en
Feedback
Yeka Millennium General Secondary School...

Yeka Millennium General Secondary School...

Open in Telegram
2 243
Subscribers
No data24 hours
-67 days
-5030 days
Posts Archive
የሪሜዲያል መግቢያ ነጥብ ይፋ ሆነ። ትምህርት ሚኒስቴር በ2018 የትምህርት ዘመን የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን በተፈጥሮ እና ማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት መስኮች ከ49.5% በታች ያስመዘገቡ ነገር ግን
የሪሜዲያል መግቢያ ነጥብ ይፋ ሆነ። ትምህርት ሚኒስቴር በ2018 የትምህርት ዘመን የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን በተፈጥሮ እና ማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት መስኮች ከ49.5% በታች ያስመዘገቡ ነገር ግን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የሚያሟሉ ተማሪዎች የRemedial ፕሮግራም ተጠቃሚ መሆናቸውን አሳውቋል። 1.  በሁሉም አማራጮች (በግል እና በመንግስት ተቋማት) የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል ተማሪዎች እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 33% ከመቶ እና ከዚያ የተቆረጠ መሆኑን። 2. ከላይ በተራ ቁጥር 1 የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ በመንግስት ተቋማት (ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖ) የ Remedial ፕሮግራም የሚከታተሉ ተማሪዎች የመቁረጫ ነጥቡን ያሟሉ ብቻ ይሆናሉ። የመቁረጫ ነጥብ ፦ ➡️ የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች 216 ➡️ የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች 204 ➡️ ታዳጊ ክልል እና አርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ እና ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 198 ➡️ የማህበራዊ እና የተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 198 ➡️ ማህበራዊ እና የተፈጥሮ ሳይንስ ዓይነስውራን ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 165 #MoE

#KUE #ScholarshipOpportunity ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ውጤት ላመጡና በትምህርት ዘርፍ መሰማራት ለሚፈልጉ አመልካቾች ለ201
#KUE #ScholarshipOpportunity ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ውጤት ላመጡና በትምህርት ዘርፍ መሰማራት ለሚፈልጉ አመልካቾች ለ2018 የትምህርት ዘመን ልዩ የስኮላርሽፕ ዕድል አመቻችቷል፡፡ የዚህ ልዩ የስኮላርሺፕ ተጠቃሚ መሆን የሚፈልጉ ተወዳዳሪዎች የትምህርት ሚኒስቴርን መመዘኛ መስፈርት ያሟሉ እና በቀጣይም ውል ገብተው በትምህርት ዘርፍ ለመሰማራት ፈቃደኛ የሆነ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡ የነጻ ትምህርት ዕድሉ ተጠቃሚ ተማሪዎች የሚያገኟቸው ጥቅሞች፦ ➫ የምግብ፣ የመኝታ እና ሙሉ የትምህርት ወጪያቸው በዩኒቨርሲቲው ይሸፈናል፣ ➫ የኪስ ገንዘብ በየወሩ ይሰጣቸዋል፣ ➫ የትምህርት ቁሶች ወጪ ይሸፈንላቸዋል። የማመልከቻ አማራጮች፦ በአካል በመቅረብ ወይም በኦንላይን በኦንላይን ለማመልከት 👇  ከላይ በምስሉ ላይ የተያያዘውን QR Code ስካን ያድርጉ (አመልካቾች ማመልከት የሚችሉባቸው የትምህርት አይነቶች ከላይ ከተያያዘው ምስል ይመልከቱ።) https://t.me/minster_of_education

+1
Advanced worldwide Eng2.pdf33.86 MB

በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ወስደው በአማካይ ውጤታቸው 49.50 - 49.99 በመቶ ያመጡ ተማሪዎች ውጤታቸው ወደ 50 በመቶ የሚጠጋጋ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋ
በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ወስደው በአማካይ ውጤታቸው 49.50 - 49.99 በመቶ ያመጡ ተማሪዎች ውጤታቸው ወደ 50 በመቶ የሚጠጋጋ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። በዚህም 49.50 እና በላይ አማካይ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች፥ ዝቅተኛውን 50 በመቶ የማለፊያ ነጥብ ያሟሉ ሆኖ የተወሰነ መሆኑን በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በቀን መስከረም 20/2018 ዓ.ም ተፈርሞ ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የተላከ ደብዳቤ ያሳያል።  በመሆኑም 49.50 እና በላይ አማካይ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመግባት መማር እንደሚችሉ ሚኒስተሩ ገልፀዋል። በዚህ ውሳኔ መሠረት 300 ነጥብ የነበረው የየኒቨርሲቲ መግቢያ ወደ 297 የተጠጋጋ መሆኑ ተገልፃል።

ማስታወቂያ በ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በመደበኛው ፕሮግራም ለመማር ያለፋችሁ እና በምደባ ወቅት አዎንታዊ ድጋፍ ለምትሹ ተማሪዎች ማመልከቻችሁን በ *https://student.ethernet.edu.et* በኩል እስከ መስከረም 16/2018 ዓ.ም ድረስ እንድታመለክቱ እየገለጽን ምንም አይነት ማመልከቻ በአካል የማንቀበል መሆኑን እንገልጻለን።

ማስታወቂያ በ2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት ላመጣችሁ ተማሪዎች በሙሉ፤ በ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ያመጣችሁና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ለመማር ፍላጎት ያላችሁ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን በየትምህርት ቤታችሁ በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ መስከረም 14/2018 ዓ.ም ድረስ ማስተካከል የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። ማሳሰቢያ፡- 1. የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ከ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ጀምሮ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ተማሪዎችን ስሚቀበል ምርጫችሁ ውስጥ ማካተት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። 2.አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እና አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ምርጫ ውስጥ የማይካተቱ መሆኑ እናሳውቃለን።

photo content
+1

ከፊዚክስ ትምህርት ፈተና ጋር በተያያዘ በውጤት ላይ ተፈጥሮ የ ነበረው ችግር ተስተካከለ። በሀገር አቀፉ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሁለተኛው ዙር የፊዚክስ ፈተና ከ60ው ወደ 100 ሳይ የቀር በመቀመጡ ተማሪዎች ውጤታቸው መውረዱን ጠቁመው መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀው ነበር። የውጤት ችግሩ ዛሬ መስተካከሉን እና ከ100 ተቀይሮ መቀመጡን አሳውቀዋል።

photo content
+1