Injibara University
📈 Analytical overview of Telegram channel Injibara University
Channel Injibara University (@injiuniversity) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 20 089 subscribers, ranking 9 853 in the Education category and 1 721 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 20 089 subscribers.
According to the latest data from 07 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 617 over the last 30 days and by 13 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 42.48%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 19.39% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 8 532 views. Within the first day, a publication typically gains 3 894 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.
📝 Description and content policy
Channel description not provided.
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 08 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Education category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 08 September | +4 | |||
| 07 September | +13 | |||
| 06 September | +42 | |||
| 05 September | +20 | |||
| 04 September | +36 | |||
| 03 September | +9 | |||
| 02 September | +15 | |||
| 01 September | +26 |
| 2 | እንኳን ከ2018 ዓ.ም ወደ 2019 ዓ.ም የአገው ማህበረሰብ የአዲስ ዘመን መሸጋገሪያ "አሱሪቴ" ክብረ-በዓል በሠላም አደረሰን ፤ አደረሳችሁ!
===============
ጳጉሜ 02/2018 ዓ.ም፤ የአገው ጥናት ኢንስቲትዩት
የአገው ጥናት ኢንስቲትዩት እንኳን ለአገው ማህበረሰብ የአዲስ ዘመን መሸጋገሪያ አሱሪቴ ክበረ-በዓል በሠላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞቱን ይገልጻል፡፡
አሱሪቴ በአገው ማህበረሰብ የአዲስ ዓመት መሸጋገሪያ ዋዜማ በህጻናት ዜማና ጭፈራ የሚደምቅ ክብረ-በዓል ነው፡፡ ህጻናት በአሱሪቴ በዓል በቡድን ሁነው የተጎነጎነ እንግጫ፣ ከስይ፣ አበባ እና የመሳሰሉትን በመያዝ “አሱሪቴ ናካማ” እያሉ በማዜም በእያንዳንዱ ቤት በመዞር እንግጫና አበባ ምሰሶ ላይ በማሰር ለአዲሱ ዓመት “የእንኳን አደረሳችሁ” መልካም ምኞታቸውን ይገልጻሉ፡፡
የአገው ጥናት ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ብርሃኑ አሳየ (ረ/ፕ) እንደገለጹት የአሱሪቴ ሀገር በቀል እውቀት የአገው ማህበረሰብ ለአያሌ ዘመናት ከአካባቢው፣ ከባህሉ እና ከተፈጥሮ ጋር አብሮ በመኖር ያከማቸው ጠቃሚ የማይዳሰስ ባህላዊ ቅርስ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የአሱሪቴ አከባበር በአገዎች ማህበራዊ፣ ባህላዊ፣ ሀይማኖታዊ እና ኢኮኖሚያዊ ህይወት ውስጥ የላቀ ጠቀሜታ ያለው በመሆኑ ማህበራዊ ትስስርን የማጠናከር፤ ባህልን ጠብቆ የማቆየት፤ ተስፋን የመሰነቅ፤ አብሮነትን የማጽደቅና የማጽናት እንዲሁም ስነ-ልቦናዊ እርካታን የመፍጠር ሚና እንዳለው ጠቁመዋል።
አሱሪቴ ቤተሰብ፣ ዘመድ እና ጓደኛ የሚገናኙበት በመሆኑ በመካከላቸው ያለውን ፍቅር እና አንድነት ያጠናክራል። ትውልዱ የራሱን ታሪክ፣ እሴትና ወግ እንዲማርና ባህሉን ጠብቆ ለቀጣዩ ትውልድ እንዲያስተላልፍ ከመርዳቱም በላይ ህጻናት በአዲስ ዓመት አዕምሯቸውን አድሰው አዲስ አስተሳሰብ እንዲኖራቸው የሚያደርግ ክብረ-በዓል መሆኑንም ገልጸዋል።
የሚመለከታቸው ተቋማትና ማህበራዊ ሚዲያዎች የተለያዩ ዶክመንተሪ ፊሰልሞችን እንዲሁም የቅኝት ጽሁፎችን በመጠቀም አሱሪቴን ለሌሎች ማህበረሰቦች ማስተዋወቅና በበዓሉ መጥተው እንዲታደሙ የማድረግ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር እንደሚገባቸውም አሳስበዋል፡፡
አጋው ማቤር አቑ ስካዊ ዝቤኑ ከይጝጝፂ አሱሪቴው ክብር ባላስ እንኳ ታምፁናስ፤ታምፅኾስ!
አጋው ፅናቱ ኢንስቲትዩት
አጋው ፅናቱ ኢንስቲትዩት እንኳ አጋው ማቤር አቑ ስካዊ ዝቤኑ ካይጝጝፂ አሱሪቴው ክብር ባላስ ታምፁናስ፤ታምፅኾስ! ንጝስ ሜልካሜ ትምኔቶ ጌሌፅካ፡፡
አሱሪቴ አጋው ማቤር አቑ ስካዊ ዝቤኑ ካይጝጝፂ ዋዚሚ፤ ስራስሪው ዜሚስስታ ጉዲብጚስ ብራማ ኬቤርስታው ክብር-ባልያኽ፡፡ ስራስሪ ኬችስ ያኼካማ ጉንጉኔ እንግቼ እስታ አቢቤ እሚካማ ድሚስ ኽሳው አቒው አኹኪ አቓው ጝንዴስ ጄሜርካማ ኩክሪስቴ ዙሬካማጊ እንኳን ታምፁናሱሳ ሜልካሜ ትምኔቶ ፌይትጝፃና፡፡
አጋው ፅናት ኢንስቲትዩት ዳይሬክታር ብርሃኑ አሳየ (ር/ፕሮፌሰር) ጌሌፁኑውስታጊ፣ አሱሪቴ አጋው ማቤር አቕ ሜንች ዝቤንስ ዙራሙሪሊ፣ ባይልሊስታ ፍትሬትሊ አብርታ ዝኩጝስ እጂፁኽ ቴኬማንቲ ዳሴስስታቲው ባይሉ ማኺቲ ያኹታ ጌሌፅካ፡፡
አሱሪቴው ክብሩ-ባይል አጋውካው ማቢሪው፣ ባይሉ፣ አይማኖቱስታ ኢኮኖሚው ይወትዳ ኸስኹስ ትክም ዝክኹ አኽጝስ፤ ማቢሪውሳ ታምትጜ ይስጝፅጙ፣ ባይሎ ማንዳማ እጂፅጙ፣ ቴስፌ ላሚታ እሚጙ፣ አብርቶ ፂኒስጙስታ ፂኒፅጙ ቴግባር ዝክኹ ያኹታ ቶኬምካ፡፡
አሱሪቴ ጝን አቕ፣ ድንግሬንካስታ አፄብካ ታምትጛኑ አኽጝስ፤ ጛ ክቻዳ ዝክኹሳ እንካኖስታ እምፕልቶ ይስጝፄ፡፡ ክምንት ጚውሳ ባይሎ፣ ታሪኮስታ ዋጎ ክንታታስታ እንጚሳ ማንዳማ ይንታው ክምንትስ ፌይትጝፃታ እርዳትጝዴስ ጃላ፣ ስራስሪ እሌትኩ ሼሌፅካ እንፅኽካዴስስታ ችንኬትካዴስ ፌካማ ፍትኽ ናኑ ክብር-ባላኽ ናኒስክላ ጌሌፅካ፤ ክርፂ አማትባላ ያኽስ ናኒስ እንጉስትካ፡፡ ታምፁናስ!
ለበለጠ መረጃ
በፌስቡክ - https://www.facebook.com/Injiuni
በቴሌግራም - https://t.me/injiuniversity
በዩቱዩብ - https://www.youtube.com/@InjibaraUniversity
በተጨማሪም በዩኒቨርሲቲው
Official Website - https://www.inu.edu.et ይከታተሉን! | 3 435 |
| 3 | No text... | 3 860 |
| 4 | No text... | 5 464 |
| 5 | No text... | 5 162 |
| 6 | ጽዱና
አረንጓዴው እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ወስዳችሁ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት
ያመጣችሁ ተማሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ እያለ ዩኒቨርሲቲው በ2019 የትምህርት ዘመን የሚገቡ አዲስና ነባር ተማሪዎችን ለመቀበለል
ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡
በአረንጓዴ
ልማትና በግቢ ውበት በሀገር አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ በመሆን የእውቅና ሰርተፊኬት የተበረከተለት ሲሆን ከሰሞኑ ደግሞ ዩኒቨርሲቲዎች
ለመማር ማስተማር ባላቸው ምቹነትና ለተማሪዎቻቸው በሚሰጡት አገልግሎት መሰረት ተደርጎ በተሰራ የተማሪዎች የእርካታ ዳሰሳ ጥናት
ቀዳሚና ተመራጭ ዩኒቨርሲቲ ለመሆን በቅቷል፡፡
ዩኒቨርሲቲው
በ7 ኮሌጆች እና በሁለት ትምህርት ቤቶች ሥር በተከፈቱ በርካታ ፕሮግራሞች ተማሪዎችን፡-
Welcome!
እንኳን
ደህና መጣችሁ!
አዲናስ!
ብሎ ለመቀበል
ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቆ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል፡፡
በድጋሜ
እንኳን አደረሳችሁ፤ እንኳን ደስ አላችሁ!!!
ያለህን
እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!
Explore
Your Creative Potential!
ነሃሴ 30/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
ለበለጠ
መረጃ፡-
በፌስቡክ
- https://www.facebook.com/Injiuni
በቴሌግራም
- https://t.me/injiuniversity
በዩቲዩብ
- https://www.youtube.com/@InjibaraUniversity
በተጨማሪም በዩኒቨርሲቲው
Official
Website - https://www.inu.edu.et ይወዳጁን ይወጁን፤
ይከታተሉን! | 4 981 |
| 7 | ጽዱና
አረንጓዴው እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ወስዳችሁ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት
ያመጣችሁ ተማሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ እያለ ዩኒቨርሲቲው በ2019 የትምህርት ዘመን የሚገቡ አዲስና ነባር ተማሪዎችን ለመቀበለል
ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡
በአረንጓዴ
ልማትና በግቢ ውበት በሀገር አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ በመሆን የእውቅና ሰርተፊኬት የተበረከተለት ሲሆን ከሰሞኑ ደግሞ ዩኒቨርሲቲዎች
ለመማር ማስተማር ባላቸው ምቹነትና ለተማሪዎቻቸው በሚሰጡት አገልግሎት መሰረት ተደርጎ በተሰራ የተማሪዎች የእርካታ ዳሰሳ ጥናት
ቀዳሚና ተመራጭ ዩኒቨርሲቲ ለመሆን በቅቷል፡፡
ዩኒቨርሲቲው
በ7 ኮሌጆች እና በሁለት ትምህርት ቤቶች ሥር በተከፈቱ በርካታ ፕሮግራሞች ተማሪዎችን፡-
Welcome!
እንኳን
ደህና መጣችሁ!
አዲናስ!
ብሎ ለመቀበል
ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቆ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል፡፡
በድጋሜ
እንኳን አደረሳችሁ፤ እንኳን ደስ አላችሁ!!!
ያለህን
እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!
Explore
Your Creative Potential!
ነሃሴ 30/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
ለበለጠ
መረጃ፡-
በፌስቡክ
- https://www.facebook.com/Injiuni
በቴሌግራም
- https://t.me/injiuniversity
በዩቲዩብ
- https://www.youtube.com/@InjibaraUniversity
በተጨማሪም በዩኒቨርሲቲው
Official
Website - https://www.inu.edu.et ይወዳጁን ይወጁን፤
ይከታተሉን! | 1 |
| 8 | No text... | 4 798 |
| 9 | No text... | 4 962 |
| 10 | ለክረምት ስቲም (STEM Summer Outreach ) ተማሪዎች የሽኝኝት መርሃ ግብር ተካሄደ፡፡
ነሀሴ 30/2018ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
ከአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ወረዳዎች ከሚገኙ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡና በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የስቲም ማዕከል ሲማሩ የቆዩ STEM ተማሪዎች ሽኝኝት የተደረገላቸው ሲሆን የፈጠራ ስራቸውንም አቅርበዋል፡፡
በመርሃ ግብሩ የተገኙት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች አገልገሎት ም/ዲን እና የፊዚክስ መምህር ተክሌ ልሳኑ (ዶ/ር) እንደተናገሩት ዩኒቨርቨርሲቲው ተማሪዎች በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጅነሪንግ እና ሂሳብ (STEM) ትምህርቶች ላይ የተሻለ ዕውቀት እንዲኖራቸው በክረምት እና በበጋ እንዲሁም ቅዳሜ እና እሁድ መርሃ ግብሮች ሲያስተምሩ እንደነበር ጠቅሰው በክረምት መርሃ-ግብር ለሚማሩ ተማሪዎች የምግብ፣ የምኝታ እና የህክምና ወጭዎች በዩኒቨርሲቲው ተሸፍኖላቸው ሲማሩ የቆዩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ተፈጥሮ እና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ዲን ታደለ ሽፈራው (ረ/ፕ) በበኩላቸው ተማሪዎቹ የተሻለ የሳይንስ ዕውቀት ያላቸው እና የፈጠራ ስራዎችንም መስራት የሚችሉ መሆናቸውን በመመልክታቸው መደሰታቸውን ገልጸው የክረምት የስቲም (STEM Summer Outreach) መርሃ ግብር በብዛት በተግባር የተደገፈ ትምህርት የሚጥበት እና ተማሪዎች የተሻለ ዕውቀት የሚጨብጡበት መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የስቲም ማዕከል አስተባባሪ አብርሃም ወዳጀ እንደተናገሩት በዩኒቨርሰቲው ከተለያዩ የብሔረሰብ አስተዳደሩ ወረዳዎች ከ10ኛ እስከ 12ኛ ክፍሎች የተውጣጡ 70 ወንድ እና 35 ሴት በድምሩ 105 ተማሪዎች የክረምት የስቲም መርሃ ግብር ሲከታተሉ ቆይተው ዛሬ የሽኝኝት መርሃ ግብር መካሄዱን ተናግረዋል፡፡
አስተባባሪው አያይዘውም ተማሪዎቹ በቆይታቸው ያበለፀጓቸውን የፈጠራ ስራዎች የወባ ትንኝ መከላከያ የኤሌክትሪክ ባጃጅ፣ ለግብርና ስራ የሚያገለግል ድሮን፣ የጤፍ ማበጠሪያ እና ለትምህርት ቤት አስተዳደር የሚያገልግል የሶፍትዌር ፕሮጀክቶ ማሳየታቸውን ጠቅሰው በቀጣይ ከዚህ የተሻለ የፈጠራ ስራ እንዲሰሩ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡
በሽኝኝት መርሃ ግብሩ አለሙ ምህረት ከእንጅባራ ከተማ አስተዳደር የወባ ትንኝ መከላከያ ማሽን፣ ተማሪ አስማማው አብዩ ከዚገም ወረዳ የኤሌክትሪክ ባጃጅ እና ለግብርና ስራ የሚያገልግል ድሮን፣ ተማሪ ጌትነት አማረ ከእንጅባራ ከተማ የጤፍ ማበጠሪያ ማሽን እና ተማሪ ገብረመስቀል ውዱ ከዳንግላ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ቤት አስተዳደር ሶፍት ዌር (Gem smart integrated education system) ፈጠራ ስራዎቸውን አቅርበዋል፡፡
ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም! | 5 153 |
| 11 | ማስታወቂያ
ለትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ፦
=================== | 6 729 |
| 12 | No text... | 6 773 |
| 13 | ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ሴት የSTEM ተማሪዎች የህይዎት ክህሎት ስልጠና ተሰጠ።
ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈጻሚ እና የዩኒቨርሲቲው የSTEM ማዕከል በመተባበር ለዩኒቨርሲቲው ሴት የSTEM ተማሪዎች የህይዎት ክህሎት ስልጠና ሰጥተዋል።
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካትቶ ትግበራ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ባንቻለም ካሴ ለSTEM ሴት ተማሪዎች የተዘጋጀው ስልጠና አላማ ከትምህርት ክትትል በተጨማሪ የህይወት ክህሎት ስልጠና በመስጠት በራሳቸው የሚተማመኑና ራሳቸውን መሆን የሚችሉ፤ ግብ ያላቸውና ውሳኔ መስጠት የሚችሉ እንዲሁም ራሳቸውን ከአሉታዊ የአቻ ግፊት ጫና መከላከል የሚችሉ መንፈሰ ጠንካራ ሴቶች መሆን እንዲችሉ ከማሰብ ባሻገር ካለፉት የእስቲም ተማሪዎች ማለትም ከተማሪ ህዳሴ ዘመኑ የህይወት ልምድ ወይም ተሞክሮ እንዲወስዱ እና እንዲነቃቁ፣ ውጤታማ እንዲሆኑ እንዲሁም ሀላፊነት የሚሰማቸው ተተኪዎች እንዲሆኑ ታስቦ መዘጋጀቱን ገልፀዋል።
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ STEM ማዕከል አስተባባሪ መ/ር አብርሃም ወዳጀ በበኩላቸው ስልጠናው የተሰጠው ከብሔረሰብ ዞኑ ተውጣጥተው በዩኒቨርሲቲው STEM ማዕከል ለሚማሩ 35 ለሚሆኑ ሴት ተማሪዎች ከOSSHD (Organizational Social Service and Health Development) ከተሰኘ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ጋር በመተባበር ሴትነታቸውን ተከትሎ የሚደርሱባቸውን ተግዳሮቶች እንዴት ማለፍ እንደሚችሉ እና እንዴት ውጤታማ መሆን እንደሚችሉ ግንዛቤ ለመፍጠር የተሰጠ ስልጠና መሆኑን ገልፀዋል።
ስልጠናውን የሰጡት ሲ/ር ብርቱካን አዳነ እንደገለፁት OSSHD (Organizational Social Service and Health Development) ባዘጋጀው ስልጠና የተካተቱት ተማሪዎች የእድሜ ክልላቸው ለአሉታዊ የአቻ ግፊትና ለመሳሰሉት ጉዳዮች ይበልጥ ተጋላጭ ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ ራሳቸውን እንዲያውቁ፣ በራሳቸው እንዲተማመኑ፣ በዝንባሌያቸው ግብ አስቀምጠው ለነገ ህይዎታቸው መሰረት እንዲይዙ፣ ለቤተሰብ ብሎም ለሀገር እንዲጠቅሙ ከማሰብ አንፃር የተዘጋጀ ስልጠና ነው ብለዋል።
በስለጠና መርሃ-ግብሩ በ2018 ዓ.ም 12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሴቶች አንደኛ የወጣችው እና የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የSTEM ተማሪ የነበረችው ተማሪ ህዳሴ ዘመኑ የህይዎት ልምዷንና ተሞክሮዋን ለተማሪዎቹ አካፍላለች።
ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም! | 6 204 |
| 14 | No text... | 6 106 |
| 15 | No text... | 6 176 |
| 16 | እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ 5 መቶ ሃምሳ ሽህ ብር የሚገመት የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ፡፡
ነሀሴ 28/2018ዓ.ም፤እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ፣ የዩኒቨርሲቲው ማህረሰብ እና ሱታና ኢንተርፕራይዝ በጋራ በመተባበር ለእንጅባራ ከተማ አስተዳደር እና ባንጃ ወረዳ ለሚገኙ ተማሪዎች ቦርሳ፣ ደብተር፣ እስክርቢቶ እና የንጽህና መጠቢቂያ ድጋፍ ተደርጎላቸዋል፡፡
ድጋፉን ያስረከቡት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈጻሚ ባንቻለም ካሴ እንደተናገሩት ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ ዘርፎች የማህበረሰብ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ጠቅሰው በተላይም በትምህርቱ ዘርፍ የተለያዩ የትምህርት የቁሳቁስ እና ሥልጠናዎችን በመስጠት ማህራዊ ኃላፊነቱን እየተሰወጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡
የድጋፉ አስተባባሪ እና የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የአዲናስ ቃል ኪዳን ቤተሰብ ትስስር አስተባበሪ መ/ር በጋሻው ቢተው በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው በብሄረሰብ አስተዳደሩ የተለያዩ ወረዳዎች ለትምህርት ቤት ግንባታ እንዲሁም የቤተ-መጽሐፍት እና ቤተ-ሙከራ ግብዓቶች እንዲሟሉ ድጋፍ ማድረጉን አስታውሰው በዛሬው ዕለትም እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ፣ የዩኒቨርሲቲው ማህረሰብ እና ሱታና ኢንተርፕራይዝ በጋራ በመሆን 5 መቶ ሀምሳ ሽህ ብር የሚያወጣ የትምህርት ቁሳቁስና የንጽህና መጠቢቂያ በማሰባሰብ እንጅባራ ከተማ አስተዳደር እና ባንጃ ወረዳ ለሚገኙ ተማሪዎች ድጋፍ መደረጉን ተናግረዋል፡፡
ድጋፉን የተረከቡት የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ደስታው ዓለሙ እንደተናገሩት እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የብሔረሰብ አስተደደሩ ትምህርት አንዲሻሻል በቁሳቁስ ድጋፍ፣ በተማሪዎች እና በመምህራን ልማት ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ የሚገኝ ተቋም መሆኑን ገልጸው ዛሬ የተደረገው ድጋፍም የዚህ ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ኃላፊው አክለውም መምሪያው እና እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በቅርበት እየሰሩ መሆኑን ጠቅሰው ዩኒቨርሲቲው ላደረገው ድጋፍ አመስግነዋል፡፡
በድጋፉ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣የዞኑ ትምህርት መምሪያ ኃላፊ፣ የባንጅ ወረዳ እና እንጅባራ ከተማ አስተዳደር አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም! | 5 717 |
| 17 | No text... | 6 591 |
| 18 | በአገው ቋንቋ፣ ባህል፣ ታሪክ እና ሀገር በቀል እውቀት ላይ ትኩረት ያደረጉ 15 ጥናቶችን ያካተተ መጽሐፍ የህትመት ሥራው ተጠናቆ ለተጠቃሚዎች ተደራሽ እየተደረገ መሆኑ ተገለፀ፡፡
ነሃሴ 27/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የአገው ጥናት ኢንስቲትዩት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ብርሃኑ አሳየ (ረ/ፕ) በአገው ባህል፣ ቋንቋ፣ታሪክ፣ ሀገር በቀል እውቀት እና ተፈጥሯዊ የቋንቋ ሂደት ላይ አምስት የምርምር ጉባኤዎች ባለፉት ተከታታይ ዓመታት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ መካሄዳቸውን ገልፀው በእነዚህ የምርምር ኮንፈረንሶች ከቀረቡ የምርምር ሥራዎች መካከል የአርትኦት ሂደቶችን አልፈው የተመረጡ 15 ጥናቶችን የያዘ “Proceedings of the Five National Research Conference on Agaw Language, Culture, Indigenous Knowledge and History” መጽሐፍ፣ International Standard Book Number (ISBN) ተሰጥቶት የታተመ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ መጽሐፉ ከኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን የቅጅ እና ተዛማጅ መብቶችን ከሚያስገኙ ሥራዎች ምዝገባ የምስክር ወረቀት (patent right) አግኝቶ የታተመ መሆኑን ዳይሬክተሩ ጨምረው ገልፀዋል፡፡
መጽሐፉ ለትምህርት ቤቶች፣ ለህዝብ ቤተ-መጽሐፍት፣ ለምርምር ተቋማት እና ለዩኒቨርሲቲዎች በቅርብ ጊዜ የሚሰራጭ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን የሶፍት ቅጂው ደግሞ በአገው ጥናት ኢንስቲትዩት ድህረ-ገጽ www//:ias.inu.edu.et ተጭኖ ለተጠቃሚዎች ተደራሽ ሆኗል፡፡
የህትመቱ አካዳሚያዊ እና ሳይንሳዊ ግቦችም በሲምፖዚየሙ የተጋሩ የመጨረሻ ደረጃ ወይም የተራዘሙ የምርምር ሀሳቦችን በታሪካዊ ሰነድነት በአርካይቭ መዝገቦች ውስጥ እንዲሰፍሩ ማስቻል፣ ሙሉ እና ረጅም የጆርናል ህትመቶች ከመካሄዳቸው በፊት አዳዲስ ዘዴዎችን እና የመጀመሪያ ደረጃ ግኝቶችን ማሰራጨት፣ በታወቁ የአካዳሚክ ውሂብ ቋቶች ውስጥ በመረጃ ጠቋሚዎች አማካይነት እንዲታዩ እና እንዲጠቀሱ ከማድረግ በተጨማሪ አጥኚዎች በአቻ ግምገማዊ ውይይቶች በስፋት ለሚካሄዱ ጥናቶች ፅንሰ-ሀሳቦችን እንዲያጣሩ ያስችላቸዋል፡፡
ህትመቱ በአጠቃላይ አዳዲስ ግኝቶች ለዓለም አቀፍ ታዳሚዎች እንዲደርሱ፣ ምርምራዊ ሳይንስ እንዲረጋገጥ እና ሌሎች ተመራማሪዎች በመጀመሪያ ደረጃ ላይ በሚገኙ ሥራዎች በመመስረት አዳዲስ የምርምር ሥራቸውን እንዲሰሩ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።
ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!
Explore Your Creative Potential!
ለተጨማሪ መረጃ
በፌስቡክ - https://www.facebook.com/Injiuni
በቴሌግራም - https://t.me/injiuniversity
በዩቱዩብ - https://www.youtube.com/@InjibaraUniversity
በተጨማሪም በዩኒቨርሲቲው
Official ዌብሳይት - https://www.inu.edu.et ይወዳጁን፤ ይከታተሉን! | 6 440 |
| 19 | በአገው ቋንቋ፣ ባህል፣ ታሪክ እና ሀገር በቀል እውቀት ላይ ትኩረት ያደረጉ 15 ጥናቶችን ያካተተ መጽሐፍ የህትመት ሥራው ተጠናቆ ለተጠቃሚዎች ተደራሽ እየተደረገ መሆኑ ተገለፀ፡፡
ነሃሴ 27/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የአገው ጥናት ኢንስቲትዩት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ብርሃኑ አሳየ (ረ/ፕ) በአገው ባህል፣ ቋንቋ፣ታሪክ፣ ሀገር በቀል እውቀት እና ተፈጥሯዊ የቋንቋ ሂደት ላይ አምስት የምርምር ጉባኤዎች ባለፉት ተከታታይ ዓመታት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ መካሄዳቸውን ገልፀው በእነዚህ የምርምር ኮንፈረንሶች ከቀረቡ የምርምር ሥራዎች መካከል የአርትኦት ሂደቶችን አልፈው የተመረጡ 15 ጥናቶችን የያዘ “Proceedings of the Five National Research Conference on Agaw Language, Culture, Indigenous Knowledge and History” መጽሐፍ፣ International Standard Book Number (ISBN) ተሰጥቶት የታተመ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ መጽሐፉ ከኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን የቅጅ እና ተዛማጅ መብቶችን ከሚያስገኙ ሥራዎች ምዝገባ የምስክር ወረቀት (patent right) አግኝቶ የታተመ መሆኑን ዳይሬክተሩ ጨምረው ገልፀዋል፡፡
መጽሐፉ ለትምህርት ቤቶች፣ ለህዝብ ቤተ-መጽሐፍት፣ ለምርምር ተቋማት እና ለዩኒቨርሲቲዎች በቅርብ ጊዜ የሚሰራጭ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን የሶፍት ቅጂው ደግሞ በአገው ጥናት ኢንስቲትዩት ድህረ-ገጽ www//:ias.inu.edu.et ተጭኖ ለተጠቃሚዎች ተደራሽ ሆኗል፡፡
የህትመቱ አካዳሚያዊ እና ሳይንሳዊ ግቦችም በሲምፖዚየሙ የተጋሩ የመጨረሻ ደረጃ ወይም የተራዘሙ የምርምር ሀሳቦችን በታሪካዊ ሰነድነት በአርካይቭ መዝገቦች ውስጥ እንዲሰፍሩ ማስቻል፣ ሙሉ እና ረጅም የጆርናል ህትመቶች ከመካሄ | 58 |
| 20 | No text... | 7 178 |
