en
Feedback
ፋአድ 𝐅𝐔𝐀𝐃 𝙰𝚋𝚞 𝚕𝚀𝚖𝚊𝚗𝚎

ፋአድ 𝐅𝐔𝐀𝐃 𝙰𝚋𝚞 𝚕𝚀𝚖𝚊𝚗𝚎

Open in Telegram
1 560
Subscribers
+124 hours
-37 days
+1030 days
Posts Archive
qsyd_mw_thr_twqz_lqlwb_y_yh_lnsn_mhl_ntbh_gmcsk7f7mas_71d8cff7.mp35.71 MB

قصيدة_مؤثرة_عن_القبر_و_الموت_لقد_فنوا_و_ما_بقى_منهم_خبر_48k.mp32.49 MB

y_yh_lnsn_mhl_ntbh_aabdlkrym_mhywb_lqd_fnw_wm_bq_mnhm_hd_ya_ayo.mp35.52 MB

وَوَصَّيْنَا الْإِنسَانَ.mp314.80 MB

የአሹራ ፆም ቱሩፋቶች.mp32.53 MB

📚 كتاب صوتي: العلم النافع.mp320.14 MB

ከተፃፉ ቆየት ቢሉም ይነበብ

“በመጨረሻይቱም (አለም) እነርሱ የሚያረጋግጡ ከሆኑት (መሪ ነው)። (አል' በቀራህ፡ 4) በዚህ የቁርኣን አንቀጽ የተፈለገው ሲቀጠሩት የነበረው ነገር እንደመጣቸው እርሱም የቂን (ሞት) እንደሆነ ይገልጻል፡፡)) ይህ አንቀጽ ፣ ዓቅለኛ ሆኖ ለአካለ መጠን ከደረሰበት ጊዜ ጀምሮ _ እስኪሞት ድረስ ዒባዳ ዋጅብ እንደሆነ ፣ ሱፍያዎች እንደሚሉት ከሞት በፊት ግዴታ የሚቆምበት “ሀል” የሚባል እንደሌለ ይጠቁማል፡፡ ይህ ፣ ድሮም ይሁን አሁን የሱፍያ ዲን ነው፡፡ ዒባዳን አስመልክቶ የሱፍያ አቋም ይህ ነው፡፡ ከሱፍያዎች ኪታብ የነቀልነው ጥቂቱን ብቻ ነው… እኔ በጥናቴ ላይ ትኩረት ያደረኩት የዒባዳውን እና በዒባዳ ላይ ያላቸውን አቋም ብቻ ነው፡፡ ሌሎችም ልክበተውሂድ ፣ በሩሡሎች መልእክተኛነት ፣ በሸሪዓው እና በቀደር ዙሪያ አቋም እንዳላቸው ሁሉ ባልተጠቀሱ የቀሩ ጉዳዮችም የተለዩ አቋሞች ያሏቸው ሲሆን ይህን ለማብራራት ተከታታይና  በጣም ሰፋ ያሉ ማብራሪያዎች ይሻል በዚህ እርስ ግን ለቅምሻ ያክል የስኳሁኑ ይበቃናል ሀቅን በሀቅነቱ እንዲያሳየን እና መከተልንም እንዲለግሰን ፤ ባጢልንም በባጢልነት እንዲያሳየን እና መራቅን እንዲቸረን ፤ ከመራን በኋላ ልቦቻችንንም እንዳያጠምብን አላህን እለምነዋለሁ፡፡ #ክፍል1 https://t.me/AbulQmane/2148 ክፍል2 https://t.me/AbulQmane/2149 ክፍል3 https://t.me/AbulQmane/2150 ክፍል4 https://t.me/AbulQmane/2172 ክፍል5 https://t.me/AbulQmane/2176 ክፍል6 https://t.me/AbulQmane/2219

🔺ሱፊያዎች በዲንና በዒባዳ መሰረቶቸ ላይ ያአላቸው ስህቱ አቋም #ክፍል6 ~~~ وموقف الصوفية من أصول العبادة والدين ስድስተኛ፡- ባጢል (ስህተት) ከሆነው የሱፍያ ዲን መካከል ፡ አንድ ሰው ከሸሪዓዊ ሀላፊነት የሚወጣበት ደረጃ አለ ማለታቸው ነው ይህ የተሶውፍ አመለካከት ድንበር አልፎ የጥመትን ጫፍ የመድረሱ ውጤት ነው፡፡ የተሶውፍ መሰረቱ ኢብን አልጀውዝይ እንደተናገረው ነበር፡-ወራዳ የሆነን ስነምግባር ታግሎ መመለስ፣ ነፍስን አሰልጥኖ ወደጥሩ ስነምግባርመውሰድ፡፡ ዙህድ ፣ ችሎታ ፣ ትዕግስት ፣ ኢኽላስ እና እውነተኛነት፡፡)) በተጨማሪ የሚከተለውን ተናግሯል፡- ((የመጀመሪያዎቹ (ሱፍዮች) ባህሪ ይህ ነበር ፤ አንዳንድ ነገሮችን ኢብሊስ እነርሱን ከዚያም ተከታዮቻቸውን ቀላቀለባቸው፡፡ አንድ ክፍለ ዘመን ባለፈ ቁጥር በሁለተኛው ክፍለ ዘመን (ሰይጣን) ወደኋላ ላሉት የበለጠ የተመቻቸ እስኪሆንለት ድረስ በሰዎች ላይ ዲናቸውን ይቀላቅልባቸዋል፡፡ ዋናው የመቀላቀል መሰረቱ ከእውቀት ማገዱ ፣ ተፈላጊው አላማ እውቀት ሳይሆን ተግባር ነው ብሎ ማሳየቱ ነው፡፡ የሰይጣን ዋና አላማ የእውቀትን መብራት በእነርሱ ላይ ካጠፋ በኋላ በጨለማ እንዲደናበሩ ማድረግ ነው፡፡ ይህ ብቻ አይደለም ዱንያን በአጠቃላይመተው አስፈላጊ እንደሆነ ያሳያቸዋል፡፡ አካላቸውን የሚያስተካክሉበትን ዱንያ እንዲተው ያደርጋቸዋል፡፡ ገንዘብን ከጊንጥ ጋር ያመሳስሉታል … ነፍስን ከአቅም በላይእንድትሸከም ያደርጓታል፡፡ ጭራሽ ከአልጋ ላይ መጋደምን አያስፈልግም እስከማለት ይደርሳሉ … ከእነርሱ መካከል እውቀት ካለመኖሩ የተነሳ ሳያውቅ በረሡል ላይበተዋሹ ሐዲሶች ለመተግበር ይሞክራል፡፡ ከዚያም ሰዎች መራብ ፣ መደህየት እንዳለባቸው በወስዋስ (በብዥታ) ላይ የሚቀሰቅሱ መጽሐፎችን የጻፉ ሰዎች መጡ፡፡ ልክ እንደ ሀሪስ አልሙሀሲቢ ማለት ነው፡፡ ሌላው ደግሞ መጣ የሱፍያን መዝሀብ ማጣራት ጀመረ ፣ እነርሱ የሚለዩበትን ባህሪዎች ነጥሎ አስቀመጠ፡፡ የሱፍያ ባህሪ በማጨብጨብ ፣ በመወዛወዝ ፣ በዜማ የተለየ እንደሆነ ግልጽ አደረገ፡፡ አሁንም ነገሩ በዚህ አላቆመም እየጨመረ ሄደ፡፡ መሻይኾቻቸው …. ከዑለማ ራቁ እነርሱ ያሉበትን “ኢልመል ባጢን”(ስውር እውቀት)በማለት ሰየሙ ፣ የሸሪዓውን እውቀት ደግሞ “ኢልመ ዟሂር” (ግልጽ እውቀት) በማለት ሰየሙ፡፡ ከእነርሱ መካከል ከረሐብ የተነሳ ብዥታ ውስጥ የወደቀውን ፣ በቃ ይህ ግለሰብ የአላህ ከፍተኛ ወዳጅ እንደሆነ አድርገው ቆጠሩ…እነዚህ ሰዎች በክህደትና በቢድዓ መካከል ሆኑ፡፡ ከዚያም ጦሪቃዎች በርካታ ሆኑ (1) ፣ ዓቂዳቸውም በዚህ ምክንያት ተበላሸ፡፡ ከእነርሱ መካከል የ “ሁሉል” ዓቂዳ ያለው አለ፡፡ ከእነርሱ መካከል የኢቲሃድ ዓቂዳ ያለው አለ፡፡ ኢብሊስ በቢድዓ የእውቀት አይነቶች እንዲዋዥቁ ከማድረግ አልተወገደም …)) ( 📕ተልቢስ አል'ኢብሊስ 157-158) ሸይኹል ኢስላም ብን ተይሚያ - ረሂመሁሏህ - የሚከተለውን ጥያቄ ተጠየቁ፡- ((አንዳንድ ሰዎች አሉ ነፍስን በማለማመድ የዘወተሩ ፣ ከዚያም እራሳቸውን ጀውሐር (በራሳቸው የተብቃቁ) ነን ብለው ያሰቡ ፤ “… ፣ ትዕዛዝ ክልከላ የተራው ማህበረሰብ መንገድ ነው ፣ እነርሱም ጀውሐር ደረጃ ቢደርሱ ሁሉም ነገር ከእነርሱ ላይይነሳላቸው ነበር፡፡ ነብይነት ተራውን ማህበረሰብ በህግ ለመዳኘት እና ስርዓት የማስያዝ ጥበብ ነው፡፡ እኛ ደግሞ ከተራው ማህበረሰብ አይደለንም፡፡ በተክሊፍ (በህግ) ጓዳ የምንገባ አይደለንም፡፡ እኛ ጀውሀር ሆነናል ጥበብን አውቀናል ይላሉ፡፡” መልስ፡- ይህ ንግግር ከአይሁድና ነሷራ ንግግር የከፋ ትልቅና ከባድ ክህደት እንደሆነ ከኢማን እና ዒልም ባለቤቶች ዘንድ ጥርጥር የለውም፡፡ አይሁድና ነሷራ በተወሰኑ ኪታቦች አመኑ በከፊሉ ካዱ፡፡ እነዚህ ከሐዲ ከመሆናቸው ጋር ለአላህ ትዕዛዝን ፣ ክልከላን ፣ ዛቻ ፣ ቀጠሮ እንዳለ ያምናሉ ይህም የተሰረዘረውን የተቀየረውን አይሁድነትን እና ነሷራነትን አጥብቀው እስከያዙ ድረስ ነው፡፡ከእነርሱ አማኞች ውስጥ ሙናፊቆቻቸው ማለትም ፈላስፎቻቸው ከዚህ ኡመት ሙናፊቆች በጣም የከፉ ናቸው፡፡ ምክንያቱም ክህደትን ይፋ አድርገው ፣ ኒፋቅን ድብቅ አደረጉ፡፡ ኢማንን ይፋ አድርጎ ንፍቅናን ከደበቀው የከፋ ሆነ፡፡ የተፈለገው አላማ ፣ በተሰረዘው ጥቅል ህግ አጥብቀው ከያዙት ነሷራ እና አይሁድ በአጠቃላይ ትዕዛዝ ክልከላ ከእኔ ላይ ወድቆልኛል ከሚለው ሱፍያ የተሻለ ነው ። እነዚህ ከማንኛውም መጽሓፍ ፣ ሸሪዓዎች እና ሚለሎች ሁሉ አፈንግጠዋል፡፡ ምክንያቱም ለአላህ መታዘዝና መከልከል የሚባል ነገር ከእነርሱ ዘንድ የለም፡፡ እንደውም ከዚህ በፊት ከኢብራሂም ቅሪት መጽሓፍትን አጥብቀው ከያዙት የአረብ ሙሽሪኮችም ይከፋሉ፡፡ እነዚህ ሙሽሪክ ከመሆናቸው ጋር እነርሱ የያዙት የተወሰነ ሐቅ አለ፡፡ እነዚህ ግን ፣ ከሐቅ የወጡ ናቸው ፤ ከሐቅ አንድም የያዙት የለም፡፡ እነርሱ ፣ ትዕዛዝንም ክልክልንም ሙሉ በሙሉ ዝግ አድርገዋል፡፡)) በመቀጠል እንዲህ ይላል፡- ((ከእነርሱ መካከል በሚከተለው ቁርኣን ማስረጃ የሚያደርግ አለ፡- وَاعْبُدْ رَبَّكَ حَتَّىٰ يَأْتِيَكَ الْيَقِينُ እውነቱም (ሞት) እስኪመጣህ ድረስ ጌታህን ተገዛ፡፡ Surah: Al-Hijr, Ayat: 99 የዚህ ትርጉሙ፡ “ጌታህን ተገዛ እውቀት እና ግንዛቤ እስክትደርስ” ማለት ነው ይላሉ፡፡ ከዚህ ደረጃ ከደረስክ ዒባዳ ከአንተ ላይ ይነሳልሃል፡፡ አንዳንዶች ደግሞ ፡ “የሆነ ባህሪ ላይ እስክትደርስ ድረስ ስራ” ይላሉ፡፡ የሱፍያ ባህሪ ላይ ከደረስክ ዒባዳ ከአንተ ላይ ይነሳልሃል፡፡ እውቀትና ግንዛቤ ላይ ከደረሱ ፈርድ ይተዋሉ ፤ ሀራም ይሰራሉ፡፡ ይህ ከዚህ በፊት እንዳስቀደምነው ግልጽ የሆነ ክህደት ነው፡፡በእነርሱ ላይ እንጅ ለእነርሱ ማስረጃ ሆኖ የሚያገለግል አይደለም፡፡ ሀሰን አልበስርይ - ረሂመሁሏህ - የሚከተለውን ተናግረዋል፡- " إن الله لم يجعل لعمل المؤمنين أجلا دون الموت" “ለሙእሚን ከሞት በፊት (ስራን የሚያቆምበት) የጊዜ (ገደብ) አላህ አላደረገም” ከዚያም የሚከተለውን ቁርኣን አነበበ፡- وَاعْبُدْ رَبَّكَ حَتَّىٰ يَأْتِيَكَ الْيَقِينُ እውነቱም (ሞት) እስኪመጣህ ድረስ ጌታህን ተገዛ፡፡ “የቂን” ማለት ሞት እና ከሞት በኋላ መሆኑን ዑለሞች በአጠቃላይ ተስማምተዋል፡፡ ለዚህ ተመሳሳይ የሚከተለው ቁርኣን ማስረጃ ይሆናል፡፡ مَا سَلَكَكُمۡ فِي سَقَرَ (ይሏቸዋልም) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?» وَلَمْ نَكُ نُطْعِمُ الْمِسْكِينَ "ምስኪኖችንም አንመግብም ነበር።" وَكُنَّا نَخُوضُ مَعَ الْخَائِضِينَ "ከከንቱ ንግግርና ከሐሰት ጋር ከሚገቡ ሰዎች ጋር እንገባ ነበር።" وَكُنَّا نُكَذِّبُ بِيَوْمِ الدِّينِ "የፍርድ ቀንንም እናስተባብል ነበር።" حَتَّىٰ أَتَانَا الْيَقِينُ "እርግጠኛው ነገር (ሞት) እስከ መጣብን ድረስ።" ሱረቱ አል ሙደሲር42-47 ይህን ቃል ሶላትንና ዘካን እንደተው ፣ በትንሳኤ ቀን መዋሸታቸውን ፣ ሞት እስኪመጣቸው ድረስ ከሚዘባርቁት ጋር መዘባረቃቸውን የተናገሩት በጀሀነም ውስጥ ሆነው ነው፡፡ እነርሱ በዚህ ባህሪ ላይ ሆነው በዱንያ ላይ አማኝ ያልነበሩ መሆናቸው የታወቀ ጉዳይ ነው፡፡ አላህ በሚከተለው ቃል ከተናገረላቸው ሰዎችም አይደለም፡፡ وَبِالْآخِرَةِ هُمْ يُوقِنُونَ

🔺ስንወለድ ሙስሊም ነን ሲባል ? ~~~~ «ፊጥራ» الْفِطْرَةِ ማለት 'ተፈጥሯዊ ዝንባሌ' natural inclination ማለት ሲሆን፥ ይህም አምላክ አጠቃላይ የሰው ልጆችን ሁሉ እኩል አድርጎ የፈጠረውን ንጹሕ ማንነታችንን የሚገልጽ ቃል ነው። በእስልምና አስተምህሮ ድቀተ-ባሕርይ ወይም ጥንተ-አብሶ 'original sin' እየተባለ ከውልደታችን ጀምረን በውርስ ያመጣነው አንድም ነገር ባለመኖሩ ሁሉም ሰው ሲወለድ ያልተበከለ እና ኃጢአት አልባ የሆነውን አዲስ ማንነት ይዞ ነው። ይህ በተፈጠሮ ንጹሕ የሆነው ማንነት 'ፊጥራ' ተብሎ ይጠራል። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رضى الله عنه قَالَ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم ‏كُلُّ مَوْلُودٍ يُولَدُ عَلَى الْفِطْرَةِ، فَأَبَوَاهُ يُهَوِّدَانِهِ أَوْ يُنَصِّرَانِهِ أَوْ يُمَجِّسَانِهِ،  የአላህ መልዕክተኛ ❲ﷺ❳ እንዲህ ብለዋል:- "ሁሉም የሚወለደው ሰው በፊጥራ ላይ ነው። ወላጆቹ ግን አይሁድ፣ ክርስቲያን ወይም ዞርስቲያን ያደርጉታል።" (📚Sahih al-Bukhari 1385: Book 23, Hadith 137) ከዚህ ሐዲስ በግልጽ የምንረዳው፥ አንድ ህጻን በወላጆቹ ጫና ወደ ኩፍር ከመግባቱ በፊት ያልተበረዘ ማንነት (ፊጥራ) ላይ መሆኑን ነው። ቡኋለ ላይ የተለያዩ ክህደቶችን በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ይፈፅማል። ያኔ ያ ንጹሕ ተፈጥሯዊ ዝንባሌው ጠፍቶ ካፊር ይሆናል። አምላካችን አላህ በቅዱስ  ቃሉ ይህን 'ንጹሕ ፈለግ' ያዙ፣ ከዚያም አትውጡ በማለት ያዘናል፥ ❲ምዕራፍ 30፥30❳...ይህን ስንል ግን አንድ ሰው ሲፈጠር (ሲወለድ) የእስልምናን ሃይማኖት ሕግ እና ስርዓት አውቆ ይመጣል ማለታችን አይደለም። የትኛውም ሰው ሃይማኖተኛ ሆኖ ወደዚህ ምድር አይመጣም። ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያህ እንዲህ ይላሉ:- ولا يلزم من كونهم مولودين على الفطرة أن يكونوا حين الولادة معتقدين للإسلام بالفعل فإن الله أخرجنا من بطون أمهاتنا لا نعلم شيئا ولكن سلامة القلب وقبوله وإرادته للحق : الذي هو الإسلام بحيث لو تعك من غير مغير لما كان إلا مسلما «በፊጥራ (ተፈጥሯዊ ዝንባሌ) ላይ ተወለዱ ሲባል በተወለዱበት ወቅት እስልምናን በተግባር ይፈፅሙታል (ያውቁታል) ማለት አይደለም። ምክንያቱም አላህ ከእናቶቻችን ሆድ ሲያወጣን ምንም የማናውቅ አድርጎን ነውና። ስለዚህ እውነትን ይፈልግ ዘንድ የልብን ንጽሕና ሰጥቶታል። አንዳች በካይ ባይቀይረው ኖሮ ከሙስሊም ውጪ ሌላ አይሆንም። ❲መጅሙዕ አል-ፈታዋ ቅፅ 4/247❳ ሸይኹ አክሎም እንዲህ ይላሉ:- ‟ይህ ተፈጥሯዊ ዝንባሌ በራሱ የአምላክን መኖር ያረጋግጣል፣ እርሱን መውደድና ብቻውን ልናመልከው እንደሚገባ ይጠቁማል።” አዎ ተፈጥሮ አንድ አምላክ መኖሩን ያሳያል፣ ያ አምላክ ሁሉን ቻይ፣ ፍቅር (ወዳድ)፣ ከእኛ ጋር የሆነ ገዢ ኃይል መኖሩን ገና ከልጅነታችን ጀምሮ እንድናውቅ ያደርገናል። አንዳች አደጋ ሲደርስብን ልባችን ቶሎ ያድናት ዘንድ የምትማፀነው ያ የማይታየው አካል እርሱ አምላክ ነው። ይህ በተፈጥሮ የምናውቀው የኃያል አምላክ ባህሪ ነው። ይህን ታላቅ አምላክ በትክክል ማወቅ ግዴታ ስለሆነ አምላክ በነቢያቱ በኩል እራሱን ለእኛ ግልጽ አድርጓል። ስናጠቃልል:- ሰው ሲወለድ ሃይማኖተኛ ሆኖ አይደለም፣ በተፈጥሮ ለአምላክ ታዛዥ ከመሆኑ አንጻር ሙስሊም መባሉ እውነት ቢሆንም ከTheological perspective በኩል ከሆነ ግን ትክክል አይደለም። ያን እስልምና የምናገኘው በነቢያት ትምህርት ብቻ ነው። https://t.me/AbulQmane

ኢንሻ አላህ ይቀጥላል

🔺የአላህ ባህሪያት አይነቶች ~~~~~~ በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኃሩኃ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው:: ሾለ አላህ ባህሪያት ስናወራ ከሰሞኑ በጣም ወሳኝ እና አንገብጋቢ ጉዳዮችን ለመዳሰስ ሞክረናል:: ዛሬም ይህንኑ ጉዙ በርዕሱ ሾር አሉ ከሚባሉ አጭር ነገር ግን ወሳኝ ሃሳቦች መካከል የሆነውን የአላህ ባህሪያት አይነቶችን አስቀምጥላቹሀለው:: የአላህን ባህሪያት ከሁለት ነገር አንጻር ለ2 እንከፍላቸዋለን:- ​1.ባህሪያቱን ከተግባር አንጻር (ሲፋት አስ-ዛት እና ሲፋት አል-ፊዕሊያ) ​ይህ ምድብ ባህሪያቱ ከአላህ ህልውና (ዛት) ጋር ያላቸውን ቁርኝት መሰረት ያደረገ ነው፡- ​ሲፋት አዝ-ዛት (የገሀዳዊ መለያ ባህሪያት)፦ በፍልስፍናው አለም Essential Attributes ወይም Ontological Attributes ብለን እንጠራቸዋለን:: እነዚህ አላህ ሁልጊዜም የነበሩትና ከእሱ የማይለዩ፣ መጀመሪያም የሌላቸው መጨረሻም የሌላቸው ባህሪያት ናቸው። ​ልክ እንደ እውቀት፣ ህያውነት፣ ችሎታ ፣ መስማት፣ ማየት እና የበላይነት (ዑሉው) እና በቁርኣንና በሐዲስ የተጠቀሱትን በሙሉ ያካታል እነሱም እጅ፣ጣት፣  እግር... ናቸው። ​ሲፋት አል-ፊዕሊያ (የተግባር ባህሪያት)፦ Active Attributes ወይም Relational Attributes ብለን እንጠራቸዋለን:: እነዚህ አላህ ከፍላጎቱና ከጥበቡ (ሒክማህ) ጋር አያይዞ በፈለገው ጊዜ የሚከውናቸው ተግባራዊ ባህሪያት ናቸው። ለ​ምሳሌ፦ መፍጠር ፣ ሲሳይን መስጠት ፣ ወደ ቅርቢቱ ሰማይ መውረድ ናቸው ። ​2.ባህሪያቱን ከማረጋገጥና ከመካድ አንጻር (ሲፋት አል-ሙስበታህ እና አስ-ሰልቢያ) ​ሲፋት አል-ሙስበታህ (የማረጋገጫ ባህሪያት)፦ አላህ በቁርኣን ውስጥ ወይም ነቢዩ (ሜ.ዐ.ወ) በሀዲስ ያረጋገጡለት የፍጹምነት ባህሪያት ናቸው። (ለምሳሌ፡- እዝነት፣ ኃያልነት፣ ጥበብ)። ​ሲፋት አስ-ሰልቢያ (የማግለያ ባህሪያት)፦ ከአላህ ባህሪ ጋር የማይመጥኑ፣ ጉድለትን የሚያሳዩ እና ከእሱ ላይ መነሳትና መራቅ ያለባቸው ባህሪያት ናቸው። ​ምሳሌ፦ አለመሞት (ሞትን ማንሳት)፣ አለመተኛት ወይም አለመንቀላፋት፣ አለመበደል፣ እና ድካም አላህን እንደማይነካው ማረጋገጥ። በቀላሉ የአላህ ባህሪያት አይነቶች እነዚህ ናቸው በጣም ቀላል ነገር ግን ልንገነዘባቸው የሚገቡ ናቸው:: በቀጣይ ዙፈቱል ፊዕሊያ እና ዛቲያህ ውስጥ የተጠቀሱ የአላህ ባሕሪያትን ወደፊት አላህ ካለ "እናያለን" https://t.me/AbulQmane

አልተገለፀም" እንዳለው፣ ክርስቲያኑም "ሚስጥር ነው / መንፈስ ነው / አይታወቅም" ወደሚል መልስ መምጣቱ አይቀርም።ታዲያ የራሳቸው የነገረ-መለኮት (Theology) ሊመልሰው ያልቻለውን፣ "ሚስጥር ነው" ብለው የሚያልፉትን ጥያቄ፣ ሙስሊሙ "ተውቂፊያህ ነው (አልተገለፀም)" ሲል ለምን ያላግጣሉ? ይህ ከድንቁርና የመነጨ ሁለት አይነት ሚዛን (Double Standard) ነው!⏱ በአጭሩ ስጠቀልለው፦"ስለ አላህ አካላዊ አወቃቀር አልተገለፀም ስንል፣ 'የምናመልከው አምላክ ማን እንደሆነ አናውቅም' ማለታችን አይደለም! እኛየምናመልከው አምላክ ማንነቱ (አዛኝነቱ፣ ኃያልነቱ፣ ፈጣሪነቱ፣ ጥበበኝነቱ) በግልፅ የታወቀ አምላክ ነው። ነገር ግን አካላዊ አወቃቀሩን (Anatomy) አልተገለፀም ያልንበት ምክንያት... እናንተ እንደምታስቡት አላህ የጨጓራ፣ የኩላሊት፣ የተጣበቀ ጅማት እና የብልት ስብስብ የሆነ 'ባዮሎጂካዊ ሮቦት' ወይም የጥንት ግሪክ አፈ-ታሪክ (Mythology) አምላክ ስላልሆነ ነው! ፈጣሪ ከፍጡር ባዮሎጂ የጠራ ነው። አዕምሯችሁን ከሳጥን ውጪ አውጥታችሁ አስቡ።የነበረው ሁኔታ ሑሱ የሰጠው መልስ ምን ያህል ክብደት ያለውና ምሁራዊ እንደሆነ፣ የጠያቂዎቹ አእምሮ ግን ምን ያህል ጥልቀት የሌለው (Superficial) እንደሆነ በሚገባ ያሳያል። https://t.me/AbulQmane/2207

🛑«አልተገለፀም» ማለት ምን ማለት ነው⁉️=========================✍️ በእስልምና የስነ-መለኮት ትምህርት (ዐቂዳህ) ውስጥ ሾለ አላህ ማንነትና ባህሪያት የምንማርበት ትልቁ ወርቃማ ህግ "ተውቂፊያህ" ይባላል። ይህ ማለት፡- áˆľáˆˆ ፈጣሪ ባህሪያት መናገር የምንችለው አላህ በቁርኣን ሾለ ልሹ የነገረንን ወይም ነብዩ  በሐዲሥ የነገሩንን ብቻ ነው áˆ›áˆˆá‰ľ ነው።አላህ በቁርኣን «እጅ አለው፣ ፊት አለው፣ ዓይን አለው» ብሎናል፤ እኛም እናምናለን። «እግሩና እጁ እንዴት ነው የተያያዘው? ጭንቅላት አለው ወይ?Âť የሚለውን ግን አላህ አልነገረንም። ስለዚህ "አልተገለፀም" (አላውቅም) ማለት ፍፁም ምሁራዊና አክብሮታዊ መልስ ነው።ይህንን መሰል ጥያቄ ከዚህ በላይ ወደ ላቀ ስነ-መለኮታዊ (Theological) እና ፍልስፍናዊ ጥልቀት ወስደን ስንመረምረው፣ እፎይ የሚባለው ተሳዳቢ ጥያቄዎች የመረጃ እጥረት ብቻ ሳይሆኑ፣ የከፍተኛ የአስተሳሰብ ድህነት እና የካቴጎሪ መዛባት (Category Mistake) የሚባል የሎጂክ ስህተት መሆናቸውን እናረጋግጣለን።ክርስቲያኖች አልተገለፀም ሲባል "ማንነቱ ያልተገለፀ አምላክ" ብለው ሙድ ለመያዝ ሲሞክቱ፣ በራሳቸው እምነት ላይ እየሳቁ መሆኑን የሚያሳይ፣ ማንም ሎጂካል የሆነ ሰው ሊክደው የማይችለውን እውነታ ላካፍላችሁ፦ 1⃣ ፈጣሪን በባዮሎጂ መነጽር ማየት፦🎀 የእፎይ ትልቁ የሎጂክ ስህተት፣ አላህ (ፈጣሪ) የፈጠረውን የባዮሎጂ፣ የፊዚክስ እና የአናቶሚ (Anatomy) ህግ፣ መልሶ ፈጣሪው ላይ ለመተግበር መሞከሩ ነው።አንድን ነገር መለካት ያለብህ በራሱ ካቴጎሪ (ምድብ) ውስጥ ብቻ ነው።  - ለምሳሌ፡- "የድምፅ ክብደቱ ስንት ኪሎ ነው?" ብለህ አትጠይቅም። ድምፅ በዴሲቤል (Decibel) እንጂ በኪሎግራም አይለካም።  ☑ "የአረንጓዴ ቀለም ጣዕሙ ምንድን ነው? ጨው ጨው ይላል ወይስ ስኳር?" ብለህ አትጠይቅም። ቀለም ይታያል እንጂ አይቀመስም።💡 ከገባችሁ ሌላ ፊልድ ምሳሌ ልጨምርላችሁ፡- አንድ የኮምፒውተር ጌም ሰሪ (Programmer) "xyz" የተባለውን ጌም ፈጠረ እንበል። xyz በጌሙ ዓለም ውስጥ እግር አለው፣ ይዘላል፣ እንጉዳይ ይበላል፣ ይሞታል። አሁን xyz (ፍጡሩ) አዕምሮ ቢኖረውና ሾለ ፈጣሪው (ሾለ ፕሮግራመሩ) ቢጠይቅ፡- "የፈጣሪዬ ጭንቅላት ስንት ፒክስል (Pixel) ነው? ፈጣሪዬ ልክ እንደኔ ለመዝለል 'Spacebar' ይጫናል ወይ? ፈጣሪዬ ጌም ኦቨር (Game Over) ሲሆን የት ነው የሚሄደው?" ብሎ ቢጠይቅምን ትለዋለህ?"አንተ ደነዝ xyz... የፕሮግራመሩ (የፈጣሪህ) ዓለም ካንተ ዓለም (Dimension) ፍፁም የተለየ ነው! እሱ ፒክስል (Pixel) እና ጌም ኦቨር የለበትም፤ ምክንያቱም እሱ ነው ፒክስልን የፈጠረው!" ነው የምትለው።እፎይ ያደረገውም ይህንኑ የ"xyz" ስህተት ነው። አላህ የቦታን፣ የጊዜን፣ የጅማትን፣ የመራቢያ አካልን (ብልትን)፣ የጭንቅላትን አፈጣጠር(Biology & Physics) የፈጠረ ጌታ ሆኖ ሳለ፣ እፎይ ግን "አላህ … አለው? እጁ ከወገቡ ጋር ተያይዟል?" ብሎጠየቀ። ፈጣሪ አካላዊ ፍጡር (Biological Organism) ስላልሆነ የዚህ ጥያቄ መልስ "አልተገለፀም" ብቻሳይሆን "ጥያቄው ልሹ ለፈጣሪ የማይመጥን (Invalid) ነው!" የሚል ነው።2⃣ አላህ ብ…ት አለው ወይ? ለሚለው፦☑ ሾለ ፈጣሪ ጥልቅነት (Transcendence) ያልገባው ሰው ብቻ ነው ይህን ጥያቄ የሚጠይቀው። የሰው ልጅም ሆነ እንስሳት "የመራቢያ ብልት" (Reproductive organs) ለምን አስፈለጋቸው? 1️⃣  ለማሸናት (ለቆሻሻ ማስወገጃ)፡- ፍጡር ይበላል፣ ይጠጣል፤ የተረፈውን ቆሻሻ ማስወገድ አለበት። 2️⃣  ለመራባት (Surivival of Species)፡- ፍጡር ይሞታል፣ ያልቃል። ስለዚህ ዘሩ እንዳይጠፋ ለመተካት ማራባት አለበት። 3️⃣  ለስሜት (Pleasure)፡- ፍጡር ደካማ ስለሆነ ከሌላ አካል ጋር በመጣመር ስሜቱን ማርካት ይፈልጋል።አላህ ግን በቁርኣን "አል-ጘኒይ" (ከፍጡራን ሐጃ የተብቃቃ)፣ "አስ-ሶመድ" (የማይራባ፣ የማይሞት፣ የዘላለም አምላክ፣ የሁሉም መጠጊያ) መሆኑን ገልጿል። የማይበላ፣ የማይጠጣ፣ የማይሞት፣ ዘርን መተካት (መራባት) የማያስፈልገው ፍፁም አምላክ... እንዴት ሆኖ ነው"የመራቢያ ብልት አለው ወይ?" ተብሎ የሚጠየቀው? ሑሱ "አልተገለፀም" ያለው አላህ ለልሹ ያላፀደቀውን፣የፍጡርን ጉድለት (Anthropomorphism) አላህ ላይ መለጠፍ ከባድ ክህደት ስለሆነ ነው።3⃣ "እጁ እና ወገቡ የተያያዘ ነው ወይ?"፦☑ በእስልምና "ማንነቱ ያልተገለፀ አምላክ" አይደለም የምናመልከው። አላህ ራሱን ከ99 በላይ በሆኑ ስሞቹና በበርካታ ባህሪያቱ በሚገባ ገልጿል።አላህ "እጅ አለው፣ ፊት አለው" ስንል አላህ ባለው መሠረት እናምናለን።ግን "እንዴት ነው? (How?)" ለሚለው ጥያቄ፣ ታላቁ ኢማም ማሊክ ያስቀመጡት ዓለምን የሚያስማማ ሎጂካዊ ህግ አለ፦"الاستواء معلوم، والكيف مجهول" (የአላህ ባህሪ በመረጃ ይታወቃል፤ እንዴትነቱ (አካላዊ አወቃቀሩ) ግንበአዕምሮ አይደረስበትም (መጅሁል ነው)! በእርሱ ማመን ግዴታ ነው፤ (እንዴት ብሎ) መጠየቅ ግን ጥመት ነው!)💡 በምሳሌ እንየው፡- እስኪ የክርስቲያን ጠያቂዎችን እንዲህ ብለን እንጠይቃቸው፡- "አንተ በውስጥህ ነፍስ (Soul/Spirit) እንዳለህ ታምናለህ? አዎ! ማለቱ አይቀሬ ነው። እሺ ንገረኝ... ነፍስህ እጅ አላት? የነፍስህ እጅና ወገብ በጅማት የተያያዘነው? ነፍስህ ብልት አላት ወይስ ፆታ የላትም?" ብትላቸው በጭራሽ ሊመልሱልህ አይችሉም። የሰው ልጅ የገዛ ነፍሱን፣ ውስጡ ያለችውንህይወት፣ ቅርጿን እና አካሏን አያውቅም። አላህ በወንጌልም ሆነ በቁርኣን "ሾለ ሩሕ (ነፍስ) ጥቂትን ዕውቀት እንጂ አልተሰጣችሁም" ብሏል። ታዲያ የሰው ልጅ የገዛ ነፍሱን ባዮሎጂካዊ ቅርፅ ማወቅ ካልቻለ፣ ይህንን ማብቂያ የሌለውን ዩኒቨርስ የፈጠረውን፣ ወሰን የለሹን አምላክ (Infinite God)፣ በአንጎሉ ስንዝር (Finite Mind) ለክቶ፣ "ወገቡና እጁ እንዴት ተያያዘ?" ብሎ መጠየቅ ምን ያህል የአስተሳሰብ ድንክነት ነው?!4⃣ ጠረጴዛውን ስናዞረው ደግሞ፦☑ "ያልተገለፀ አምላክ ነው የምታመልኩት" ብለው ሲያላግጡ፣ ክርስትና ልሹ በዚህ ጉዳይ ላይ ያለበትን የከፋ ማጥ አላስተዋሉም።እስኪ ይህንን ጥያቄ ለእፎይ እና መሰሎቹ ወርውሩላቸው፦⬇️ መጽሐፍ ቅዱሳችሁ እግዚአብሔር "መንፈስ ነው" ይላል (ዮሐንስ 4፡24)። ግን ያው መጽሐፍ ቅዱስ ሾለ እግዚአብሔር አካላዊ መገለጫዎች በብዙ ቦታ ይናገራል፦   ☑ ክንፍና ላባ አለው፡- መዝሙረ ዳዊት 91፡4 "በላባዎቹ ይጋርድሃል በክንፎቹም በታች ትጠጋለህ።"  ☑ አፍንጫ አለው፣ ጢስም ይወጣዋል፡- መዝሙረ ዳዊት 18፡8 "ከአፍንጫው ጢስ ወጣ፥ ከአፉም የሚያባላ እሳት ነደደ።"አሁን የክርስቲያን ጠያቂዎችን የራሳቸውን ሎጂክ ተጠቅመን እንዲህ እንጠይቃቸው፡-«እግዚአብሔር አብ (God the Father) ክንፍና ላባ ካለው፣ ልክ እንደ እርግብ ባዮሎጂካዊ የሆነ ላባ፣ ስጋና ደም አለው ማለት ነው? አፍንጫ ካለውስ? የአፍንጫ ቀዳዳና የመተንፈሻ ቱቦ (Trachea) አለው ማለት ነው? እግዚአብሔር የተያያዘ አካል ካለው፣ አብ ብልት አለው ወይ?»መልሱ ምን ይሆናል? ወይ "እግዚአብሔር መንፈስ ስለሆነ እንደሰው አካል የለውም (ምስጢር ነው)" ይላል፤ አሊያም "ይህ ዘይቤያዊ (Metaphorical) አገላለፅ ነው" ይላል። አያችሁ? ልክ ሑሱ"እንዴትነቱ