en
Feedback
ወልድ ዋሕድ ሚዲያ welid wahid media

ወልድ ዋሕድ ሚዲያ welid wahid media

Open in Telegram

ይህ የኮተቤ መካነ ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና ቤተክርስቲያን ወልድ ዋሕድ ሰንበት ትምህርት ቤት ቻናል ነው 👉👉ለጠቅላላ @weldwahid 👉👉ለአብነት እና ግእዝ ቋንቋ ትምህርት @weldwahidabinet 👉👉 ለቤተ መጻሕፍት አገልግሎት @Abaiyesuslib 👉👉ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት @mels_asteyayet

Show more
2 120
Subscribers
+724 hours
+57 days
+2830 days
Posts Archive
ይቅርታ
"በጸሎት በቆማችሁ ጊዜ በሰማያት ያለው አባታችሁ ደግሞ ኃጢአታችሁን ይቅር እንዲላችሁ በማንም ላይ አንዳች ቢኖርባችሁ ይቅር በሉት" ማር 11÷25
በፋርስ ገዳም የነበሩ ሁለቱ አኃው በመንፈሳዊ ተጋድሎ ጸንተው የሚኖሩ እጅግ የሚፋቀሩ ሁለት መነኮሳት በእንድ የፋርስ ገዳም ውስጥ ይኖሩ ነበር፡፡ ሰይጣን በፍቅራቸውና በተጋድ እቸው እጅግ ስለ ቀና በመካከላቸው ጠብንና ክርክርን አስነሳ ሊግባቡም ስላልቻለ እንደኛው ገዳሙን ለቆ ሔደ፡፡ ከብዙ ጊዜ በኋላ በገዳሙ የቀረው ስለ ክርስቶስ እየመሰከረ ተይዞ በእስር ቤት ውስጥ ተጣለ፤ ወደ አገረ ገዥውም ቀርቦ ብዙ የተለያየ ዓይነት ሥቃይ ቢያበዙበትም ክርስቶስን ፈፅሞ ሊያስክዱት አልተቻላቸውም። ገዳሙን ለቆ የወጣው ሌላኛው አባት ወንድሙ ስለ ክርስቶስ በመመስከር ብዙ መከራን እየተቀበለ መሆኑን ሲሰማ በልቡ "ወንድሜ በሃይማኖቱ ከፀናና ስለ ክርስቶስ በመመስከር በሰውነቱ ላይ ከጨከነ በሰማዕትነት መሞቱ የማይቀር ነው፡፡ ታዲያ አንዳችን በአንዳችን ላይ የነበረንን ቁጣ እንደ ተሸከምን መሥዋዕት ቢሆን ከእርሱ ይልቅ ለእኔ የባሰ ፍርድ ይጠብቀኛል፡፡ ስለዚህ ወደ ወንድሜ በመሔድ ማረኝ ልለው ይገባኛል "በማለት ተፀፀተ፡፡ ካለበትም ተነስቶ ወንድሙ ወደታሠረበት ወኅኒ ቤት መጣ፡፡ ወደ ውስጥ ገብቶ በደሉን ይቅር እንዲለው እግሩ ላይወድቆ ለመነው፡፡ በወኅኒ የነበረው ወንድም ግን ይቅርታውን ሊቀበለው አልፈቀደም፡፡ ይልቁን ከቀድሞው በበለጠ በቁጣ መለሰለት እንጂ፡፡ ይህም ወንድም ይቅር ሊለው እንዳልወደደ ባየ ጊዜ እያዘነ መንገዱን ሔደ፡፡ በማግስቱ በወኅኒ የነበረው አባት በድጋሚ በገዥው ፊት ቀርቦ ክርስቶስን እንዲክድና ለጣዖት እንዲሠዋ ተጠየቀ፡፡ ገዢው እንዳልተቀበለው ባየ ጊዜ እንዲገርፋትና እንዲያሠቃዩት አዘዘ፡፡ ወታደሮቹ ቀርበው ገና ሁለት ጊዜ እንደ ገረፉት ክርስቶስን መካዱንና ለጣዖት ለመሠዋት መስማማቱን ገለፀ፡፡ አገረ ገዥው ከመገረሙ የተነሣ “እስከዛሬ የበለጡ መከራዎችንና ብሎ ጠየቀው፡፡ እርሱም መልሶ “ዛሬ እንዲህ በቀላሉ ለመካድ የበቃሁት ኃጢአትን በመሥራቴ ነው፡፡ በገዳም አብሮኝ ይኖር የነበረ ነገር ግን ተጣልተን የተለያየን እንድ ወንድም ነበረኝ:: ያለሁበትን ሁኔታ ስምቶ ይቅርታ ሊጠይቀኝና ከእኔ ጋር ሰላም ሊያደርግ ትናንትና ወኅኒ ቤት ድረስ መጥቶ ለመነኝ፡፡ እኔ ግን ይቅርታውን አልቀበልም በማለት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “እርስ በርስ ይቅር ተባባሉ የባልንጀራችሁንም በደል አታስቡ" ብሎ ያዘዘንን ትዕዛዝ ሳልፈፀም ቀረሁ። በዚህ በደሌ የተነሣ የእግዚአብሔር ጥበቃና እርዳታው ተለየኝ፡፡ በትንሹም ካድሁ፡፡ ከዚህ በፊት ግን ልታሠቃዩኝ ስትጀምሩ እጆቹ በእኔ ላይ ተዘርግተው ይታዩኝ ነበር። ስቃዩ እንዲሠማኝም አይፈቅድም ነበር፡፡ ዛሬ ግን ተለይቶኛል። በመሆኑም በትንሹ ፍርሃት ያዘኝና ካድኩ" ሲል ለገዥው ነገረው:: ገዥውም ማሠቃየታቸውን እንዲተውና እንዲፈቱት አዘዘ፡፡ እርሱም ወንድሙን ፍለጋ ሔደ ባገኘው ጊዜ እግሩ ላይ ወድቆ ይቅርይለው ዘንድ ለመነው፡፡ በመካከላቸውም ሰላም ሆነ፡፡ አንዳቸው ለአንዳቸው ከጸለዩም በኋላ በፍቅር ተለያዩ፡፡ አስቀድሞ ጌታችንን የካደውም ተመልሶ በገዥው ደጃፍ ላይ በመቆም ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር አምላክየለም እያለ መጮኸ ጀመረ፡፡ ምላሽ እንዳልሠጠው ባየ ጊዜም በከተማዋ ያለው የጣዖት ቤት በመሄድ አመድና ትቢያ እየበተነ ንጉሡንና ጣዖቱን ይራገም ጀመር፡፡ ከዚያም አልፎ ጣዖት የሚያመልኩትን ሁሉ በግልዕ ይገሥፅና ይዘልፋቸው ነበር፡፡ አገረ ገዥው ይህ ሊታገሠው ከሚችለው በላይ ስለሆነ አንገቱን ሰይፈው እንዲገድሉት ትዕዛዝ ሰጠ ።ወታደሮቹ ወደ መግደያው ይዘውት ሲሄዱ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይበእውነት ስምህ ቅዱስ ነው) ቸርነትህና ለኃጢአተኞች ያለህን ይቅርታ ብዙ የብዙ ጊዜ ብዙ ኃጢአት ሊክድነው አይችልም በማለት አመሰገነ: አንገቱንም ተሰይፎ በሰማዕትነት ዐረፈ። 📚ፍና ቅዱሳን 📝 ቀሲስ ታምራት ውቤ

“ ትሕትናን እንደ ልብስ ታጠቁ፥ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማልና፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል።”   — 1ኛ ጴጥሮስ 5፥5

"የወደድኩህ በጣም  ዘግይቼ ነው። ቀዳማዊ ብትሆንም ምን ጊዜም አዲስ ነህ። የወደድኩህ በጣም ዘግይቼ ነው አንተ በእኔ ውስጥ እያለህ እኔ በውጪ እፈልግህ ነበር። አንተ በፈጠርከውና ባሳመርከው ውስጥ ሁሉ ያለማስተዋል እባዝን ነበር። በዚህ ሁሉ ጊዜ ግን አንተ ከእኔ ጋር ነበርክ እኔ ግን ከአንተ ጋር አልነበርኩም።" ሊቀ ጳጳስ አውግስጢኖስ

"በሰዎች ዘንድ መናቅን፣ መሰደብንና መዋረድን የሚጠላ ስው የእግዚአብሔርን ክብር አያይም መንግሥቱንም አይወርስም፡ እንግዲያው ነፍሱን ሊያድን የሚወድድ ይህን ይወቅ፡፡ የሰዎችን ንቀትና ማዋረድ ብንታገሥ ምንም ነገር ሊስተካከለው በማይችል ክብርበእግዚአብሔር ዘንድ እንከብራለን፡፡ ምስጋናና ክብር ካለበት ሥፍራ ሁሉ ግን እንሽሽ፤ ነፍሳችንን ልናድንና መንግሥቱን ልንወርስ የምንችል እንደዚያ ስንሆን ብቻ ነውና፡፡ ቅዱስ ወንጌልና የምስጋና ዝማሬ ለቤተክርስቲያን በምንም የማይተኩ እንደሆኑ ሁሉ ለእግዚእብሔር አገልጋዮችም በስዎች መናቅና መዋረድ በምንም የማይተኩ ናቸው፡፡ በሰዎች መከበር ግን ለእኛ አንዳች ጥቅም አይገኝበትም"   ቅዱስ ኒፎን

"ያለፉት ቁስሎች ልብህን የመራራነት ምንጭ እንዲያደርጉላት ከቶ አትፍቀድ። ይቅር ለማለት ፈቃደኛ ሳትሆን ስትቀር የደስታህን ቁልፍ በበደሉህ ሰዎች እጅ ላይ እየተውከው ነው።"   ሊቁ አውግስጢኖስ

እንደ እግዚአብሔር ያለ አስተማሪ ማን ነው? (ኢዮ 36፤22)

" አፍህን እንደ ገና ሳቅ ይሞላል፥ ከንፈሮችህንም እልልታ ይሞላል። ኢዮብ 8፣21

🔔ቅዳሴ🔔 የ2018 ዓ.ም የመጨረሻዋ ሰንበትን በማስቀድስ እናሳልፍ!
+2
🔔ቅዳሴ🔔 የ2018 ዓ.ም የመጨረሻዋ ሰንበትን በማስቀድስ እናሳልፍ!

🎉 ለውድ ተመዝጋቢዎቻችን በሙሉ፤ በቅድሚያ እንኳን ደስ አላችሁ እያልን! 🎉 ​ ⛪️ የኮተቤ መካነ ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና ወልድ ዋሕድ ሰ/ት/ቤት የ2019 ዓ.ም የ4ኛ ዙር የርቀት ትምህርት ዝግጅታችንን አጠናቅቀን ምዝገባ እያካሄድን መሆኑን እያሳወቅን ​ 🗓 የትምህርቱ ቆይታ እና አጠቃላይ መርሃ ግብር (ለ1 ዓመት) የሚቆይ ሲሆን 📖 ከ1ኛ - 10ኛ ወር፦ በወር 1 ቀን የሚሰጡ 10 ተከታታይ ትምህርቶች 📝 በ5ኛው እና 10ኛው ወር አጋማሽ፦ አጠቃላይ የትምህርት ምዘና (ፈተና) 🏕 በ11ኛው ወር፦ ትምህርታዊ ጉዞ እና በምክረ አበው የታገዘ ተግባራዊ ሥልጠና 🎓 በ12ኛው ወር፦ የትምህርቱ ማጠቃለያ እና ታላቅ የምርቃት ስነ-ስርዓት! 📚 በርቀት ትምህርቱ የሚሰጡ  ትምህርቶች 🔹 ሀልዎተ እግዚአብሔር 🔹 አምስቱ አዕማደ ምሥጢራት 🔹 ነገረ ድኅነት 🔹 ነገረ ማርያም 🔹 ነገረ መላእክት 🔹 ነገረ ቅዱሳን ​
📅 መስከረም 10 ቀን ስለ ትምህርቱ አሰጣጥ ሰፋ ያለ የገለጻ (Orientation) መርሃ ግብር ይኖረናል።
​ 📲 ከትምህርቱ ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ተጨማሪ መረጃዎች እና መልእክቶችን በቴሌግራም ግሩፓችን ላይ የምናሳውቅ መሆኑን እየገለጽን፤ ይህ መንፈሳዊ ትምህርት ለሌሎችም እህት ወንድሞች እንዲደርስ፣ ከታች ያለውን ሊንክ ለወዳጅ ዘመድዎ ሼር (Share) በማድረግ ሁሉም እንዲመዘገቡ የበኩልዎን ይወጡ ስንል በትህትና እንጠየቃለን! 🙏 ​ 🔗 ለመመዝገብ እና ግሩፑን ለመቀላቀል ይህንን ይጫኑ፦ 👉 https://t.me/hanadistance2019 👈

“እግዚአብሔር በጥምቀት ልጅነትን ካገኘንባት ጊዜ ጀምሮ እነዚህን ሦስት ነገሮች ከእኛ ይሻል፦ በፍጹም እምነት የተሞላ ልብን፣ እውነትን ብቻ የሚናገር አንደበትን፣ ራስን በመግዛት የተሸለመ ሰውነትን።”
“እግዚአብሔር በጥምቀት ልጅነትን ካገኘንባት ጊዜ ጀምሮ እነዚህን ሦስት ነገሮች ከእኛ ይሻል፦ በፍጹም እምነት የተሞላ ልብን፣ እውነትን ብቻ የሚናገር አንደበትን፣ ራስን በመግዛት የተሸለመ ሰውነትን።” ቅዱስ ጎርጎርዮስ እንደመከረን!

"እነሆ በፊትህ የተከፈተች ደጅ ሰጥቼሀለሁ ሊዘጋት የሚችል የለም"ራዕ 3:7 "በእርግጥም እግዚአብሔር ለአንድ ሰው በርን በከፈተለት ጊዜ ሊዘጋበት የሚችል ማንም የለም።በመሆኑም እግዚአብሔር እንዲከፍትልህ ብትሻ የሚያስፈልግህ ነገር ቢኖር መጸለይ ነው። ስለዚህ ፕሮጀክትህን ሁሉ ዕቅድህንም ሁሉ ልትጀምር በፈለግህ ጊዜ ይህንን ጸሎት አድርስ።" አቡነ ሺኖዳ

"አምላካችን ያያል፣ አምላካችን ይሰማል፣ አምላካችንም ይፈታዋል (ያከናውነዋል)"። ቄስ ሚናስ አቡድ

Repost from N/a
🔔ተጀመረ🔔 በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው 4 ኛ ዙር የርቀት ትምህርት ምዝገባ ተጀመረ ቃለ እግዚአብሔር ለመማር ጊዜ የልዎትም እንግዲያስ በወር አንድ ቀን እየተገኙ መንፈሳዊ ዕውቀት ያዳብሩ። አዲስ ተማ
🔔ተጀመረ🔔 በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው 4 ኛ ዙር የርቀት ትምህርት  ምዝገባ ተጀመረ  ቃለ እግዚአብሔር ለመማር ጊዜ የልዎትም እንግዲያስ በወር አንድ ቀን እየተገኙ መንፈሳዊ ዕውቀት ያዳብሩ። አዲስ ተማሪዎች ለመመዝገብ ከፈለጉ በተቀመጠው ሊንክ በመግባት ሙሉ ስም፣ስልክ እና አድራሻዎትን በማሰቀመጥ መመዝገብ ይችላሉ። መልእክቱ  ለሁሉም እንዲደረስ በምንጠቀማቸው ማህበራዊ ሚዲያ እናሰተዋውቅ ​📝 ለመመዝገብ፦ ​ሊንኩን በመጫን ይሙሉ፦ 🔗 https://forms.gle/z3kBqFwfVubTKvhR6 ​ወይም በቴሌግራም @hanadistance2019 መረጃዎን እዚሁ በቴሌግራም ይላኩልን፦ ​🔹 ሙሉ ስም፦ 🔹 ስልክ ቁጥር፦ 🔹 አድራሻ፦ ያስቀምጡልን

በእግዚአብሔር አምኖ ያፈረ ማን ነው? በእግዚአብሔር አምኖ ያፈረ ማን ነው? እርሱን በመፍራት የታገሠና የተጣለ ማን ነው? ጠርቶትስ ቸል ያለው ማን ነው? እግዚአብሔር መሐሪ ይቅር ባይም ነውና፣ ኃጢአትን ይቅር ይላል፣ በመከራ ቀንም ያድናል። ሲራክ 2፡10-11

"ባሪያህ ወደዚህ ስፍራ የሚጸልየውን ጸሎት ትሰማ ዘንድ፦በዚያ ስሜ ይሆናል ወዳልኸው ስፍራ ወደዚህ ቤት ዐይኖችህ ሌሊትና ቀን የተገለጡ ይሁኑ።" 1ኛ ነገ 8፥29 🕯ሳምንታዊው የአርብ ጸሎት🕯 👉
"ባሪያህ ወደዚህ ስፍራ የሚጸልየውን ጸሎት ትሰማ ዘንድ፦በዚያ ስሜ ይሆናል ወዳልኸው ስፍራ ወደዚህ ቤት ዐይኖችህ ሌሊትና ቀን የተገለጡ ይሁኑ።" 1ኛ ነገ 8፥29 🕯ሳምንታዊው የአርብ ጸሎት🕯 👉 ውዳሴ ማርያም 👉 መሐረነ አብ 👉ስንክሳር 📆አርብ 4/07/2018 ዓ.ም 🕰12:30 በወልድ ዋሕድ ሰንበት ትምህርት ቤት አዳራሽ

“አንድ ሰው ራሱን ብቻ የሚወድ ከሆነ፥ እግዚአብሔርንም ሆነ ወንድሙን አይወድም። እንዲያውም በውስጡ ያለውን እውነተኛ ማንነት እንኳ አይወድም፤ ይልቁንም የሚወደው ስለ ራሱ ያለውን ሃሳብና ስለ ራሱ የ
“አንድ ሰው ራሱን ብቻ የሚወድ ከሆነ፥ እግዚአብሔርንም ሆነ ወንድሙን አይወድም። እንዲያውም በውስጡ ያለውን እውነተኛ ማንነት እንኳ አይወድም፤ ይልቁንም የሚወደው ስለ ራሱ ያለውን ሃሳብና ስለ ራሱ የፈጠረውን ቅዠት ብቻ ነው። በውስጡ ያለውን እውነተኛ ማንነት ቢወድ ኖሮ ግን፥ በእርሱ ውስጥ ያለውን የእግዚአብሔርን አምሳል ይወድ ነበር፤ በዚያው ቅጽበትም የእግዚአብሔርና የሰው ወዳጅ ይሆን ነበር። ምክንያቱም በሌሎች ሰዎች ውስጥም እግዚአብሔርንና የእርሱን አምሳል በፍቅር ይፈልግ ነበርና።” ቅዱስ ኒቆላስ

“ክፉ ሥራ የሚሠራው ክፋት በሚሠራበት ሰው ላይ ብቻ ተፈጽሞ አይቀርም፥ ይልቁንም ወደ አድራጊው ይመለሳል እንጂ። “ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

​✨ የረቡዕ ጉባኤ ✨ ​✨ መምህር፦ ሐብታሙ 📅 ቀን፦ ነሀሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ⏰ ሰዓት፦ ከምሽቱ 12:30 - 1:30 📍 ቦታ፦ ወልድ ዋሕድ ሰንበት ትምህርት ቤት አዳራሽ
+1
​✨ የረቡዕ ጉባኤ ✨ ​✨ መምህር፦  ሐብታሙ 📅 ቀን፦ ነሀሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ⏰ ሰዓት፦ ከምሽቱ 12:30 - 1:30 📍 ቦታ፦ ወልድ ዋሕድ ሰንበት ትምህርት ቤት አዳራሽ

✨ አቤቱ፥ መንገድህን አስተምረኝ፥ ስለ ጠላቶቼም በቀና መንገድ ምራኝ።✨ ፬ ቀናት ብቻ ቀሩን
✨ አቤቱ፥ መንገድህን አስተምረኝ፥ ስለ ጠላቶቼም በቀና መንገድ ምራኝ።✨ ፬ ቀናት ብቻ ቀሩን

“አንድ ሰው ራሱን ብቻ የሚወድ ከሆነ፥ እግዚአብሔርንም ሆነ ወንድሙን አይወድም። እንዲያውም በውስጡ ያለውን እውነተኛ ማንነት እንኳ አይወድም፤ ይልቁንም የሚወደው ስለ ራሱ ያለውን ሃሳብና ስለ ራሱ የፈጠረውን ቅዠት ብቻ ነው። በውስጡ ያለውን እውነተኛ ማንነት ቢወድ ኖሮ ግን፥ በእርሱ ውስጥ ያለውን የእግዚአብሔርን አምሳል ይወድ ነበር፤ በዚያው ቅጽበትም የእግዚአብሔርና የሰው ወዳጅ ይሆን ነበር። ምክንያቱም በሌሎች ሰዎች ውስጥም እግዚአብሔርንና የእርሱን አምሳል በፍቅር ይፈልግ ነበርና።” ቅዱስ ኒቆላስ