Fuad Mohammed
Open in Telegram
قناة لفوائد متنوعة (Barnootaafii muhaadaraa oromiffaa garaagaraa) Yaadaaf @FuadMohammed
Show more4 963
Subscribers
+14924 hours
+3047 days
+44530 days
Posts Archive
4 962
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
📢 ልዩ የቀጥታ ስርጭት ፕሮግራም!
❝ሰይድ ቁጥብ ማን ነው? ለተሳሳቱ ውዳሴዎችና ማደናገሪያዎች የሚሰጥ ምላሽ❞
🎙 አቅራቢ፦ ኢብኑ ሙነወር
🗓 ቀን፦ ነገ ማክሰኞ
⏰ ሰዓት፦ ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ
◇ የቀጥታ ስርጭት አድራሻ👇
t.me/IbnuMunewor
t.me/IbnuMunewor
4 962
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
"በሰሞኑ የሰይዪድ ቁጥብ ጉዳይ ከተመቸኝ ዛሬ ከመግሪብ በኋላ በድምፅ ለመግባት አስቤያለሁ" ብዬ ነበር። አሁን ላይ ስላልቻልኩኝ ከቻልኩ ምሽት 3:00 ላይ በቴሌግራም ቻናሌ ( https://t.me/IbnuMunewor ) በቀጥታ (live) ለማቅረብ እሞክራለሁ ኢንሻ አላህ።
4 962
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የዐቂዳ መሰረታዊ እውቀትን የማስጨበጥ ፕሮግራም
~
ፕሮግራሙ የተዘጋጀው الجمعية العلمية السعودية لعلوم العقيدة والأديان والفرق والمذاهب ነው። ማህበሩ በመሰረታዊ የዐቂዳ ትምህርቶች እና የተለያዩ አፈንጋጭ አመለካከቶች ላይ ጥናት በማካሄድ ላይ የተሰማራ የሳዑዲ ድርጅት ነው። ሸይኽ ሷሊሕ ሲንዲ የዚህ ማህበር ሊቀመንበር ሆነው ያገለገሉ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት አባል ናቸው።
የምትችሉ ብተመዘገቡ ትጠቀማላችሁ ኢንሻአላህ።
ለአንድ ዓመት የሚቆይ የዓቂዳ ትምህርት ነው።
በማሰራጨት የኸይር ሰበብ ሁኑ ባረከላሁ ፊኩም።
4 962
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የምትችሉ በተመዘገቡ ትጠቀማላችሁ ኢንሻአላህ።
ለአንድ ዓመት የሚቆይ የዓቂዳ ትምህርት ነው።
በማሰራጨት የኸይር ሰበብ ሁኑ ባረከላሁ ፊኩም።
◼️ الجمعية العلمية السعودية لعلوم العقيدة والأديان والفرق والمذاهب تدعوكم للمشاركة في:
📄 برنامج (التأصيل العقدي) لعام ١٤٤٨هـ
4 962
አስቸኳይ የሕክምና ሪፖርት
ቀን: ኦገስት 24, 2026 እ.ኤ.አ.
የታካሚዋ ስም: ሀናን አህመድ
የሕክምና ቦታ: መካ ሆስፒታል
የጤና ሁኔታ እና የምርመራ ዝርዝር:
የቀድሞ ህክምና ዓይነት: ታካሚዋ ቀደም ሲል ሶስት (3) የቀዶ ሕክምናዎችን አድርጋለች።
አሁን ያለችበት ሁኔታ: የቀዶ ሕክምናው ቦታ በጣም አሳሳቢ፣ ተነካኪ እና በከፍተኛ ደረጃ አስቸጋሪ (አስጊ) ሁኔታ ላይ ይገኛል።
አደጋው: የቀዶ ሕክምናውን ቦታ ለመነካካት፣ ለመክፈት ወይም ፈሳሽ ለመጭመቅ/ለማፍሰስ የሚደረግ ማንኛውም ሙከራ ቀጥተኛ አደጋ የሚያስከትል እና በህይወቷ ላይ እውነተኛ ስጋት የሚፈጥር ነው።
የሕክምና ማስታወሻዎች: በቀዶ ሕክምናው ቦታ ላይ የደም እና የነጭ ደም (መግል) ስብስብ አለ፤ በመሆኑም አሁን ባለው ሁኔታ ቦታውን መነካካት ወይም የቀዶ ሕክምና ጣልቃ ገብነት ማድረግ እጅግ አደገኛ በመሆኑ ሁሉም ሰው እንዳይነካው ይሰጋል።
ኑ እህታትን እነተባበራ በዚህመም ምክንያት ምንም ነገር እንዳሰሪ ስለተባለች ወደ ሀገር መግባት ትፈልጋለች ህግ ውጥ ናት ፡
ለዚህም ወደ ሀገር ለመግባት
ወረቀት ያስፈልጋታ
የአየር ትኬት ያስፈልጋታል
9.000ሺርያል እዳ አለባት
ከዚህ በፊት በነበራት ሶስትጊዜ ኦፕሬሽን 25.000ርያል አውጥታለች በዚህም ምክንያት እዳ፡ገባች ፡ይሄ ሁሉ መነሻው ደም ማነስ ፡ነው በሁለት ወር ውስጥ ነው ሁሉም ነገር የተቀያየረው ፡ ሌላ አማራጭ ስለሌ ብቻ ነው ፡
"ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው፣ ያንን መልካም ስራ እንደሰራው ሰው አይነት ምንዳ (አጅር) አለው።"
አካውት እህታችንን ለመርዳት
ንግድ ባንክ፡1000586128977
አሚነት ጡሃ ዑመር
https://t.me/+pT5OceZcGRU3ZDNk
4 962
عشرون وصية في دعوة الكفار – موقع الإسلام العتيق
https://www.islamancient.com/%D8%B9%D8%B4%D8%B1%D9%88%D9%86-%D9%88%D8%B5%D9%8A%D8%A9-%D9%81%D9%8A-%D8%AF%D8%B9%D9%88%D8%A9-%D8%A7%D9%84%D9%83%D9%81%D8%A7%D8%B1/
4 962
Repost from قناة عبد القادر الجنيد العلمية
💎 رسالة بعنوان:
«أمور لا تُغفَل ويُتنبَّه لها عند القراءة في باب الرُّدود والدفاع عن أهل العلم وطلابه».
✏️ كتبها:
عبد القادر الجنيد.
4 962
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የአካል ጉዳት ሊደርስ የሚችልበት፣ ከዚህም አልፎ ህይወት የመጥፋት አደጋ ያለበት ስፖርት በኢስላም የተከለከለ ለመሆኑ የቁርኣንና የሐዲሥ ማስረጃዎች እና አጠቃላይ የሸሪዐ መርሆዎች አጉልተው ያሳያሉ። እንዲህ አይነት ስፖርታዊ ውድድር እንደማይፈቅድ የሚገልፁ የዑለማእ ፈትዋዎችንም ማየት እንችላለን። ይሄ እውነታ በተለያዩ አካላት ሲገለፅ ስለነበር ከሞላ ጎደል ግልፅ ይመስለኛል። ስፖርቱ የሚታወቅባቸው አላስፈላጊ ስድድቦች፣ ጉራዎች፣ ውሸቶች ሲጨመሩ ደግሞ ጥፋቱ ከፍ ይላል። ተወዳዳሪዎቹ ሴቶች ሲሆኑ ደግሞ የበለጠ ይብሳል።
እዚህ ድረስ ያለው ሐቅ ለአብዛኛው ሙስሊም የሚሰወር ባይሆንም እጅግ ብዙ ወገን በተለያዩ መንገዶች ለግርግሩ ድምቀት እየሰጠ ነው። ቀላል የማይባል አካል ደግሞ ተሳታፊዎቹ ባልተፈቀደ ተግባር ላይ የተሰማሩ ሳይሆን ትልቅ ገድል የፈፀሙ ያክል ሃይማኖታዊ ውግንና እያሳየ ነው። አንድ ነገር በኢስላም የማይፈቀድ ከሆነ በሃይማኖትም፣ በሃገርም፣ በብሄርም፣ በአካባቢም ፣ በፆታም መነፀር እየተመለከትን ልንወግን አይገባም። የማይፈቀድ ከሆነ በቃ አይፈቀድም።
ያልተፈቀደን ነገር ለመመልከት ገንዘብ ማውጣት፣ ያልተፈቀደን ነገር በሚያበረታታ መልኩ ድርጅቶችን ማስተዋወቅ አብሮ የማይፈቀድ ተግባር ነው። ሌላው ጊዜያችንን፣ ገንዘባችንን፣ ትኩረታችንን የምንሰጠው ምሳሌ ለሚሆነንና ከኛ የሚሻል ጉዳይ ላይ ለሚሰማራ አካል ነው።
በተረፈ ጤናን ለመጠበቅ እና ከራስ ላይ ለመከላከል አካልን ብቁ የሚያደርጉ የ"ስፖርት" አይነቶችን መሰልጠን ጥሩ ነው። ይሄኛው ቀደም ብዬ ከገለፅኩት የሚለይ ነው።
በመጨረሻም በቦክስና መሰል ስፖርታዊ ውድድሮች ላይ የደረሱ የነፍስ መጥፋቶችና ቋሚ ጉዳቶችን መጥቀስ ፈልጌ ጄሚናይን ጠይቄ ነበር። ያገኘሁት እንደወረደ የሚከተለውን ይመስላል:-
በቦክስና በሌሎች መሰል ከባድ የውጊያ ስፖርቶች (እንደ MMA/Mixed Martial Arts ያሉ) ላይ በውድድር እና በልምምድ ወቅት የሚደርሱ የነፍስ ማለፍና ከፍተኛ ቋሚ የአካል/የአእምሮ ጉዳቶች አሉ።
የነፍስ መጥፋት (ሞት)
* በቦክስ፡ በቦክስ ታሪክ ውስጥ በመቶዎች የሚቆጠሩ ተወዳዳሪዎች በጨዋታ ወቅት ወይም ከጨዋታ በኋላ በተከሰተ የጭንቅላት ጉዳት ሕይወታቸውን አጥተዋል። ለምሳሌ ያህል፡
* ዱክ ኩ-ኪም (Duk Koo Kim - 1982)፦ የደቡብ ኮሪያው ቦክሰኛ ሬይ ማንሲኒን በተጋጠመበት ጨዋታ ላይ በደረሰበት የጭንቅላት ደም መፍሰስ ምክንያት ሕይወቱ አልፏል። ይህ አደጋ ዓለም አቀፉ የቦክስ ማህበር የዙር ብዛትን ከ15 ወደ 12 እንዲቀንስ ትልቅ ምክንያት ሆኗል።
* ፓትሪክ ዴይ (Patrick Day - 2019)፦ አሜሪካዊው ቦክሰኛ በውድድር ወቅት ባጋጠመው ከባድ የጭንቅላት ጉዳት (Traumatic Brain Injury) ምክንያት ሕይወቱ አልፏል።
* በሌሎች ስፖርቶች፦ በኤምኤምኤ (MMA)፣ በሙአይ ታይ (Muay Thai) እና በባዶ እጅ ውጊያዎች (Bare-knuckle boxing) ላይም ተመሳሳይ የነፍስ ማለፍ አደጋዎች ተመዝግበዋል።
ቋሚ እና የረጅም ጊዜ ጉዳቶች
* የአእምሮ እና የነርቭ ጉዳት (Chronic Traumatic Encephalopathy - CTE)፦ በየጊዜው በጭንቅላት ላይ በሚያርፉ ጠንካራ ምቶች ምክንያት የሚከሰት የረጅም ጊዜ የአእምሮ ጉዳት ነው። ይህም የማስታወስ ችሎታ ማጣት፣ ድብርት፣ የባህሪ ለውጥ እና የነርቭ መታወክ ያመጣል።
* ቦክሰኛ ዲሜንሽያ (Punch-Drunk Syndrome / Dementia Pugilistica)፦ በብዙ የቦክስ ተወዳዳሪዎች ላይ የሚታይ ሲሆን፣ የመናገር ችግርን፣ የእጅ መንቀጥቀጥን (እንደ ፓርኪንሰን በሽታ) እና የእንቅስቃሴ መዛባትን ያስከትላል።
* የዓይን እና የአካል ጉዳቶች፦
* የዓይን ሌንስ መንሸራተት ወይም የሬቲና መቀደድ (Retinal Detachment) እስከ ሙሉ እይታ ማጣት የሚያደርስ ቋሚ ጉዳት ያስከትላል።
* የፊት አጥንቶች ስብራት፣ የጆሮ ቅርጽ መበላሸት (Cauliflower Ear) እና የቋሚ መንጋጋ ጉዳቶች።
* የውስጥ አካላት (እንደ ኩላሊት እና ጉበት) ደም መፍሰስ እና ስብራት።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
4 962
ይህን የተባረከ ቻናል እንድትከታተሉ እመክራችኋለሁ። ይህ ቻናል ከክፉ ምኞቶችና ልብን ከሚያበላሹ ስሜቶች የሚያስጠነቅቅ፣ ነፍስንም የሚያጠራ ነው። ወንድማችን ወጣቱ ኡስታዝ አቡ ሱፍያንም በዚህ መስክ በጣም ጠቃሚ ከሆኑ ወንድሞች አንዱ ነው። አላህ በእርሱ እኔንም እናንተንም ይጠቅመን፣
ቻናሉን በቲክቶክ እንዲሁም በኢሞ (imo) መተግበሪያ መከታተል ትችላላችሁ።
4 962
📓በለይላ ፍቅር ያበደው ሰው!
(የመጅኑን ለይላ አስገራሚ ታሪክ)
🎥ልዩ የቀጥታ ስርጭት (TikTok Live)
✅ ከ«መጅኑን ለይላ» ታሪክ የምንማራቸው ትልልቅ ቁምነገሮች፤
✅ ከሐራም ፍቅር ጋር የተያያዙ አንገብጋቢ ነጥቦችና አደጋዎች፤
✅ ልባችንን ካልተፈቀደ ሐራም ፍቅር እንዴት እንጠብቅ?፤
✅ በሐራም ፍቅር ለተያዙ ሰዎች ተግባራዊ የመውጫ መፍትሔዎች እና ሌሎች ነጥቦችን እንዳስሳለን...
🗓ቀን፦ እሁድ፣ ነሐሴ 17
⏰ ሰዓት፦ ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ
🎙️ አቅራቢ፦ ወንድም አቡ ሱፍያን
🔠---በቲክ ቶክ---👇👇
https://www.tiktok.com/@sle_qelbachn1?_r=1&_t=ZS-992wv4fSSc0
4 962
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ለምንድን ነው የመውሊድ ተቃውሞ ኢኽዋኖችን ምቾት የሚነሳቸው?
~
በርካታ የኢኽዋነል ሙስሊሚን አስተሳሰብ አራማጆች በመውሊድ ቢድዐ ላይ የሚደረገው ዘመቻ ክፉኛ ሲረብሻቸው ይታያሉ፡፡ አብዛኛው የመውሊድ አፈፃፀም ውስጥ ሺርክ እንዳለበት እያወቁ "ለምን በትንንሽ ነገሮች እንጨቃጨቃለን?" ይላሉ። የሺርክ ጉዳይ ለነሱ ከትንንሽ ነገሮች ውስጥ ነው። የተውሒድ ዋጋው ከነሱ ቡድናዊ አላማ በታች ነው። ራሳቸውን መካከለኛ ለማድረግ የመውሊድ ፅንፈኛ ደጋፊዎችን በስሱ ከነኩ በኋላ (እሱም ከስንት አንዴ ከኖረ ነው) ያለ የሌለ ሃይላቸውን መውሊድን በሚነቅፉት ላይ ነው የሚያደርጉት፡፡ መውሊድ ላይ የሚሰነዘረው ተቃውሞ ክፉኛ እንዲረብሻቸው የሚያደርጓቸው ብዙ ምክንያቶች አሉ፡፡ ለምሳሌ ያክል፡-
1. ኢኽዋነል ሙስሊሚን እንደ ቡድን መሰረቱ ሱፊያ ነው፡፡ የቡድኑ መስራች ሐሰን አልበና የሻዚሊያ ጦሪቃ ቅርንጫፍ የሆነው የ“ሐሷፊያ ጦሪቃ” ተከታይ የነበረ ሲሆን ራሱ እንደገለፀው “የሐሷፊያን አስተሳሰብ የጠገብኩ ሆኜ ወደ ደመንሁር ወረድኩ” ይላል፡፡ [ሙዘኪራቱ ዳዕዋ ወዳዒያ፡ 31 - 34] ከቡድኑ አመራሮች አንዱ የሆነው ሰዒድ ሐዋ “የኢኽዋነል ሙስሊሚን ንቅናቄ ራሱ ሱፊ ነው የመሰረተው፡፡ አሉታዊ ጎኖቹን በመተው የተሶውፍን እውነታ ወስዷል” ይላል፡፡ [ጀውለቱን ፊል ፊቅሀይን፡ 154]
አንዳንዶች ይሄኛው አቋሙ ከመመለሱ በፊት የነበረበት ነው ቢሉም እውነታው ግን እንደዚያ አይደለም። እስከ ፍፃሜው ተሶውፍ ላይ እንደዘለቀ ታላላቅ የኢኽዋን ቁንጮዎች መስክረዋል፡፡ ስለዚህ ዛሬ የኢኽዋን ፀሐፊዎች በተለያየ ስልት ከሱፍዮች የሚከላከሉት ከራሳቸው፣ ከመሪዎቻቸው እና ከቡድናቸው ለመከላከል ነው፡፡ ሱፍያ ተነካ ማለት ኢኽዋን ተነካ ማለት ነው፡፡ ሙስሊሞች ሱፍያን ተፀየፉ ማለት የኢኽዋን መሰረቱ ተናጋ ማለት ነው፡፡
አንዳንዶች “እነሱ ነፍስን ማጥራት ላይ የሚያተኩረውን፣ ንፁሁን ተሶውፍ ነው የተከተሉት” ይላሉ፡፡ እውነታው እንደዚያ እንዳልሆነና ተሶውፍን ከነሺርኩ ከነ ግሳንግሱ የሚያራምዱ እንደሆኑ በተከታዮቹ ነጥቦች የምናይ ይሆናል።
2. የቡድኑ መስራች ሐሰን አልበና ረቢዑል አወል አንድ ካለ ጀምሮ እስከ 12 ድረስ መውሊድን ያከብር እንደነበር ራሱ ፅፏል፡፡ [ሙዘኪራ፡ 58] ዛሬም ድረስ ለመውሊድ ሽንጣቸውን ገትረው የሚሟገቱ ኢኽዋኖችን የምናየው ያለ ምክንያት አይደለም፡፡
3. በርካታ ሱፍዮች ዘንድ ነብዩ ﷺ ከመውሊዱ ጭፈራ ላይ ይገኛሉ ተብሎ ይታመናል፡፡ ነብዩ ﷺ ፈፅሞ ከእንዲህ አይነቱ የባእድ አምልኮ ድግስ ላይ አይገኙም፡፡ ይሄ ቅጥፈታዊ እምነት በኢኽዋነል ሙስሊሚን መስራቹ ሐሰን አልበናም ጭምር ሲስተጋባ የነበረ ነው፡፡ ይሄው እነ ሐሰን አልበና መውሊድ ላይ ሲያንጎራጉሯቸው ከነበሩ ስንኞች ውስጥ እንዲህ የሚል ይገኝበታል፡-
هذا الحبيب مع الأحباب قد حضرا …
… لا شك أن حبيب القوم قد حضرا
“ይህ ወዳጃችን (ነብዩን ነው) ከወዳጆች ጋር ተገኝቷል።
…
… ያለጥርጥር የሰዎቹ ወዳጅ ተገኝቷል፡፡” [ሐሰን አልበናህ ቢአቅላሚ ተላሚዘቲሂ ወሙዓሲሪሂ፡ 71-72]
ይህ እምነት ዛሬም ድረስ ከሱፍዮች ዘንድ በሰፊው ያለ ነው፡፡ በመውሊድ ጭፈራቸው መሃል መብራት አጥፍተው ነብዩ መጡ ይሉና “መርሐባ ነቢ መርሐባ! መርሐባ!” እያሉ ይዘፍናሉ፡፡ በዚህን ጊዜ ታዳሚው እንዳለ ይቆማል፡፡ ክቡሩ ነቢይ ﷺ የነሱን በሺርክ የተጨማለቀ፣ በውዝዋዜ የታጀበ ድግስ ሊታደሙ መሆኑ ነው፡፡ “አይ ይሄ'ኮ ስማቸው ሲወሳ ለአክብሮት ያክል የሚፈፀም እንጂ ቦታው ላይ ይገኛሉ ተብሎ አይደለም” የሚል ሊኖር ይችላል፡፡ ቦታው ላይ ይገኛሉ የሚል እምነት እንዳለማ ይሄው የሐሰን አልበናን ንግግር አጣቀስኩልህ፡፡ በሃገራችንም በሰፊው የሚታወቅ እምነት ስለሆነ መወሻሸት አያስፈልግም፡፡ ደግሞስ በየደዕዋው ላይ፣ በየ መስጂዱ፣ በየ መድረኩ ስማቸው ሲወሳ ትቆማላችሁ እንዴ? ውሸት!
በነገራችን ላይ ነብዩ ﷺ በህይወት ሳሉ ማንም እንዲቆምላቸው አይወዱም ነበር፡፡ አነስ ብኑ ማሊክ ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ይላሉ፡- “እነሱ (ሶሐቦች) ዘንድ ዱንያ ውስጥ እንደ ነብዩ ﷺ ሊያዩት የሚወዱት ሰው አልነበራቸውም፡፡ ሆኖም ግን መጥላታቸውን ስለሚያውቁ ለሳቸው አይቆሙም ነበር፡፡” [አሶሒሐህ፡ 358]
ሌላ በነገራችን ላይ! ይህንን ነብዩ መጡ እያሉ መነሳትን - የሚሰማ ጠፋ እንጂ - ከመውሊድ አክባሪዎች ውስጥ ሳይቀር የኮነኑት ነበሩ፡፡ ሀይተሚ እንዲህ ይላል፡-“የዚህ አምሳያው ብዙዎች የነብዩ ﷺ ልደትና እናታቸው እሳቸውን መውለዷ ሲወሳ የሚያደርጉት መቆም ሲሆን ይህም ምንም አይነት መረጃ ያልመጣበት ቢድዐ ነው፡፡ ሰዎች ይህን የሚያደርጉት እሳቸውን ﷺ ለማላቅ ነው፡፡ መሃይማኑ ከአዋቂዎቹ በተለየ በዚህ ድርጊታቸው ይታለፋሉ (መዕዙሮች ናቸው፡፡)” [አልፈታዋ አልሐዲሢያህ፡ 58]
4. መውሊድን ያክል እጅግ በርካታ ቢድዐዎችን አቅፎ የያዘን ቢድዐ አቅልሎ ማቅረብ ቡድናዊ ስሜት እየጋረዳቸው እንጂ ላስተዋለ ሁሉ በቀላሉ የሚታይ ነው፡፡ በስፍራዎቹ የሚፈፀሙትን አላስፈላጊ የወንድና የሴት ቅልቅል፣ በመስጂድ ውስጥ መጨፈር፣ መስጂዶችን በጫትና በተረፈ ምግብ ማቆሸሽ፣ አንዳንድ ቦታ ዝሙት፣ … ይቅርና ብዙ ከባባድ ሺርክ ይፈፀማል፡፡ ግና በርካታ ኢኽዋኖችን የሺርክ ጉዳይ ሲያስጨንቃቸው አይታይም፡፡ እንጂማ በነቢዩ ﷺ እና በ“ወልዮች” ላይ ብዙ ድንበር ይታለፋል፡፡ በመውሊድ ቦታዎች ላይ ብዙ አይነት ሺርክ ይፈፀማል፡፡ ለቀብር ሱጁድ ይወረዳል፡፡ ጦዋፍ ይደረጋል፡፡ ለበረካ እየተባለ የቀብር አፈር እየተበጠበጠ ይጠጣል፡፡ ከዘመናት በፊት ያለፉ ሙታኖችን ሰዎች ይማፀናሉ፡፡ ስለት ይፈፅማሉ፡፡ ያርዳሉ፡፡ በሺርክ የተሞሉ መንዙማዎች ይቀነቀናሉ፡፡
ይህን ሁሉ ጥፋት አጭቆ የያዘን ቢድዐ የሚያወግዙ ሰዎችን ነው እንደ ጠርዘኛ የሚስሉት፡፡ መውሊድ በመጣ ቁጥር ሰዎችን ከዚህ ጥፋት ስላስጠነቀቁ ነው ጨቅጫቃ የሚያደርጉት፡፡ “ረቢዕን የመጨቃጨቂያ ወር አደረጉት” ይላሉ፡፡ የጥፋቱን ጠንሳሾችና አራጋቢዎች እንዳላዩ እያለፉ ከሺርክና ቢድዐ የሚያስጠነቅቁ ሰዎችን ማብጠልጠል መንስኤው ምን እንደሆነ አይጠፋንም፡፡ እውነት ለህዝብ ብትቆረቆሩ ኖሮ ወገናችንን ከዚህ በሺርክ ከተወረረ በዓል ለማዳን ድርሻ በነበራችሁ ነበር፡፡ “ወላኪን ላ ሐያተ ሊመን ቱናዲ!”
“ይህን ሁሉ ጉድ እያወቁ እንዴት ለመውሊድ ይሟገታሉ?” የሚሉ የዋሆች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ ጉዳዩ ከራስ የመከላከል ጉዳይ ነው። የኢኽዋን ቡድን መስራች ሐሰን አልበናና ጭፍሮቹ መውሊድ ላይ ሲያቀነቅኑት ከነበሩ ዜማዎች ውስጥ እነዚህ ነበሩ፡-
هذا الحبيب مع الأحباب قد حضرا …وسامح الكل فيما قد مضى وجرى
“ይህ ወዳጃችን ከወዳጆች ጋር ተገኝቷል፡፡
#ያለፈ_የሆነውን_ሁሉ_ይቅር_ብሏል፡፡” [ሐሰን አልበናህ ቢአቅላሚ ተላሚዘቲሂ ወሙዓሲሪሂ፡ 71-72]
ይሄ ከኢስላም የሚያስወጣ ትልቁ ሺርክ አይደለምን? ከአላህ ውጭ ወንጀልን የሚምር አለ ወይ?! አላህ ምን እንዳለ አስተውሉ፡-
وَمَنْ يَغْفِرُ الذُّنُوبَ إلاَّ اللهُ
“ከአላህ በስተቀር ወንጀሎችን የሚምረው ማነው?” [ኣሊ ዒምራን፡ 135]
ነብዩም ﷺ "አላህ ሆይ! ... ካንተ በስተቀር ወንጀሎችን የሚምር የለም" ይላሉ። [አልቡኻሪይ፡ 8585] [ሙስሊም፡ 2705]
