ወልድ ዋሕድ ሚዲያ welid wahid media
Ir al canal en Telegram
ይህ የኮተቤ መካነ ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና ቤተክርስቲያን ወልድ ዋሕድ ሰንበት ትምህርት ቤት ቻናል ነው 👉👉ለጠቅላላ @weldwahid 👉👉ለአብነት እና ግእዝ ቋንቋ ትምህርት @weldwahidabinet 👉👉 ለቤተ መጻሕፍት አገልግሎት @Abaiyesuslib 👉👉ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት @mels_asteyayet
Mostrar más2 052
Suscriptores
-224 horas
Sin datos7 días
+1430 días
Archivo de publicaciones
ሰላም ለኪ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
👉"ሰኔ 20 ቀንም ሐዋርያት የተሰበሰቡበት ልጅዋም ቤቷን ለመሥራት የወረደበት ነው" መቅድመ ተአምረ ማርያም ቁጥር 29
👉“እርሱም፦ ቤቴ የጸሎት ቤት ይሆናል ተብሎ ተጽፎአል፤ እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችሁት አላቸው።”
— ሉቃስ 19፥46
"ሰላም ለኪ ቅድስት ቤተክርስቲያን
አምሳለ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት
ማኅደረ መለኮት
ምስአል ወምስጋድ ወመስተስርየ ኃጢያት"
"ማንም ሰው የሚናገር ቢሆን፥ እንደ እግዚአብሔር ቃል ይናገር፤ የሚያገለግልም ቢሆን፥ እግዚአብሔር በሚሰጠኝ ኃይል ነው ብሎ ያገልግል፤ ክብርና ሥልጣን እስከ ዘላለም ድረስ ለእርሱ በሚሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።"
1ኛ ጴጥ 4፥11
"ወደ እግዚአብሔርም በብርቱ ይጩሁ ሰዎችም ሁሉ ከክፉ መንገዳቸውና በእጃቸው ካለው ግፍ ይመለሱ።" ትን.ዮና. 3÷8
🕯ልዩ የአርብ ጸሎት🕯
👉 ውዳሴ ማርያም
👉 መሐረነ አብ
👉ስንክሳር
🗓 ሰኔ 19ቀን 2018 ዓ.ም
⏰ ከቀኑ 12:30 ሰዓት ጀምሮ
💒 በሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ
ኑ በህብረት ስለ ወልድ ዋሕድ ስለ ቤተክርስቲያናችን ሰላም እና አንድነት ወደ ፈጣሪያችን በጋራ እንጸልይ‼
(AI)በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስዕላት እየታደሱና እየተተኩ ያሉት የቅድስት ቤተክርስቲያናችን ቅዱሳት ስዕላት
"ሁሉ በአግባብና በሥርዓት ይሁን" (፩ ቆሮ. ፲፬፡፵)ክፍል -፩ መግቢያ- የቅዱሳት ስዕላት ምንነት፣ አገልግሎትና አሰራር ቅዱሳት የሚለው ቃል ደግሞ «ቀደሰ» ከሚለው የግዕዝ ግሥ ሲሆን ትርጉሙም ለየ፣ አከበረ፣ መረጠ ማለት ነው።ከዚህም በመነሳት ቅዱሳት ስዕላት ለእግዚአብሔር የተለዩ፣ የተቀደሱ ፣ልዩ ፣ ምርጥ፣ ንጹሕ እና ጽሩይ የሆኑ የቤተመቅደሱ መገልገያ ንዋያተ ቅድሳት በመሆናቸው «ቅዱሳት» ተብለው ይጠራሉ። ዳግመኛም የቅዱሳንን ታሪክ እና ማንነት በጊዜው ላልነበርን በመንፈስ ዓይን እንድናይ ስለሚያደርጉን፤ አንድም ሥጋዊውን ዓለም ከሚያንጸባርቁ ዓለማውያን ስዕላት ፈጽመው የተለዩ በመሆናቸው፤ አንድም የቅዱሳን ቅድስና ስዕላቱን ቅዱስ ስላሰኛቸው፤ አንድም በስዕላቱ አድሮ እግዚአብሔር ስለሚፈጽመው ገቢረ ተአምራት የተነሣ ስዕላቱ «ቅዱሳት ስዕላት» ተብለው ይጠራሉ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱሳት ስዕላት ተብለው የሚጠሩት ሐዋርያዊ ትውፊትንና ቀኖናን ጠብቀው የሚሣሉ የቅዱስ እግዚአብሔር፣ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ የቅዱሳን መላእክት፣ የቅዱሳን ነቢያት፣ የቅዱሳን ሐዋርያት እና የሌሎች ቅዱሳን ጻድቃን ማንነት፣ ሕይወትና ታሪክ የሚያሳዩ እና የሚወክሉ ስዕላት ናቸው፡፡ ዘጸ25፣18-22፤ 37፣7-9፤ዘጸ 26-31፤36፣8-35፡፡ በቅድስት ቤተክርስቲያናችን የምንገለገልባቸው ቅዱሳት ስዕላት የተሣሉት ባለቤቱ እግዚአብሔር በመረጣቸው ሰዎች አማካኝነት ነው፡፡ ለምሳሌ ያህልም ለመጀመሪያ ጊዜ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የስቅለቱን ስዕል ለንጉሥ ጢባርዮስ የሳለው ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ነበር፡፡ ቅዱሳት ስዕላት ቀኖና ቤተክርስቲያንን መሠረት ያደረገ የአሣሣል እና የአጠቃቀም ሥርዓት አላቸው፡፡ በቤተክርስቲያን ውስጥ ስለሚሰቀሉ ምእመናን በስዕሉ ፊት በመቆም የሚጸልዩበትና ልመናቸውን የሚያቀርቡበት ነው፡፡ ቅዱሳት ስዕላት በሚሣሉበት ወቅት አስቀድሞ የቅድስና ባለቤት ልዑል እግዚአብሔርን በጸሎት መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡ ይኸውም የዕውቀት እና የጥበብ ባለቤት እርሱ ስለሆነ ስዕላቱን ለመሣል የሚያስችል ጸጋ እንዲያድለን ነው፡፡ የቅዱሳት ስዕላት የቀለም አጠቃቀምም በሥርዓተ ቤተክርስቲያን አንድምታ ያለው እንጂ በዘፈቀደ የሚሆን አይደለም፡፡ ለምሳሌ ያህል ቀይ ቀለም ለቅዱሳን፣ ለጻድቃን እና ለሰማዕታት ወኪል የሆነ ሰማዕትነትን እና ተጋድሎን የሚያሳይ ነው፡፡ በመሆኑም በሰማዕታት ስዕላት ላይ ቀይ ቀለም በብዛት ሊስተዋል ይችላል፡፡ ነጭ ቀለም ንጽሐ ባሕርይን ስለሚያመለክት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እና በቅድስት ድንግል ማርያም የትንሣኤ እና የዕርገት ስዕላት ላይ ሊስተዋል ይችላል፡፡ ሰማያዊ ቀለም የእግዚአብሔርን ዘለዓለማዊ አምላክነት እና ቀዳማዊነት ስለሚያመለክት በቅድስት ሥላሴ ስዕለ አድኅኖ ልንመለከተው እንችላለን፡፡ ቅዱሳት ስዕላትን ለጸሎት እና ለተለያዩ አገልግሎቶች በምንጠቀምበት ጊዜ ልናስተውላቸው የሚገቡ ነገሮች አሉ፡፡ በዋነኛነትም እንዳይበላሹ እና እንዳይደበዝዙ በክብር ማስቀመጥ አስፈላጊ ነው፡፡ ስዕላቱ የሚገልጹት የስዕሉ ባለቤት የሆነውን አምላክ ወይም ቅዱስ፤ ጻድቅ ወይም ሰማዕት ስለሆነ ተገቢውን ክብር እና ሥርዓተ አምልኮ ማቅረብ ያስፈልጋል፡፡ ይቆየን ምንጭ ከመራሔ ብርሃናት ሰንበት ትምህርት ቤት የፌስቡክ ገጽ የተወሰደ
“ጊዜ ስላላችሁ ወደ እግዚአብሔር በንስሐ ተመለሱ በሲኦል ኃጢአትን መናዘዝና ንስሐ መግባት የሚችል ማንም የለም።’’ በንስሐ ወደ ቤተ ክርስቲያን አንድነት ለመግባት ከፈለጉ
እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ ቃል ሊኖሩ ይገባል።
✍️ቅዱስ አግናጥዮስ
ይህን ያደረገው መቃሪ ነውአንድ ባህታዊ ከበረሃ ተቀምጦ ሳለ ስይጣን መጥቶ “ምነው ከዚህ ብቻህን ተቀመጥክ'' አለው፡፡ ባህታዊውም “እጸድቅ ብዬ" አለው። ዝም ብሎት ሔደ፡፡ ለሁለተኝ ጊዜ ሰይጣን መጥቶ “ምነው ብቻህን” አለው፤ “ክርስቶስን ባገኝው ብዬ ተቀምጪያለው” አለው፡፡ “ያሁኑ ይባስ'' ብሎት ሰይጣን ከአጠገቡ ራቅ፡፡ በኋላም አባ መቃርስ ሔዶ “ከአንተ ዘንድ ሰው አልመጣምን?'' አለው፤ “አልመጣም” አለ፡፡ የግድ ንገረኝ ቢለው “መጥቶ ነበር' አለው፡፡ “ምን አለህ?'' አለው፤ “ብቻህን ለምን ተቀምጠሀል አለኝ እጸድቅ ብዬ አልሁት ዝም ብሎ ሔደ፤ ሁለተኛ ጊዜ መጥቶ ምነው ብቻህን አለኝ ክርስቶስን ባገኝ ብዬ አልሁት ያሁኑ ይባስ ብሎኝ ሔደ'' አለው፡፡ አባ መቃርስም “ምነው እንዲህ ማለትህ ስለ ምንድነው? ክርስቶስን የምታገኝ አንተ ብቻ ነህን? በዓለሙ ያለው ክርስቶስን የማያገኘው ሆኖ ነውን? አሁን ደግሞ የመጣ እንደሆነ ግብሩ የከፋ ውሻን አስረው ለብቻው እንዲያኖሩት ባሕርዬ ቢከፋ ግብሬ ከሰው ባያስማማ ከዚህ መጥቼ ተቀምጫለሁ በለው እንጂ እንዲህ አትበለው።" ሰይጣንም ዳግመኛም መጣ “ምነው ብቻህን?'' አለው። ባህታዊውም መቃርስ እንዳለው ተናገረ፤ ይህን የሰማ ሰይጣንም “ይህን ያደረገው መቃሪ ነው እንጂ አንተ አይደለህም'' ብሎት ሔዷል፡፡ መጸሐፈ መነኮሳት
"ማንም እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ ወንድሙን ቢጠላ ሐሰተኛ ነው ፤ ያየውን ወንድሙን የማይወድ ያላየውን እግዚአብሔርን ሊወደው እንዴት ይችላል ?"
1ኛ ዮሐ 4÷20
"ከአፍህ የሚወጣውን ቃል መቆጣጠር ስትጀምር፣ ማር ይስሐቅ ሶርያዊ፦የልብህን ደጃፍ ዘጋህ ማለት ነው። ራሱን የሚገዛ ሰው፣ ማዕበል በሚያናውጠው ባሕር ላይ ጸጥ ብሎ እንደሚጓዝ መርከብ ነው።"
ማር ይስሐቅ ሶርያዊ
“ፈጣሪዬ ሆይ
በፊትህ የምንቀጠቀጥና
ኃይል የሌለኝ ባሪያህን አንተ አስበኝ
በሞገስና በቸርነትህ አትለየኝ።’’
✍️አቡነ ቄርሎስ
"ስለ ፈተና፣ ትዕግሥትና የነፍስ ፈውስ"የነፍስ ሐኪም የሚባለው ቅዱስ ይስሐቅ፣ ልባቸው ለደከመና በሐዘን ለተጠቁ ሰዎች የሰጠው ረጅም ተግሳጽና ምክር እንዲህ ይላል፡- "ነፍስህ በሐዘን ስትከበብ፣ በዙሪያህ ያሉት ሁሉ የጨለሙ ሲመስሉህ መጸለይ እንኳ ቢከብድህ በዝምታ በፈጣሪህ ፊት ተንበርከክ። ዝምታህ ራሱ ጸሎት ነው። እግዚአብሔር ካለ ፈቃዱ መከራ እንዲነካህ አይፈቅድም። ፈተናዎች የሚበዙት እግዚአብሔር ስለጠላህ ሳይሆን፣ ለአንተ ስላዘጋጀው ትልቅ የነፍስ ማደጊያ ነው። ያለ ፈተና የሚኖር ሰው ካለ እርሱ ከእግዚአብሔር መንገድ የወጣ ነው። ስለዚህ ሕመምህ፣ ስብራትህ፣ በሰው ዘንድ መናቅህ ሁሉ በሰማይ መዝገብ እየተጻፈልህ ነው። ልብህን ለቂምና ለጥላቻ አትስጥ። ሰውን አትውቀስ፤ ይልቁኑ 'አቤቱ በዚህ መከራ ውስጥ የምማረውን ጥበብ ስጠኝ በል። ሕመምህን በትዕግሥት ስትቀበለው፣ ያ ሕመም ራሱ ኃጢአትህን የሚያጥብልህ እሳት ይሆናል። ነፍስህ ስትታመም ወደ እግዚአብሔር ጩህ፤ እርሱ በጊዜው ያጽናናሃል።" ቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊ
“ሕይወታችን ብሩህ ቢሆን ኖሮ
በድርጊታችን ከመሰከርን
ቃላት ባላስፈለገም ነበር፣
እውነተኛ ክርስቲያኖች ብንሆን
አረማውያን አይኖሩም ነበር።’’
✍️ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
"ጌታ እውነተኛ ወዳጅ ነው ጓደኞችህ ወንድሞችህ ሲረሱህ እርሱ አይረሳህም አይለይህም ካንተ ጋር ነው።"
ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
"ሰዎች ስምህን ቢያጠፋና በሐሰት ቢከሱህ ለመከላከል ፈጽሞ አትከራከር ።እግዚአብሔር ስምህን በሕየወት መጽሐፍ ላይ እስከጻፈው ድረስ ፣ ሰዎች በምድር ላይ ስምህን ቢያጠፉት ምን ያሳጣሃል ? የአንተ ዝምታ እግዚአብሔር ለአንተ እንዲሟገትልህ መንገዱን ይከፍታል ፣ አንተ ለመሟገት ስትነሣ ግን እግዚአብሔር እጁን ያነሣል።"
ቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊ
"እግዚአብሔር ይነሣ፥ ጠላቶቹም ይበተኑ፥ የሚጠሉትም ከፊቱ ይሽሹ።ጢስ እንደሚበንን እንዲሁ ይብነኑ፤ ሰም በእሳት ፊት እንደሚቀልጥ፥ እንዲሁ ኅጥኣን ከእግዚአብሔር ፊት ይጥፉ።" መዝ 68÷1-2
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
