ የበለጸጉ ሮማዊ ናቸው፡፡ ልጃቸውን አባ ሊባኖስን በሃይማኖት በምግባር ኮትኩተው ካሳደጓቸው በኋላ ዕድሜያቸው ሲደርስ በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ያጋቧቸው ዘንድ ከቁስጥንጥንያ አገር ሚስት ባመጡለት ጊዜ እርሱ ግን ፈጽሞ እምቢ አለ፡፡ ወደጫጉላቤትም መግባትን እምቢ አለ፡፡ በዚህም ጊዜ ነቢዩ ሳሙኤልን እንደጠራው አባታችንንም እግዚአብሔር ሦስት ጊዜ በስማቸው ጠራቸውና "ከአባትህ ተለይ አንተ የመንግሥተ ሰማያት ሙሽራ ነህ እንጂ የዚህ ምድራዊ ዓለም ሙሽራ አይደለህም" አላቸው፡፡ አባታችንም "ወዴት እሄዳለሁ? ምንስ ላድርግ?" ባሉ ጊዜ ወዲያው የታዘዘ መልአክ በሌሊት መጥቶ ከአባታቸው ቤት አውጥቶ ታላቁ አባት አባ ጳኩሚስ ዘንድ አደረሳቸው፡፡ ታላቁ አባት አባ ጳኩሚስም ለአባ ሊባኖስ በዓት በመስጠት ገዳመ ሥርዓትን፣ አስኬማ መላእክትን፣ ቅናተ ዮሐንስን አስተምረዋቸው አመነኰሷቸውና ከ8ቱ ቅዱሳን ጋር እንዲገናኙ አደረጓቸው፡፡
❤ ከዚህም በኋላ ያ ከአባታቸው ቤት ወስዶ አባ ጳኩሚስ ገዳም ያደረሳቸው ያ መልአክ ድጋሚ ተገለጠላቸውና "ወደ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ ሂድና ተጋድለህን በዚያ ፈጽም ዝናህ በስፋት ይነገራል፣ ለብዙዎችም አባት ትሆናቸዋለህ" አላቸው፡፡ ቀጥሎም ራሱ መልአኩ ወደ ኢትዮጵያ አመጣቸውና በአክሱም ተቀመጡ፡፡ በዚያም ብዙ ከተጋደሉ በኋላ ወደ ሸዋ መጡና ወንጌልን ዞረው አስተምረው ብዙ ድውያንን ፈውሰው ከዓመታት ቆይታ በኋላ ተመልሰው አክሱም ሄዱ፡፡ በአክሱምም 7 የተለያዩ ጸበሎችን ከድንጋይ ላይ በተአምራት አፍልቀው ድውያንን ፈውሰው ዕውራንን አበሩ፡፡ በዓታቸውንም ከአክሱም ጽዮን ፊት ለፊት አድርገው ሲኖሩ ከዕለታት በአንደኛው ቀን አባታችን በተአምራት ከጭንጫ ካፈለቁት ጸበል "ተራ ውሃ ነው" ብላ አንዲት ሴት ልጇን አዝላ ልትቀዳ መጣች፡፡ ወዲውም ከቦታው ስትደርስ አድጧት ወደቀችና ልጇም አምልጥጧት ልቡን ድንጋይ መቶት ሞተ፡፡ ሴትዮዋም ስትጮህ አባ ሊባኖስ ፈጥነው ወጡና በልጁ ላይ ጸልየው በመስቀል ምልክት አማትበው ከሞት አስነሥተውታል፡፡ ሕፃኑ ልጅ ከሞት እንደተነሣ "አምላከ አባ ሊባኖስ" ብሎ አመሰገነ፡፡
❤ ይህንንም ደግ ሥራቸውንና ተአምራታቸውን ያዩ አንዳንድ እኩይ ካህናት በቅናት ተመልተው "ምትሃት ነው የሚያሳየው" ብለው በጻድቁ ላይ ሕዝቡን አሳደሙባቸው፡፡ አባታችንም ካህናቱን ለመምከር ቢሞክሩም አላስቀምጥ አሏቸው፡፡ ይልቁንም ጦር ጦራቸውን ይዘው አሳደዷቸው፡፡ አባታችንም በዚህ እጅግ አዝነው ከአክሱም ተነሥተው ደርቃ ወደምትባል ቦታ ሄዱ፡፡ በዚያም በጾም በጸሎት እየተጋደሉ ሲኖሩ በእነዚያ በጠሏቸውና በክፋት በተነሡባቸው ካህናት አገር ግን ለ3 ዓመት ምንም ዝናብ ሳይዘንብ ቀረ፡፡ አባታችን በተሰደዱባት በደርቃ አገር ግን ብዙ ዝናብ ይዘንብ ነበር፡፡ አባታችን በዚያችም አገር እንደልማዳቸው ከዐለት ላይ ውኃ አፍልቀው በውኃው ብዙ ድውያንን ፈውሰውበታል፡፡ በዚያም ትልቅ በዓት መሥርተው በተጋድሎ ሲኖሩ በክፉ የተነሡባቸው እኩይ የሆኑ ካህናት መጥተው "አባታችን በከንቱ አምተንሃል በድለንሃልና ይቅር በለን፣ በድርቅ ማለቃችን ነውና ዝናብም እንዲዘንብልን ጸልይን" ብለው ከእግራቸው ሥር ወደቁ፡፡ አባታችንም ይቅር ብለው ከፈጣሪ አማለዷቸው፡፡ ዝናቡም ወዲያው ዘነበላቸውና በአገሪቱ ጥጋብ ሆነ፡፡
❤ ከዚህም በኋላ አባታችን አስቀድመው ወዳዩአት ወደ ሸዋ ምድር ግራርያ መጡና በዓታቸውን በአሰቦት ጫካ አደረጉ፡፡ ነገር ግን መልአኩ ተገልጦላቸው "ሊባኖስ ሆይ! ከዚህ ቦታ የአንተ መኖሪያ አይደለም፣ በዚህ ቦታ ላይ እግዚአብሔርንና ሰውን የሚያገናኝ የሚያስታርቅ ታላቅ ጻድቅ ይወጣበታልና ይህ ቦታ የእርሱ ርስት ነው፣ የብዙ መነኰሳትም መንደር ይሆናል ነገር ግን የቦታው ስም በአንተ ስም ይጠራልሃል" አላቸው፡፡ በኋላ አባታችን ተክለ ሃይማኖት ተወልደው በዓታቸውን በዚያ ቦታ ላይ ሲያጸኑ ቦታው ግን "ደብረ ሊባኖስ" ተብሎ በመጀመሪያው አባት ስም ተሰየመ፡፡ መልአኩም በሌሊት እየመራ ወደ አክሱም ወሰዳቸው፡፡ ከዚያም "ታሪክ ወደምትሠራበት ዕጣ ክፍልህ ወደሆነው ቦታ አደርስሃለሁ" አላቸውና ወደ ኤርትራ አካለ ጉዛይ አውራጃ ልዩ ስሙ መጣዕ ወደተባለው ቦታ ወሰዳቸው፡፡ በዚያም አባታችን ድውያንን እየፈወሱ፣ ለምፃሞችን እያዳኑ፣ ሙታንን እያስነሡ ብዙ ተአምራትን እያደረጉ ወንጌልን እየሰበኩ "ሊባኖስ ዘመጣዕ" የሚባለውን ትልቁን ገዳማቸውን መሠረቱ፡፡ በወቅቱ የነበረው ዐፄ ገብረ መስቀልም የመጀመሪያውን ቤተ ክርስቲያን አሠራላቸው፡፡
❤ ቅዱስ ላሊበላ 23 ዓመት ሙሉ ካነጻቸው እጅግ ድንቅ 11 ቤተ መቅደሶች ውስጥ አንደኛውን በአባ ሊባኖስ ስም ሰይሞላቸዋል፡፡ ዐፄ ገብረ መስቀል ያሠራላቸው ሌላኛው ገዳማቸው ትግራይ ተንቤን ውስጥ ይገኛል፡፡ እጅግ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን በማድረግ የሚታወቁት አባታችን እንደ ተስዓቱ ቅዱሳን ከሮም በመምጣት በሀገራችን ላይ ብርሃንን አብርተዋል፡፡ ምንጭ፦ ከገድላት አንደበት።
❤️ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤️
❤️ እንኳን #ለዐቢይ_ጾም_ሰባተኛ_ሳምንት_ለቅዱስ_ኒቆዲሞስ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰ።
✝️ ✝️ ✝️
❤️ #የዚህ_ሳምንት_የኒቆዲሞስ_መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ በ፭ "ሖረ ኀቤሁ #ዘስሙ_ኒቆዲሞስ ወይቤሎ #ለኢየሱስ_ረቢ_ንህነ_ነአምን ብከ ከመ እምኀበ #አብ_መጻእከ መራሔ ሕይወትነ ወሠራየ ኀጢአትነ ከመ #እምኀበ_አብ_መጻእከ ከመ ትኩን መምህረ ዕጓለ አንበሳ ሰከብከ ወኖምከ አንሥአኒ በትንሣኤከ። ትርጉም፦ አስቀድሞ ሌሊት ወደ እርሱ ይሄድ የነበረ #ስሙ_ኒቆዲሞስ የሚባል መምህር ሆይ #ከአብ_አካል_ዘእምአካል ባሕርይ ዘእምባሕርይ ተወልደህ ወደዚህ ዓለም እንደ መጣህ ፈጽሞ እናምንብሃለን፤ የሕይወታችን መሪ ኀጢአታችንን ይቅር የምትል ነህ አለው"። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በጾመ_ድጓው_ላይ።
✝️ ✝️ ✝️
❤️ #ቅዱስ_ኒቆዲሞስ፦ ከፈሪሳውያን ወገን የአይሁድ አለቃ የነበረው ሰው ነው፡፡ የአይሁድ አለቆች አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስን "ምልክት አሳየን" እያሉ ይፈታተኑት ነበር፡፡ ጌታችን ስለ ሞቱና ትንሣኤው በምሳሌ እያስረዳ ቢያስተምራቸውም እነርሱ ግን አልገባቸውም ነበር፡፡ ከዚህም አልፎ ጌታችን በተአምራቱ የታመሙትን ሲፈውስ "ሕጋችን ተሻረ" ይሉ ነበር፡፡ በዚህ ዅሉ ተአምራትና ትምህርት የአይሁድ አለቆች ክርስቶስን ለመክሰስ በሚፈልጉበት ወቅት ከአይሁድ አለቆች አንዱ ኒቆዲሞስ በቀን እንዳያደርገው አይሁድን ቢፈራ፣ አንድም ጊዜ ባያደርሰው እንደ ባልንጀሮቹ ክርስቶስን ሳይቃወም በሌሊት ወደ ጌታችን ዘንድ እየሔደ ወንጌልን ይማር ነበር፡፡
❤️ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በነፍስ የታመሙትን በቃሉ፣ በሥጋ የታመሙትን በተአምራቱ ሲፈውስ ኒቆዲሞስ ሰምቶ፣ ተመልክቶ በመምህርነቱ ሳይኮራ አለቅነቱን መመኪያ ሳያደርግ በልቦናው የተሳለውን እውነትን የመፈለግ ስሜት አንግቦ ከጌታው፣ ከመምህሩ ከክርስቶስ ዘንድ በሌሊት ይገሰግስ ነበር (ዮሐ. ፫፥፩)፡፡ ምስክርነቱንም እንዲህ ሲል መስጠት ጀመረ፤ "መምህር ልታስተምር ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደ መጣህ እናውቃለን፡፡ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ከኾነ በቀር አንተ የምታደርገውን ተአምራት ሊያደርግ የሚችል የለምና" (ዮሐ. ፱፥፳፬፤ ሐዋ. ፲፥፴፰)፡፡
❤️ ይህን ምስክርነቱን በሚሰጥበት ጊዜም ጎዶሎን የሚሞላ፤ አላዋቂነት በአዋቂነት የሚለውጥ፤ ከምድራዊ ዕውቀት ወደ ሰማያዊው ምሥጢር የሚያሸጋግር አምላክ "ዳግመኛ ያልተወለደ የእግዚአብሔርን መንግሥት ለማየት አይችልም"። በማለት የአይሁድ መምህር ለኾነው ኒቆዲሞስ ቢያስተምረው ምሥጢሩ አልተገለጠለትም ነበርና "ሰው ከሸመገለ በኋላ ዳግመኛ መወለድ እንደምን ይቻላል? ዳግመኛ ይወለድ ዘንድወደ እናቱ ማኅፀን ተመልሶ መግባት ይችላልን?" በማለት ጥያቄ አቅርቧል (ዮሐ. ፫፥፮፤ ፩ኛጴጥ. ፩፥፳፫)፡፡ "እውነትእውነት እልሃለሁ፤ ዳግመኛ ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ ያልተወለደ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም፡፡ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፡፡ ከመንፈስም የተወለደ መንፈስነውና"። (ኤፌ. ፭፥፳፮) በማለት አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለኒቆዲሞስ ቢያስረዳውም ምሥጢሩ ከአቅሙ በላይ ስለ ኾነበት እንደምን ይቻላል? በማለት ጠይቋል፡፡
❤️ አበ ብዙኃን አብርሃም ከአምላኩ ሞገስን አግኝቶ የሰዶምና ገሞራ ጥፋት እንዳይደርስ ለመማለድ ከእግዚአብሔር ጋር ሲነጋገር እንደ ነበረ፤ ኒቆዲሞስም አላዋቂነቱን አምኖ ያልገባውን ምሥጢር ከአምላኩ በጠየቀ ጊዜ ኢየሱስ ክርስቶስም፡- "አንተ የእስራኤል መምህራቸው ኾነህ ሳለ ይህን ነገር አታውቅምን? በምድር ያለውን ስንነግራችሁ ካላመናችሁ በሰማይ ያለውን ብንነግራችሁ እንደምንታምናላችሁ? ከሰማይ ከወረደው ከሰው ልጅ በቀር ወደ ሰማይየወጣ የለም … ሙሴ በምድረ በዳ እባቡን እንደ ሰቀለ የሰውልጅ እንዲሁ ይሰቀላል፡፡ ያመነበት ዅሉ ለዘለዓለም ሕያው ኾኖ እንዲኖር እንጂ እንዲጠፋ አይደለም ..." እያለ ሰው በመብል ምክንያት የአምላኩን ትእዛዝ አፍርሶ ከእግዚአብሔር ቢለይም የሰው ልጅ ያጣውን ልጅነት ለመመለስ፣ ስመ ክርስትናን፣ ሀብተ ወልድን ለመስጠት ጌታችን መምጣቱን አስረዳው (ዮሐ. ፫፥፲፬)፡፡ ይህን የክርስቶስን የማዳን ሥራና በሥጋ መገለጥም "ሐወጽከኒ ሌሊተ ወፈተንኮ ለልብየ አመከርከኒ ወኢተረክበ ዐመፃ በላዕሌየ ከመ ኢይንብብ አፉየ ግብረ እጓለ እመሕያው፤ ልቤን ፈተንኸው፡፡ በሌሊትም ጐበኘኸኝ፤ ፈተንከኝም፡፡ ምንም አላገኘህብኝም፡፡ የሰውን ሥራ አፌ እንዳይናገር ፈቃዴ ነው" (መዝ. ፲፮፥፫) በማለት ቅዱስ ዳዊት ከኒቆዲሞስ ሕይወት ጋር በማዛመድ አመሥጥሮታል፡፡
❤️ በሌሊት ከአምላኩ ተምሮ ምሥጢሩ የተገለጸለት ኒቆዲሞስ ቀድሞ በአደባባይ ሔዶ መማርን ይፈራ እንዳልነበረ ምሥጢሩ ሲገለጽለት ግን አይሁድ ጌታችንን በሰቀሉት ዕለት ፍርኃት ርቆለት ከአርማትያሱ ዮሴፍ ጋር ቅዱስ ሥጋውን ገንዞ ለመቅበር በቃ፡፡ "ወአልቦ ፍርኃት ውስተ ተፋቅሮትነ፤ ፍጹም ፍቅር ፍርኃትን አውጥቶ ይጥላል" ተብሎ እንደ ተጻፈ (ማቴ. ፳፯፥፶፰፤ ፩ኛዮሐ. ፬፥፲፰)፡፡
✝️ ✝️ ✝️
❤️ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ሐወጽከኒ ሌሊተ ወፈተንኮ ለልብየ። አመከርከኒ ወኢትረክበ ዐመፃ በላዕሌየ። ከመ ኢይንብብ አፉየ ግብረ እጓለ እመሕያው። መዝ16፥3-4። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 7፥1-14፣ 1ኛ ዮሐ 4፥18-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 5፥34-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 3፥1-12። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም ዕለተ ሰንበት (የቅዱስ ኒቆዲሞስ)ና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
❤️ ከዚህ በኋላ አንድ ጸሐፊ ምዕመን ዮሐንስ የሚባል መጥቶ ለዚህ ለከበረ አባት አባ ሚካኤል ዋስ ሆነው ለመኰንኑም አባ ሚካኤል ሃያ ሺህ የወርቅ ዲናር እንዲሰጠው ሆኖ ከወህኒ ወቶ ወደ ቤቱ ሄደ ጥቂት ቀንም ተቀመጠ። ታላላቆች ምዕመናንና የአስቄጥስ ገዳም መነኰሳት ዐሥር ሺህ የወርቅ ዲናር ሰበሰቡ ደግሞ የእስክንድርያ አገር ሰዎች ከምድራቸው አንዱን ለዐሥራ ሺህ ዲናር ሸጡ ሃያ ሺህ እስኪሞላ ሰበሰቡ።❤️ ሊቀ ጳጳሳቱም ለመኰንኑ ይህንን ሃያ ሺህ የወርቅ ዲናር ሰጠው መኰንኑም ዐሥር ዐሥር ሺህ የወርቅ ዲናር እንደ ግብር ሆኖ በየዓመቱ እንዲከፈል ጽፊ አስፈረመው ጊዜውም ሲቀርብ ይህ አባት አባ ሚካኤል ከምዕመናን ሊሊምን ተነስቶ ወጣ በልበይስ ወደተባለም አገር ደርሶ አንድ ቀን ዋለ። ወደርሱም አንድ ምስኪን ድሃ መነኵስ ገባ ከሊቀ ጳጳሳቱም ቡራኬ ተቀቡሎ ተመልሶ በበር አጠገቡ ከረድኡ ጎን ቆሞ "አትዘን በልብህም አትተክዝ ከዛሬይቱ ዕለት እስከ አርባ ቀኖች ትድናለህ በላይህ ያለውን የእዳ ደብዳቤ ትቀበላለህና ለመኰንኑም ምንም አትስጠውም ብለህ ለአባት ሊቀ ጳጳሳት ንገረው" አለው። ያ ረድኡም እንዳለው ነገረው ደሃውንም መነኵስ ፈለጉት ግን አላገኙትም አርባ ቀኖችም ሳይፈጸሙ ያ መኰንን በክፉ አሟሟት ሞተ። በእርሱ ፋንታም ልጁ ተሾመ ለዚህም አባት ያንን የእዳ ደብዳቤ መለሰለት። ይህም አባት ድሃው መነኰስ ትንቢት እንደ ተናገረ ደብዳቤውን ተቀብሎ ቀደደው ከዕዳም ዳነ።
❤️ ይህም አባት በታላቅ መከራና በኀዘን በሹመቱ ዘመን ሃያ ዘጠኝ ዓመት ከኖረ በኋላ መጋቢት20 ቀን በፍቅር በሰላም ዐረፈ። በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት20 ስንክሳር።
✝️ ✝️ ✝️
❤️ "#ሰላም_ለሑረትከ_እግዚአብሔር_ኬንያ። እምኢየሩሳሌም ለቢታንያ። ከመ ታንሥእ በድኖ #ለአልዓዛር_እኅወ_ማርያ። ትሴፈወከ ነፍስየ ወትጸንከ ነያ። እሞተ ኃጢአት ታሕይዋ በዝንቱ አርአያ። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የመጋቢት_20።
❤️ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤️
❤️ #መጋቢት ፳ (20) ቀን።
❤️ እንኳን #ለክብር_ባለቤት_ለጌታችን_ለአምላካችን #ለመድኃኒታችን_ለኢየሱስ_ክርስቶስ የሚወደው ጻድቅ ሰው #ቅዱስ_አልዓዛርን ከሞተ በኋላ በአራተኛው ቀን ከሙታን ለይቶ አስነስቶት ነበርና ስለዚች ምልክት ገናናነት ብዙዎች በጌታችን ላመኑበት በዓል፣ ለተጋዳይም በተአምራቷ ከ5,685 በላይ ሰዎችን በጌታችን እንዲያም ላደረገ #ለቅድስት_አስጠራጦኒቃ ሰማዕትነት ለተቀበለችበት ለዕረፍቷ በዓልና ለእስክንድርያ ሃምሳ ሰባተኛ ሊቀ ጳጳሳት #ለአባ_ሚካኤል ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡት፦ ከተጋዳይዋ #ከቅድስት_ጽጌ_ሥላሴ ከመታሰቢያዋና #ከቅዱስ_አስቃራን ቤተ ክርስቲያኑ ከከበረችበት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝️ ✝️ ✝️
❤️ በዚች ዕለት የክብር ባለቤት #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ_ጻድቅ_ሰው_አልዓዛርን ከሞተ በኋላ በአራተኛው ቀን ከሙታን ለይቶ አስነስቶት ነበርና ስለዚህ ምልክት ገናናነት ብዙዎች አመኑበት። ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቸር አባቱና ሕይወት ከሆነ መንፈስ ቅዱስ ጋር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።
✝️ ✝️ ✝️
❤️ #ቅድስት_አስጠራጦኒቃ፦ የዚች ቅድስት አባቷ ጣዖት አምላኪ ነው እርሷ ግን በክብር ባለቤት በክርስቶስ የምታምን ናት ሥጋዋም እስቲከሣና እስቲደርቅ መልኳም እስቲለወጥ ድረስ በሥውር ትጾማለች ትጸልያለችም።
❤️ ዐሥራ አምስት ዓመት በሆናት ጊዜ እናትና አባቷ "ምነው ያከሣሻል?" አሏት፡፡ እርሷም "እኔስ ኃጢአቴን ይቅር ይለኝ ዘንድ የክብር ባለቤት ወደሆነ ወደ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ እጸልያለሁ" አለቻቸው፡፡ አባቷም በሰማ ጊዜ ወደ ጢባርዮስ ሒዶ የልጁን ሥራ ነገረው እርሱም ወታደሮች ልኮ ወደ ርሱ አመጣት። ለጣዖትም እንድትሰግድ መኰንኑ አባበላት እምቢ በአለችም ጊዜ ወደ ወህኒ ቤት አስገቧት እናቷም ክርስቲያናዊት ናት እየመጣች በክብር ባለቤት በክርስቶስ እምነት ታበረታታት ነበር።
❤️ ከዚህ በኋላ የብረት የሆነ የሰሌዳ ክርታስ ይሠሩላት ዘንድ በእሳትም አግለው ክንዶቿ ከወገቦቿ ጋራ አንድ እስቲሆኑ እንዲያጣብቋት አዘዘ። ይህንንም በአደረጉባት ጊዜ ያንን የብረት ክርታስ ሰብራ በድኅና ወጣች ሕዝቡም ይህን አይተው በክብር ባለቤት በክርስቶስ አራት ሺህ ሰባት መቶ ያህል አምነው በሰማዕትነት ሞቱ የሰማዕትነትንም አክሊል ተቀበሉ።
❤️ ሁለተኛም ደግመው ከእሥር ቤት አስገቧት ጥፍሮች ያሉት የብረት በሬ ሠሩላት ሆዷን ያስወጓት ዘንድ ሊሰቅሏትም ወርሷ አቀረቡት ይህንንም በአደረጉባት ጊዜ በጌታ ኃይል በሬው ወዲያና ወዲህ ተከፈለ ሕዝቡም ይህን በአዩ ጊዜ በክብር ባለቤት በጌታችን ዘጠኝ መቶ ሰማንያ አምስት ያህል ሰው አምነው በሰማዕትነት ዐረፋ።
❤️ ከዚህም በኋላ መርዝን ከተመሉ እባቦች ጒድጓድ ውስጥ ጨመሯት በጸየለች ጊዜ እንደ ትቢያ ሆኑ። ሁለተኛም አራት ሰዎች የሚሸከሙትን ከባድ ደንጊያ አምጥተው በአንገቷ ላይ ሰቀሉ በጸለየችም ጊዜ ደንጊያው ወደ ሦስት ተከፈለ። ብዙዎች አረማውያንም በክርስቶስ አምነው በሰማዕትነት ዐረፉ።
❤️ ለቅድስቲቱ ግን የብረት ምንቸት አዘጋጁላት በውስጡ የፈላ እርሳስ በላይዋ ያፈሱባት ዘንድ በነኩት ጊዜ በላያቸው ተሰብሮ የሚያሰቃዩአትን ገዳላቸው።
ንጉሡም አይቶ ተቆጣ ራሷንም በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ። ምስክርነቷን ከምትፈጽምበት ቦታም በደረሰች ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ጸለየች "አስጠራጦኒቃ ሆይ አንቺ ብፅዕት ነሽ ስምሽ በሕይወት መጽሐፍ ተጽፏልና" የሚል ቃል መጣላት ከዚያም በኋላ በሰይፍ አንገቷ ተቆረጠች። በቅድስት አስጠራጦኒቃ በጸሎቷ የሚገኝ በረከቷ ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ይኑር አሜን።
✝️ ✝️ ✝️
❤️ #አባ_ሚካኤል፦ ይህም አባት በእስክድርያ ከተሾሙ አባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሃምሳ ሰባተኛ የሆነ ነው። በሹመቱ ወራት ብዙ ኀዘንና መከራ ደረሰበት። ጎሕ በሚባል አገር የተሾመ የዚህን ኃላፊውን ዓለም ክብር የሚወድ አንድ ክፉ ኤጲስቆጶስ ነበር። በአገረ ስብከቱም ውስጥ ደነውስር በሚባል አገር ያሉ ምዕመናን የቤተ ክርስቲያናቸውን ሕንፃዋን አደሱ ሊያከብሩዋትም በፈለጉ ጊዜ የአገር ታላላቆች ከእርሳቸውም ሊባረኩ ወደው ሊቀ ጳጳሳት ልኮ እንዲያመጣቸውና ይህን ክፉ ኤጲስቆጶስ ለመኑት እርሱ ግን አምቢ አላቸው ልመናቸውን መቀበል አልወደደም እነርሱም በራሳቸው ፈቃድ ይህ ክፉ ኤጲስቆጶስ ሳይፈቅድ ሊቀ ጳጳሳቱንና ኤጲስቆጶሳቱን ሁሉ ልከው አስመጧቸው ሊቀ ጳጳሳት አባ ሚካኤልና ኤጲስቆጶሳቱ ሁሉ በመጡ ጊዜ ምሳ አዘጋጅላችኋለሁ ብሎ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ትቷቸው ሄደ "ማርታ ማርታ ብዙ በማዘጋጀት ብዙ ትደክሚያለሽ ግን ጥቂቱ ይበቃል" ያለውን የጌታችን ቃል አላሰበም በቁርባን ጊዜ ሊያልፍ ስለሆነ ሊቃውንቱና ኤጲስቆጶሳቱን የቅዳሴውን ሥርዓት ይጀምር ዘንድ ሊቀ ጳጳሳቱን ለመኑት ግድ ባሉት ጊዜ በሊቀ ጵጵስና ማዕረግና ክብር ተሰይሞ ተነሳ እርሱ ለሁሉ አባት የሆነ ስልጣኑም ከስልጣናቸው በላይ ነውና የቅዳሴውን ሥርዓት ጀመረ ያክፉ ኤጲስቆጶስም በሰማ ጊዜ በልቡ ሰይጣን አደረበትና ተቆጥቶ መጣ መስዋዕቱንም ከመቅደስ ገብቶ ከጻህሉ ውስጥ ነጥቆ መደ ምድር ወረወረው ሊቀ ጳጳሳቱም ሌላ መስዋዕት አምጡ ብሎ አዘዘ። አምጥተውለትም ቀድሶ ለሕዝቡ ሥጋውና ደሙን አቀበላቸውና አሰናበታቸው።
❤️ በማግስቱም ይህ አባት አባ ሚካኤል ሕዝቡ ሰበሰበ ከእርሱ ጋራ ያሉትንም ኤጲስቆጶሳት ካህናቱንና የምዕመናን አንድነት ሰብስቦ ይህን ክፉ ኤጲስቆጶስ ከሹመቱ ሽረው በእርሱ ፋንታ ሌላ ኤጲስቆጶስ ሾሙ። ይህም የአስቆሮቱ ሰው ለይሁዳ ሁለተኛው የሆነ የምስርን አገር ወደሚገዛ ስሙ አህመድ ወልደ በጥሎን ወደተባለው ሹም ሆደ ይህንን አባት አባ ሚካኤልን እንዲህ ሲል ነገር ሰራበት "በሊቀ ጳጳሳቱ ዘንድ ብዙ የወርቅና የብር ገንዘብ እንዳለ እንዲሁም አብያተክርስቲያናት የወርቅና የብር ነዋየ ቅድሳትን የተመሉ እንደሆኑ መኰንን ሆይ እወቅ" አለው። መኰንኑም ይህን አባት ወደ እርሱ አስቀርቧ ነዋየ ቅድሳቱን እንዲሰጠው ፈለገ እርሱም "ሥጋዬን እንደፈለገህ አድርግ ነፍሴ ግን በእግዚአብሔር እጅ ናት" ብሎ ከለከለው። እጆቹንና እግሮቹን አስረው በእስር ቤት እንዲጥሉት አዘዘ። በእስር ቤትም ከአንድ ዓመት በላይ ኖረ። በእስር ቤት ውስጥ በኖረበት ዘመን ከለምለም እንጀራና ከጨው ከበሰለ አተር በቀር ሳይባላ ሁል ጊዜ ይጾም ነበር።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #መጋቢት (፲፱) 19 ቀን።
❤ እንኳን #ከሰባ_ሁለቱ_አርድእት ለአንዱ ለሐዋርያው #ቅዱስ_ጳውሎስ ደቀ መዝሙር #ለቅዱስ_አርስጥቦሎስ ለዕረፍት በዓል፣ #ለቅዱስ_አሰከናፍርና_ለሚስቱ ማርታ፣ ለልጆቹ #አርቃድዮስና_ዮሐንስ ለዕረፍታቸው በዓልና #ለሰባቱ_ሰማዕታት ለዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱስ_አርስጥቦሎስ፦ እርሱም ጌታችን ከመረጣቸውና ከመከራው በፊት ወንጌልን እንዲሰብኩ ከላካቸው ከሰባ ሁለቱ አርድእት ውስጥ የተቈጠረ ነው።
❤ በሃምሳኛው ቀን በዓልም መንፈስ ቅዱስ በላዩ በወረደ ጊዜ ከሐዋርያት ጋራ ጸጋንና ኃይልን ተመልቶ ሕይወት በሚገኝበት በወንጌል ትምህርት ሐዋርያትን ተከትሎ በመሔድ አገለገላቸው። ብዙዎችንም ወደ ድኅነት መንገድ መልሶ የክብር ባለቤት ወደ ሆነ ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ሃይማኖት አስገባቸው የክርስትና ጥምቀትንም አጥቆ የአምላክን ሕግና ትዕዛዝ ከማስጠበቁ የተነሣ ነፍሳቸውን አዳነ።
❤ አባቶቻችን ሐዋርያትም ይህን ቅዱስ አብራጣብያስ በሚባል አገር ላይ ኤጲስቆጶስነት ሾሙት። ወደርሷም ሒዶ በውስጥዋ ወንጌልን ሰበከ ብዙዎቹንም በቀናች ሃይማኖት እግዚአብሔር ወደ ማወቅ መለሳቸው። በፊታቸው ድንቆች ተአምራትን በማድረግ በሃይማኖት አጸናቸው ነገር ግን ከአይሁድና ከዮናናውያን ብዙ መከራ ደረሰበት። ብዙ ጊዜም ወደ ፈራጆች አደባባይ ወስደው በደንጊያ ወገሩት ጌታችንም ከመከራው ሁሉ ጠብቆ አዳነው መልካም ተጋድሎውንም በፈጸመ ጊዜ መጋቢት19 በሰላም በፍቅር ዐረፈ።
❤ እነሆ ለሮሜ ሰዎች በጻፈው መልክቱ ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ አስታውሶታል። ከቅዱስ አርስጥቦሎስ በጸሎቱ የምትገኝ በረከት ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱሳን_አሰከናፍርና_ሚስቱ_ማርታ፣ ልጆቹ #አርቃድዮስና_ዮሐንስ፦ ይህም አስከናፍር ብዙ ገንዘብ ያለው ባለጠጋ ነው። ለእግዚአብሔር ሕግ የሚጠነቀቅ ነበር ልጆቹንም መንፈሳዊ ምክርና ተግሣጽ በማስተማር አሳደጋቸው። በአደጉም ጊዜ የጥበብንና የተግሣጽን ትምህርት እንዲማሩ ተይሩት ወደምትባል አገር ሰደዳቸውና ትምህርታቸውን በፈጸሙ ጊዜ ሊድራቸውና በሰርጋቸው ደስ ሊለው ሽቶ ያመጧቸው ዘንድ ላከ በመርከቡም ሁነው ሲመጡ ማዕከል ተነሥቶ መርከቡ ተሰበረ። እግዚአብሔርም ከሰጥመት አድኖ በየብስ አወጣቸው ዮሐንስ የተባለውን በአንድ ቦታ ማዕከል አውጥቶ ጣለው።
❤ ዮሐንስም ተስፋ በቆረጠ ጊዜ ወደ ቅዱሳን ገዳም ሒዶ መነኰሰ።ስለ ወንድሙ ስለ አርቃድዮስም እንተሞተ ተጠራጥሮ በጾም በጸሎትና በስግደትም ሥጋውን አደከመ። አርቃድዮስም ወደ ዮርዳኖስ ገዳም ገብቶ ከአንድ ቅዱስ አረጋዊ ሰው ዘንድ መንኵሶ እየተጋደለ ሦስት ዓመት ኖረ።
❤ አስከናፍር ግን ልጆች በማዕበል እንደ ሰጠሙ በሰማ ጊዜ ከሚስቱ ጋራ ማቅ ለብሰው አመድ አንጥፈው እያለቁሱ ተቀመጡ። በአንዲት ሌሊትም አስከናፍር በሕልሙ ልጁ ዮሐንስ በራሱ ላይ ከዕንቊ የተሠራ አክሊል ተቀዳጅቶ መስቀል ይዞ አየው። አርቃድዮስንም በኮከብ አምሳል የሆነ አክሊል በራሱ ላይ ደፍቶ አየ ከእንቅልፉም ነቅቶ ለሚስቱ ያየው ነገራት።
❤ ከዚህም በኋላ በየአድባራቱና በየገዳማቱ የልጆቻችንን ወሬ እንመርምር ዘንድ ተነሺ እንሒድ አላትና ወደ ዮርዳኖስ ሒደው ከመጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ ገዳም ደረሱ። ልጃቸውን አርቃድዮስን ያመነኰሰውን አረጋዊ አባትን አገኙት ችግራቸውን ነገሩት እርሱም "የክርስቶስ ወዳጆች አትዘኑ ወደ ቤተ መቅደስ ስትመለሱ ልጆቻችሁን በሕይወት ታገኛላችሁ" አላቸው ደስ እያላቸውም ተመለሱ።
❤ ዮሐንስም በመስቀል በዓል ሊሳለም መጣ አረጋዊውም ጠርቶ ከአርቃድዮስ ከወንድሙ አገናኘው ተያይዘውም አለቀሱ። ደግሞ አስከናፍርን ከሚስቱ ጋራ ጠርቶ ከልጆቻቸው ጋር አገናኛቸውና በላያቸው ወድቀው እየሳሟቸው አለቀሱ።
❤ ከዚህ በኋላ ከዚያ አረጋዊ ዘንድ የምንኵስና ልብስ ለበሱ ሚስቱን ማርታንም ከሴቶች ገዳም አስገባት አገልጋዮችንም ነፃ አውጥቶ አሰናበተ። ገንዘቡንም ለድኆችና ለችግረኆች በተነ ከገዳምም ገብቶ በጾም በጸሎት ተወሰነ እንዲሁም የተባረኩ ልጆቹ በገድል በትሩፋት የተጠመዱ ሁነው ኖሩ ጌታችንንም ደስ አሰኙት በፍቅር በአንድነት መጋቢት19 ዐረፉ። የቅዱሳን አሰከናፍርና የሚስቱ ማርታ፣ የልጆቹ አርቃድዮስና ዮሐንስ በረከታቸው ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ይኑር አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #ሰባቱ_ሰማዕታት፦ እነርሱም የግብጽ ሰው እለእስክንድሮስና እስክንድሮስ፣ ከጋዛ መንደር አጋብዮስ፣ ከቡንጥስ ከተማ ኒሞላስ ከጠራልብስ፣ ዲዮናስዮስ፣ ሮሜሎስና ተላስዮስ ከግብጽ አውራጃዎች የሆኑ ናቸው።
❤ እነርሱም በመንፈሳዊ ፍቅር ጸንተው ስለ ሃይማኖት ምስክሮች ሊሆኑ ተስማሙ። በፍልስጥዔም ውስጥ ወደ አለው ቂሣርያ ደርሰው በመኰንኑ ፊቱ ቆሙ። በከሀዲው ከዲዮቅልጥያኖስ ዘመን በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማመናቸውን ገለጡ መኰንኑም በጹኑ ሥቃይ አሠቃይቶ መጋቢት19 ገደላቸው። የሰማዕትነትንም አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀበሉ። በረከታቸው ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት 19 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለአርስጦቦሎስ_ዘተፈነወ_ለምሮ። ምስለ ሐዋርያት በጽዮን ውኂዘ መንፈስ ሰኪሮ። ጽሒፎ በእዱ እም አምኀ ማኅበሮ። እንዘ ያስተበፅዕ ወይዌድስ ግብሮ። በውስተ መልእክቱ ዘሮሜ ጳውሎስ ዘከሮ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የመጋቢት_19።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦"ወይርአዩ አሕዛብ በቅድመ አይንቲነ። በቀለ ደሞሙ ለአግብርቲከ ዘተክዕወ። ይባእ ቅድሜከ ገዓሮሙ ለሙቁሓን"። መዝ 78፥10-11። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 16፥3-17፣ 1ኛ ጴጥ 3፥7-15 እና የሐዋ ሥራ 22፥22-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 10፥1-21። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱሳን ሐዋርያት ቅዳሴ ነው። መልካም የጾም ጊዜና በዓል።ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ❤
❤ #መጋቢት፲፰ (18) ቀን።
❤ እንኳን #ለሰማዕት_ቅዱስ_ፃና ጓደኛው የበግ ጸጒር ልብሶችን በመስራት የሚያገኘው ገንዘብ ለድኆች ይመጸውት ለነበረው ለከበረ #ለቅዱስ_ኤስድሮስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱሳን_ፃናና_ኤስድሮስ፦ ፃና ግን ፈርማ በሚባል አገር ለአገረ ገዥው ከጦር ሠራዊቱ ውስጥ ወታደር ነበር እርሱም ከደቅስያ ሰዎች ወገን ነው ከበግ ጸጒር ልብሶችን ለሚሠራ ለኤስድሮስ ወዳጁ ነው። ሁለቱም ሠርተው ከሚያገኙት ለድኆችና ለችግረኞች ይመጸውታሉ።
❤ በአንዲት ሌሊትም ከእርሷ ጋር አክሊሎች ያሉ ድንግል ሴት በራሳቸው ላይ ስታኖረው ሁለቱም ራእይን አዩ። ከእንቅልፋቸውም በነቁ ጊዜ ያዩትን እንዴት እንዳዩ ተነጋገሩ። ምስክሮቹ ሊሆኑ የጠራቸው እግዚአብሔር እንደሆነ አውቀው እጅግ ደስ አላቸው።
❤ ከዚያም ተነሥተው ሒደው ወደ መኰንኑ ደረሱ ቅዱስ ፃናም ትጥቁን ፈትቶ በመኰንኑ ፊት ጣለው ሁለቱም በጌታችን በክብር ባለቤት ኢየሱስ ክርስቶስ ማመናቸውን ገለጡ። መኰንኑም ነገራቸውን ሰምቶ አሥረው ይደበድቧቸው ዘንድ አዘዘ እግዚአብሔር መልአኩን ልኮ አዳናቸው።
❤ ከዚህም በኋላ መኰንኑ ወደ እስክንድርያ ቅዱስ ፃናን ላከው ቅዱስ ኤስድሮስን ግን በዚያው ተወው ከጥቂት ቀኖችም በኋላ የእስክንድርያው መኰንን ቅዱስ ፃናን ወደ ፈርማ ከተማ መለሰው። ሁለቱ ቅዱሳንም ተገናኙ በመገናኘታቸው ደስ ብሏቸው በላያቸው በየአንዳንዳቸው የደረሰውን መከራ ተነጋገሩ።
❤ ዳግመኛም ለቅዱስ ኤስድሮስ ዐዘቅትን ይቆፍሩለት ዘንድ በዐዘቅቱም ውሰጥ እሳትን አንድደው ቅዱስ ኤስድሮስን እንጨምሩት መኰንኑ አዘዘ። ቅዱሱም ጥቂት እስቲጸልይ ይታገሡት ዘንድ ወታደሮቹን ለመናቸው ወደ ጌታችንም ነፍሱን ይቀበል ዘንድ ለሥጋውም ያስብ ዘንድ ጸለየ። ከዚያም ወደ እሳት ጒድጓድ ቀረበ ወደ እሳቱም ውስጥ ጨመሩት ነፍሱንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ በሥጋውም ላይ ምንም ጒዳት አልደረሰም መልኩም አልተለወጠም።
❤ የቅዱስ ፃና እናትም ከሚወደው ጓደኛው ስለመለየቱ ታላቅስለት ነበር። ከዚያም ሥጋውን ተሸክመው ወሰዱ የስደቱም ወራት እስቲፈጸው በመልካም ቦታ አኖሩት።
❤ ቅዱስ ኤስድሮስ ምስክር ሁኖ በሞተ ጊዜ የቅዱስ ፃና እናት ብዙ መላእክት የቅዱስ ኤስድሮስን ነፍስ ይዘው በታላቅ ክብር ወደ ሰማያት ሲያሳርጓት አየች። እግዚአብሔር ሁላችንን የክርስቲያን ወገኖችን በቅዱሳን ፃናና ኤስድሮስበጸሎቱ ይማረን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት18 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለኤስድሮስ_እምነ_ሤመ_ፀምር_ግብረ እዱ። ዘይሁብ ምጽዋተ ለእለ ፈቀዱ። ምንዳቤያተ ፈጺሞ ወኵነኔያተ ለለ፩ዱ። በዕለተ ውዕየ ለዐዘቅት እሳት በነዱ። መላእክት ነፍሶ በስብሐት ወሰዱ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የመጋቢት_18።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦"ብፁዓን እለ ንጹሐን በፍኖቶሙ።ወእለ የሐውሩ በሕገ እግዚአብሔር። ብፁዓን እለ የኃሡ ስምዖ"። መዝ 118፥1-2። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 16፥1-12፣ 1ኛ ጴጥ 2፥1-11። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 18፥18-23። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ ቅዳሴ ነው። መልካም የጾም ወራትና በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።
