ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ
Open in Telegram
ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።
Show more638
Subscribers
-224 hours
-57 days
-1130 days
Data loading in progress...
Similar Channels
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
July '26
July '26
+2
in 0 channels
June '26
+6
in 0 channels
Get PRO
May '26
+6
in 0 channels
Get PRO
April '26
+5
in 0 channels
Get PRO
March '26
+7
in 0 channels
Get PRO
February '26
+8
in 0 channels
Get PRO
January '26
+7
in 0 channels
Get PRO
December '25
+5
in 0 channels
Get PRO
November '25
+10
in 0 channels
Get PRO
October '25
+6
in 0 channels
Get PRO
September '25
+111
in 0 channels
Get PRO
August '25
+4
in 0 channels
Get PRO
July '25
+5
in 0 channels
Get PRO
June '25
+11
in 0 channels
Get PRO
May '25
+6
in 0 channels
Get PRO
April '25
+9
in 0 channels
Get PRO
March '25
+9
in 0 channels
Get PRO
February '25
+18
in 0 channels
Get PRO
January '25
+28
in 0 channels
Get PRO
December '24
+29
in 0 channels
Get PRO
November '24
+22
in 0 channels
Get PRO
October '24
+20
in 0 channels
Get PRO
September '24
+43
in 0 channels
Get PRO
August '24
+67
in 0 channels
Get PRO
July '24
+111
in 0 channels
Get PRO
June '24
+81
in 0 channels
Get PRO
May '24
+82
in 0 channels
Get PRO
April '24
+69
in 0 channels
Get PRO
March '24
+74
in 1 channels
Get PRO
February '24
+74
in 0 channels
Get PRO
January '24
+64
in 0 channels
Get PRO
December '23
+17
in 1 channels
Get PRO
November '23
+229
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 09 July | 0 | |||
| 08 July | 0 | |||
| 07 July | 0 | |||
| 06 July | +1 | |||
| 05 July | 0 | |||
| 04 July | 0 | |||
| 03 July | 0 | |||
| 02 July | 0 | |||
| 01 July | +1 |
Channel Posts
| 2 |
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "እነግሮሙ ስመከ ለአኃውየ። ወበማዕከለ ማኅበር እሴብሓከ። እለ ትፈርህዎ ለእግዚአብሔር ሰብሕዎ"። መዝ 21፥22-23። የሚነበቡት መልዕክታት ቲቶ 3፥18-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 3፥15-ፍ.ም የሐዋ ሥራ 20፥28-31። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 18፥15-21። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ቄርሎስ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ ቄርሎስ በዓልና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን። | 16 |
| 3 | ❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን" ❤
❤ #ሐምሌ ፫ (3) ቀን።
❤ እንኳን ለእስክድርያ ሃያ አራተኛ ሊቀ ጳጳስ ለዐምደ ሃይማኖት መናፍቁ ንስጥሮስ በጉባኤ ኤፌሶን ተከራክሮ ረቶ ላወገዘው ለታላቁ #ለአቡነ_ቄርሎስ_ለዕረፍት መታሰቢያ በዓልና ከእርሱ በፊት ለነበረው ሊቀ ጳጳሳት ዮናክንዲኖስ ደቀ መዝሙሩ ለነበረው ለሮሜ ሊቀ ጳሳት ለቅዱስ አባት #ለአባ_ክልስቲያኖስ ለዕረፍት መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ቄርሎስ፦ ይህም አባት ለእስክንድርያ (ለግብጽ) ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሃያ አራተኛ ነው። ይህም ቅዱስ የእናቱ ወንድም በሆነው በአባ ቴዎፍሎስ ዘንድ አደገ፤ ጥቂት ከፍ ባለ ጊዜም ወደ አስቄጥስ ወደ መቃርስ ገዳም ላከው በዚያም አምላካውያን የሆኑ መጻሕፍትን ተማረ እግዚአብሔርም መጽሐፍትን አንድ ጊዜ አንብቦ እስከሚአጸናው ድረስ ዕውቀትንና ማስተዋልን ሰጠው።
❤ ከዚህም በኋላ ደግሞ ያስተምረው ዘንድ ለአባ ሰራብዮን ሰጠው ከእርሱም ዘንድ ያለውን ትምህርትን በፈጸመ ጊዜ ወደ ሊቀ ጳጳሳት ቴዎፍሎስ መለሰው። እርሱም እጅግ ደስ ተሰኘበት እግዚአብሔርንም አመሰገነው።
❤ ከዚህም በኋላ ሁል ጊዜ መጻሕፍትን እንዲያነብና ሕዝቡን እንዲያስተምር ለሊቀ ጵጵስና ሥራ ውስጥ ሾመው። ከትምህርቱም ጣዕም የተነሣ ዝም ይል ዘንድ ማንም አይወድም ነበር።
❤ አባ ቴዎፍሎስ በዐረፈ በኋላ በእስክንድርያ ከተማ ላይ ይህን አባ ቄርሎስነ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት በዘመኑም በትምህርቱ ቤተ ክርስቲያን በራች። ይኸው አባት ቄርሎስ የቊስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳሳት የነበረው ንስጥሮስ በካደ ጊዜ በንጉሥ ቴዎዶስዮስ ዘመን የሁለት መቶ ኤጲስቆጶሳት ጉባኤ ማኅበርን በኤፌሶን ከተማ ሰበሰበ። ይህ አባት ቄርሎስን መረጠው ሊቀ ጉባኤ አደረጉት ንስጥሮስንም ተከራከረው ስህተቱንም ገለጠለት ከስህተቱም ባልተመለሰ ጊዜ አውግዘው ከመንበረ ሲመት አሳደዱት።
❤ ይህም አባት ቄርሎስ አሥራ ሁለት አንቀጾችን ደረሰ። በውስጣቸውም የቀናች ሃይማኖትን ገለጠ። ከዚህም በኋላ ግን ብዙዎች ድንሳናትን ተግሳጻትንና መልእክቶችን ደረሰ። እሊህም በሁሉ ቦታ በመምእመናን እጆች ይገኛሉ።
❤ ይህም አባት ቄርሎስ እግዚአብሔር ቃል ከትሥብእቱ ጋራ ከተዋሐደ በኋላ በሥራ ሁሉ በምንም በምን የማይለያይ አንድ አካል አንድ ባሕሪይ እንደሆነ አስረዳ። ይህኀኀዕዐዐዐዘፈዐጸዐሬፈጰም አባት ቄርሎስ ሃይማኖታቸው ከቀና ከሦስት መቶ አሥራ ስምንት አባቶ ሃይማኖት ወጥተው ክርስቶስ ወደ ሁለት የሚከፍሉት መናፍቃንን ሁሉንም አውግዞ ለያቸው።
❤ ወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ መንበር ላይ ሠላሳ ሁለት ዓመት ኖረ መልካም የሆነኄዐጸዘጨዐዐዐው ሥራውም ፈጽሞ ሐምሌ 3 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ቄርሎስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላዓለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #የሮሜ_ሊቀ_ጳጳሳት_ቅዱስ_አባት_አባ #ክልስቲያኖስ፦ ይህ አባ ዮናክንዲዮስ በሚያርፍበት ጊዜ በእርሱ ፈንታ አባ ክልስቲያኖስን ሊቀ ጵጵስና እንዲሾሙት አዘዘ እርሱንም አባ ክልስቲያኖስን "በሮሜ አገር ነጣቂ ተኩላዎች አሉና ልጄ ሆይ ተጠበቅ" ብሎ አዘዘ።
❤ ከዚህም በኋላ አባ ዮናክንዲዮስ በዐረፈ ጊዜ ይህን አባት ክልስቲያኖስን በእርሱ ፈንታ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት። በዚያ ወራት ደግ ንጉሥ አኖርዮስ ነበር ከእርሱም በኋላ አመጸኛ ሉልያኖስ ነገሠ እርሱም ክርስቲያኖስን ከመንበሩ አሳድዶ መናፍቁን ንስጥሮስን ሊቀ ጵጵስና ሾመው። የከተማ ሰዎች ግን አባረሩት እንጂ አልተቀበሉትም በከሀዲው ንጉሥም ልብ በክርስቲያስ ላይ ቂም ነበረ ሊገድለውም ይሻ ነበር። እርሱ አባ ክልስቲያኖስ ግን በሮሜ ከተማ የሚገኙ ገዳማት በንዱ ገብቶ ኖረ እግዚአብሔርም ብዙ ድንቆችንና ተአምራቶችን በእጆቹ ያደርግ ነበር።
❤ ከዚህም በኋላ ከሀዲው ንጉሥ ወደ ጦርነት ሆደ የእግዚአብሔር መልአክ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሩፋኤልን ለክልስቲያኖስ ተገለጠለት ወደ አንጾክያ ከተማ ወደ ሊቀ ጳጳሳት ድምትርያኖስ ይሔድ ዘንድ አዘዘው "በዚያም ኑር" አለው። "ንጉሡ ከጦርነት እንደተመለሰ ይገድልህ ዘንድ በልቡ አስባልና"። ከእንቅልፉም በነቃ ጊዜ ከዚያ ገዳም ወጣ ከእርሱም ጋራም ሁለት መነኰሳት ነበሩ ወደ አንጾኪያ ከተማ ወደርሶ ቅዱስ ድምትርያኖስ አገኘው ከአመጸኛው ንጉሥም የደረሰበትን ሁሉ ነገረው እርሱም በአንጾኪያ ከተማ የሚገኙ ገዳማት በአንዱ ገዳም አኖረው።
❤ ከዚህ በኋላ ቅዱሳን ሊቃ ጳጳሳት አግናጥዮስና ዮናክንዲዮስ በሌሊት ዕራይ ለንጉሡ ተገለጡለት ከእርሳቸውም ጋራ የነበረው አንዱ እጅግ የሚያስፈራና ግሩም ነበር። እርሱም ንጉሡን እንዲህ አለው "ሊቀ ጳጳሳቱን ክልስቲያኖስን አገሩን ለምን አስተውከው እነሆ እግዚአብሔር ነፍስህን ከአንተ ይወስዳል በጠላቶችህም እጅ ትሞታለህ"። ንጉሥም ጌታዬ "ምን ላድርግ" አለው እነዚያም ሁለትም አባቶች "በእግዚአብሔር ልጅ ሕማም በመቀበሉ ታምናለህን" ብለው መለሱለት "እኔ አምናለሁ" አላቸው "ዳግመኛም መልእክትን ልከህ ልጃችን ክልስቲያኖስ ወደ መንበሩ መልሰው" አሉት።
❤ ከእንቅልፉም በነቃ ጊዜ መልክትን ጽፌ ወደ ድምትራያኖስ እንዲህ ብሎ ላከ "ስለ ሊቀ ጳጳሳት ክልስቲያኖስ በእኔ ላይ አትዘን ወደ መንበረ ሲመቱ ይመልሱት ዘንድ ሊቀ ጳጳሳት ክልስቲያኖስ ያለበትን በመላእክተኞቼ ታመላክታቸውና ታደርሳቸው ዘንድ እለምንሀለሁ"። መልአክተኞችም በሔዱ ጊዜ አገኙትና መለሱት ሕዝቡም በታላቅ ክብርና በብዙ ደስታ ተቀበሉት በዚያም ወራት ንጉሡ ከጦርነት በደና ተመለሰ ቤተ ክርስቲያንም በዕረፍትና በሰላም ኖረች።
❤ የንስጥሮስም ክህደቱ በተገለጠ ጊዜ በእርሱ ምንክያት አንድነት ያላቸው ማኅበር ተሰበሰቡ ይህ አባት ክልስቲያኖስ በደዌውና በእርጅናው ምክንያት ወደ ጉባኤው መምጣት አልተቻላቸውም ነገር ግን ንስጥሮስን ከሚያወግዝ ደብዳቤ ጋር ሁለት ቀሳውስትን ላከ።
❤ ክብር ይግባውና ጌታችንም ከዚህ ኃላፊ ዓለም ድካም ሊያሳርፈው በፈቀደ ጊዜ ዮናክንዲዮስና አትናስዮስ ተገለጡለት እንዲህም አሉት "ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሕይወት ጠርተሀልና አንተ ወደ እኛ ስለምትመጣ አስጠንቅቃቸው" አሉት። ከእንቅልፉ ነቅቶ ወገኖቹን ጠራቸው እንዲህም አላቸው "ተኩላዎች ወደዚች ከተማ ይገቡ ዘንድ አላቸውና ተጠንቀቁ"።
❤ ይህንም ከተናገረ በኋላ ዳግመኛ እንዲህ አለ "እንነሳና እንሂድ እነሆ ቅዱሳን ይሹኛልና ሁለቱ ሌሎች ናቸው በዚችም ሰዓት በዚች ዓለም በአንድነት እንወጣለን እነርሱም የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ቄርሎስና የፃን አገር ኤጲስቆጶስ ሉቅያስ ናቸው" ይህንንም ብሎ ሐምሌ 3 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን አባቶቻችን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሐምሌ 3 ሰንክሳር። | 16 |
| 4 | No text... | 9 |
| 5 | ❤"በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን" ❤
❤ #ሐምሌ_፫ (3) ቀን።
❤ እንኳን #ከዘጠኙ_ቅዱሳን ቀድመው ወደ አገራች ኢትዮጵያ ለመጡ #ደብረ_ሊባኖስ_ገዳም በስማቸው ለተሰየመላቸው ከዐለት ጠበል እያፈለቁ ድውያንን ለሚፈውሱት ለተአምረኛው ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ሊባኖስ (መጣዕ) ለልደት በዓልና ዐፄ ገብረ መስቀል በስማቸው ለመጀመሪያ ጊዜ ያሠራው ቤተ ክርስቲያን ለቅዳሴ ቤት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #የአቡነ_ሊባኖስ_ልደት፦ የዚህም የቅዱስ አባታችን የአባ ሊባኖስ የአባቱ ስም አብርሃም የእናቱ ስም ንግሥት ነው። እነርሱም በወርቅና በብር እጅግ የከበሩ ነበሩ ሀገራቸውም ሮም ትባላለች ይህቺውም በቊስጥንጥንያ ሀገር አቅራቢያ ናት፤ ከኒህም ደጎች ሰዎች አባታችን አባ ሊባኖስ ሐምሌ ሦስት ቀን ተወለዱ።
❤ ከዚህም በኋላ በመልካም አስተዳደግ አሳደጉት በነፃነትም ሁሉ መልካም ሆኖ አደገ የመልኩም ደም ግባት ያማረ ነገሩም እንደ ማር የጣፈጠ ነበር፤ ጥበብንና ተግሣፅን ብሉይና ሐዲስን ሁሉ ተማረ።
✝ ✝ ✝
❤ #ዐፄ_ገብረ_መስቀል_ስለአሠሩት_የአቡነ_ሊባኖስ_ቤተ_ክርስትያን_ቅዳሴ_ቤት፦ ...ንጉሡ ገብረ መስቀልም የአባታችን ዕረፍት በሰማ ጊዜ ደብረ ወርቅ ወደ ምትባል ደብር ሄዶ እስከ ሦስት ዓመት ድረስ ቤተ ክርስቲያኑን ሠራ ሠርቶም ከጨረሰ በኋላ ጳጳስ አምጥቶ ሐምሌ ሦስት ቀን አስባረካት። በዚች ቀን ክቡር አባታችን አባ ሊባኖስ ተወልዶባታልና ስሙንም ገበዘ ገብረ መስቀል አለው። ሚስቱም የማርያምን ደብር ሠራች ልጁም አምስት አድባራትን ሠራ። እኒህም ሰባቱ አድባራት የመናንያን መቀመጫዎች ታላላቅ ገዳማት ሆኑ፤ ብዙ ርስት ጉልትም ተከለላቸው፤ በአባታችን በአባ መጣዕ (ሊባኖስ) ማደሪያም ዐሥራ ዘጠኝ አብያተ ክርስቲያናት ተሰሩ፤ በስሙም የተሠሩት አድባራት ቁጥሮቸው ሰማንያ ይሆናሉ። ይህም ሁሉ ሐሰት አይምሰላችሁ በአክሱም ታሪክ ይገኛል። ከጽዮን ሕግ ይወጣል በኢየሩሳሌምም ሕግ ይነገራል እንደተባለ።
❤ የካሌብ ልጅ ንጉሡ ገብረ መስቀልም ቤተ ክርስቲያኑን ሠርቶ በጨረሰ ጊዜ ደሙን ከጎን አንቅቶ አባቴ ሆይ ሥጋዬ ከሥጋህ ጋር እንደተጨመረ በመንግሥተ ሰማያት ከአንተ ጋር ጨምረኝ ብሎ ከክቡር አባታችን ከአባ ሊባኖስ መቃብር ላይ ደሙን ጨመረው፤ እኛንም ለመንግሥተ ሰማያት ከእርሱ ጋር ያኑረን ለዘለዓለሙ አሜን። ከአባታችን አቡነ ሊባኖስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን። ምንጭ፦ ገድለ አቡነ ሊባኖስ። | 14 |
| 6 | No text... | 50 |
| 7 | ❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን" ❤
❤ #ሰኔ ፴ (30) ቀን።
❤ እንኳን #ለነቢዩ_ለሰማዕቱ_ለካህኑ_ለሐዋርያው #ለመጥምቀ_መለኮት_ለቅዱስ_ዮሐንስ_ለተወለደበት_ለልደት_በዓልና #በሕንደኬ_ካሉ_ደሴቶቸ በአንዲቱ ውስጥ ለሚኖር ለገድለኛ ለሆነ #ለአባ_ጌራን_ለዕረፍት_መታሰቢያ_በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከቅዱሳን_ማርያና_ከማርታ_ከመነኰስ #ገብረ_ክርስቶስ_ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #ነቢይ_ሰማዕት_ሐዋርያ_መጥምቁ_ቅዱስ #ዮሐንስ_ልደት፦ ይህም በእናቱ ማኅፀን ውስጥ ሳለ ለእግዚአብሔር ልጅ የሰገደው ነው። ይህም በመድኅን ክርስቶስ ራስ ላይ እጁን ጭኖ በውኃ ያጠምቀው ዘንድ የተገባው ነው።
❤ በቅዱስ ወንጌል እንደ ተነገረ ወንድ ልጅን ትወልድ ዘንድ የኤልሳቤጥ የፅንሷ ወራት በተፈጸመ ጊዜ ወንድ ልጅን ወለደች። ዘመዶቿና ጎረቤቶቿ እግዚአብሔር ቸርነቱን እንዳበዛላት በሰሙ ጊዜ ስለርስዋ ደስ አላቸው። በስምንተኛውም ቀን ሊገዝሩት መጡ በአባቱ ስም ዘካርያስ ብለው ጠሩት። እናቱ ግን "አይሆንም ዮሐንስ ይባል" አለች። "ከዘመዶችሽ ስሙ እንዲህ የሚባል የለም" አሏት።
❤ አባቱንም ጠቅሰው "ማን ሊባል ትወዳለህ" አሉት። እርሱም ብራና ለምኖ ስሙ "ዮሐንስ ይባል" ብሎ ጻፈ። ሁሉም አደነቁ። ያን ጊዜም አንደበቱ ከድዳነት ተፈትቶለት ተናገረ እግዚአብሔርንም ፈጽሞ አመሰገነው። ስለ ልጁና ስለ መድኃኒታችን መምጣት ልጁ ዮሐንስም የልዑል ነቢይ እንደሚባልና በእግዚአብሔርም ፊት እንደሚሔድ ትንቢት ተናገረ።
❤ ሰብአ ሰገልም መጥተው ከሔዱ በኋላ ሄሮድስ ሕፃናትን በገደላቸው ጊዜ ስለ ሕፃናትን በገደላቸው ጊዜ ስለ ሕፃኑ ዮሐንስ ለሄሮድስ ነገሩት እንዲገድሉትም ጭፍሮችን ላከ ጭፍሮችም ወደ አባቱ ዘካርያስ መጡ ሕፃኑንም ከእርሱ ፈለጉት አባቱም አንሥቶ በትከሻዎቹ ተሸክሞ ወደ ቤተ መቅደስ ከእርሱ ጋራ እንዲሔዱና ሕፃኑን ከዚያ እንዲወስዱት ወታደሮችን ለመናቸው።
❤ ከዚህም በኋላ ሕፃኑን በመሠዊያው ጠርዝ ላይ አኖረውና "ከዚህ ራሳችሁ ተቀብላችሁ ውሰዱት" አላቸው ወዲያውኑ የእግዚአብሔር መልአክ ነጥቆ ወደ በረሀ ወሰደው። ጭፍሮችም ባላገኙት ጊዜ አባቱ ዘካርያስን ገደሉት። ሕፃኑ ግን አድጎ ለእስራኤል እስከተገለጠበት ጊዜ ድረስ በበረሀ ውስጥ ኖረ።
❤ "የእግዚአብሔርን መንገድ ጥረጉ ጥርጊያውንም አስተካክሉ እያለ በምድረ በዳ የሚጮህ የዐዋጅ ነጋሪ ድምጽ እነሆ" ብሎ ኢያሳያስ የተናገረለት ይህ ነው። ሚልክያስም ስለርሱ እንዲህ አለ "በፊትህ ጎዳናዬን አስተካክሎ የሚጠርግ መልአክተኛዬን እኔ እሰዳለሁ"።
❤ ራሱ መድኃኒታችንም ስርሱ ሲናገር "ሴቶች ከወለዱአቸው መጥምቁ ዮሐንስን የሚበልጠው የለም" ብሏል። ይህ የእግዚአብሔር ልጅ በአጠመቀውና የማትዳሠሥ ራሱን በዳሠሠው ጊዜ "የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት" የሚል የአብን ቃል ሰምቷልና።
❤ ዳግመኛም ክብር ይግባውና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ራስ ላይ መንፈስ ቅዱስ ወርዶ ሲቀመጥ አየ። እኛንም መድኃኒታችን እንዲምረንና ይቅር እንዲለን በአማላጅነቱ እያመን መታሰቢያውን እናድርግ የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስ በረከቱም እኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #ገድለኛው_የሆነ_አባ_ጌራን፦ ይህም ቅዱስ በሕንደኬ ካሉ ደሴቶች በአንዲቱ ውስጥ የሚኖር ነው። እርሱም እግዚአብሔርን የሚፈራና የሚወደው ጾምና ጸሎትንም የሚወድ ነበር። ወደ እግዚአብሔርም የሚለምነውን ሁሉ ይሰማው ነበር። በጸሎቱም ከዚያች አገር ንዳድ፣ አባር፣ ድርቅ፣ በጠላት መማረክ፣ የደም መፍሰስና የመርከቦች መሥጠም ተወገደ የፈለገውንም ሁሉ በጸሎቱ ያገኝ ነበር።
❤ ሰይጣንም ስለዚህ ስለ ተሰጠው ጸጋ ቀናበት በዕንቊ ያጌጠ ነገሥታትን ልብስ በለበሰች መልከ መልካም ሴት አምሳልም ታየው እርሷም ብቻዋን ትንጎራደድ ነበር። በአያትም ጊዜ ወደርሷ ሒዶ ሥራዋን ጠየቃት እርሷም እንዲህ አለችው "የንጉሥ ሰርስባን ልጅ ነኝ እኅቴ ከአባቷ ባሮች ጋራ በአመነዘረች ጊዜ ሁላችንንም ሊገድለን ፈለገ። ስለዚህ ፈርቼ በሌሊት ወጣሁ ወደዚች በረሀም መጣሁ ቅዱሱን ሰው አንተን በማግኘቴም እድለኛ ነኝ" አለችው። እርሱም "ወደ እኔ የሚመጡ ሰዎች እንዳያዩሽ ወደዚያች የዐለት ዋሻ ሒጂ" አላት።
❤ በሌሊትም ከአራዊት የተነሣ እንደፈራ ሰው እየጮኸች መጥታ "የዱር አራዊት እንዳይበሉኝ ክፈትልኝ" አለችው። እርሱም ከፈተላትና ገባች በጎኑም ተኝታ ደረቱን አቀፈችው ልቡን ወደ ፍቅርዋ እስከ አዘነበለችው ድረስ ነገሯን አለሰለሰችለት። ያን ጊዜ ያደረበት የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ተለየው ከእርሷም ጋራ ተኝቶ ኃጢአት እደሚሠራ ሆነ። ከስህተት ስካርም በነቃ ጊዜ በጠላት ሰይጣን ተንኰል ተሸንፎ እንደ በደለ አወቀ።
❤ ከዚህም በኋላ ከሰይጣን ተንኰል የተነሣ ያገኘውን ሁሉ በሥጋውም ኃጢአት እንደሠራ ጻፈ። ከዚህ በኋላም ከደሴቱ ተራራ ድንጊያ አንሥቶ እስከሚሞት ድረስ ራሱንና ደረቱን እየደበደበ ኖረ። ነፍሱም ድና ወደ ዘላለም ሕይወት በጌታ ቸርነት ገባች።
❤ ከዚህም በኋላ እንደ ልማዳቸው ከእርሱ ቡራኬ ሊቀበሉ ሰዎች መጥተው አላገኙትም በፈለጉትም ጊዜ ተኝቶ አገኙትና ያንቀላፋ መስሏቸው ጀምሩ ግን ሞቶ አገኙት አለቀሱለት ተሳለሙት ገንዘውም ቀበሩት።
❤ ከዚህም በኋላ ሞቱ በጠላት ሰይጣን ተንኮል ምክንያት ስለመሆኑ የጻፈውን አገኙ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ጻድቃንና ሰማዕታት ጸሎት መንፈሳውያን በሆኑ በቅዱሳን መላእክትም አማላጅነት ይልቁንም አምላክን በወለደች በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በጸሎቷና በአማላጅነቷ ከሰይጣን ወጥመድ ያድነን።
❤ የተባረ የሰኔ ወር በእግዚአብሔር ቸርነት ተፈጸመ አሜን። ምንጭ፦ የሰኔ 30 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "አሜሃ ይቤሉ አሕዛብ። አዕበየ ገቢረ ሎሙ እግዚአብሔር። ወኮነ ፍሡሓነ። መዝ 125፥2፥3። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 1፥76-ፍ.ም።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወተወከልኩከ እንዘ ሀሎኩ ውስተ አጥባተ እምየ። ላዕሌከ ተገደፍኩ እማኅፀን። እምከርሠ እምየ አንተ አምላኪየ"። መዝ 21፥9-10። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 7፥14-ፍ.ም፣ 1ኛ ዮሐ 3፥7-10 እና የሐዋ ሥራ 19፥1-21። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 1፥57-80። የሚቀደሰው ቅዳሴ የወልደ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቅዳሴ ነው። መልካም የመጥምቀ መለኮት የልደት በዓልና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን። | 49 |
| 8 | No text... | 37 |
| 9 | No text... | 35 |
| 10 | ✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ዘይገለብቦ ለሰማይ በደመና። ወያስተዴሉ ክረምተ ለምድር። ዘያበቊል ሣዕረ ውስተ አድባር"። መዝ 146፥8። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ጢሞ 3፥13-ፍ.ም፣ 1ኛ ዮሐ 1፥4፥9-18 እና የሐዋ ሥራ 9፥20-23። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 16፥24-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ባስልዮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የጻድቁ ንጉሥ የቅዱስ ቴዎድሮስ የዕረፍት በዓልና የጾም ጊዜ ለሁላችን ይሁንልን። | 32 |
| 11 | ❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን" ❤
❤ #ሰኔ ፳፱ (29) ቀን።
❤ እንኳን #ለንጹሕ_ጻድቅ ለሆነ ለሮሜ ንጉሥ #ለቅዱስ_ማርቆስ_ለዕረፍቱ_መታሰቢያ_በዓል፣ #ከቆና_ገዳም_ለሆኑ_ለሰባት_መስተጋድላን ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዐረፍታቸው በዓል መታሰቢያና #ለቅዱሳን_ለአባ_ሖር_ለአባ ብሶይና #ለእናታቸው_ይድራ ከአንጾኪያ ንጉሥ ሠራዊት ውስጥ ለሆነ #ለአባ_ሖርሳም_ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰበው፦ ከክብር ባለቤት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታች ቅድስት ድንግል ማርያም በሥጋ ከተወለደበት #ከልደቱ _ከበዓለ_ወልድ_ከወራዊ_ከመታሰቢያ_በዓል እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #ለሮሜ_ንጉሥ_ቅዱስ_ማርቆስ፦ ይህም ቅዱስ ንጹሕ ጻድቅ ነበር። በድንግልናው አምስት ዓመት ነገሠ ሕዝቡንም እግዚአብሔርን በመፍራትና በቅን ፍርድ ጠበቀ። እርሱንም ከመውደዳቸው የተነሣ ሚስቱን እንዲአገባ መኳንንቱ አስገደዱት እርሱ ግን በሌሊት ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥዕል ፊት ቁሞ ጸለየ "እመቤቴ ሆይ ላንቺና ለማይሻር ንጉሥ ልጅሽ እገዛ ዘንድ ወደ ምሔድበት ምሪኝ" አላት። እርሷም "ወደ ቶርማቅ ተራራ ሒድ እግዚአብሔር ከአንተ ጋራ ይኑር" አለችው።
❤ ከዚህም በኋላ በሌሊት ወጥቶ ሔደ ወደ ባሕር ወደብም በደረሰ ጊዜ ያለ መርከብ ተሻግሮ ወደ ቶርማቅ ተራራ ደረሰ ያም ቦታ ደረቅ ነበረ ከአጋንት ጋራም እየተጋደለ በውስጡ ስልሳ ዓመት ኖረ። ሰኔ 29 ቀን በዐረፈ ጊዜም መላእክት በክብር ቀበሩት። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጻድቁ ንጉሥ በቅዱስ ማርቆስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #በቆና_ገዳም_የነበሩ_ሰባት_መስተጋድላን ሰማዕታት፦ የእሊህም ስማቸው አባ አብሲዳ፣ አባ ኮቶሎስ፣ አባ አርድማ፣ አባ ሙሴ፣ አባ እሴይ፣ አባ ኒኮላስና አባ ብሶይ ናቸው የእግዚአብሔርም መልአክ ተገልጾ እንዲህ ብሎ "አዘዛቸው ክብር ይግባውና የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ስም ግለጡ"።
❤ ያን ጊዜም ወደ መኰንኑ ሊሔዱ ተነሡ መርከብንም አገኙ በመርከቧም ውስጥ አምስቱን መስተጋድላን አገኙአቸውና ከእነርሱ ጋር ተስማሙ ወደ መኰንኑም ደርሰው በፊቱ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ታመኑ። መኰንኑም ከእርሳቸው አንዱን ስለ ሀገራቸው ጠየቀው እርሱም ቆና ከሚባል አገር እንደሆኑ አስረዳው መኰንኑም ያሥሩዋቸው ዘንድ አዘዘ።
❤ ከዚህም በኋላ ደግሞ ከእሥር ቤት አውጥተው ጽኑ ሥቃይን ያሠቃዩአቸው ዘንድ ደግሞም በአንገቶቻቸው ከባድ ደንጊያዎችን አንጠልጥለው እንዲአሥሩዋቸው አዘዘ። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በውህኒ ቤት ውስጥ ተገለጠላቸው አጽናናቸውም ቃል ኪዳንም ገባላቸው።
❤ ከዚህ በኋላ ንጉሥ ወደ እስክንድርያ ከተማ ላካቸው በዚያም ጽኑ ሥቃይን አሠቃዩአቸው። ከዚህም በኋላ ዝፍትና ድኝ በተመሉ ከሁለት የብረት ምጣዶች ውስጥ ጨመሩአቸው ነበልባሉም ሃያ ክንድ ከፍ ከፍ እስሚል ድረስ ከታች እሳትን አነደዱባቸው ከምጣዶችም ውስጥ አውጥተው በእሳት ምድጃ ውስጥ ጨመሩአቸው ጌታችንም ዳግመኛ ተገልጾ ያለ ምንም ጉዳት አዳናቸው።
❤ ከዚህም በኋላ ወደ መኰንኑ ቀርበው ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመኑ ይህንንም ድንቅ ሥራ አይተው መቶ ሠላሳ ሰዎች በጌታችን አምነው በሰማዕትነት ሞቱ። ከዚህም በኋላ አስጨናቂ የሆነ ሥቃይን አሠቃያቸው ወደ እነርሱም አጵሎን የሚሉትን ጣዖት በወንበር እንደ ተቀመጠ አምጥቶ እንዲሰግዱለት አዘዛቸው እነርሱም ግን በእግሮቻቸው ረገጡትና ከመንበሩ ወድቆ ተሰበረ።
❤ መኰንኑም አይቶ እጅግ ተቆጣ እግሮቻቸውንም እንዲቆርጡ አዘዘ የቅዱስ ቀሲስ አብሲዳንን ግን ራሱን በሰይፍ ቆረጡትና ምስክርነቱን ፈጸመ እንዲሁ ደግሞ እሊያ አምስቱንም ራሶቻቸውን ቆረጡ ቅዱስ ኮቶሎስን ግን በእሳት አቃጠሉት ሁሉም የሰማዕትነት አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀዳጁ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሰባቱ መስተጋድል ሰማዕታት በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ይኑር አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱሳን_አባ_ሖር_አባ_ብሶይና እናታቸው #ቅድስት_ይድራ ከአንጾኪያ ንጉሥ ሠራዊት ውስጥ የሆነ #አባ_ሖርሳ፦ እሊህም ወደ እስክንድርያ በደረሱ ጊዜ በመኰንኑ ፊት ክብር ይግባውና በጌታች ኢየሱስ ክርስቶስ ታመኑ መኰንኑም አባ ብሶይን ይዘው ቀኝ እጁንም አሥረው በከተማዎች ሁሉ በበሬዎች እንዲጐትቱት አዘዘ።
❤ ከዚህም በኋላ የተዘረጉ ብረቶችን በእሳት አግለው በሥጋው ውስጥ አደረጉ የግራ እጁንም ቆረጡ እርሳስም አቅልጠው በአፉ ጨመሩ ጊንጦችና እባቦች ወደ ተከማቹበት ውስጥ ጣሉት እነርሱ ግን ከቶ አልቀረቡትም።
❤ ከዚህም በኋላ በብረት በትሮች ይደበድቡት ጀመር እርሱም "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ርዳኝ ከዚህ ሥቃይም አድነኝ" ብሎ ጮኸ ጌታችንም አጸናው እንደቀድሞውም ያለ ምንም ጉዳት ጤነኛ አድርጎ አስነሣው።
❤ ከዚህም በኋላ እናቱ ወደርሱ መጥታ አረጋጋቸው በመጋደሉም ደስ ተሰኘችበት። ስለ እርሷም ለመኰንኑ ነገሩት እርሱም ወደ እርሱ አስቀርቦ እያስፈራራ "ለአማልክት ሠዊ" አላት። እርሷ ግን አልፈራችውም ትእዛዙንም አልሰማችም የብረት በትሮችንም አግለው በጎኖቿ ውስጥ እንዲአደርጉ አዘዘ ይህንም በእርስዋ ላይ በአደረጉ ጊዜ ደስ ብሏት ዘመረች ስለ ቅዱስ ስሙም መከራ እንድትቀበል ያደረጋት እግዚአብሔርን አመሰገነችው ከዚህም በኋላ ነፍሷን ሰጠች የሰማዕትነትም አክሊል ተቀዳጀች።
❤ ቅዱስ አባ ሖርንም ከቅባትና ከተቀመመ የነዳጅ ቅመም ጋራ በብረት ምጣድ ውስጥ አበሰሉት እርሱም ያለ ሕማም ሁኖ እግዚአብሔርን ያመሰግን ነበር ይህንንም ለመኰንኑ ነገሩት እርሱም እጅግ አደነቀ ደነገጠም። ንጉሡ ግን ተቆጣ በእጁም ጦር እንዳያዘ ወደ ብረት ምጣዱ ሒዶ ቅዱስ ሖርን ወጋው ነፍሱንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ።
❤ እንዲሁም ወንድሙ አባ ብሶይን ብዙ ሥቃይን ካሠቃዩት በኋላ ራሱን በይፍ ቆረጡት። ሁሉም በመንግሥተ ሰማያት የሰማዕትነት አክሊልን ተቀዳጁ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በእሊህ ሰማዕታት በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለማርቆስ_ጊዜ_ተሠልጠ_ዘመኑ። እንዘ ሀሎ ደብረ ቶርማቆ መካኑ። ወንጌል ቅዱሰ እንተ ማቴዎስ ይዜኑ። ሶበ ይብይ ለመልአከ ሰማይ ልሳኑ። መነጠ ፭ቱ እመት ተለዓለ በድኑ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የሰኔ29።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ምስሌከ ቀዳማዊ በዕለተ ኃይል። ወብርሃኖሙ ለቅዱሳን። ወለድኩከ እምከርሥ እምቅድመ ኮከበ ጽባሕ"። መዝ 109፥3።የሚነበበው ወንጌል ማቴ 2፥1-13። | 27 |
| 12 | ❤"በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን" ❤
❤ #ሰኔ ፳፱ (29) ቀን።
❤ እንኳን #ለንጉሥ_ዳዊት ልጅ ለኢትዮጵያዊው ንጉሥ #ለጻድቁ_ለቅዱስ_ቴዎድሮስ ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል፣ #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ ለከበረ #ለቅዱስ_ዐምደ_ሚካኤል ለሥጋው ፍልሰት እግዚአብሔር አምላክ በሰላም በጤና አደረሰን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የንጉሥ_ዳዊት_ልጅ_የኢትዮጵያ_ንጉሥ #ቅዱስ1ቴዎድሮስ፦ ይህም ቅዱስ ከታናሽነቱ በዕውቀትና በተግሣጽ አደገ የቤተ ክርስቲያንንም መጻሕፍት የተማረ ደግሞም ቀስት ማፈናጠርንና ፈረስ ግልቢያን ተማረ ኃይል ያለውም ብርቱ ሰው ሆነ።
❤ ከታናሽነቱም ጀምሮ በእግዚአብሔር ፍቅር ታሠረ ገንዘቡን ለድኆችና ለችግረኞች ይመጸውት ነበር። አብያተ ክርስቲያንንም እጅ መንሻ ከመያዝ ጋራ ይጎበኝ ነበረ በጸሎቱና በጾምም ይጋደል ነበር። ካንዲት ሴት በቀር አላገባም በማንም ላይ ዐመጻና ግፍ ከቶ አልሠራም።
❤ ወደ ኢየሩሳሌም ለመሔድ በአሰበ ጊዜ አባ ማርቆስን አማከረው እነርሱም በመንፈስ ቅዱስ ያውቅ ነበርና "ክፍልህ አይደለም" አለው።
❤ ከዚህም በኋላ ባረፈ ጊዜ በክረምት ወራት በድኑን ሲወስዱ ሞልቶ የነበረው ወንዝ ወዲያና ወዲህ ተከፍሎ ተሻገሩ በቀበሩበትም ቦታ ሕይወትነት ያለው ውኃ መነጨ እስከ ዛሬም አለ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጻድቁ ንጉሥ በቅዱስ ቴዎድሮስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ በዚችም ቀን #የከበረ_ዐምደ_ሚካኤል የሥጋው ፍልሰት ሆነ መጀመሪያ በንጉሥ እስክንድር ዘመነ መንግሥት ወደ አባቶቹ መቃብር ዳግመኛም በንጉሥ ልብነ ድንግል ዘመን በአረፈ በአርባ ዓመቱ ፈለሰ አባቶቹ ነገሥታት ወደተቀበሩበት ወደ አትሮንሰ ማርያም አፍልሰው እንዲወስዱት ንጉሡ አዝዞ ነበርና። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ሁሉ ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ "#ሰላም_ለከ_ለብሔረ_አግዓዚ_ንጉሣ። ቴዎድሮስ ዕጓለ አንበሳ። ተዝካረ በዓልከ ዮም በጥብሐ አባግዕ ወእንሰሳ። አኮ ዘገብረት ባሕቲታ እምከ ጽዮን ሞገሳ። ደመናትኒ አንጠብጠቡ ዓሣ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሰኔ_29። | 26 |
| 13 | No text... | 45 |
| 14 | ❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን" ❤
❤ እንኳን #ለዘመነ_ክረምት መግቢያ ለሚታሰብበት #ለመጀመሪያ_ዕለተ_ሰንበት (እሑድ) እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዚህ_ሳምንት_መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ በ፪ "#ደምፀ_እገሪሁ_ለዝናም ሶበ ይዘንም ዝናም ይጸግቡ ርኁባን፤ ደምፀ እገሪሁ ለዝናም ይትፌሥሑ ነዳያን፤ አዝ፣ ወሠርዐ ሰንበት ለሰብእ ዕረፍት ደምፀ እገሪሁ ለዝናም #ደምፀ_እገሪሁ_ለዝናም"። ትርጉም፦ #የዝናም_ኮቴው ተሰማ ዝናብ በሚዘንብ ጊዜ ረኀብተኞች ይጠግባሉ፤ ዝናብ በዘነበ ጊዜ ድኆዎች ደስ ይሰኛሉ፤ ሰንበትን ለሰው ዕረፍት ፈጠረ #የዝናም_ኮቴው_ተሰማ። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በድጓው_ላይ።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #ዘመነ_ክረምት፦ "ክረምት" የሚለው ቃል ከርመ፣ ከረመ ሰነበተ ኖረ ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ሁለት ትርጉም አለው የመጀመሪያው ብዙ ዓመት መቆየትን፣ መሰንበትንና ወቅትን ዘመንን የሚያመለክት ሊኾን ሁለተኛም ትርጓሜ መዝነምን መፍሰስን የሚያመለክት ነው።
❤ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመዝገበ ቃላቸው ላይ ስለክረምት ሲያብራሩ "ክረምት በቁሙ ዝናም የዝናም ወራት፤ በጸደይና በመጸው መካከል ያለ ክፍለ ዓመት፤ ከሰኔ 25 እስከ መስከረም 25 ዓመት ድረስ ያለ ወቅት ነው"። ብለው ገልጸውታል። ስለዚህ ክረምት ወርኃ ዝናም፣ ወርኃ ነጎድጓድ፣ ዘመነ ባሕር፣ ዘመነ ነጎድጓድ፣ ዘመነ አፍላግ፣ ዘመነ ጠል፣ ዘመነ ደመና፣ ዘመነ መብረቅ ማለት ነው።
❤ በዘመነ ከረምት ውኃ ይሠለጥናል፣ ዝናም አፈርን ያጥባል፣ እሳትን ያጠፋል። ሆኖም ግን በብሩህነቱ ከእሳት፤ በቀዝቃዛነቱ ነፍስ፤ በእርጥብነቱ ከመሬት ጋር አስማምቶ ከሦስቱ ባሕርያት ጋር ይኖራል። ይህ ወቅት ስለ ሥነ ፍጥረት መግቦት ዘርዘር ባለ መልኩ የሚነገርበት ወቅት ስለሆነ ፍጡርን ከፈጣሪ ምግብን ከመጋቢ ለይቶ የሚያሳይና የሚያሳውቅ ወቅት ነው። ወርኃ ክረምት የዝናም፣ የዘርና የአዝመራ ወቅት በመሆኑ ምድር በጠልና በዝናም ትረካለች።
❤ ባሕረ ጥበባት ቅዱስ ያሬድ ሲዘምር በድጓው ላይ "አንተ ኬንያሁ ለኵሉ ፍጥረት አንተ ሠራዕከ ክረምተ ወወሀብከ ለዝናማት ወሠራዕከ መፀወ ወወሀብከ ለጽጌያት። የፍረት ሁሉ ተጠባቢው አንተ ነህ፤ አንተ ክረምትን ሠራህ የሠራኸውንም ክረምት ለዝናም ሰጠኽ፤ አንተ መፀውን ሠራህ የሠራኸውም መፀው ለአበቦችም ሰጠኽ"። ሲል አመስጥሯል። ምንጭ፦ ኆኅተ ስብከት ዘቅዱስ ያሬድ ቅጽ ፪ ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዚህ_ሳምንት_የዕለቱ_ምስባክ፦ "ዘይገለብቦ ለሰማይ በደመና። ወያስተዴሉ ክረምተ ለምድር። ዘያበቊል ሣዕረ ውስተ አድባር"። መዝ 146፥8። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 15፥33-51፣ ያዕ 5፥16-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 27፥11-21። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 8፥1-22። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ኤጲፋንዮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የክረምት መግቢያ (ሰንበት)ና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን። | 37 |
| 15 | ❤ ጊዜው (5ኛውና 6ኛው መቶ ክ/ዘመን) ወዲህ ወርቃማ ወዲያ ደግሞ ጨለማ ተብሎ ሊጠራ የሚችል ዘመን ነበር በብርሃንነቱ በተለይ በምሥራቁ ዓለም ያበሩ አበው እነ ያዕቆብ ዘሥሩግ፣ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያ፣ ያዕቆብ ዘእልበረዲን የመሰሉ አበው ተገኝተውበታል ሲያልፍ ደግሞ ዘይኑንና አንስጣስዮስን የመሰሉ ደጋግ ነገሥታት በዘመኑ መነሳታቸውን እናስባለን።
❤ በተቃራኒው ግን ዘመኑ ቤተ ክርስቲያን ለ2 የተከፈለችበት መለካውያን የነገሥታቱ ደጀን አላቸውና ተዋሕዶ ሃይማኖትን ከሥሯ ነቅሎ ለማጥፋት ብዙ የሞከሩበት ዘመን ነውና ጨለማነቱ ይጐላብናል። በእርግጥም ከመርቅያን እስከ ዮስጢኖስ ዳግማዊ ዘመን ድረስ ለ100 ዓመታት መለካውያኑ የልዮን ልጆች ሁለት ባሕርይ ማለትን ሊያሰፉ ተዋሕዶንም ሊያጠፉ የከፈቱት ዘመቻ ሊሳካ ጫፍ የደረሰ ይመስል ነበር።
ግን አማናዊት ቤቱን የማይተው አማናዊው ጌታ መድኃኔ
ዓለም አርመኖቹን ስቦ በ490ዎቹ ወደ መንጋው ቀላቀለ።
በግብጽ አባ ቴዎዶስዮስን፤ በሶርያ ደግሞ ታላቁን ሊቅ ቅዱስ ሳዊሮስን አስነስቷል። ከቤተ መንግስትም ስም አጠራሯ ያማረ ንግሥት ታኦድራን ማርኳል። በእነዚህ ቅዱሳን ትጋት የለመለመችው ተዋሕዶ እንደ ቅዱስ ያዕቆብ ዘእልበረዲ ያለ አርበኛን ግን ያገኘችው በጭንቅ ቀን ነበር።
❤ ሰው መሆን ሰው በጠፋባቸው ቀናት ነውና በግብጽና በቁስጥንጥንያ በትምህርትና ምናኔ ላይ የነበረው ቅዱሱ ታጥቆ ለአገልግሎት የተሰለፈው በ530ዎቹ አካባቢ ነበር። ጊዜው ወዲህ አንበሳው ቅዱስ ሳዊሮስ ከሶርያ ወደ ግብጽ እንደተሰደደ ያረፈበት ነበር ወዲያ ደግሞ ሊቁ አባ ቴዎዶስዮስ የግብጹ ለግዞት የተዳረገበት ነበርና የተዋሕዶ ምዕመናን ያለ እረኛ ተቅበዘበዙ። የቤተ መንግስቱ ተጽዕኖ ደግሞ ሁለት ባሕርይ በማይሉት ላይ እሥራትና ግድያን ወደ ማወጅ ተሸጋግሯልና የምእመናን ቁጥር እጅጉን
መመንመኑ ቀጠለ።
❤ ይህ ዕረፍት የነሳው ቅዱስ ያዕቆብ በበኩሉ ነገሩን በዝምታ ሊያልፈው አልወደደምና አገልግሎቱን አሰፋ። ሌሊቱን በጸሎት ያድራል። ቀን በቤተ ክርስቲያን አካባቢ ማስተማር ባይችል በየቦታው እየዞረ ያስተምር ነበር።
ከትምህርቱ ጣዕምና ከመልእክቱ ሥምረት የተነሳም ምእመናን እንደገና ተነቃቁ። እርሱም ከግብጽ እስከ ሶርያ አልፎም እስከ ቁስጥንጥንያ ድረስ ያለ ዕረፍት ሲሰብክ 40 ዘመናትን አሳለፈ። በተለይ አዲስ አማኞችን ያጠምቅ ዘንድ በእሥረኛው ቅዱስ ቴዎዳስዮስ ኤጲስ ቆዾስነትን ተቀብሏል። የሶርያ (አንጾኪያ) የፕትርክና መንበሩ ክፍት ሆኖ እርሱን ቢጠብቀውም እርሱ ግን የዚህ (የስልጣን) ፈላጊ አልነበረምና ሌሎች እንዲሾሙበት አድርጉዋል።
❤ ቅዱስ ያዕቆብ በስብከት አገልግሎት ምሥራቁን ዓለም ሲያበራ የተባበሩት ደቀ መዛሙርት ቢኖሩም ያሳለፈው ድካምና መከራ ግን ተወዳዳሪ አልነበረውም። በተለይ የወቅቱ የአንጾኪያ ኃያላን መኳንንትና ሹመኛ መናፍቃን ብዙ አሳደውታል። እርሱ ግን በጥበብና በፈሊጥ እዚያው ደጃቸው ላይ የነበሩ ምዕመናንን በእረኝነት ጠብቁአል። ለዚህ ሲባልም ራሱን እየቀያየረ የመሣፍንቱን አጥሮችና ቅጥሮች አልፏል። ለቤተ
ክርስቲያን ክብርም እንደ እብድ እንደ ሴትም መስሎ የወንጌልን ዘር ዘርቷል። ከብዙ ፈተናና አገልግሎት በሁዋላም በተወለደ በ78 ዓመቱ በ578 ዓ.ም ዐርፎ በክብር ተቀብሯል።
❤ ትልቁ መታሰቢያው የሶርያ ቤተ ክርስቲያን "ያዕቆባዊት" ምዕመኑ "ያዕቆባውያን" መባላቸው ሲሆን እኛ ደግሞ በአንገታችን ላይ እንድናስራት ባስተማረን ማዕተብ (ማኅተም) ዘወትር እናስበዋለን። ለመጀመሪያ ጊዜ ማዕተብን በአንገት ላይ ስለ ማሰር ያስተማረ እርሱ ነውና::
❤ የምሥራቁን ኮከብ እል-በረዲ ያዕቆብን በየዓመቱ ሰኔ 28 ቀን በነገረ ቅዱሳን መደበኛ ጉባኤ ጐንደር እናከብራለን። ሶርያውያን ደግሞ July 31 ሐምሌ 24 ቀን) ያከብሩታል። ከቅዱስ ያዕቆብ ዘእልበረዲ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎቱ ሁላችንንም ይማረን!። ምንጭ፦ ዝክረ ቅዱሳን። | 32 |
| 16 | ❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን" ❤
❤ #ሰኔ ፳፰ (28) ቀን።
❤ እንኳን #ለእስክድርያ (ለግብጽ) አገር ሊቃነ ጳጳሳት ሠላሳ ሦስተኛ ለሆነው ሃያ ስምንት ዓመት ሙሉ በስደትና በመከራ ላሳለፈ ለታላቁ አባት #ለአባ_ቴዎዶስዮስ ለዕረፍት መታሰቢያ በዓልና ለታላቁ አባት የክርስትና የአንገትን ማዕተብ ማሠር ለጀመረ #ለአባ_ያዕቆብ_እል-በረዲ ለመታሰቢያ በዓሉ በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰብ፦ #ከቅዱስ_ባስልዮስና_ከቢፋሞን፣ #ከባሊዲስና #ከኮቶሎስ_ከአርዳሚስ_ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #አባ_ቴዎዶስዮስ፦ ይህም አባት ለእስክንድርያ አገር ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሠላሳ ሦስተኛ ነው። በዚህም ቅዱስ በስሙ በግብጽ ምድር ውስጥ ምእመናን ቴዎዶስዮሳውያን ተብለው ተጠርተውበታል። ይህም የሆነው እንዲህ ነው ሊቀ ጵጵስና ከተሾመ በኋላ ክፉዎች ሰዎች በእርሱ ላይ ተነሥተው በንጉሥ ምክር ከመንበረ ሢመቱ አሳደዱት በእርሱ ፈንታም አስቀድሞ በእስክንድርያ ከተማ ሊቀ ዲያቆናት የነበረ ስሙ አቃቅያኖስ የሚባለውን አንድ ሰው ሾሙ እርሱም ለአባ ቴዎዶስዮስ ሊቀ ጵጵስና እንዲገባው ከፈረሙት ቁጥር ውስጥ ነበር።
❤ ይህም አባት ወደ ግርማኖስ አገር ሒዶ ሦስት ወሮች ኖረ በዚያም ወራት በግብጽ አገር ንቡረ እድ አባ ሳዊሮስ ነበር እርሱም በአባቶቻችን ሐዋርያት እንዲሁም በአትናቴዎስና በዮሐንስ አፈወርቅ የደረሰባቸውን መከራ እያስታወሰ ያጽናናቸው ነበር። ከዚያም ተነሥቶ መሊግ ወደሚባል አገር ሔደ በዚያም ሁለት ዓመት ተቀመጠ።
❤ የእስክንድርያ ከተማ ሰዎችም የጠባቂያቸው የቴዎዶስዮስ መመለስ ሺተው በእስክንድርያው መኰንን ላይ ተነሡበት መኰንኑም ወደ መንበረ ሢመቱ መለሰው አቃቅያኖስንም አባረሩት። ይህም ነገር በንጉሥ ዮስጣቲያኖስና አምላክን በምትወድ በንግሥት ታዖድራ ዘንድ ተሰማ ንግሥቲቱም አስቀድሞ የተሾመው በሹመት ወንበሩ ይቀመጥ ብላ ጻፈች።
❤ ሃምሳ ስምንት ካህናትም ጉባኤ አደረጉ "አስቀድሞ የተሾመ አባ ቴዎዶስዮስ ነው" ሲሉም ጻፉ። ያን ጊዜም አቃቅያኖስ በሕዝብ ፊት ቁሞ "ክፋዎች ሰዎች ስለ አስገደዱኝ ይህን ሥራ ለመሥራት ሕግን ተላልፌአለሁ" አለ። ከዚህም በኋላ አቃቅዮስን ከውግዘቱ እንዲፈታው ነገር ግን ክህነትም ሆነ ሊቀ ዲቁና ለዘለዓለም እንዳይኖረው ሕዝቡ አባ ቴዎዶስዮስን ለመኑት። አቃቅያኖስ "አዎ እንዲሁ ይሁን" አለ ይህም አባት ከግዝቱ ፈታው።
❤ ሃይማኖቱን ያጠፋ ንጉሡ ግን በከፋች ሃይማኖቱ ሊቀ ጳጳሳት አባ ቴዎዶስዮስ ከእርሱ ጋራ የሚስማማ መስሎት በእስክንድርያ ወዳሉ መኳንንቶቹ እንዲህ ብሎ ጻፈ ሊቀ ጳጳሳት አባ ቴዎዶስዮስ በሃይማኖት ከእኛ ጋራ የሚስማማ ከሆነ ሹመት ይጨመርለታል። ለእስክንድር ከተማ ገዥ ይሆናል። ይህ ካልሆነ ከሹመቱ ይሻር።
❤ ይህም አባት ይህን ነገር በሰማ ጊዜ እንዲህ አለ ሰይጣን "በበረሀ ጌታችንን ብትሰግድልኝ የዓለም መንግሥታትንና ክብራቸውን ሁሉ እሰጥሃለሁ" አለው። ያን ጊዜም ይህ አባ ቴዎዶስዮስ ተነሥቶ ከእስክንድርያ ወጣ ወደ ላይኛው ግብጽም ሔደ በዚያም ሕዝቡን እያስተማራቸው በቀናች ሃይማኖትም እያጸናቸው ጥቂት ቀኖች ኖረ። ንጉሥም አባ ቴዎዶስዮስ ከእስክንድርያ ከተማ እንደ ወጣ በሰማ ጊዜ እየሸነገለው ወደ እርሱ መልእክት ላከ እንዲህም አለው እኔ ከአንተ ጋራ ልነጋገር ከአንተም ልባረክ እንድትመክረኝም እሻለሁ"።
❤ ከዚህም በኋላ ወደ ቊስጥንጥንያ ከተማ ሔደ የጳጳሳት አለቆችና ሕዝቡ ሁሉ ሠራዊቱም ተቀበሉት ከፍተኛ ወንበርም ላይ አስቀመጡት። እርስ በርሳቸውም ስለ ሃይማኖት ተከራከሩ ንጉሡም አብዝቶ ሲሸነግለውና ሲአባብለው ሰነበተ ቅዱስ አባት ቴዎዶስዮስ ከቅዱሳት መጻሕፍት በመጥቀስ ይረታው ነበር። ከእርሱም ጋራ ባልተስማማ ጊዜ ከመንበረ ሢመቱ ወደ ላይኛው ግብጽ አሳደደው። በእርሱም ፈንታ ጳውሎስ የሚባለውን ሰው ሾመው።
❤ ጳውሎስም ወደ እስክንድርያ ከተማ በመጣ ጊዜ ሕዝቡ አልተቀበሉትም ዓመት ሙሉም ኖረ በእጁም ማንም ቊርባንን አልተቀበለም። ንጉሡም ይህን በሰማ ጊዜ ጳውሎስ እስከሚታዘዙ ድረስ አብያተ ክርስቲያናት እንዲዘጉ አዘዘ። ምእመናንም ከእስክንድርያ በመውጣት ወደ ቅዱስ ወንጌላዊ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ወደ ቆዝሞስና ድምያኖስ ቤተ ክርስቲያን ይሔዱ ነበር ካህናቱም በዚያ እየቀደሱ ያቆርኳቸው ነበር የአገር ልጆችንም የክርስትና ጥምቀትን ያጠምቋቸው ነበር።
❤ ንጉሡም ይህን በሰማ ጊዜ አብያተ ክርስቲያናትን እንዲከፍቱላቸው አዘዘ አባ ቴዎዶስዮስም ሰምቶ ንጉሡ እንዳያስታቸው ፈራ ማጽናኛ ቃልን የተመላች መልእክትም ጽፎ በቀናች ሃይማኖት እያበረታቸው ወደ ምእመናን ላካት እንዲህም አላቸው "በዚያ ጳውሎስ እንዳትታዘዙ ተጠበቁ"።
❤ ይህም አባት ሃያ ስምንት ዓመት በስደት ኖረ። መላው የሹመቱ ዘመን ሠላሳ ሁለት ነበር። ይኸውም በእስክንድርያ አራት ዓመት በስደትም ሃያ ስምንት ዓመት ነው።
❤ ይህም አባት ብዙ ድርሳናትን ደርሷል ምእመናንም በያዕቆብ ዘመን ያዕቆባውያን እንደ ተባሉ በስሙ ቴዎዶስዮሳውያን እየተባሉ ሲጠሩ ኖሩ። መልካም ጉዞውንም ፈጽሞ ሰኔ 28 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሰኔ 28 ስንክሳር።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #ቅዱስ_ያዕቆብ_ዘእልበረዲ (እል-በረዳይ) በተለይ በሃገራችን የተዘነጋ የሚመስለው የምሥራቅ ኮከብ_ ኮከበ ጽባሕ "ያዕቆብ" ለሚል ስም ትርጉምን የሰጡ አበው በ2 መንገድ ያትቱታል።
1.አኃዜ ሰኮና፦ነገሩ ከወልደ ይስሐቅ ወርብቃው ርዕሰ አበው ያዕቆብ ጋር የተያያዘ ቢሆንም አበው ግን ለትህትና ይተረጉሙታል።
2.አእቃጺ (አሰናካይ)፦ ነገሩ ስድብ (አሉታዊ) ይምሰል እንጂ በዚህ ስም የተጠሩ አበው ሁሉ ለአጋንንትና ለመናፍቃን ትልቅ መሰናክል ሆነውባቸው ኑረዋልና አባባሉ ምስጋና እንጂ ነቀፋን አይወክልም።
❤ የ6ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ምሥራቃዊ ኮከብ ቅዱስ ያዕቆብም ለመለካዊ መናፍቃንና ለተዋሕዶ ተገዳዳሪዎች ትልቅ መሰናክል ሆኖባቸዋል የቀናችውን ቀርነ ሃይማኖትንም አጽንቷል። ብዙ ጊዜ "ዘ"-እልበረዲ መባሉን ይዘው በ"ዘ" ምክንያት እልበረዲን እንደ ሀገር የቆጠሯት አልጠፉም በረከታቸው ይድረሰንና ትጉሑ ዻዻስ አቡነ ጐርጐርዮስ ካልዕ ግን ለዚሁ መላምት "የለም!" ባይ ናቸው። የቤተ ክርስቲያን ታሪክ በዓለም መድረክ' በተሰኝ ተወዳጅ መጽሐፋቸው "እል-በረዲ" ማለትን በዓረብኛ ከሠጋር በቅሎ ከሥሙር ሠረገላ ጋር አነጻጽረው አስቀምጠውታል። ለምን ቢባል እንደ ሠረገላ በተፋጠነ አገልግሎቱ ወዳጅንም ጠላትንም አስደምሟልና።
❤ ቅዱስ ያዕቆብ የተወለደው በ6ኛው መቶ ክ/ዘመን መጀመሪያ (በ500 አካባቢ) ሲሆን ያረፈው ደግሞ በ578 ዓ/ም እንደሆነ ይታመናል። ነገሩን ልብ ስንለው ቅዱስ ማኅሌታይ ያሬድን ወዲህ በዘመን ወዲያ ደግሞ በአገልግሎት ይመስለዋል። እርግጥ ነው ለውለታው የሶርያ ቤተ ክርስቲያን "ያዕቆባዊት" ስትባል የእኛዋስ ምናለ "ያሬዳዊት" ብትባል የሚል ቁጭትን ያመጣል። | 32 |
| 17 | No text... | 42 |
| 18 | ❤ አብርሃም የተባለው ደቀ መዝሙራቸውም ወደ ጉድጓዱ አብሯቸው በመግባት የአቡነ ክፍለ ሥላሴን እጆቻቸውንና እግሮቻቸውን በሰንሰለት ካሠራቸው በኋላ ወጣ፣ ጻድቁም እንዳዘዙት ጉድጓዱን ዘጉትና ሰው እንዳያውቀው አንድ ትልቅ መደብ ሠሩለት። ነገር ግን በማግሥቱ "ወዳጄ ክፍለ ሥላሴ ሆይ! ለምን እንደዚህ አደረግህ? አንተ ከዚህ ጉድጓድ ውስጥ ገብተህ ማነው ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን የሚያቀርብ? ማንስ ዕጣን ያጥናል? ስለዚህ አሁን ና ከዚህ ተነሥተህ ውጣ" የሚል ራእይ ተመለከቱ ወዲያውም የተዘጋው ጉድጓድ በተአምር ተከፈተ ታስሮ የነበረው እጅና እግራቸውም ሰንሰለቱ በተአምር ተፈታ። እርሳቸውም ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብተው በእጃቸው ሲያጨበጭቡ አስሯቸው የነበረው ልጃቸው ድምፅ ሰምቶ ሲመጣ አባታችንን ሲመለከት ደነገጠና "አባቴ ሆይ! ማን አወጣህ? ማንስ እጅህንና እግርህን ፈታህ" አላቸው። እርሳቸውም ለልጆቻቸው የሆነውን ሁሉ ነገሯቸው።
❤ አቡነ ክፍለ ሥላሴ ደብረ መድኀኒት ብለው በሰየሟት ገዳማቸው ባምብቆ አካባቢ የከብት በሽታ (ጉልሓይ) ተከስቶ ነበር ነገር ግን ያንን በሽታ ያመጣውን ክፉ ሰይጣን ጻድቁ በጸሎታቸው ኀይል እያስጮኹ አባረው ጣሉት፤ ድምፁንም ሰምተው የአካባቢው ሰዎች ጠላታቸው እንደወደቀ ዐውቀው ከብቶቻቸውም ጤነኞች ስለሆኑላቸው የአቡነ ክፍለ ሥላሴን አምላክ አመሰገኑ።
❤ ጻድቁ የተሰወረውን ሁሉ ያውቁ ነበር፤ አንድ ቀን ወደ ቤተ ክርስቲያን መሔድ የማያስችል ሕማም አጋጠማቸውና በእርሳቸው ፋንታ አንድ እግሩን የሚያመው ወዳጃቸውን ሔዶ ዕጣን እንዲያጥን ነገሩት። እርሱም ሔዶ ግድግዳውን ተጠግቶ በሰሜንና በደቡብ አጥኖ በምዕራንና በምሥራቅ ሳያጥን ተመልሶ ሊጠይቃቸው ሲመጣ አባታችንም "አንተ ወንድሜ ስለምን እንደዚህ ታደርጋለህ? ለምን እንደአባቶቻችን አድርገህ በምዕራብና በምሥራቅ አላጠንክም?" አሉት ይህንንም ሲሰማ ያ ካህን ደንግጦ በሠራው ስሕተት ንስሓ ገባና እግዚአብሔርን አመሰገነ።
❤ በመጨረሻም የአቡነ ክፍለ ሥላሴ ጊዜ ዕረፍታቸው ሲደርስ ለአንድ ወዳጃቸው ለሆነ ካህን "ወንድሜ ሆይ! እኔ ማክሰኞ ቀን በአባታችን በአብርሃም በዓል ዕለት እሞታለሁ" በማለት የሚያርፉበትን ቀን ነገሩት። በተናገሩትም መሠረት ከምንኵስናቸው በፊት 20 ዓመት ከምንኩስናቸው በኋላ 8 ዓመት ኖረው በ28 ዓመታቸው ሰኔ 28 ቀን በዕለተ ማክሰኞ ዐረፉ። ጻድቁ ራሳቸው በተከሏትና በጸለዩባት በደብረ መድኀኒት ቅድስት ሥላሴ ባምብቆ ከተቀበሩ በኋላም ብዙ ተአምራት አድርገዋል። ዝክራቸውን ያደረገ በጸሎታቸው የተማጸነ በዚህ ዓለም ከመከራ ሥጋ፣ በሚመጣውም ዓለም ከመከራ ነፍስ እንደሚድን ጌታችን በአምላካዊ ቅዱስ ቃሉ ቃልኪዳን ስለገባላቸው የባምብቆ ሕዝብና የዛውል ሕዝብ ሰኔ 28 ቀን በዓላቸውን በታላቅ ክብር ያከብራሉ። ከአቡነ ክፍለ ሥላሴ ዘዛውል ወዘባንብቆ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከት ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን መጽሐፍ። | 39 |
| 19 | ❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን" ❤
❤ #ሰኔ ፳፰ (28) ቀን።
❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ የእግዚአብሔር ከተጠራባቸው በፍርሀት ይታዘዙ ለነበሩት፤ ዳግመኛም ለነቢዩ ዕዝራ ታቦተ ጽዮን ባዘነች ሴት አምሳል እንደታየችው እንዲሁ ለአባታችንም አንዲት ያዘነች ሴት በራእይ መጥታ ዕጣን በማይታጠንበትና መሥዋዕተ ቍርባን በሌለበት ቦታ እንደ ሽኮኮ በጉድጓድ ውስጥ እንዳስቀመጧት ለነገረቻቸው #አቡነ_ክፍለ_ሥላሴ_ዘዛውል_ወዘባንብቆ_ዕረፍታቸው_በዐል እግዚአብሔር አምላከ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #አቡነ_ክፍለ_ሥላሴ_ዘዛውል_ወዘባንብቆ፦ ከአባታቸው ከተክለ ማርያም ወልደ ዘኪዎስ እና ከእናታቸው ከርግበ ዳዊት ዛውል በሚባለው ቦታ ተወለዱ። በመጀመሪያ የወጣላቸው ስም "መሓርየ እግዚ" የሚባል ነው። አእምሮአቸው ንጹሕና ብሩሕ የሆኑት አቡነ ክፍለ ሥላሴ በልጅነታቸውም በጎችንና ፍየሎችን እያገዱ (እየጠበቁ) ወላጆቻቸውን ያገለግሉ ነበር።
❤ አቡነ ክፍለ ሥላሴ በእናታቸው ማሕፀን ሳሉ የተመረጡ ስለነበሩ እግዚአብሔርን በመፍራት ይታወቁ ነበር ስመ ሥላሴን በከንቱ አያነሡም ነበር። ስመ እግዚአብሔርም ከተጠራባቸው በፍርሃት ይታዘዛሉ። እረኞችም ከብቶቻቸውን እንዲመልሱላቸው የእግዚአብሔርን ስም ከጠሩባቸው ይታዘዟቸው ነበር። በዚኸም ነገር አቡነ ክፍለ ሥላሴ ታላቁን ጻድቅ አቡነ ዐቢየ እግዚእን መሰሉ።
❤ በትግራይና በጎንደር በእጅጉ የሚታወቀው ታላቁ ጻድቅ አቡነ ዐቢየ እግዚእ ገና ከልጅነቱ ጀምሮ የእግዚአብሔርን ስም ከጠሩበት ምንም ነገር ከማድረግ ወደኋላ አይልም ነበር። ከልጆችም ጋር ሲጫወቱ ልጆቹ "ስለ እግዚአብሔር ብለህ ይህን አድርግልን" ሲሉት ያደርግላቸዋል። በእረኝነት ሳሉ ምሳውንም ሆነ እራቱን ለምስኪኖች ይሰጣል። ለእግዚአብሔር ስም እጅግ ቀናተኛ ስለነበረ ስሙን በመፍራት ስመ እግዚአብሔርን ጠርተው "ይህን ክፉ ነገር በራስህ ላይ አድርግ" ባሉት ጊዜ እንኳን በራሱ ላይ አንዳች ክፉ ነገር ወይም አደጋ ለማድረስ ወደኋላ አይልም ነበር። ይህንንም ሊፈትኑት ብለው አንድ ቀን ስለታም ጦር አምጥተው "ስለ እግዚአብሔር ብለህ እስቲ ራስህን በዚህ ስለታም ጦር ትወጋ ዘንድ ና" ባሉት ጊዜ አብርሃም ልጁን ይስሐቅን ሊሠዋ በሕሊናው እንደወሰነ እርሱም በቁርጥ ሕሊና ሆኖ ራሱን በጦሩ ሊወጋ ሲል ዘለው ያዙት።
❤ በሌላም ጊዜ እንዲሁ ሊፈትኑት በጭነት ምክንያት ጀርባው የቆሰለ አህያ አምጥተው ዐቢየ እግዚእ "ስለ እግዚአብሔር ብለህ የዚያችን አህያ ቁስሏን ላስ" አሉት። እርሱም ያን ጊዜ "ርኩስን ብስም ኃጢአት ይሆንብኛል፣ አይሆንም ካልኳቸው ደግሞ ስመ እግዚኣብሔርን ጠርተንበት እምቢ አለ ስለሚሉ የፈጣሪዬን ስም መዳፈር ይሆንብኛል" ብሎ በልቡ አሰበና ያን ጊዜ ይስም ዘንድ ተመለሰ። ባልንጀሮቹም በቁርጥ ሕሊናው እንደወሰነ ባወቁ ጊዜ ሊያደርገውም ሲሔድ ተመልክተው ቶሎ ብለው ሮጠው ከኋላው ያዙት። እርሱም "እኔስ የፈጣሪዬን ስም እፈራለሁ ስሙን ተደፋፍሬ በምድር በሕይወት ከምኖር ሞት ይሻለኛል" አላቸው። አቡነ ክፍለ ሥላሴም እንዲሁ በፈሪሃ እግዚአብሔር ይታወቃሉ። ስመ ሥላሴን በከንቱ ፈጽመው ጠርተው አያውቁም፣ ስመ እግዚአብሔር ከተጠራባቸው ማንኛውንም ነገር ያደርጉ ነበር።
❤ ከዚኸም በኋላ አቡነ ክፍለ ሥላሴ ወደ አቡነ ሳሙኤል ገዳም ደብረ ዓባይ ሔደው በሚያስደንቅ ትሕትና ለአባቶች እየታዘዙ መዝሙረ ዳዊትን ተማሩ፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን አጠኑ። ከዚያም የአባቶችን ቡራኬ በመቀበል ወደ ደብረ ቢዘን በመሔድ የአቡነ ፊሊጶስንና የአቡነ ዮሐንስን ልጆች በማገልገል የቅዱሳኑን አሠረ ፍኖታቸውን ተከትለው በተጋድሎ ኖሩ። ሌሊትና ቀን በእያንዳንዱ ሥርዓተ ጸሎት ላይ አንድ አንድ ሺህ እየሰገዱ ይጸልዩ ስለነበር የእንቅልፍና የዕረፍት ጊዜ አልነበራቸውም። በእንደዚህም ዓይነት ተጋድሎ ከቆዩ በኋላ ከአቡነ ፊሊጶስ 6ኛ አበ ምኔት ከሆኑት ከአባ ገብረ ማርያም እጅ ምንኵስናን ተቀበሉ።
❤ ከመነኰሱም በኋላ መነኰሳቱ እህል እንዲፈጩ ሲያዟቸው አባታችን ክፍለ ሥላሴ በመታዘዝ ወደ እህል መፍጫው ቤት ገቡ፣ ነገር ግን አባታችን እህል መፍጨት አይችሉም ነበር። እርሳቸውም ወደ እግዚአብሔር ቢጸልዩ ሁሉም ሊፈጭ ተዘጋጅቶ የነበረው እህል በተአምራት ተፈጭቶ ተገኘ። መነኰሳቱ ግን ይህን አላወቁም ነበር።
❤ አቡነ ክፍለ ሥላሴ ከዚኽ በኋላ ወደ ሀገረ ደምብያ ሔደው ከጳጳሱ እጅ ሥልጣነ ክህነትን ተቀበሉ። ከዚያም ሲመለሱ መረብ ወንዝ ሲደርሱ አብሯቸው የነበረውን የሥጋ ወንድማቸውን "ኦ ወንድሜ እነሆ በሥጋ የወለደን አባታችን ዛሬ ዐረፈ" በማለት የአባታቸውን መሞት በመንፈስ ቅዱስ ዐውቀው ነገሩት ወደ ሀገራቸውም ከገቡ በኋላ የሀገራቸው የውል ሰዎች ያላወቁ መስሏቸው የአባታቸውን መሞት ለአቡነ ክፍለ ሥላሴ ነገሯቸው። አባታችንም "አባቴ እንደሞተ አስቀድሜ ዐውቄያለሁ፤ እግዚአብሔር ወደ ገነት እንዲያስገባው በጸሎት አግዙኝ እንጂ አታልቅሱ" አሏቸው። ሰዎቹም የተሰጣቸውን ጸጋ አድንቀው እግዚአብሔርን አመሰገኑ።
❤ ጻድቁ ወደ ደብረ ቢዘን ተመልሰው ሔደው በክህነት እያገለገሉ ሳለ ወደ አቡነ እንድርያስ ሰፍኣ ደብረ ጽጌ ገዳም ለመሔድ አሰቡ፤ ነገር ግን ትልቅ ዋርካ ያለበትን ባምብቆ የተባለውን ተራራ በራእይ ከተመለከቱ በኋላ ወደዚያ እንዲሔዱ እምላካዊ መልእክት መጣላቸው። እርሳቸውም የመንፈስ ቅዱስን ፈቃድ በደስታ ተቀብለው ወደ ባምብቆ በመሔድ ቤተ ክርስቲያን አንጸው የቅድስት ሥላሴን ታቦት አስገብተው በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመሩ፤ በርካታ ደቀ መዛሙርትንም አፈሩ።
❤ አቡነ ክፍለ ሥላሴ በባምብቆ ሳሉ ታቦተ ጽዮን ለነቢዩ ዕዝራ ባዘነች ሴት አምሳል እንደታየችው እንዲሁ ለአባታችንም አንዲት ያዘነች ሴት በራእይ መጥታ ዕጣን በማይታጠንበትና መሥዋዕተ ቍርባን በሌለበት ቦታ እንደ ሽኮኮ በጉድጓድ ውስጥ እንዳስቀመጧት ነገረቻቸው። በዚያም በበረሓ ውስጥ ደብቀው ያስቀመጧት ዮልዮስ የተባለ አንድ አመጸኛ መኰንን ቤተ ክርስቲያንን ሊያቃጥል በፈለገ ጊዜ ነው። አቡነ ክፍለ ሥላሴም ወደተነገራቸው ቦታ በመሔድ ካህናቱን በጉድጓድ ውስጥ ስላስቀመጡት ታቦት ሲጠይቋቸው እነርሱ ግን "የደበቅነው ታቦት የለንም" አሏቸው። አባታችንም "ወንድሞቼ ሆይ! እውነቱን ተናገሩ" በማለት በራእይ የተመለከቱትን ነገር ነገሯቸው። ካህናቱም ፈርተው "አዎን አባታችን ይቅር በሉን፣ ዮልዮስን ፈርተን ታቦቱን ዋሻ ውስጥ ደብቀነዋል" ብለው ቦታውን አሳዩአቸውና አውጥተው ወደ ቤተ ክርስቲያን መለሱት።
❤ ከዚህም በኋላ አቡነ ክፍለ ሥላሴ በገዳማቸው በጽኑ ተጋድሎ ላይ ሳሉ የጌታችን ጾም በደረሰ ጊዜ ልጆቻቸውን ጠሩና "ሰባት ክንድ የሚሆን ጉድጓድ ቆፍራችሁ እኔ እዚያ ውስጥ ከገባሁ በኋላ ጉድጓዱን ሸፍኑት፣ ከላይ የዕንጨት ሰሌዳ አድርጋችሁ በድንጋይና በጠጠር አድርጋችሁ በመቃብር ምልክት ዝጉት" በማለት ነገሯቸው። ዳግመኛም "ሰዎች የት ናቸው? ብለው ቢጠይቋችሁ የት እንዳለ አናውቅም በሏቸው፤ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ሲሆን ግን ከፍታችሁ አረጋግጡ" አሏቸው። | 27 |
| 20 | No text... | 24 |
