1 555
Subscribers
+424 hours
+77 days
-1830 days
Posts Archive
1 555
“በመጨረሻይቱም (አለም) እነርሱ የሚያረጋግጡ ከሆኑት (መሪ ነው)። (አል' በቀራህ፡ 4)
በዚህ የቁርኣን አንቀጽ የተፈለገው ሲቀጠሩት የነበረው ነገር እንደመጣቸው እርሱም የቂን (ሞት) እንደሆነ ይገልጻል፡፡))
ይህ አንቀጽ ፣ ዓቅለኛ ሆኖ ለአካለ መጠን ከደረሰበት ጊዜ ጀምሮ _ እስኪሞት ድረስ ዒባዳ ዋጅብ እንደሆነ ፣ ሱፍያዎች እንደሚሉት ከሞት በፊት ግዴታ የሚቆምበት “ሀል” የሚባል እንደሌለ ይጠቁማል፡፡
ይህ ፣ ድሮም ይሁን አሁን የሱፍያ ዲን ነው፡፡ ዒባዳን አስመልክቶ የሱፍያ አቋም ይህ ነው፡፡ ከሱፍያዎች ኪታብ የነቀልነው ጥቂቱን ብቻ ነው… እኔ በጥናቴ ላይ ትኩረት ያደረኩት የዒባዳውን እና በዒባዳ ላይ ያላቸውን አቋም ብቻ ነው፡፡ ሌሎችም ልክበተውሂድ ፣ በሩሡሎች መልእክተኛነት ፣ በሸሪዓው እና በቀደር ዙሪያ አቋም እንዳላቸው ሁሉ ባልተጠቀሱ የቀሩ ጉዳዮችም የተለዩ አቋሞች ያሏቸው ሲሆን ይህን
ለማብራራት ተከታታይና በጣም ሰፋ ያሉ ማብራሪያዎች ይሻል በዚህ እርስ ግን ለቅምሻ ያክል የስኳሁኑ ይበቃናል
ሀቅን በሀቅነቱ እንዲያሳየን እና መከተልንም እንዲለግሰን ፤ ባጢልንም በባጢልነት እንዲያሳየን እና መራቅን እንዲቸረን ፤ ከመራን በኋላ ልቦቻችንንም እንዳያጠምብን
አላህን እለምነዋለሁ፡፡
#ክፍል1 https://t.me/AbulQmane/2148
ክፍል2 https://t.me/AbulQmane/2149
ክፍል3 https://t.me/AbulQmane/2150
ክፍል4 https://t.me/AbulQmane/2172
ክፍል5 https://t.me/AbulQmane/2176
ክፍል6 https://t.me/AbulQmane/2219
1 555
🔺ሱፊያዎች በዲንና በዒባዳ መሰረቶቸ ላይ ያአላቸው ስህቱ አቋም #ክፍል6
~~~
وموقف الصوفية من أصول العبادة والدين
ስድስተኛ፡- ባጢል (ስህተት) ከሆነው የሱፍያ ዲን መካከል ፡ አንድ ሰው ከሸሪዓዊ ሀላፊነት የሚወጣበት ደረጃ አለ ማለታቸው ነው
ይህ የተሶውፍ አመለካከት ድንበር አልፎ የጥመትን ጫፍ የመድረሱ ውጤት ነው፡፡ የተሶውፍ መሰረቱ ኢብን አልጀውዝይ እንደተናገረው ነበር፡-ወራዳ የሆነን ስነምግባር ታግሎ መመለስ፣ ነፍስን አሰልጥኖ ወደጥሩ ስነምግባርመውሰድ፡፡ ዙህድ ፣ ችሎታ ፣ ትዕግስት ፣ ኢኽላስ እና እውነተኛነት፡፡))
በተጨማሪ የሚከተለውን ተናግሯል፡- ((የመጀመሪያዎቹ (ሱፍዮች) ባህሪ ይህ ነበር ፤ አንዳንድ ነገሮችን ኢብሊስ እነርሱን ከዚያም ተከታዮቻቸውን ቀላቀለባቸው፡፡ አንድ ክፍለ ዘመን ባለፈ ቁጥር በሁለተኛው ክፍለ ዘመን (ሰይጣን) ወደኋላ ላሉት የበለጠ የተመቻቸ እስኪሆንለት ድረስ በሰዎች ላይ ዲናቸውን ይቀላቅልባቸዋል፡፡ ዋናው የመቀላቀል መሰረቱ ከእውቀት ማገዱ ፣ ተፈላጊው አላማ እውቀት ሳይሆን ተግባር ነው ብሎ ማሳየቱ ነው፡፡ የሰይጣን ዋና አላማ የእውቀትን መብራት በእነርሱ ላይ ካጠፋ በኋላ በጨለማ እንዲደናበሩ ማድረግ ነው፡፡ ይህ ብቻ አይደለም ዱንያን በአጠቃላይመተው አስፈላጊ እንደሆነ ያሳያቸዋል፡፡ አካላቸውን የሚያስተካክሉበትን ዱንያ እንዲተው ያደርጋቸዋል፡፡ ገንዘብን ከጊንጥ ጋር ያመሳስሉታል … ነፍስን ከአቅም በላይእንድትሸከም ያደርጓታል፡፡ ጭራሽ ከአልጋ ላይ መጋደምን አያስፈልግም እስከማለት ይደርሳሉ … ከእነርሱ መካከል እውቀት ካለመኖሩ የተነሳ ሳያውቅ በረሡል ላይበተዋሹ ሐዲሶች ለመተግበር ይሞክራል፡፡ ከዚያም ሰዎች መራብ ፣ መደህየት እንዳለባቸው በወስዋስ (በብዥታ) ላይ የሚቀሰቅሱ መጽሐፎችን የጻፉ ሰዎች መጡ፡፡ ልክ እንደ ሀሪስ አልሙሀሲቢ ማለት ነው፡፡
ሌላው ደግሞ መጣ የሱፍያን መዝሀብ ማጣራት ጀመረ ፣ እነርሱ የሚለዩበትን ባህሪዎች ነጥሎ አስቀመጠ፡፡ የሱፍያ ባህሪ በማጨብጨብ ፣ በመወዛወዝ ፣ በዜማ የተለየ እንደሆነ ግልጽ አደረገ፡፡ አሁንም ነገሩ በዚህ አላቆመም እየጨመረ ሄደ፡፡ መሻይኾቻቸው …. ከዑለማ ራቁ እነርሱ ያሉበትን “ኢልመል ባጢን”(ስውር እውቀት)በማለት ሰየሙ ፣ የሸሪዓውን እውቀት ደግሞ “ኢልመ ዟሂር” (ግልጽ እውቀት) በማለት ሰየሙ፡፡ ከእነርሱ መካከል ከረሐብ የተነሳ ብዥታ ውስጥ የወደቀውን ፣ በቃ ይህ ግለሰብ የአላህ ከፍተኛ ወዳጅ እንደሆነ አድርገው ቆጠሩ…እነዚህ ሰዎች በክህደትና በቢድዓ መካከል ሆኑ፡፡ ከዚያም ጦሪቃዎች በርካታ ሆኑ (1) ፣ ዓቂዳቸውም በዚህ ምክንያት ተበላሸ፡፡ ከእነርሱ መካከል የ “ሁሉል” ዓቂዳ ያለው አለ፡፡ ከእነርሱ መካከል የኢቲሃድ ዓቂዳ ያለው አለ፡፡ ኢብሊስ በቢድዓ የእውቀት አይነቶች እንዲዋዥቁ ከማድረግ አልተወገደም …)) (
📕ተልቢስ አል'ኢብሊስ 157-158)
ሸይኹል ኢስላም ብን ተይሚያ - ረሂመሁሏህ - የሚከተለውን ጥያቄ ተጠየቁ፡-
((አንዳንድ ሰዎች አሉ ነፍስን በማለማመድ የዘወተሩ ፣ ከዚያም እራሳቸውን ጀውሐር (በራሳቸው የተብቃቁ) ነን ብለው ያሰቡ ፤ “… ፣ ትዕዛዝ ክልከላ የተራው ማህበረሰብ መንገድ ነው ፣ እነርሱም ጀውሐር ደረጃ ቢደርሱ ሁሉም ነገር ከእነርሱ ላይይነሳላቸው ነበር፡፡ ነብይነት ተራውን ማህበረሰብ በህግ ለመዳኘት እና ስርዓት የማስያዝ ጥበብ ነው፡፡ እኛ ደግሞ ከተራው ማህበረሰብ አይደለንም፡፡ በተክሊፍ (በህግ) ጓዳ የምንገባ አይደለንም፡፡ እኛ ጀውሀር ሆነናል ጥበብን አውቀናል ይላሉ፡፡”
መልስ፡- ይህ ንግግር ከአይሁድና ነሷራ ንግግር የከፋ ትልቅና ከባድ ክህደት እንደሆነ ከኢማን እና ዒልም ባለቤቶች ዘንድ ጥርጥር የለውም፡፡ አይሁድና ነሷራ በተወሰኑ ኪታቦች አመኑ በከፊሉ ካዱ፡፡ እነዚህ ከሐዲ ከመሆናቸው ጋር ለአላህ ትዕዛዝን ፣ ክልከላን ፣ ዛቻ ፣ ቀጠሮ እንዳለ ያምናሉ ይህም የተሰረዘረውን የተቀየረውን አይሁድነትን እና ነሷራነትን አጥብቀው እስከያዙ ድረስ ነው፡፡ከእነርሱ አማኞች ውስጥ ሙናፊቆቻቸው ማለትም ፈላስፎቻቸው ከዚህ ኡመት ሙናፊቆች በጣም የከፉ ናቸው፡፡ ምክንያቱም ክህደትን ይፋ አድርገው ፣ ኒፋቅን ድብቅ አደረጉ፡፡ ኢማንን ይፋ አድርጎ ንፍቅናን ከደበቀው የከፋ ሆነ፡፡
የተፈለገው አላማ ፣ በተሰረዘው ጥቅል ህግ አጥብቀው ከያዙት ነሷራ እና አይሁድ በአጠቃላይ ትዕዛዝ ክልከላ ከእኔ ላይ ወድቆልኛል ከሚለው ሱፍያ የተሻለ ነው ። እነዚህ ከማንኛውም መጽሓፍ ፣ ሸሪዓዎች እና ሚለሎች ሁሉ አፈንግጠዋል፡፡ ምክንያቱም ለአላህ መታዘዝና መከልከል የሚባል ነገር ከእነርሱ ዘንድ የለም፡፡ እንደውም ከዚህ በፊት ከኢብራሂም ቅሪት መጽሓፍትን አጥብቀው ከያዙት የአረብ ሙሽሪኮችም ይከፋሉ፡፡ እነዚህ ሙሽሪክ ከመሆናቸው ጋር እነርሱ የያዙት የተወሰነ ሐቅ አለ፡፡ እነዚህ ግን ፣ ከሐቅ የወጡ ናቸው ፤ ከሐቅ አንድም የያዙት የለም፡፡ እነርሱ ፣ ትዕዛዝንም ክልክልንም ሙሉ በሙሉ ዝግ አድርገዋል፡፡))
በመቀጠል እንዲህ ይላል፡- ((ከእነርሱ መካከል በሚከተለው ቁርኣን ማስረጃ የሚያደርግ አለ፡-
وَاعْبُدْ رَبَّكَ حَتَّىٰ يَأْتِيَكَ الْيَقِينُ
እውነቱም (ሞት) እስኪመጣህ ድረስ ጌታህን ተገዛ፡፡
Surah: Al-Hijr, Ayat: 99
የዚህ ትርጉሙ፡ “ጌታህን ተገዛ እውቀት እና ግንዛቤ እስክትደርስ” ማለት ነው ይላሉ፡፡ ከዚህ ደረጃ ከደረስክ ዒባዳ ከአንተ ላይ ይነሳልሃል፡፡ አንዳንዶች ደግሞ ፡ “የሆነ ባህሪ ላይ እስክትደርስ ድረስ ስራ” ይላሉ፡፡ የሱፍያ ባህሪ ላይ ከደረስክ ዒባዳ ከአንተ ላይ ይነሳልሃል፡፡ እውቀትና ግንዛቤ ላይ ከደረሱ ፈርድ ይተዋሉ ፤ ሀራም ይሰራሉ፡፡ ይህ ከዚህ በፊት እንዳስቀደምነው ግልጽ የሆነ ክህደት ነው፡፡በእነርሱ ላይ እንጅ ለእነርሱ ማስረጃ ሆኖ የሚያገለግል አይደለም፡፡
ሀሰን አልበስርይ - ረሂመሁሏህ - የሚከተለውን ተናግረዋል፡-
" إن الله لم يجعل لعمل المؤمنين أجلا دون الموت"
“ለሙእሚን ከሞት በፊት (ስራን የሚያቆምበት) የጊዜ (ገደብ) አላህ አላደረገም” ከዚያም የሚከተለውን ቁርኣን አነበበ፡-
وَاعْبُدْ رَبَّكَ حَتَّىٰ يَأْتِيَكَ الْيَقِينُ
እውነቱም (ሞት) እስኪመጣህ ድረስ ጌታህን ተገዛ፡፡
“የቂን” ማለት ሞት እና ከሞት በኋላ መሆኑን ዑለሞች በአጠቃላይ ተስማምተዋል፡፡ ለዚህ ተመሳሳይ የሚከተለው ቁርኣን ማስረጃ ይሆናል፡፡
مَا سَلَكَكُمۡ فِي سَقَرَ
(ይሏቸዋልም) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?»
وَلَمْ نَكُ نُطْعِمُ الْمِسْكِينَ
"ምስኪኖችንም አንመግብም ነበር።"
وَكُنَّا نَخُوضُ مَعَ الْخَائِضِينَ
"ከከንቱ ንግግርና ከሐሰት ጋር ከሚገቡ ሰዎች ጋር እንገባ ነበር።"
وَكُنَّا نُكَذِّبُ بِيَوْمِ الدِّينِ
"የፍርድ ቀንንም እናስተባብል ነበር።"
حَتَّىٰ أَتَانَا الْيَقِينُ
"እርግጠኛው ነገር (ሞት) እስከ መጣብን ድረስ።"
ሱረቱ አል ሙደሲር42-47
ይህን ቃል ሶላትንና ዘካን እንደተው ፣ በትንሳኤ ቀን መዋሸታቸውን ፣ ሞት እስኪመጣቸው ድረስ ከሚዘባርቁት ጋር መዘባረቃቸውን የተናገሩት በጀሀነም ውስጥ ሆነው ነው፡፡ እነርሱ በዚህ ባህሪ ላይ ሆነው በዱንያ ላይ አማኝ ያልነበሩ መሆናቸው የታወቀ ጉዳይ ነው፡፡ አላህ በሚከተለው ቃል ከተናገረላቸው ሰዎችም አይደለም፡፡
وَبِالْآخِرَةِ هُمْ يُوقِنُونَ
1 555
🔺ስንወለድ ሙስሊም ነን ሲባል ?
~~~~
«ፊጥራ» الْفِطْرَةِ ማለት 'ተፈጥሯዊ ዝንባሌ' natural inclination ማለት ሲሆን፥ ይህም አምላክ አጠቃላይ የሰው ልጆችን ሁሉ እኩል አድርጎ የፈጠረውን ንጹሕ ማንነታችንን የሚገልጽ ቃል ነው። በእስልምና አስተምህሮ ድቀተ-ባሕርይ ወይም ጥንተ-አብሶ 'original sin' እየተባለ ከውልደታችን ጀምረን በውርስ ያመጣነው አንድም ነገር ባለመኖሩ ሁሉም ሰው ሲወለድ ያልተበከለ እና ኃጢአት አልባ የሆነውን አዲስ ማንነት ይዞ ነው። ይህ በተፈጠሮ ንጹሕ የሆነው ማንነት 'ፊጥራ' ተብሎ ይጠራል።
عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رضى الله عنه قَالَ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم كُلُّ مَوْلُودٍ يُولَدُ عَلَى الْفِطْرَةِ، فَأَبَوَاهُ يُهَوِّدَانِهِ أَوْ يُنَصِّرَانِهِ أَوْ يُمَجِّسَانِهِ،
የአላህ መልዕክተኛ ❲ﷺ❳ እንዲህ ብለዋል:- "ሁሉም የሚወለደው ሰው በፊጥራ ላይ ነው። ወላጆቹ ግን አይሁድ፣ ክርስቲያን ወይም ዞርስቲያን ያደርጉታል።"
(📚Sahih al-Bukhari 1385: Book 23, Hadith 137)
ከዚህ ሐዲስ በግልጽ የምንረዳው፥ አንድ ህጻን በወላጆቹ ጫና ወደ ኩፍር ከመግባቱ በፊት ያልተበረዘ ማንነት (ፊጥራ) ላይ መሆኑን ነው። ቡኋለ ላይ የተለያዩ ክህደቶችን በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ይፈፅማል። ያኔ ያ ንጹሕ ተፈጥሯዊ ዝንባሌው ጠፍቶ ካፊር ይሆናል። አምላካችን አላህ በቅዱስ ቃሉ ይህን 'ንጹሕ ፈለግ' ያዙ፣ ከዚያም አትውጡ በማለት ያዘናል፥ ❲ምዕራፍ 30፥30❳...ይህን ስንል ግን አንድ ሰው ሲፈጠር (ሲወለድ) የእስልምናን ሃይማኖት ሕግ እና ስርዓት አውቆ ይመጣል ማለታችን አይደለም። የትኛውም ሰው ሃይማኖተኛ ሆኖ ወደዚህ ምድር አይመጣም።
ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያህ እንዲህ ይላሉ:-
ولا يلزم من كونهم مولودين على الفطرة أن يكونوا حين الولادة معتقدين للإسلام بالفعل فإن الله أخرجنا من بطون أمهاتنا لا نعلم شيئا ولكن سلامة القلب وقبوله وإرادته للحق : الذي هو الإسلام بحيث لو ترك من غير مغير لما كان إلا مسلما
«በፊጥራ (ተፈጥሯዊ ዝንባሌ) ላይ ተወለዱ ሲባል በተወለዱበት ወቅት እስልምናን በተግባር ይፈፅሙታል (ያውቁታል) ማለት አይደለም። ምክንያቱም አላህ ከእናቶቻችን ሆድ ሲያወጣን ምንም የማናውቅ አድርጎን ነውና። ስለዚህ እውነትን ይፈልግ ዘንድ የልብን ንጽሕና ሰጥቶታል። አንዳች በካይ ባይቀይረው ኖሮ ከሙስሊም ውጪ ሌላ አይሆንም። ❲መጅሙዕ አል-ፈታዋ ቅፅ 4/247❳
ሸይኹ አክሎም እንዲህ ይላሉ:- ‟ይህ ተፈጥሯዊ ዝንባሌ በራሱ የአምላክን መኖር ያረጋግጣል፣ እርሱን መውደድና ብቻውን ልናመልከው እንደሚገባ ይጠቁማል።” አዎ ተፈጥሮ አንድ አምላክ መኖሩን ያሳያል፣ ያ አምላክ ሁሉን ቻይ፣ ፍቅር (ወዳድ)፣ ከእኛ ጋር የሆነ ገዢ ኃይል መኖሩን ገና ከልጅነታችን ጀምሮ እንድናውቅ ያደርገናል። አንዳች አደጋ ሲደርስብን ልባችን ቶሎ ያድናት ዘንድ የምትማፀነው ያ የማይታየው አካል እርሱ አምላክ ነው። ይህ በተፈጥሮ የምናውቀው የኃያል አምላክ ባህሪ ነው። ይህን ታላቅ አምላክ በትክክል ማወቅ ግዴታ ስለሆነ አምላክ በነቢያቱ በኩል እራሱን ለእኛ ግልጽ አድርጓል። ስናጠቃልል:- ሰው ሲወለድ ሃይማኖተኛ ሆኖ አይደለም፣ በተፈጥሮ ለአምላክ ታዛዥ ከመሆኑ አንጻር ሙስሊም መባሉ እውነት ቢሆንም ከTheological perspective በኩል ከሆነ ግን ትክክል አይደለም። ያን እስልምና የምናገኘው በነቢያት ትምህርት ብቻ ነው።
https://t.me/AbulQmane
1 555
🔺የአላህ ባህሪያት አይነቶች
~~~~~~
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኃሩኃ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው::
ስለ አላህ ባህሪያት ስናወራ ከሰሞኑ በጣም ወሳኝ እና አንገብጋቢ ጉዳዮችን ለመዳሰስ ሞክረናል:: ዛሬም ይህንኑ ጉዙ በርዕሱ ስር አሉ ከሚባሉ አጭር ነገር ግን ወሳኝ ሃሳቦች መካከል የሆነውን የአላህ ባህሪያት አይነቶችን አስቀምጥላቹሀለው:: የአላህን ባህሪያት ከሁለት ነገር አንጻር ለ2 እንከፍላቸዋለን:-
1.ባህሪያቱን ከተግባር አንጻር (ሲፋት አስ-ዛት እና ሲፋት አል-ፊዕሊያ)
ይህ ምድብ ባህሪያቱ ከአላህ ህልውና (ዛት) ጋር ያላቸውን ቁርኝት መሰረት ያደረገ ነው፡-
ሲፋት አዝ-ዛት (የገሀዳዊ መለያ ባህሪያት)፦ በፍልስፍናው አለም Essential Attributes ወይም Ontological Attributes ብለን እንጠራቸዋለን::
እነዚህ አላህ ሁልጊዜም የነበሩትና ከእሱ የማይለዩ፣ መጀመሪያም የሌላቸው መጨረሻም የሌላቸው ባህሪያት ናቸው።
ልክ እንደ እውቀት፣ ህያውነት፣ ችሎታ ፣ መስማት፣ ማየት እና የበላይነት (ዑሉው) እና በቁርኣንና በሐዲስ የተጠቀሱትን በሙሉ ያካታል እነሱም እጅ፣ጣት፣ እግር... ናቸው።
ሲፋት አል-ፊዕሊያ (የተግባር ባህሪያት)፦ Active Attributes ወይም Relational Attributes ብለን እንጠራቸዋለን::
እነዚህ አላህ ከፍላጎቱና ከጥበቡ (ሒክማህ) ጋር አያይዞ በፈለገው ጊዜ የሚከውናቸው ተግባራዊ ባህሪያት ናቸው።
ለምሳሌ፦ መፍጠር ፣ ሲሳይን መስጠት ፣ ወደ ቅርቢቱ ሰማይ መውረድ ናቸው ።
2.ባህሪያቱን ከማረጋገጥና ከመካድ አንጻር (ሲፋት አል-ሙስበታህ እና አስ-ሰልቢያ)
ሲፋት አል-ሙስበታህ (የማረጋገጫ ባህሪያት)፦ አላህ በቁርኣን ውስጥ ወይም ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) በሀዲስ ያረጋገጡለት የፍጹምነት ባህሪያት ናቸው። (ለምሳሌ፡- እዝነት፣ ኃያልነት፣ ጥበብ)።
ሲፋት አስ-ሰልቢያ (የማግለያ ባህሪያት)፦ ከአላህ ባህሪ ጋር የማይመጥኑ፣ ጉድለትን የሚያሳዩ እና ከእሱ ላይ መነሳትና መራቅ ያለባቸው ባህሪያት ናቸው።
ምሳሌ፦ አለመሞት (ሞትን ማንሳት)፣ አለመተኛት ወይም አለመንቀላፋት፣ አለመበደል፣ እና ድካም አላህን እንደማይነካው ማረጋገጥ።
በቀላሉ የአላህ ባህሪያት አይነቶች እነዚህ ናቸው በጣም ቀላል ነገር ግን ልንገነዘባቸው የሚገቡ ናቸው:: በቀጣይ ዙፈቱል ፊዕሊያ እና ዛቲያህ ውስጥ የተጠቀሱ የአላህ ባሕሪያትን ወደፊት አላህ ካለ "እናያለን"
https://t.me/AbulQmane
1 555
አልተገለፀም" እንዳለው፣ ክርስቲያኑም "ሚስጥር ነው / መንፈስ ነው / አይታወቅም" ወደሚል መልስ መምጣቱ አይቀርም።ታዲያ የራሳቸው የነገረ-መለኮት (Theology) ሊመልሰው ያልቻለውን፣ "ሚስጥር ነው" ብለው የሚያልፉትን ጥያቄ፣ ሙስሊሙ "ተውቂፊያህ ነው (አልተገለፀም)" ሲል ለምን ያላግጣሉ? ይህ ከድንቁርና የመነጨ ሁለት አይነት ሚዛን (Double Standard) ነው!⏱ በአጭሩ ስጠቀልለው፦"ስለ አላህ አካላዊ አወቃቀር አልተገለፀም ስንል፣ 'የምናመልከው አምላክ ማን እንደሆነ አናውቅም' ማለታችን አይደለም! እኛየምናመልከው አምላክ ማንነቱ (አዛኝነቱ፣ ኃያልነቱ፣ ፈጣሪነቱ፣ ጥበበኝነቱ) በግልፅ የታወቀ አምላክ ነው። ነገር ግን አካላዊ አወቃቀሩን (Anatomy) አልተገለፀም ያልንበት ምክንያት... እናንተ እንደምታስቡት አላህ የጨጓራ፣ የኩላሊት፣ የተጣበቀ ጅማት እና የብልት ስብስብ የሆነ 'ባዮሎጂካዊ ሮቦት' ወይም የጥንት ግሪክ አፈ-ታሪክ (Mythology) አምላክ ስላልሆነ ነው! ፈጣሪ ከፍጡር ባዮሎጂ የጠራ ነው። አዕምሯችሁን ከሳጥን ውጪ አውጥታችሁ አስቡ።የነበረው ሁኔታ ሑሱ የሰጠው መልስ ምን ያህል ክብደት ያለውና ምሁራዊ እንደሆነ፣ የጠያቂዎቹ አእምሮ ግን ምን ያህል ጥልቀት የሌለው (Superficial) እንደሆነ በሚገባ ያሳያል።
https://t.me/AbulQmane/2207
1 555
🛑«አልተገለፀም» ማለት ምን ማለት ነው⁉️=========================✍️ በእስልምና የስነ-መለኮት ትምህርት (ዐቂዳህ) ውስጥ ስለ አላህ ማንነትና ባህሪያት የምንማርበት ትልቁ ወርቃማ ህግ "ተውቂፊያህ" ይባላል። ይህ ማለት፡- ስለ ፈጣሪ ባህሪያት መናገር የምንችለው አላህ በቁርኣን ስለ ራሱ የነገረንን ወይም ነብዩ ﷺ በሐዲሥ የነገሩንን ብቻ ነው ማለት ነው።አላህ በቁርኣን «እጅ አለው፣ ፊት አለው፣ ዓይን አለው» ብሎናል፤ እኛም እናምናለን። «እግሩና እጁ እንዴት ነው የተያያዘው? ጭንቅላት አለው ወይ?» የሚለውን ግን አላህ አልነገረንም። ስለዚህ "አልተገለፀም" (አላውቅም) ማለት ፍፁም ምሁራዊና አክብሮታዊ መልስ ነው።ይህንን መሰል ጥያቄ ከዚህ በላይ ወደ ላቀ ስነ-መለኮታዊ (Theological) እና ፍልስፍናዊ ጥልቀት ወስደን ስንመረምረው፣ እፎይ የሚባለው ተሳዳቢ ጥያቄዎች የመረጃ እጥረት ብቻ ሳይሆኑ፣ የከፍተኛ የአስተሳሰብ ድህነት እና የካቴጎሪ መዛባት (Category Mistake) የሚባል የሎጂክ ስህተት መሆናቸውን እናረጋግጣለን።ክርስቲያኖች አልተገለፀም ሲባል "ማንነቱ ያልተገለፀ አምላክ" ብለው ሙድ ለመያዝ ሲሞክቱ፣ በራሳቸው እምነት ላይ እየሳቁ መሆኑን የሚያሳይ፣ ማንም ሎጂካል የሆነ ሰው ሊክደው የማይችለውን እውነታ ላካፍላችሁ፦
1⃣ ፈጣሪን በባዮሎጂ መነጽር ማየት፦🎀 የእፎይ ትልቁ የሎጂክ ስህተት፣ አላህ (ፈጣሪ) የፈጠረውን የባዮሎጂ፣ የፊዚክስ እና የአናቶሚ (Anatomy) ህግ፣ መልሶ ፈጣሪው ላይ ለመተግበር መሞከሩ ነው።አንድን ነገር መለካት ያለብህ በራሱ ካቴጎሪ (ምድብ) ውስጥ ብቻ ነው። - ለምሳሌ፡- "የድምፅ ክብደቱ ስንት ኪሎ ነው?" ብለህ አትጠይቅም። ድምፅ በዴሲቤል (Decibel) እንጂ በኪሎግራም አይለካም። ☑ "የአረንጓዴ ቀለም ጣዕሙ ምንድን ነው? ጨው ጨው ይላል ወይስ ስኳር?" ብለህ አትጠይቅም። ቀለም ይታያል እንጂ አይቀመስም።💡 ከገባችሁ ሌላ ፊልድ ምሳሌ ልጨምርላችሁ፡- አንድ የኮምፒውተር ጌም ሰሪ (Programmer) "xyz" የተባለውን ጌም ፈጠረ እንበል። xyz በጌሙ ዓለም ውስጥ እግር አለው፣ ይዘላል፣ እንጉዳይ ይበላል፣ ይሞታል። አሁን xyz (ፍጡሩ) አዕምሮ ቢኖረውና ስለ ፈጣሪው (ስለ ፕሮግራመሩ) ቢጠይቅ፡- "የፈጣሪዬ ጭንቅላት ስንት ፒክስል (Pixel) ነው? ፈጣሪዬ ልክ እንደኔ ለመዝለል 'Spacebar' ይጫናል ወይ? ፈጣሪዬ ጌም ኦቨር (Game Over) ሲሆን የት ነው የሚሄደው?" ብሎ ቢጠይቅምን ትለዋለህ?"አንተ ደነዝ xyz... የፕሮግራመሩ (የፈጣሪህ) ዓለም ካንተ ዓለም (Dimension) ፍፁም የተለየ ነው! እሱ ፒክስል (Pixel) እና ጌም ኦቨር የለበትም፤ ምክንያቱም እሱ ነው ፒክስልን የፈጠረው!" ነው የምትለው።እፎይ ያደረገውም ይህንኑ የ"xyz" ስህተት ነው። አላህ የቦታን፣ የጊዜን፣ የጅማትን፣ የመራቢያ አካልን (ብልትን)፣ የጭንቅላትን አፈጣጠር(Biology & Physics) የፈጠረ ጌታ ሆኖ ሳለ፣ እፎይ ግን "አላህ … አለው? እጁ ከወገቡ ጋር ተያይዟል?" ብሎጠየቀ። ፈጣሪ አካላዊ ፍጡር (Biological Organism) ስላልሆነ የዚህ ጥያቄ መልስ "አልተገለፀም" ብቻሳይሆን "ጥያቄው ራሱ ለፈጣሪ የማይመጥን (Invalid) ነው!" የሚል ነው።2⃣ አላህ ብ…ት አለው ወይ? ለሚለው፦☑ ስለ ፈጣሪ ጥልቅነት (Transcendence) ያልገባው ሰው ብቻ ነው ይህን ጥያቄ የሚጠይቀው። የሰው ልጅም ሆነ እንስሳት "የመራቢያ ብልት" (Reproductive organs) ለምን አስፈለጋቸው?
1️⃣ ለማሸናት (ለቆሻሻ ማስወገጃ)፡- ፍጡር ይበላል፣ ይጠጣል፤ የተረፈውን ቆሻሻ ማስወገድ አለበት።
2️⃣ ለመራባት (Surivival of Species)፡- ፍጡር ይሞታል፣ ያልቃል። ስለዚህ ዘሩ እንዳይጠፋ ለመተካት ማራባት አለበት።
3️⃣ ለስሜት (Pleasure)፡- ፍጡር ደካማ ስለሆነ ከሌላ አካል ጋር በመጣመር ስሜቱን ማርካት ይፈልጋል።አላህ ግን በቁርኣን "አል-ጘኒይ" (ከፍጡራን ሐጃ የተብቃቃ)፣ "አስ-ሶመድ" (የማይራባ፣ የማይሞት፣ የዘላለም አምላክ፣ የሁሉም መጠጊያ) መሆኑን ገልጿል። የማይበላ፣ የማይጠጣ፣ የማይሞት፣ ዘርን መተካት (መራባት) የማያስፈልገው ፍፁም አምላክ... እንዴት ሆኖ ነው"የመራቢያ ብልት አለው ወይ?" ተብሎ የሚጠየቀው? ሑሱ "አልተገለፀም" ያለው አላህ ለራሱ ያላፀደቀውን፣የፍጡርን ጉድለት (Anthropomorphism) አላህ ላይ መለጠፍ ከባድ ክህደት ስለሆነ ነው።3⃣ "እጁ እና ወገቡ የተያያዘ ነው ወይ?"፦☑ በእስልምና "ማንነቱ ያልተገለፀ አምላክ" አይደለም የምናመልከው። አላህ ራሱን ከ99 በላይ በሆኑ ስሞቹና በበርካታ ባህሪያቱ በሚገባ ገልጿል።አላህ "እጅ አለው፣ ፊት አለው" ስንል አላህ ባለው መሠረት እናምናለን።ግን "እንዴት ነው? (How?)" ለሚለው ጥያቄ፣ ታላቁ ኢማም ማሊክ ያስቀመጡት ዓለምን የሚያስማማ ሎጂካዊ ህግ አለ፦"الاستواء معلوم، والكيف مجهول" (የአላህ ባህሪ በመረጃ ይታወቃል፤ እንዴትነቱ (አካላዊ አወቃቀሩ) ግንበአዕምሮ አይደረስበትም (መጅሁል ነው)! በእርሱ ማመን ግዴታ ነው፤ (እንዴት ብሎ) መጠየቅ ግን ጥመት ነው!)💡 በምሳሌ እንየው፡- እስኪ የክርስቲያን ጠያቂዎችን እንዲህ ብለን እንጠይቃቸው፡- "አንተ በውስጥህ ነፍስ (Soul/Spirit) እንዳለህ ታምናለህ? አዎ! ማለቱ አይቀሬ ነው። እሺ ንገረኝ... ነፍስህ እጅ አላት? የነፍስህ እጅና ወገብ በጅማት የተያያዘነው? ነፍስህ ብልት አላት ወይስ ፆታ የላትም?" ብትላቸው በጭራሽ ሊመልሱልህ አይችሉም። የሰው ልጅ የገዛ ነፍሱን፣ ውስጡ ያለችውንህይወት፣ ቅርጿን እና አካሏን አያውቅም። አላህ በወንጌልም ሆነ በቁርኣን "ስለ ሩሕ (ነፍስ) ጥቂትን ዕውቀት እንጂ አልተሰጣችሁም" ብሏል። ታዲያ የሰው ልጅ የገዛ ነፍሱን ባዮሎጂካዊ ቅርፅ ማወቅ ካልቻለ፣ ይህንን ማብቂያ የሌለውን ዩኒቨርስ የፈጠረውን፣ ወሰን የለሹን አምላክ (Infinite God)፣ በአንጎሉ ስንዝር (Finite Mind) ለክቶ፣ "ወገቡና እጁ እንዴት ተያያዘ?" ብሎ መጠየቅ ምን ያህል የአስተሳሰብ ድንክነት ነው?!4⃣ ጠረጴዛውን ስናዞረው ደግሞ፦☑ "ያልተገለፀ አምላክ ነው የምታመልኩት" ብለው ሲያላግጡ፣ ክርስትና ራሱ በዚህ ጉዳይ ላይ ያለበትን የከፋ ማጥ አላስተዋሉም።እስኪ ይህንን ጥያቄ ለእፎይ እና መሰሎቹ ወርውሩላቸው፦⬇️ መጽሐፍ ቅዱሳችሁ እግዚአብሔር "መንፈስ ነው" ይላል (ዮሐንስ 4፡24)። ግን ያው መጽሐፍ ቅዱስ ስለ እግዚአብሔር አካላዊ መገለጫዎች በብዙ ቦታ ይናገራል፦
☑ ክንፍና ላባ አለው፡- መዝሙረ ዳዊት 91፡4 "በላባዎቹ ይጋርድሃል በክንፎቹም በታች ትጠጋለህ።"
☑ አፍንጫ አለው፣ ጢስም ይወጣዋል፡- መዝሙረ ዳዊት 18፡8 "ከአፍንጫው ጢስ ወጣ፥ ከአፉም የሚያባላ እሳት ነደደ።"አሁን የክርስቲያን ጠያቂዎችን የራሳቸውን ሎጂክ ተጠቅመን እንዲህ እንጠይቃቸው፡-«እግዚአብሔር አብ (God the Father) ክንፍና ላባ ካለው፣ ልክ እንደ እርግብ ባዮሎጂካዊ የሆነ ላባ፣ ስጋና ደም አለው ማለት ነው? አፍንጫ ካለውስ? የአፍንጫ ቀዳዳና የመተንፈሻ ቱቦ (Trachea) አለው ማለት ነው? እግዚአብሔር የተያያዘ አካል ካለው፣ አብ ብልት አለው ወይ?»መልሱ ምን ይሆናል? ወይ "እግዚአብሔር መንፈስ ስለሆነ እንደሰው አካል የለውም (ምስጢር ነው)" ይላል፤ አሊያም "ይህ ዘይቤያዊ (Metaphorical) አገላለፅ ነው" ይላል። አያችሁ? ልክ ሑሱ"እንዴትነቱ
1 555
#የአህሉ ሱንና ወልጀመዓ (የሰለፎች) መዝሀብ በሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚይያህ ቃል ሲጠቃለል፦
«مذهب سلف الأمة: إثبات الصفات لله كما جاءت: إثباتا بلا تمثيل، وتنزيها بلا تعطيل»
«የሰለፎች መዝሀብ፡ ለአላህ ባህሪያቱን በመጡት መሰረት ማፅደቅ ነው፡- ሳያመሳስሉ ማፅደቅ፤ ሳያስተባብሉም
ማጥራት!»
📚 [ሙኽተሶር አል-ፈታዋ አል-ሚስሪያህ፣ ገፅ 203]
የምናመልከው አምላክ አዛኝነቱ፣ ኃያልነቱ፣ ሰሚነቱ እና ባህሪው በግልፅ የታወቀ አምላክ ነው። ነገር ግን እኛ፣ አላህን የጨጓራ፣ የኩላሊት፣ የተጣበቀ ጅማት እና የብልት ስብስብ የሆነ 'ባዮሎጂካዊ አካል' አድርገን አናስበውም! አዕምሯችሁን ከሳጥን ውጪ አውጥታችሁ አስቡ!
ይህ ነው ጥርት ያለችው የሰለፎች እምነት (ዐቂዳህ)! አላህ በእውነት ላይ ያፅናን! እንማር፣ እንወቅ!
1 555
«كما أخبر أن في الجنة لحما ولبنا وعسلا وماء وخمرا ونحو ذلك، وهذا يشبه ما في الدنيا لفظا ومعنى، ولكن ليس هو مثله، ولا حقيقته كحقيقته...»
«አላህ በጀነት ውስጥ ስጋ፣ ወተት፣ ማር፣ ውሃ እና ወይን (ኸምር) እንዳለ ነግሮናል። ይህ በዱንያ ካለው ጋር በስምና በትርጉም ይመሳሰላል፤
ነገር ግን (በጀነት ያለው) እሱን አይደለም፤ ሐቂቃውም (እውነታውና ጣዕሙ) እንደዚህኛው ሀቂቃ አይደለም...»
📚 ምንጭ፡ አር-ሪሳላህ አት-ተድሙሪያህ
አየህ! አላህ በጀነት ውስጥ "ወተት" አለ ሲለን፣ "ይህ ወተት ላሟ አርግዛ፣ ታልባ፣ በባልዲ ተቀድቶ ነው እንዴ የመጣው?" ብለህ አትጠይቅም! ስሙ ወተት ነው، እውነታው ግን ከባዮሎጂ የጠራ ፍፁም ሌላ ነው! የፈጣሪም እጅ (የድ) ስሙ እና ትርጉሙ እጅ ነው። እውነታው ግን ከጅማትና ከአጥንት የጠራ ለርሱ ብቻ የሚመጥን ታላቅ ባህሪ ነው!
💡 ምሳሌ 3፡ የጌም ፕሮግራመሩ ጉዳይ፦
አንድ የኮምፒውተር ጌም ፕሮግራመር (Mario) የተባለውን ጌም ፈጠረ እንበል። ማርዮ በጌም ውስጥ ይዘላል፣ ይበላል፣ ይሞታል። ማርዮ አዕምሮ ኖሮት ስለ ፈጣሪው (ስለ ፕሮግራመሩ) ቢጠይቅ፡ "የፈጣሪዬ ጭንቅላት ስንት
ፒክስል (Pixel) ነው? ፈጣሪዬ ልክ እንደኔ ለመዝለል 'Spacebar' ይጫናል ወይ?" ቢልህ ምን ትለዋለህ? "አንተ
ደዩስ... ፈጣሪህ ያንተ ዓለም (Dimension) ውስጥ ያለ ፍጡር አይደለም! እሱ ፒክሴል እና አጥንት የለበትም፤ ምክንያቱም እሱ ነው ፒክስልን የፈጠረው!" ትለዋለህ።
የክርስቲያኖችና አሕባሾች ጥያቄም ልክ እንደ ማርዮ ጥያቄ ነው! ጊዜን፣ ቦታን፣
ባዮሎጂንና ፊዚክስን የፈጠረውን አምላክ "አካሉ ተያይዟል ወይ?" ብሎ መጠየቅ ሎጂካዊ ስህተት (Category
Mistake) ነው።
👌ዐሊሞች በተከታታይ ያፀደቁት የሰለፎች ኢጅማዕ (Consensus) አለ።
ማንም ተነስቶ ይህንን የሰለፎች መንገድ "ወሀብያ" ብሎ እንዳይፈርጀው፣ ከጥንት ጀምሮ የነበሩ የሁሉም መዝሀብ ታታላቅ ኡለማዎች የተስማሙበት መሆኑን የሚያረጋግጡ መረጃዎች እነሆ፦
የኢማም ሙሐመድ ኢብኑል ሐሰን አሽ-ሸይባኒ (የሞቱት 189 ሂጅሪያ) (የአቡ ሐኒፋ ተማሪ)፦
«اتفق الفقهاء كلهم من المشرق إلى المغرب على الإيمان بالقرآن والأحاديث... في صفة الرب عز وجل، من غير تفسير، ولا وصف، ولا تشبيه...»
«ከምስራቅ እስከ ምዕራብ ያሉ የፊቅህ ሊቃውንት በሙሉ የጌታችንን ባህሪያት አስመልክቶ በቁርኣንና በሐዲሦች ለማመን... (በዘይቤያዊ) ትርጉም ሳይተረጉሙ፣ አካላዊ ገለፃ
ሳያወጡለትና፣ (ከፍጡር ጋር) ሳያመሳስሉ ተስማምተዋል።»
📚 (ምንጭ፡ አል-ላሊካኢ "ሸርሑ ኡሱል ኢዕቲቃድ አህሊ-ሱና" 3/432)
📌 የኢማም አል-በጘዊ (የሞቱት 516 ሂጅሪያ)፦
«والإصبع المذكورة في الحديث صفة من صفات الله عز وجل، وكذلك كل ما جاء به الكتاب أو السنة من هذا القبيل في صفات الله تعالى، كالنفس، والوجه، واليدين، والعين...
فهذه ونظائرها صفات لله تعالى، ورد بها السمع، يجب الإيمان بها، وإمرارها على ظاهرها، معرضاً عن التأويل، مجتنباً عن التشبيه...»
«በሐዲሡ የተጠቀሰችው 'ጣት' ከአላህ
ባህሪያት አንዷ ናት። እንዲሁም በቁርኣንና በሱንና የመጡት እንደ ነፍስ፣ ፊት፣ ሁለት እጆች፣ አይን፣ መምጣት... እነዚህና መሰሎቹ የአላህ ባህሪያት ናቸው። በእነርሱ ማመን እና በገሀድ ትርጉማቸው ማሳለፍ ግዴታ ነው፤ መአዛዊ ትርጉም (ተእዊል) ከመስጠት ርቆ፣ ከማመሳሰል (ተሽቢህ) ተቆጥቦ!»
📚 [ምንጭ፡ ሸርሕ አስ-ሱንና 1/163-171]
📌 የኢማም ኢብኑ ቁዳማህ አል-መቅዲሲ (የሞቱት 620 ሂጅሪያ)፦
«فقد ثبت ما ادعيناه من مذهب السلف... أمرّوها كما جاءت من غير تفسير ولا تأويل، مع نفي التشبيه عنها...»
«ስለ ሰለፎች መዝሀብ የተናገርነው እውነት መሆኑ ፀድቋል... እንዳመጣጧ (በሐቂቃዋ) ያሳልፏታል፣ (ዘይቤያዊ) ትርጓሜ ሳይሰጧትና፣ ማመሳሰልንም ከእሷ ላይ በማራቅ..."
📚 [ምንጭ፡ ዘሙ አት-ተእዊል፣ ገፅ 26]
📌 የአል-ሓፊዝ ኢብኑ ረጀብ አል-ሐንበሊ (የሞቱት 795 ሂጅሪያ)፦
«والصواب ما عليه السلف الصالح من إمرار آيات الصفات وأحاديثها كما جاءت، من غير تفسير لها ولا تكييف ولا تمثيل...»
«እውነታው ሰለፎች የነበሩበት መንገድ ነው። ይኸውም የባህሪያትን (የሲፋት) አያቶችና ሐዲሦች (ወደ ሌላ ትርጉም) ሳይተረጉሙ፣ እንዴትነትን ሳያበጁና (ተክዪፍ)، ሳያመሳስሉ (ተምሢል)
እንዳመጣጣቸው ማለፍ ነው።»
📚 [ምንጭ፡ ፈድሉ ዒልም አስ-ሰለፍ ዐላ አል-ኸለፍ፣ ገፅ 55]
አስገራሚው ነገር የኢልመል-ከላም (የፍልስፍና/አሽዓሪ) ሊቅ የነበሩት ኢማም አል-ጁወይኒ (የሞቱት 478 ሂጅሪያ) በመጨረሻ ህይወታቸው ከፍልስፍናቸው ተመልሰው ወደዚሁ የሰለፎች መንገድ መግባታቸው ነው፦
«وذهب أئمة السلف إلى الانكفاف عن التأويل... والذي نرتضيه دينا ونعتقده... اتباع سلف الأمة...»
«የሰለፍ አኢማዎች ከመተርጎም (ከማጣመም) ርቀዋል... አሁን እኛም በዲንነት የምንወደውና የምናምነው
የዚህችን ኡማ ሰለፎች (ቀደምቶች) መከተልን ነው...»
📚 [ምንጭ፡ አር-ሪሳላህ አን-ኒዛሚያህ፣ ገፅ 32]
#ኳሱን ወደ ክርስቲያኖቹ ሜዳ ስንመልሰው፦
አሁን ክርስቲያኖቹ በገዛ ወጥመዳቸው እንዴት እንደሚወድቁ ተመልከት! እፎይ አላህን "ጭንቅላት አለው? ወገቡ ተያይዟል?" እንዳለው፣
የገዛ መጽሐፍ ቅዱሱን አምጥተን እንዲህ እንጠይቀው፦
1. መጽሐፍ ቅዱሳችሁ "እግዚአብሔር መንፈስ ነው" (ዮሐንስ 4፡24) ይላል።
2. ግን ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስ፡ "በላባዎቹ ይጋርድሃል በክንፎቹም በታች ትጠጋለህ" (መዝሙረ ዳዊት 91፡4) ይላል።
3. እንዲሁም፡ "ከአፍንጫው ጢስ ወጣ፥ ከአፉም የሚያባላ እሳት ነደደ" (መዝሙረ ዳዊት 18፡8) ይላል።
አሁን ስንጠይቃቸው፦ "እግዚአብሔር አብ (God the Father) ላባና ክንፍ ካለው፣ ልክ እንደ ዶሮና እርግብ ባዮሎጂካዊ የሆነ ክንፍና አጥንት አለው ማለት ነው? አፍንጫ ካለውስ፣ አፍንጫው ከሳንባው ጋር በመተንፈሻ ቱቦ (Trachea) የተያያዘ
ነው ወይስ አይደለም? አብ የተያያዘ አካል ካለውስ የመራቢያ ብልት አለው ወይ?»
ክርስቲያኑ ይህን ሲጠየቅ ወይ "እግዚአብሔር መንፈስ ስለሆነ አካል የለውም (ሚስጥር ነው)" ይላል፤ አሊያም "እነዚህ ዘይቤያዊ
(Metaphor) አገላለፆች ናቸው" ይላል።
ስለዚህ «እኛ ሙስሊሞች 'አልተገለጸም / ቢላ ከይፍ (እንዴትነቱ አይታወቅም)' ስንል፣ እናንተ 'ሚስጥር
ነው' እንደምትሉት መሆኑን አታውቁም እንዴ? እኛ አላህ እጅ አለው ስንል، እንደናንተ አማልክት ደም፣ ስጋ፣ ኩላሊትና ብልት ያለው ባዮሎጂካዊ ፍጡር አድርገን አስበነው አይደለም! አላህ ከዚህ ሁሉ የጠራ ነው። አላህ በቁርኣን ያልገለፀውን የባዮሎጂ ውቅር፣ አላህ ላይ ለመተግበር የምትሞክሩት እናንተው ራሳችሁ ናችሁ!» እንላቸዋለን።
እኛ አልተገለፀም የምንለው ያልተነገረንን ነገር ከመቆጠብ አንፃር እንጂ ሌላ አይደለም።
1 555
ስለ አላህ ስሞችና ባህሪያት‼️
=======================
(«የማናውቀውን አምላክ አናመልክም!» - ስለ አስማእ ወስ'ሲፋት የሰለፎች ወርቃማው መንገድ!)
||
✍️ በእስልምና ውስጥ ከዕውቀቶች ሁሉ እጅግ የላቀውና ክቡሩ ዕውቀት አላህን ማወቅ ነው። ፈጣሪያችንን የምናውቀው ደግሞ እርሱ ራሱን በገለፀበት ስሞቹና ባህሪያቱ ነው። በዚህ ርዕስ ዙሪያ አንዳንድ "ሱኒ ነን" የሚሉ ወንድሞችና እህቶች እንኳ ሳይቀሩ «አላህ እጅ አለው፣ አላህ ፊት አለው፣ በሌሊቱ ⅓ኛ ይወርዳል!…» ሲባል የሚሰቀጥጣቸውና የሚደነግጡት፣ የሰለፎችን ንፁህ መንገድ በቅጡ ስላልተረዱ እና አላህን በአዕምሯቸው ውስጥ እንደ ፍጡር ስለሚስሉ (ተጅሲም ውስጥ ስለሚገቡ) ነው።
ክርስቲያኖችም ሆኑ አንዳንድ የጥመት ቡድኖች (እንደ አሕባሽ፣ አሽዐሪ፣ ሙዕተዚላህ ያሉት) የሰለፎችን መንገድ ሲተቹ ትልቁ ስህተታቸው፣ «የአላህን ባህሪያት ማፅደቅ ማለት አላህን የሰውነት አካል (Anatomy) ካለው ፍጡር ጋር ማመሳሰል (ተጅሲም) ነው» ብለው ማሰባቸው ነው።
የአንዳንድ አሕባሽን የሚመስሉ ክርስቲያኖች ጥያቄም፦ "አላህ እጅ አለው? አዎ! እጁ ከወገቡ ጋር ተያይዟል ወይ?፣ ጥፍር አለው ወይ? ጭንቅላት አለው ወይ?" የሚለው መሠረቱ ይኸው የድንቁርና መነጽር ነው።
የሰለፎች ዐቂዳህ ግን ከዚህ እጅግ የጠራ እና በሚከተሉት ጥልቅ መርሆች ላይ የቆመ ነው፦
#መርህ አንድ፡ "እውነታው (ትርጉሙ) ይታወቃል፤ አካላዊ እንዴትነቱ (ከይፍያው) ግን አይታወቅም!"
#አላህ በቁርኣን "እጅ (የድ) አለው" ሲለን፣ ቃሉ ዘይቤያዊ (Metaphor/መጃዝ) ሳይሆን እውነተኛ (ሐቂቃ) ነው። ነገር ግን ይህ "ሐቂቃ/እውነታ" የሆነ እጅ፡ ስጋ፣ ደም፣ አጥንት እና ጅማት ያለው ባዮሎጂካዊ እጅ ነው ማለት አይደለም!!
አላህ አቻ የሌለው ፈጣሪ ስለሆነ፣ የእጁ እውነታ ለርሱ ታላቅነት በሚመጥን መልኩ እንጂ በፍጡር ሚዛን "እንዴት
(How)?" ተብሎ አይጠየቅም።
💥 የኢማም አቡ ሐኒፋን ማስረጃ (የሞቱት 150 ሂጅሪያ)፦
ታላቁ ኢማም አቡ ሐኒፋ አላህ "አካላት" አለው ብለው ለሚያስቡትም ሆነ፣ ቃላቱን ወደ "ችሎታ" ቀይረው ለሚተረጉሙት እንዲህ ሲሉ አስገራሚ ምላሽ ሰጥተዋል፦
«وله يد ووجه ونفس كما ذكره الله تعالى في القرآن، فما ذكره الله تعالى في القرآن
من ذكر الوجه واليد والنفس، فهو له صفات بلا كيف، ولا يقال: إن يده قدرته أو نعمته؛ لأن فيه إبطالَ الصفة، وهو قول أهل القدر والاعتزال...»
«አላህ በቁርኣን እንደገለፀው እጅ፣ ፊት እና ነፍስ አለው። እነዚህም ባህሪያቱ ናቸው፤ 'እንዴት' አይባልም (ቢላ ከይፍ)። እጁ ማለት ችሎታው ወይም ፀጋው ነው አይባልም፤ ይህን ማለት ባህሪውን ማስተባበል ነውና፤ ይህም የቀደሪያና የሙዕተዚላህ (የጥመት ቡድኖች) አባባል ነው።» 📚
[ምንጭ፡ አል-ፊቅሁ-ል-አክበር፣ ከሙላ ዐሊ አል-ቃሪ ማብራሪያ ጋር፣ ገፅ 58]
💥የኢማም አት-ቲርሚዚ ማስረጃ (የሞቱት 279 ሂጅሪያ)፦
«...قد ثبتت الروايات في هذا، ويؤمن بها، ولا يتوهم ولا يقال كيف؟ هكذا روي عن مالك وسفيان بن عيينة وعبد الله بن المبارك أنهم قالوا في هذه الأحاديث: أمروها بلا كيف... وقال إسحاق بن إبراهيم: إنما يكون التشبيه إذا قال: يد كيد، أو مثل يد، أو سمع كسمع، أو مثل سمع... وأما إذا قال، كما قال الله تعالى: يد وسمع وبصر، ولا يقول: كيف؟ ولا يقول: مثل سمع ولا كسمع، فهذا لا يكون تشبيها، وهو كما قال الله تعالى: {لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ}» "...
«ዘገባዎቹ ፀድቀዋል፣ እናምንባቸዋለንም፤ በአዕምሮ (እንደ ሰው) አንስላቸውም፤ 'እንዴትስ ነው?' አንልም! ከማሊክ፣ ሱፍያን እና
ኢብኑል ሙባረክ እንደተዘገበው፡ 'እንዴት (ቢላ ከይፍ) ሳትሉ እለፉት' ብለዋል።... ኢስሐቅ ብኑ ኢብራሂም እንዳሉት፡
'ማመሳሰል (ተሽቢህ) የሚሆነው «እንደኔ እጅ ያለ እጅ አለው፣ እንደኔ መስሚያ ያለ መስሚያ አለው» ካለ ብቻ
ነው። አላህ እንዳለው «እጅ፣ መስሚያና ማየቻ አለው» ካለ እና «እንዴት ነው?» ወይም «እንደኔ ነው» ካላለ፣ ይህ ፈጽሞ
ማመሳሰል (ተሽቢህ) አይሆንም! አላህ (ليس كمثله شيء) ብሏልና!'"
📚 [ምንጭ፡ ሱነን አት-ቲርሚዚ (ጃሚዕ
አት-ቲርሚዚ)፣ ከሐዲስሥ ቁጥር 662 ቀጥሎ የተሰጠ ማብራሪያ]
መርህ ሁለት፡ "ትርጉሙን አናውቅም (ተፍዊዱል መዕና)" ማለት በሰለፎች ዘንድ ክህደት ነው!
#አንዳንድ ክርስቲያኖችና አሽዐሪዎች፡ «ማንነቱና ትርጉሙ ያልተገለፀ (የማይታወቅ) አምላክ ነው የምታመልኩት» በማለት ትክክለኛውን
ሙስሊም ለማውገዝ የሞከሩት ይህንን ባለመረዳት ነው። እኛ ሙስሊሞች «አናውቅም የምንለው የአካሉን እንዴትነት (الكيف) እንጂ የቃሉን ትርጉም (المعنى) አይደለም!! ትርጉሙማ እጅግ የታወቀና ግልፅ ነው።
[የኢማም ኢብኑል ቀይዪም ማብራሪያ (የሞቱት 751 ሂጅሪያ)]፦
ኢብኑል ቀዪም እነዚህን የአላህ ቃል ትርጉም አይገባንም የሚሉትን
አላዋቂዎች (አህሉ-ተጅሂል) ሲያጋልጡ፦
«أصحاب التجهيل قالوا: نصوص الصفات ألفاظ لا تعقل معانيها، ولا ندري ما أراد الله ورسوله منها... وظن هؤلاء أن هذه طريقة السلف... ولازم قولهم أن الرسول كان يتكلم بذلك ولا يعلم معناه!»
«የመሀይምነት አራማጆች (አህሉ-ተጅሂል) እንዲህ አሉ፡- 'የአላህን ባህሪ በተመለከተ የመጡ መረጃዎች ትርጉማቸው የማይታወቅ ቃላት ናቸው፣ አላህና መልክተኛው ምን እንደፈለጉባቸው አናውቅም።' እነዚህ ሰዎች ይህ የሰለፎች መንገድ
መሰላቸው።... የዚህ አባባላቸው መዘዝ ደግሞ «ረሱል ﷺ እንኳን ሳይቀሩ ሲናገሩት ትርጉሙን ሳያውቁት ነው
የተናገሩት» ወደማለት ይወስዳቸዋል (ይህ ደግሞ የከፋ ክህደት ነው)!»
🤚የካቴጎሪ ስህተት፡-
ክርስቲያኑ ተሳዳቢ አላህን "ጭንቅላት አለው? ወገቡስ ከእጁ ጋር ተያይዟል?…" ብሎ የጠየቀው፣ አላህን የባዮሎጂ፣ የጅማት፣ የስጋና የፊዚክስ ህግጋት ተገዥ የሆነ ትልቅ ሮቦት አድርጎ ስላሰበ ነው። ይህ ፍፁም ሎጂካዊ መዛባትና አውቆ ብሽሽቅ ነው።
💥ምሳሌ 1፡ የነፍስ / ሩሕ ሚስጥር፦
ኢብኑ ተይሚይያህ ( በ"አር-ሪሳላህ አት-ተድሙሪያህ" ላይ እንደገለፁት፣ የሰው ልጅ ነፍስ (Soul) አለው። ይህች ነፍስ፡ ትወጣለች፣ ትወርዳለች፣ ትሰማለች፣ ታያለች፣ ደስታና ስቃይ ይሰማታል። እስኪ ክርስቲያኑን እንጠይቀው፡ "የነፍስህ እጅ ከነፍስህ ወገብ ጋር በጅማት ተያይዟል? ነፍስህ አፍንጫና የመራቢያ ብልት አላት
ወይስ የላትም?" መቼም ሊመልስ አይችልም! ታዲያ የሰው ልጅ የገዛ ነፍሱን አካላዊ "እንዴትነት" ማወቅ ካልቻለ፣ ይህንን ማብቂያ የሌለውን ዩኒቨርስ የፈጠረውን ወሰን የለሽ አምላክ (Infinite God)፣ በአንጎሉ ስንዝር ለክቶ፣ "ወገቡና እጁ እንዴት ተያያዘ?" ብሎ መጠየቅ ምን ያህል የአስተሳሰብ ድንክነት ነው?!
💡ምሳሌ 2፡ የጀነት ፍራፍሬዎች ትርጉም፦
ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚይያህ ሌላ ድንቅ ምሳሌ ይሰጣሉ፦
1 555
በፈተና በመከራ በችግ እያለፍችሁ ያላችሁ ሁሉ።
እናንተ ከሰው የተለዬ ምን ደረሰባችሁ?
ሁሉም ሰው አይነቱ ይለያይ እንጅ በአቅሙ ይፈተናል ይወድቃን ይነሳል። እናንተ ቤት ዘግታችሁ ተስፍ ቆርጣችሁ እድታለቅሱ የሚያደርግ ምድነው? ይህንን ጠይቁ። እኔ ከሰው የተለዬ ምን ደረሰብኝ?ሸይጧን ነው ችግራችሁን አግዝፎ የሚያሳያችሁ ተስፍ እንድትቆርጡ። የምሬን ነው። እዚህ ምድር ላይ ከሁሉም በላይ የሚፈተኑትን ነብያት ህዩ ምን. ምን የመከራ አይነት ደረሰባቸው እንደት አለፉት? ወደ አአእምሮችሁ የነሱን ችግር ስታስቡ እኔ ምን ሁኘ አላሃምዱሊላህ አላላችሁም? በቃ ችግራችሁ የዚህን ያህል በጣምምም ትኒሽ እና ማለፍ የምትችሉት ነው። አብሽሩ እሺ።
ዱንያ ፈተና እኮት ሲጀመር አይደል?
وَلَنَبْلُوَنَّكُم بِشَيْءٍ مِّنَ الْخَوْفِ وَالْجُوعِ وَنَقْصٍ مِّنَ الْأَمْوَالِ وَالْأَنفُسِ وَالثَّمَرَاتِ ۗ وَبَشِّرِ الصَّابِرِينَ
ከፍርሃትና ከረኃብም በጥቂት ነገር፣ ከገንዘቦችና ከነፍሶችም፣ ከፍራፍሬዎችም በመቀነስ በእርግጥ እንሞክራችኋለን፡፡ ታጋሾችንም (በገነት) አብስር፡፡
البقرة 2:155📖
እና ነገሮችን አክብዳችሁ በማዬት እራሳችሁን እና የወደፊት ሂዎታችሁን አኼራችሁን አታበላሹ ለማለት ነው
አላህዬ ፈተናችን በሶብር እና አላህን በማመስገን የምናልፍ ያድርገን አሚን🤲
https://t.me/WATESiMU/5715
1 555
Repost from 🏷አል-በያን / البــيان
#ተለቀቀ_ተለቀቀ 🏷️አዲስ በያን #ለተ_ክ_ፊ_ሪ_ዮች ማጭበርበሪያ 📮
🎙️በኡስታዝ አቡ ሀቲም ሰኢድ ሼይኽ ሀሰን አላህ ለጠብቀው።
⚠️በያኑ የያዛቸው ዋና ዋና ነጥቦች 👇
6:34⏱
እዚህ ደቂቃ ላይ👇👇
ሀጁሪዮችን/ጀምዕዮችን እንዳታገቡ ኩፍር ውስጥ ናቸው
21:20 🕚
እዚህ ደቂቃ ላይ 👇👇👇
❌አዚሮች እኩፍር ላይ ናቸው ሁጃ ከቆመ በኃላ ክፍር ብሎ ይክፍራል ማለቱን ማስታወስ
26:00 ⏰
28:20 🕘
እነዚህ ደቂቃዎች ላይ ደግሞ 👇👇👇
❌በሀኪምያ ጊዳይ ያዳከረው ተዳሶበታል
35:40 🕤
እዚህ ላይ ደግሞ 👇👇
❌ስድብ ኡስታዙ ሙስጠፋ በሰው ክብር የተፈቀበት ሁኔታ ተካተታል
https://t.me/al_beyann/1775
https://t.me/Hudhud_Studio/16378
1 555
🔺የፁሁፍ ማውጫ
──━━✺✿✺━━──
📚ዑዝር ቢልጀህል ምን ማለት ነው? https://t.me/AbulQmane/230
──━━✺✿✺━━──
📚ዑዝር ቢልጀህል ምን ማለት ነው? https://t.me/AbulQmane/230
──━━✺✿✺━━──
📚 ዑዝር ቢልጀህል እንደሌሎች ኢጅቲሃድን እንደሚያስተናግዱ ርእሶች ነውን?
https://t.me/AbulQmane/230
──━━✺✿✺━━──
🔺ዑዝር ቢልጀህል በኢስላም እንዳለ ቁራአናዊ ማስረጃዎች
──━━✺✿✺━━──
📚 ክፍል1 https://t.me/AbulQmane/232
──━━✺✿✺━━──
📚ክፍል2 https://t.me/AbulQmane/233
──━━✺✿✺━━──
📚ክፍል3 https://t.me/AbulQmane/235
──━━✺✿✺━━──
🔺ዑዝር ቢልጀህል በኢስላም እንዳለ ሐዲሳዊ ማስረጃዎች
──━━✺✿✺━━──
📚ክፍል4 https://t.me/AbulQmane/235
──━━✺✿✺━━──
📚ክፍል5 https://t.me/AbulQmane/238
──━━✺✿✺━━──
የ ዚህ ኡማህ ታላላቅ ዑለሞች ንግግር A
──━━✺✿✺━━──
📚ክፍል 6 https://t.me/AbulQmane/240
──━━✺✿✺━━──
📚ክፍል7 https://t.me/AbulQmane/241
──━━✺✿✺━━──
📚የሙሐመድ ኢብኑ አብዲልወሃብ (ረሒመሁሏህ) አቋምና ንግግሮችA
https://t.me/AbulQmane/244
──━━✺✿✺━━──
📚ከዘመናችን ታላላቅ ዑለማኦች ንግግሮች A
https://t.me/AbulQmane/296
──━━✺✿✺━━── 📚ሸይኽ ሙሐመድ ኢብን ሷሊሕ ዑሠይሚን
https://t.me/AbulQmane/299
──━━✺✿✺━━──
📚አሸ፞ይኽ ሙቅቢል ኢብኑ ሃዲ አል ዋዲዒይ ረሒመሁላህ
https://t.me/AbulQmane/304
──━━✺✿✺━━──
📚አሸ፞ይ ኢማሙ አልባኒ ረሒመሁላህ
https://t.me/AbulQmane/308
──━━✺✿✺━━──
📚እውን ለሁሉም ሁጃ ደረሶታልን?
https://t.me/AbulQmane/323
──━━✺✿✺━━──
📚እውን በአቂዳ ጉዳይ ላይ ኡዝር ቢልጀህል የለም?
https://t.me/AbulQmane/329
──━━✺✿✺━━──
📚ሁጃ ቁሞበት በሽርኩ ላይ ከቀጠለ
https://t.me/AbulQmane/332
──━━✺✿✺━━──
📚የተጠንጣዮች ሁነኛ ምሽግ(
መሳኢል ዟሂራ እና መሳኢል ኸፊያA
📚#ክፍል1 https://t.me/AbulQmane/356
ክፍል 2 https://t.me/AbulQmane/358
──━━✺✿✺━━──
📚ክፍል 3 https://t.me/AbulQmane/362
──━━✺✿✺━━──
📚ክፍል 4 https://t.me/AbulQmane/374
──━━✺✿✺━━──
📚ክፍል 5 https://t.me/AbulQmane/379
──━━✺✿✺━━──
📚ክፍል 6 https://t.me/AbulQmane/387
──━━✺✿✺━━──
📚በዛሂሩ መፍረድና ኡዝር ቢል ጀህልB
──━━✺✿✺━━──
📚 #ክፍል1 https://t.me/AbulQmane/395
──━━✺✿✺━━──
📚 #ክፍል 2 https://t.me/AbulQmane/397
──━━✺✿✺━━──
📚 ሺርክ እያወቀ የሰራና ሳያውቅ የሰራ ሰው ልዩነቱ
https://t.me/AbulQmane/538
──━━✺✿✺━━──
📚 ሺርኩል አክበር ና ኡዝር ቢል ጀህል
https://t.me/AbulQmane/624
──━━✺✿✺━━──
📚 አል ዑዝር ቢልጀህልና የአሰጣጥ ሁኔታና ማስረጃዎች
https://t.me/AbulQmane/627
──━━✺✿✺━━──
📚 የተክፊሮች ማምታቻና መልሶቻችን
https://t.me/AbulQmane/632
──━━✺✿✺━━──
📚 ስህተት ላይ ለወደቀ ግለሠብ ወይም((ሙክጢእ )) ለሆነ የተቀመጡ የማስረጃ አይነቶች
https://t.me/AbulQmane/637
──━━✺✿✺━━──
📚 “ኸጠእ (خطأ ) “የሚለውን ቃል ትርጉም አሰጣጥ
https://t.me/AbulQmane/643
──━━✺✿✺━━──
📚 የበኑ ኢስራኢልና የሙሳ ዐለይሂ ስሰላም ታሪክ
https://t.me/AbulQmane/637
──━━✺✿✺━━──
📚 ስለ"ሀሪቁኒ” የተሰኘዉን ሀዲስ ሰፋ ያለ ትንተና
https://t.me/AbulQmane/650
──━━✺✿✺━━──
📚 "ሀሪቁኒ” የተሰኘዉን ሀዲስ ባለቤት ላለመክፈሩ ከልካይ ነገር ምንድነው
https://t.me/AbulQmane/644
──━━✺✿✺━━──
📚 የተክፊሮች ማምታቻና መልሶቻችን
https://t.me/AbulQmane/650
──━━✺✿✺━━──
📚 ሐዲስ አቢ ዋቂድ አልለይሲይ
https://t.me/AbulQmane/664
──━━✺✿✺━━──
📚 ዛቱ አንዋጥ ና የኡለሞች አቶረጋገም
https://t.me/AbulQmane/665
──━━✺✿✺━━──
📚 የአላህ ሱብሐነሁ ወተዓላ ማስረጃ (ሑጀቱሏህ) በሰው ልጆች ላይ
https://t.me/AbulQmane/672
──━━✺✿✺━━──
📚 የተክፊሮች ማምታቻና መልሶቻችን መቋጫ
https://t.me/AbulQmane/666
──━━✺✿✺━━──
📚 አልዑዝሩ ቢልጀህል የተገነባባቸው #መሰረቶች (አል ኡሱል
https://t.me/AbulQmane/676
──━━✺✿✺━━──
📚 ለዚህ ሸሪዓዊና የመጀመሪያው ማስረጃ ማረጋገጫ
https://t.me/AbulQmane/683
──━━✺✿✺━━──
📚 የኢብኑ ተይሚያ ግልፅ ንግግሮች ለአምታቾች
https://t.me/AbulQmane/709
──━━✺✿✺━━──
📚 እውን የኡለሞችን ኢስጢላህ ያልገባው ማንነው?!
https://t.me/AbulQmane/683
──━━✺✿✺━━──
📚 12ነጥቦች https://t.me/AbulQmane/691
──━━✺✿✺━━──
📚 ካፊር አስልይ ና ሙርተድክፍል1
https://t.me/AbulQmane/773
──━━✺✿✺━━──
📚 የሙሀመድ ኢብኑ አብል ወሐብ ልጆች ና ተማሪዎች
https://t.me/AbulQmane/775
──━━✺✿✺━━──
📚 ኸዋሪጆች እና ኢብን አባስ
https://t.me/AbulQmane/485
──━━✺✿✺━━
📚የዘመኖችን ኸዋሪጆች ማራቆት
https://t.me/AbulQmane/473
──━━✺✿✺━━──
📚የዘመኖችን ኸዋሪጆች ማራቆት2
https://t.me/AbulQmane/474
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
