en
Feedback
ወልድ ዋሕድ ሚዲያ welid wahid media

ወልድ ዋሕድ ሚዲያ welid wahid media

Open in Telegram

ይህ የኮተቤ መካነ ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና ቤተክርስቲያን ወልድ ዋሕድ ሰንበት ትምህርት ቤት ቻናል ነው 👉👉ለጠቅላላ @weldwahid 👉👉ለአብነት እና ግእዝ ቋንቋ ትምህርት @weldwahidabinet 👉👉 ለቤተ መጻሕፍት አገልግሎት @Abaiyesuslib 👉👉ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት @mels_asteyayet

Show more
2 054
Subscribers
+124 hours
+17 days
+1930 days
Posts Archive
" እግዚአብሔር፥ ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ እስከ አሁንም ስለምታገለግሉአቸው፥ ያደረጋችሁትን ሥራ ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመፀኛ አይደለምና።" ዕብራውያን 6:10 🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓
     " እግዚአብሔር፥ ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ እስከ አሁንም ስለምታገለግሉአቸው፥ ያደረጋችሁትን ሥራ ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመፀኛ አይደለምና።"             ዕብራውያን 6:10 🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓 🎓🎓🎓 እንኳን ደስ አለህ🎓🎓🎓 🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓   በትላንትናው ዕለት የሰንበት ት/ት ቤታችን አገልጋይ ዲ/ን ፊሊሞን መክብብ ከ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ  የተመረቅህው ውድ  አባላችን እንኳን ደስ አለህ መልካም የስራና የአገልግሎት ዘመን እንዲሆንልህ ወልድ ዋህድ ሰንበት ትምህርት ቤት ትመኝልሀለች።

" እግዚአብሔር፥ ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ እስከ አሁንም ስለምታገለግሉአቸው፥ ያደረጋችሁትን ሥራ ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመፀኛ አይደለምና።" ዕብራውያን 6:10 🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓
     " እግዚአብሔር፥ ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ እስከ አሁንም ስለምታገለግሉአቸው፥ ያደረጋችሁትን ሥራ ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመፀኛ አይደለምና።"             ዕብራውያን 6:10 🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓 🎓🎓🎓 እንኳን ደስ አለህ🎓🎓🎓 🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓   በዛሬው ዕለት የሰንበት ት/ት ቤታችን አገልጋይ ሚኪያስ ሣህሌ ከ ባህርዳር ዩኒቨርስቲ  የተመረቅህው ውድ  አባላችን እንኳን ደስ አለህ መልካም የስራና የአገልግሎት ዘመን እንዲሆንልህ ወልድ ዋህድ ሰንበት ትምህርት ቤት ትመኝልሀለች።

“የማይቆጣጠሯትን ምላስ ያህል መጥፎ ጾር የለም፤ እርሷ የፈተናዎች ሁሉ እናት ናት፡፡”      አባ_አጋቶን

"እግዚአብሔር ዓለቴ፥ አምባዬ፥ መድኃኒቴ፥ አምላኬ፥ በእርሱም የምተማመንበት ረዳቴ፥ መታመኛዬና የደኅንነቴ ቀንድ መጠጊያዬም ነው።"              መዝ 18÷2

"ሳትደክም ሁሉን ትሸከማለህ ሳታጓድል ሁሉን ትመግባለህ ሳትዘነጋ ሁሉን ትሰማለህ ሳትበቀል ሁሉን ይቅር ትላለህ።"                 ቅዳሴ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ

🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜ እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ ሕንፀተ ቤታ (ሕንፀታ) በሰላም አደረሳችኹ ሰኔ ፳፩ (ሕንፀታ ወቅዳሴ ቤታ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን) ከእመቤታችን ፴፫ቱ በዓላት አንዱ ነው፡፡ ጌታችንም ከእመቤታችን እና ከቅዱሳን መላእክት ጋር ከሰማየ ሰማያት ወርዶ እመቤታችንን ታቦት፣ ሐዋርያትን ልዑካን አድርጎ፣ እርሱ ሠራዒ ካህን ኾኖ ቀድሶ ካቈረባቸው በኋላ ‹‹እምይእዜሰ አንትሙኒ ከመዝ ግበሩ፤ ከዛሬ ጀምሮ እናንተም እንደዚህ አድርጉ›› ብሎ አዝዟቸው በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐርጓል፡፡ ከዚህ በኋላ ሐዋርያት ከጌታ እንዳዩት በዓለም ዞረው ቤተክርስቲያንን አንፀዋል። እግዚአብሔር አምላክ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ፍቅር፥ ረድኤት፥ ጸጋ - የቡሩካን ሐዋርያቱን በረከት ያሳድርብን!  አሜን🙏 🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱🔱

🔔ሥርዓተ ማኀሌት🔔 🔔ዘሰኔ 21🔔 🔔ሕንፀታ ለማርያም🔔
+5
🔔ሥርዓተ ማኀሌት🔔 🔔ዘሰኔ 21🔔 🔔ሕንፀታ ለማርያም🔔

"እንደማይሰማ ቸል ይላል እንደማያይ ዝም ይላል እንደማያውቅ ይታገሣል እንደማይሰጥ ያዘገያል።"    ቅዳሴ ዘሠለሥቱ ምእት

"የጌታ ቀን ድንገት እንደ ሌባ በሌሊት ይመጣልና"        1ተሰ 5÷2

ሰላም ለኪ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን 👉"ሰኔ 20 ቀንም ሐዋርያት የተሰበሰቡበት ልጅዋም ቤቷን ለመሥራት የወረደበት ነው" መቅድመ ተአምረ ማርያም ቁጥር 29 👉“እርሱም፦ ቤቴ የጸሎት ቤት ይሆናል ተብ
ሰላም ለኪ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን 👉"ሰኔ 20 ቀንም ሐዋርያት የተሰበሰቡበት ልጅዋም ቤቷን ለመሥራት የወረደበት ነው" መቅድመ ተአምረ ማርያም ቁጥር 29 👉“እርሱም፦ ቤቴ የጸሎት ቤት ይሆናል ተብሎ ተጽፎአል፤ እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችሁት አላቸው።”   — ሉቃስ 19፥46 "ሰላም ለኪ ቅድስት ቤተክርስቲያን    አምሳለ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት         ማኅደረ መለኮት ምስአል ወምስጋድ ወመስተስርየ ኃጢያት"

"ማንም ሰው የሚናገር ቢሆን፥ እንደ እግዚአብሔር ቃል ይናገር፤ የሚያገለግልም ቢሆን፥ እግዚአብሔር በሚሰጠኝ ኃይል ነው ብሎ ያገልግል፤ ክብርና ሥልጣን እስከ ዘላለም ድረስ ለእርሱ በሚሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።"                 1ኛ ጴጥ 4፥11

"ወደ እግዚአብሔርም በብርቱ ይጩሁ ሰዎችም ሁሉ ከክፉ መንገዳቸውና በእጃቸው ካለው ግፍ ይመለሱ።" ትን.ዮና. 3÷8 🕯ልዩ የአርብ ጸሎት🕯 👉 ውዳሴ ማርያም 👉 መሐረነ አብ 👉ስንክሳር 🗓 ሰኔ
"ወደ እግዚአብሔርም በብርቱ ይጩሁ ሰዎችም ሁሉ ከክፉ መንገዳቸውና በእጃቸው ካለው ግፍ ይመለሱ።"  ትን.ዮና. 3÷8 🕯ልዩ የአርብ ጸሎት🕯 👉 ውዳሴ ማርያም 👉 መሐረነ አብ 👉ስንክሳር           🗓 ሰኔ 19ቀን 2018 ዓ.ም          ⏰ ከቀኑ 12:30 ሰዓት ጀምሮ                💒 በሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ ኑ በህብረት  ስለ ወልድ ዋሕድ ስለ ቤተክርስቲያናችን ሰላም እና አንድነት  ወደ ፈጣሪያችን በጋራ  እንጸልይ‼

(AI)በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስዕላት እየታደሱና እየተተኩ ያሉት የቅድስት ቤተክርስቲያናችን ቅዱሳት ስዕላት
"ሁሉ በአግባብና በሥርዓት ይሁን" (፩ ቆሮ. ፲፬፡፵)
ክፍል -፩ መግቢያ- የቅዱሳት ስዕላት ምንነት፣ አገልግሎትና አሰራር ቅዱሳት የሚለው ቃል ደግሞ «ቀደሰ» ከሚለው የግዕዝ ግሥ ሲሆን ትርጉሙም ለየ፣ አከበረ፣ መረጠ ማለት ነው።ከዚህም በመነሳት ቅዱሳት ስዕላት ለእግዚአብሔር የተለዩ፣ የተቀደሱ ፣ልዩ ፣ ምርጥ፣ ንጹሕ እና ጽሩይ የሆኑ የቤተመቅደሱ መገልገያ ንዋያተ ቅድሳት በመሆናቸው «ቅዱሳት» ተብለው ይጠራሉ። ዳግመኛም የቅዱሳንን ታሪክ እና ማንነት በጊዜው ላልነበርን በመንፈስ ዓይን እንድናይ ስለሚያደርጉን፤ አንድም ሥጋዊውን ዓለም ከሚያንጸባርቁ ዓለማውያን ስዕላት ፈጽመው የተለዩ በመሆናቸው፤ አንድም የቅዱሳን ቅድስና ስዕላቱን ቅዱስ ስላሰኛቸው፤ አንድም በስዕላቱ አድሮ እግዚአብሔር ስለሚፈጽመው ገቢረ ተአምራት የተነሣ ስዕላቱ «ቅዱሳት ስዕላት» ተብለው ይጠራሉ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱሳት ስዕላት ተብለው የሚጠሩት ሐዋርያዊ ትውፊትንና ቀኖናን ጠብቀው የሚሣሉ የቅዱስ እግዚአብሔር፣ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ የቅዱሳን መላእክት፣ የቅዱሳን ነቢያት፣ የቅዱሳን ሐዋርያት እና የሌሎች ቅዱሳን ጻድቃን ማንነት፣ ሕይወትና ታሪክ የሚያሳዩ እና የሚወክሉ ስዕላት ናቸው፡፡ ዘጸ25፣18-22፤ 37፣7-9፤ዘጸ 26-31፤36፣8-35፡፡ በቅድስት ቤተክርስቲያናችን የምንገለገልባቸው ቅዱሳት ስዕላት የተሣሉት ባለቤቱ እግዚአብሔር በመረጣቸው ሰዎች አማካኝነት ነው፡፡ ለምሳሌ ያህልም ለመጀመሪያ ጊዜ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የስቅለቱን ስዕል ለንጉሥ ጢባርዮስ የሳለው ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ነበር፡፡ ቅዱሳት ስዕላት ቀኖና ቤተክርስቲያንን መሠረት ያደረገ የአሣሣል እና የአጠቃቀም ሥርዓት አላቸው፡፡ በቤተክርስቲያን ውስጥ ስለሚሰቀሉ ምእመናን በስዕሉ ፊት በመቆም የሚጸልዩበትና ልመናቸውን የሚያቀርቡበት ነው፡፡ ቅዱሳት ስዕላት በሚሣሉበት ወቅት አስቀድሞ የቅድስና ባለቤት ልዑል እግዚአብሔርን በጸሎት መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡ ይኸውም የዕውቀት እና የጥበብ ባለቤት እርሱ ስለሆነ ስዕላቱን ለመሣል የሚያስችል ጸጋ እንዲያድለን ነው፡፡ የቅዱሳት ስዕላት የቀለም አጠቃቀምም በሥርዓተ ቤተክርስቲያን አንድምታ ያለው እንጂ በዘፈቀደ የሚሆን አይደለም፡፡ ለምሳሌ ያህል ቀይ ቀለም ለቅዱሳን፣ ለጻድቃን እና ለሰማዕታት ወኪል የሆነ ሰማዕትነትን እና ተጋድሎን የሚያሳይ ነው፡፡ በመሆኑም በሰማዕታት ስዕላት ላይ ቀይ ቀለም በብዛት ሊስተዋል ይችላል፡፡ ነጭ ቀለም ንጽሐ ባሕርይን ስለሚያመለክት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እና በቅድስት ድንግል ማርያም የትንሣኤ እና የዕርገት ስዕላት ላይ ሊስተዋል ይችላል፡፡ ሰማያዊ ቀለም የእግዚአብሔርን ዘለዓለማዊ አምላክነት እና ቀዳማዊነት ስለሚያመለክት በቅድስት ሥላሴ ስዕለ አድኅኖ ልንመለከተው እንችላለን፡፡ ቅዱሳት ስዕላትን ለጸሎት እና ለተለያዩ አገልግሎቶች በምንጠቀምበት ጊዜ ልናስተውላቸው የሚገቡ ነገሮች አሉ፡፡ በዋነኛነትም እንዳይበላሹ እና እንዳይደበዝዙ በክብር ማስቀመጥ አስፈላጊ ነው፡፡ ስዕላቱ የሚገልጹት የስዕሉ ባለቤት የሆነውን አምላክ ወይም ቅዱስ፤ ጻድቅ ወይም ሰማዕት ስለሆነ ተገቢውን ክብር እና ሥርዓተ አምልኮ ማቅረብ ያስፈልጋል፡፡ ይቆየን ምንጭ ከመራሔ ብርሃናት ሰንበት ትምህርት ቤት የፌስቡክ ገጽ የተወሰደ

“ጊዜ ስላላችሁ ወደ እግዚአብሔር በንስሐ ተመለሱ በሲኦል ኃጢአትን መናዘዝና ንስሐ መግባት የሚችል ማንም የለም።’’ በንስሐ ወደ ቤተ ክርስቲያን አንድነት ለመግባት ከፈለጉ እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ ቃል ሊኖሩ ይገባል።                ✍️ቅዱስ አግናጥዮስ

ይህን ያደረገው መቃሪ ነው
አንድ ባህታዊ ከበረሃ ተቀምጦ ሳለ ስይጣን መጥቶ “ምነው ከዚህ ብቻህን ተቀመጥክ'' አለው፡፡ ባህታዊውም “እጸድቅ ብዬ" አለው። ዝም ብሎት ሔደ፡፡ ለሁለተኝ ጊዜ ሰይጣን መጥቶ “ምነው ብቻህን” አለው፤ “ክርስቶስን ባገኝው ብዬ ተቀምጪያለው” አለው፡፡ “ያሁኑ ይባስ'' ብሎት ሰይጣን ከአጠገቡ ራቅ፡፡ በኋላም አባ መቃርስ ሔዶ “ከአንተ ዘንድ ሰው አልመጣምን?'' አለው፤ “አልመጣም” አለ፡፡ የግድ ንገረኝ ቢለው “መጥቶ ነበር' አለው፡፡ “ምን አለህ?'' አለው፤ “ብቻህን ለምን ተቀምጠሀል አለኝ እጸድቅ ብዬ አልሁት ዝም ብሎ ሔደ፤ ሁለተኛ ጊዜ መጥቶ ምነው ብቻህን አለኝ ክርስቶስን ባገኝ ብዬ አልሁት ያሁኑ ይባስ ብሎኝ ሔደ'' አለው፡፡ አባ መቃርስም “ምነው እንዲህ ማለትህ ስለ ምንድነው? ክርስቶስን የምታገኝ አንተ ብቻ ነህን? በዓለሙ ያለው ክርስቶስን የማያገኘው ሆኖ ነውን? አሁን ደግሞ የመጣ እንደሆነ ግብሩ የከፋ ውሻን አስረው ለብቻው እንዲያኖሩት ባሕርዬ ቢከፋ ግብሬ ከሰው ባያስማማ ከዚህ መጥቼ ተቀምጫለሁ በለው እንጂ እንዲህ አትበለው።" ሰይጣንም ዳግመኛም መጣ “ምነው ብቻህን?'' አለው። ባህታዊውም መቃርስ እንዳለው ተናገረ፤ ይህን የሰማ ሰይጣንም “ይህን ያደረገው መቃሪ ነው እንጂ አንተ አይደለህም'' ብሎት ሔዷል፡፡ መጸሐፈ መነኮሳት

“የኃጢአት መጀመሪያና መንደርደሪያው ግዴለሽነት (አለ መጠንቀቅ) ነው።’’                       ✍️አባ ጴሜን

"ማንም እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ ወንድሙን ቢጠላ ሐሰተኛ ነው ፤ ያየውን ወንድሙን የማይወድ ያላየውን እግዚአብሔርን ሊወደው እንዴት ይችላል ?"      1ኛ ዮሐ 4÷20

Wednesday, 6h38m PM.m4a40.71 MB

"ከአፍህ የሚወጣውን ቃል መቆጣጠር ስትጀምር፣ ማር ይስሐቅ ሶርያዊ፦የልብህን ደጃፍ ዘጋህ ማለት ነው። ራሱን የሚገዛ ሰው፣ ማዕበል በሚያናውጠው ባሕር ላይ ጸጥ ብሎ እንደሚጓዝ መርከብ ነው።" ማር ይስሐቅ ሶርያዊ