en
Feedback
ፋአድ 𝐅𝐔𝐀𝐃 𝙰𝚋𝚞 𝚕𝚀𝚖𝚊𝚗𝚎

ፋአድ 𝐅𝐔𝐀𝐃 𝙰𝚋𝚞 𝚕𝚀𝚖𝚊𝚗𝚎

Open in Telegram
1 554
Subscribers
-124 hours
-17 days
+1530 days
Posts Archive
አልተገለፀም የሚለው አባባል በልቁ ከሆነ ይታረም! ~~~ ቆሻሻው እፎይ «ፈጣሪ ብልት አለው ወይ» ?ብሎ እየጠየቀው «እርሱም አልተገለፀም» ብሎ መመለሱ ስህተት ነው በዚህም ላይ ማንም ሊከተለው አይገባም። አል-አስማእ ወሲፋት (ስም እና ባሕሪያት) ተውቅፊይ መሆኑ እሙን ነው። አላህ ለራሱ ያፀደቀውን ወይም መልእክታኛው ለአላህ ያፀደቁትን እንጂ አናፀድቅም አላህ ከራሱ ውድቅ ያደረገውን ወይም መልእክተኛው ከራሳቸው ውድቅ ያደረጉትን እንጂ ውድቅም አናደርግም። ስለዚህ በመፅደቅም ሆነ ውድቅ በመደረግ ያልመጣን ነገር ዝም ማለት የአንድ ሙእሚን መገለጫ ነው። የፀደቀውን እናፀድቃለን ወድቅ የተደረገውን ውድቅ እናደርጋለን ኢስባትም ነፍይም ያልማጣበትን ደግሞ ምላሳችን እንሰበስበታለን። ይህ ማለት ግን አ'ሲፋት አል-ከማልን (የ ምሉዕነት መገለጫን ) የሚጋጭ እና የሚቃረኑ ነገር በዝርዝር በተጠቀሰልን ቁጥር «አልተገለፀም» እያልን  መመለስ አለብን ማለት አይደለም። ከመለኮት አኳያ ሲፈተ ነቃኢሶችን (የጉድለት መገለጫዎችን) ኢጅማለን በጥቅሉ ውድቅ ማድረግ ሸርዕያዊ ግዴታችን ነው። አንድ ካፊር መጥቶ ከፆታ የፀዳውን አምላክ “ብልት አለው ወይ” በሚል  የአማኝ ቆዳ ሚያኮማትር ጥያቄ ሲጠይቅ አልተገለፀም ብሎ መመለስ ኢስላም ሚወክል ኻሰተን ደግሞ አህሉ ሱናን ሚወክል መልስ አይደለም ثبوت الكمال يستلزم نفي نقيضه “ምሉዕነት ማፅደቃችን ተቃራኒውን ውድቅ ማድረግ ያስፈርዳል"  በሚለው ቃዒዳ (መርሆ) ስር አስገብተን ካፊሮች ሚጠይቋቹን ግልጽ የሆኑ ማያወላውሉ ሰውኛ ነጎሮችን ከአላህ ውድቅ አድርጉ። ሁሱ “አልተገለፀም" ስላለ እየዞራቹ አልተገለፀም እንዳትሉ። ወይም ደግሞ አው ወይ አይ  ከማለት መልሳቹን እነዚህን የቁርአን አንቀጽ አድርጉ  سُبْحَانَ اللَّهِ عَمَّا يَصِفُونَ  ( الصافات :159) سُبْحَانَ رَبِّكَ رَبِّ الْعِزَّةِ عَمَّا يَصِفُونَ  وَسَلَامٌ عَلَى الْمُرْسَلِينَ * وَالْحَمْدُ لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ [الصافات: 180-182]  እና ሌሎችም...... በነገራችን ይህን ብላስፌሚ  በግልጽ በማስቀመጤ አላህ ይቅር እንዲለኝ እለምነዋለሁ ። ግልጽ መሆን ስላለበት በተመሳሳይ መልኩ እንዳይደገም እንጂ ይህን ቃል ከምጠቀም ዝምታ 100 እጥፍ ይሻል ነበር ። ግን ጉዳዩ ልብን የሚያደማ وما قدرو الله حق قدره ሚለው ውስጥ የሚገባ ስለሆነ መዋረስ ስለሌለበት ግልጽ አድርጌዋለሁ!

🔺የሸይኸ ፈውዛን ና የተክፊሪዮች አቋም እውን አንድ ነው? #ክፍል1 https://t.me/AbulQmane/1819 #ክፍል2 https://t.me/AbulQmane/1823 #ክፍል3 https://t.me/AbulQmane/1825 #ክፍል4 https://t.me/AbulQmane/1830 #ክፍል5 https://t.me/AbulQmane/1833 #ክፍል6 https://t.me/AbulQmane/1835

ﺃَﺳْﻠَﻢَ) ﻓﻲ ﺍﻵﻳﺘﻴﻦ ﺃﻱ : ﺍﻧﻘﺎﺩ《እርሱ መልካም ሠሪ ኾኖ ፊቱን ለአላህ ከሰጠና የኢብራሂምንም መንገድ ቀጥተኛ ሲኾን ከተከተለ ሰው ይበልጥ ሃይማኖቱ ያማረ ማን ነው አላህም ኢብራሂምን ፍጹም ወዳጅ አድርጐ ያዘው፡፡》  (📚አል ኒሳእ) ﻭﻣﻌﻨﻰ (ﺃَﺳْﻠِﻤُﻮﺍ) ﻭ ( ﻭﺃﺫﻋﻦ . 👆 ከላይ ባሉት አንቀፆች ላይ እጅ ስጡ እና ፊቱን ወደ አላህ ያዞረ በመባል የተጠቀሱት ለአላህ ታዘዙ ዝቅ በሉ ለማለት ነው!! ******                   ▪️👉 7ኛ ﺍﻟﻘﺒﻮﻝ ﺍﻟﻤﻨﺎﻓﻲ ﻟﻠﺮﺩ ؛ ﻓﻼﺑﺪ ﻣﻦ ﻗﺒﻮﻝ ﻫﺬﻩ ﺍﻟﻜﻠﻤﺔ ﻗﺒﻮﻻً ﺣﻘﺎً ﺑﺎﻟﻘﻠﺐ ﻭﺍﻟﻠﺴﺎﻥ ، ﻭﻗﺪ ﻗﺺَّ ﺍﻟﻠﻪ ﻓﻲ ﺍﻟﻘﺮﺁﻥ ﺍﻟﻜﺮﻳﻢ ﻋﻠﻴﻨﺎ ﺃﻧﺒﺎﺀ ﻣﻦ ﻗﺪ ﺳﺒﻖ ﻣﻤﻦ ﺃﻧﺠﺎﻫﻢ ﺍﻟﻠﻪ ﻟﻘﺒﻮﻟﻬﻢ ﻟـ ‏« ﻻ ﺇﻟﻪ ﺇﻻ ﺍﻟﻠﻪ ‏» ، ﻭﺍﻧﺘﻘﺎﻣﻪ ﻭﺇﻫﻼﻛﻪ ﻟﻤﻦ ﺭﺩﻫﺎ ﻭﻟﻢ ﻳﻘﺒﻠﻬﺎ·  ☂ ሰባተኛውና የመጨረሻው ሸርጥ ይቺን ንግግር እንቢተኝነትን በማስወገድ መቀበል ሲሆን አላህ በቁርአኑ ይቺን ላ ኢላሀ ኢለላህን ከልቡና በምላሱ በሙሉ ተቀባይነት የተቀበለን እንዳዳነና እንቢ ብለው ያፈነገጡትን ደግሞ እንዳጠፋ የበፊት ሰዎችን ታሪክ ነግሮናል!!  💥 አላህም እንዲህ ይላል፦  ﺛُﻢَّ ﻧُﻨَﺠِّﻲ ﺭُﺳُﻠَﻨَﺎ ﻭَﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺁﻣَﻨُﻮﺍ ﻛَﺬَﻟِﻚَ ﺣَﻘًّﺎ ﻋَﻠَﻴْﻨَﺎ ﻧُﻨْﺞِ ﺍﻟْﻤُﺆْﻣِﻨِﻴﻦَ ‏[ﻳﻮﻧﺲ 103‏] 《ከዚያም መልክተኞቻችንን እነዚያንም ያመኑትን እናድናለን፡፡ እንደዚሁም ምእምናንን (ከጭንቅ ሁሉ) እናድናለን፡፡ (ይህ) በእኛ ላይ ተረጋገጠ፡፡》 (📚ዩኑስ)  ﺇِﻧَّﻬُﻢْ ﻛَﺎﻧُﻮﺍ ﺇِﺫَﺍ ﻗِﻴﻞَ ﻟَﻬُﻢْ ﻟَﺎ ﺇِﻟَﻪَ ﺇِﻟَّﺎ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﻳَﺴْﺘَﻜْﺒِﺮُﻭﻥ★َ ‏ﻭَﻳَﻘُﻮﻟُﻮﻥَ ﺃَﺋِﻨَّﺎ ﻟَﺘَﺎﺭِﻛُﻮ ﺁﻟِﻬَﺘِﻨَﺎ ﻟِﺸَﺎﻋِﺮٍ ﻣَﺠْﻨُﻮﻥٍ‏ [ﺍﻟﺼﺎﻓﺎﺕ36-35]  《እነርሱ ከአላህ ሌላ አምላክ የለም በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ፡፡★እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን? ይሉም ነበር፡፡》 (📚አል ሷፋት)        ★ እንግዲህ አንተ ሀቅን ፈላጊ የሆንክ ባሪያ ሆይ የ "ላ ኢላሀ ኢለላህ" መስፈርቶች ከአጭር ማብራሪያ ጋር ይሄን ይመስላል። በስተመጨረሻም በዚህ ርእስ ዙሪያ ላይ የአንድን ዑለማ ንግግር እየጋበዝኳቹህ ይህን መስፈርት ያላሟል ከእስልምና ክልል በምኑም እንደሌለበት በማስታወስ ፅሁፌን እጨርሳለሁ!!  ✍ {[ውዱ የመሀመድ አብዱልወሀብ የልጅ ልጅ ሸይኽ *አብዱረህማን ኢብኑ ሀሰን* እንዲህ ይላል፦ ]} لا بد فى شهادة أن لا إله إلا الله من سبعة شروط ، لا تنفع قائلها إلا باجتماعها ، أحدها : _العلم المنافي للجهل . الثانى : اليقين المنافي للشك . الثالث : القبول المنافي للرد . الرابع : الانقياد المنافي للترك . الخامس : الإخلاص المنافي للشرك. السادس: الصدق المنافي للكذب . السابع : المحبة المنافي لضدها_ . ላ ኢላሀ ኢለሏህ ሰባት ሸርጥ(መስፈርት) እንዳላት ጥርጥር የለውም፤ ላ ኢላሀ ኢለሏህ የሚልም ሰው እኒህን ሸርጦች በመሰበሰብ ቢሆን እንጂ አይጠቅመውም፦ 1ኛ ጅህልናን ያስወገደ እውቀት፣  2ኛ ጥርጣሬን ያስወገደ እርግጠኝነት፣ 3ኛ እምቢተኝነትን ያስወገደ ተቀባይነት፣  4ኛ መተውን ያስወገደ ታዛዥነት፣  5ኛ ሽርክን ያስወገደ ኢኽላስ፣  6ኛ ውሸትን ያስወገድ እውነተኝነት፣ 7ኛ የቃሏን ተቃራኒ ያስወገደ የሆነ ውዴታ!  _ﺍﻟﻠﻪ ﻳﻮﻓﻘﻨﺎ ﺟﻤﻴﻌﺎً ﻟﺘﺤﻘﻴﻖ ﻛﻠﻤﺔ ﺍﻟﺘﻮﺣﻴﺪ ‏« ﻻ ﺇﻟﻪ ﺇﻻ ﺍﻟﻠﻪ ‏» ﻗﻮﻻً ﻭﻋﻤﻼً ﻭﺍﻋﺘﻘﺎﺩﺍً ، ﻭﻫﻮ ﺍﻟﻤﻮﻓﻖ ﻭﺣﺪﻩ ﻭﺍﻟﻬﺎﺩﻱ ﺇﻟﻰ ﺳﻮﺍﺀ ﺍﻟﺴﺒﻴﻞ· ﻭﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻭﺳﻠﻢ ﻭﺑﺎﺭﻙ ﻭﺃﻧﻌﻢ ﻋﻠﻰ ﻋﺒﺪ_ _ﺍﻟﻠﻪ ﻭﺭﺳﻮﻟﻪ ﻧﺒﻴﻨﺎ ﻣﺤﻤﺪ ﻭﻋﻠﻰ ﺁﻟﻪ ﻭﺻﺤﺒﻪ ﺃﺟﻤﻌﻴﻦ· https://t.me/AbulQmane

 💥 አላህም በዚህ ጉደይ ላይ የሚከተለውን ይላል፦  ﺃَﻟَﺎ ﻟِﻠَّﻪِ ﺍﻟﺪِّﻳﻦُ ﺍﻟْﺨَﺎﻟِﺺُ ‏[ﺍﻟﺰﻣﺮ 3] ﻣُﺨْﻠِﺼِﻴﻦَ ﻟَﻪُ ﺍﻟﺪِّﻳﻦَ [ﺍﻟﺒﻴﻨﺔ 5]  《አላህን ሃይማኖትን ለእርሱ ብቻ አጥሪዎች፣ ቀጥተኞች ኾነው ሊግገዙት፣(አንጂ አልታዘዙም)》  (📚አል በይነህ)  📜 በሀዲስ በመጣ ዘገባ ላይ ደግሞ፦ ﻋﻦ ﺃﺑﻲ ﻫﺮﻳﺮﺓ ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻪ ﻋﻦ ﺍﻟﻨﺒﻲ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ : ))ﺃَﺳْﻌَﺪُ ﺍﻟﻨَّﺎﺱِ ﺑِﺸَﻔَﺎﻋَﺘِﻲ ﻳَﻮْﻡَ ﺍﻟﻘِﻴَﺎﻣَﺔِ، ﻣَﻦْ ﻗَﺎﻝَ ﻻَ ﺇِﻟَﻪَ ﺇِﻟَّﺎ ﺍﻟﻠَّﻪُ، ﺧَﺎﻟِﺼًﺎ ﻣِﻦْ ﻗَﻠْﺒِﻪ 🎤 አቡ ሁረይራ(ረ·ዐ) ከረሱል ﷺ ይዞ እንደዘገበልን፦ ረሱል እንዲህ አሉ፤ «በትንሳኤ ቀን በእኔ ሸፍዐ(ማማለድ) እድለኛው ከልቡ ጥርት አድርጎ ላ ኢላሀ ኢለሏህ ያለ ነው።ِ» *******                        ▪️👉 4ኛ ﺍﻟﺼﺪﻕ ﺍﻟﻤﻨﺎﻓﻲ ﻟﻠﻜﺬﺏ ؛ ﻭﺫﻟﻚ ﺑﺄﻥ ﻳﻘﻮﻝ ﻫﺬﻩ ﺍﻟﻜﻠﻤﺔ ﺻﺎﺩﻗﺎً ﻣﻦ ﻗﻠﺒﻪ ﻳﻮﺍﻃﺊ ﻗﻠﺒﻪ ﻟﺴﺎﻧﻪ ☂ አራተኛው መስፈርት ውሸትን ያስወገደ እውነተኝነት ሲሆን ይህም ማለት ይቺን ንግግር ሲናገር ልቡ እውነተኛ ሁኖ እንደውም ልቡ ከምላሱ ጋር የተመሳሰለሽ ወይም የገጠመች ሁኖ ማለት ነው። 💥 አላህም ሙናፊቆችን ሲወቅስ የሚከተለውን ይላል፦ ﺇِﺫَﺍ ﺟَﺎﺀَﻙَ ﺍﻟْﻤُﻨَﺎﻓِﻘُﻮﻥَ ﻗَﺎﻟُﻮﺍ ﻧَﺸْﻬَﺪُ ﺇِﻧَّﻚَ ﻟَﺮَﺳُﻮﻝُ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻭَﺍﻟﻠَّﻪُ ﻳَﻌْﻠَﻢُ ﺇِﻧَّﻚَ ﻟَﺮَﺳُﻮﻟُﻪُ ﻭَﺍﻟﻠَّﻪُ ﻳَﺸْﻬَﺪُ ﺇِﻥَّ ﺍﻟْﻤُﻨَﺎﻓِﻘِﻴﻦَ ﻟَﻜَﺎﺫِﺑُﻮﻥَ ‏[ﺍﻟﻤﻨﺎﻓﻘﻮﻥ 1] 《መናፍቃን በመጡህ ጊዜ «አንተ የአላህ መልክተኛ መኾንህን በእርግጥ (ምለን) እንመሰክራለን» ይላሉ፡፡ አላህም አንተ በእርግጥ መልክተኛው መኾንህን ያውቃል፡፡ አላህም መናፍቃን (ከልብ እንመሰክራለን በማለታቸው) ውሸታሞች መኾናቸውን ይመሰክራል፡፡》  (📚አል ሙናፊቁን) ﺍﻟﻢ★ﺃَﺣَﺴِﺐَ ﺍﻟﻨَّﺎﺱُ ﺃَﻥْ ﻳُﺘْﺮَﻛُﻮﺍ ﺃَﻥْ ﻳَﻘُﻮﻟُﻮﺍ ﺁﻣَﻨَّﺎ ﻭَﻫُﻢْ ﻟَﺎ ﻳُﻔْﺘَﻨُﻮﻥَ★ﻭَﻟَﻘَﺪْ ﻓَﺘَﻨَّﺎ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﻣِﻦْ ﻗَﺒْﻠِﻬِﻢْ ﻓَﻠَﻴَﻌْﻠَﻤَﻦَّ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺻَﺪَﻗُﻮﺍ ﻭَﻟَﻴَﻌْﻠَﻤَﻦَّ ﺍﻟْﻜَﺎﺫِﺑِﻴﻦَ ‏[ﺍﻟﻌﻨﻜﺒﻮﺕ 3-1: ‏] 《አ.ለ.መ (አሊፍ ላም ሚም)★ሰዎቹ አምነናል በማለታቸው ብቻ እነሱ ሳይፈተኑ የሚተው መኾናቸውን ጠረጠሩን★ እነዚያንም ከእነሱ በፊት የነበሩትን በእርግጥ ፈትነናል፡፡ እነዚያንም እውነት የተናገሩትን አላህ በእርግጥ ያውቃል፡፡ ውሸታሞቹንም ያውቃል፡፡》  (📚አል አንከቡት) ★ ከላይኛው አንቀፅ ውሸት ያልተወገደበት የምስክርነት ቃል ሙናፊቅነትን(አስመሳይነትን) እንጂ ሌላን እንደማይገልፅ ግልፅ ነው።  በተጨማሪም በሀዲስ ዘገባ የተጠቀሰው የሚከተለውን ይመስላል፦  ﻋﻦ ﻣﻌﺎﺫ ﺑﻦ ﺟﺒﻞ ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻪ ﻋﻦ ﺍﻟﻨﺒﻲ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ ﻣَﺎ ﻣِﻦْ ﺃَﺣَﺪٍ ﻳَﺸْﻬَﺪُ ﺃَﻥْ ﻻَ ﺇِﻟَﻪَ ﺇِﻟَّﺎ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﻭَﺃَﻥَّ ﻣُﺤَﻤَّﺪًﺍ ﺭَﺳُﻮﻝُ ﺍﻟﻠَّﻪِ، ﺻِﺪْﻗًﺎ ﻣِﻦْ ﻗَﻠْﺒِﻪِ، ﺇِﻟَّﺎ ﺣَﺮَّﻣَﻪُ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﻋَﻠَﻰ ﺍﻟﻨَّﺎﺭ 🎤 ሙዐዝ ኢብኑ ጀበል(ረ·ዐ) ከረሱል ﷺ ይዞ እንደዘገበልን ረሱል እንዲህ አሉ፦ «ከመካከላችሁ "ከልቡ እውነተኛ ሁኖ" ላ ኢላሀ ኢለላህ ሙሀመድ ረሱሉላህ ብሎ አንዳችሁም አይመሰክርም አላህ ከእሳት እርም(ሀራም) ያደረገው ቢሆን እንጂ!!» *****  ▪️👉 5ኛ ﺍﻟﻤﺤﺒﺔ ﺍﻟﻤﻨﺎﻓﻴﺔ ﻟﻠﺒﻐﺾ ﻭﺍﻟﻜﺮﻩ ؛ ﻭﺫﻟﻚ ﺑﺄﻥ ﻳﺤﺐ ﻗﺎﺋﻠﻬﺎ ﺍﻟﻠﻪ ﻭﺭﺳﻮﻟﻪ ﻭﺩﻳﻦ ﺍﻹﺳﻼﻡ ﻭﺍﻟﻤﺴﻠﻤﻴﻦ ﺍﻟﻘﺎﺋﻤﻴﻦ ﺑﺄﻭﺍﻣﺮ ﺍﻟﻠﻪ ﺍﻟﻮﺍﻗﻔﻴﻦ ﻋﻨﺪ ﺣﺪﻭﺩﻩ ، ﻭﺃﻥ ﻳﺒﻐﺾ ﻣﻦ ﺧﺎﻟﻒ ‏« ﻻ ﺇﻟﻪ ﺇﻻ ﺍﻟﻠﻪ ‏» ﻭﺃﺗﻰ ﺑﻤﺎ ﻳﻨﺎﻗﻀﻬﺎ ﻣﻦ ﺷﺮﻙ ﺃﻭ ﻛﻔﺮ ﺃﻭ ﻳﻨﺎﻗﺾ ﻛﻤﺎﻟﻬﺎ ﻣﻦ ﺑﺪﻉ ﻭﻣﻌﺎﺻﻲ ☂ አምስተኛው መስፈርት ደግሞ ጥላቻን ያስወገደ ውዴታ ሲሆን ይህም ማለት በላ ኢላሀ ኢለሏህ የሚናገረው ሰው አላህን፣ መልእክተኛውን፣ እስልምናንና በአላህ ትእዛዝ ላይ ያሉትንና ድንበሩን የማያልፉትን መውደድ እንዲሁም ላ ኢላሀ ኢለላህን በሚንድ በሆነ ሽርክና ኩፍር ወይም ቢድዐና አመፅ ላይ ያለን ተቃራኒ አካል መጥላት ማለት ነው!! 💥 አላህም በዚህ ዙሪያ እንዲህ ይላል፦ ﻭَﻣِﻦَ ﺍﻟﻨَّﺎﺱِ ﻣَﻦْ ﻳَﺘَّﺨِﺬُ ﻣِﻦْ ﺩُﻭﻥِ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺃَﻧْﺪَﺍﺩًﺍ ﻳُﺤِﺒُّﻮﻧَﻬُﻢْ ﻛَﺤُﺐِّ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻭَﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺁﻣَﻨُﻮﺍ ﺃَﺷَﺪُّ ﺣُﺒًّﺎ ﻟِﻠَّﻪِ ‏[ﺍﻟﺒﻘﺮﺓ 165]  《ከሰዎችም ከአላህ ሌላ ባለንጣዎችን (ጣዖታትን) አላህን እንደሚወዱ የሚወዷቸው ኾነው የሚይዙ አሉ፡፡ እነዚያ ያመኑትም አላህን በመውደድ (ከነርሱ) ይበልጥ የበረቱ ናቸው፡፡》 (📚አል በቀራህ) 📜 በሀዲስ በመጣ ዘገባ ደግሞ፦  ﻋﻦ ﺃﻧﺲ ﺑﻦ ﻣﺎﻟﻚ ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻪ ﻗﺎﻝ : ﻗﺎﻝ ﺭﺳﻮﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ ﺛَﻠَﺎﺙٌ ﻣَﻦْ ﻛُﻦَّ ﻓِﻴﻪِ ﻭَﺟَﺪَ ﺣَﻠَﺎﻭَﺓَ ﺍﻟْﺈِﻳﻤَﺎﻥِ : ﺃَﻥْ ﻳَﻜُﻮﻥَ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﻭَﺭَﺳُﻮﻟُﻪُ ﺃَﺣَﺐَّ ﺇِﻟَﻴْﻪِ ﻣِﻤَّﺎ ﺳِﻮَﺍﻫُﻤَﺎ ، ﻭَﺃَﻥْ ﻳُﺤِﺐَّ ﺍﻟْﻤَﺮْﺀَ ﻟَﺎ ﻳُﺤِﺒُّﻪُ ﺇِﻟَّﺎ ﻟِﻠَّﻪِ ، ﻭَﺃَﻥْ ﻳَﻜْﺮَﻩَ ﺃَﻥْ ﻳَﻌُﻮﺩَ ﻓِﻲ ﺍﻟْﻜُﻔْﺮِ ﻛَﻤَﺎ ﻳَﻜْﺮَﻩُ ﺃَﻥْ ﻳُﻘْﺬَﻑَ ﻓِﻲ ﺍﻟﻨَّﺎﺭ· 🎤 አነስ ኢብኑ ማለኪ(ረ·ዐ) ከረሱል ﷺ ይዞ እንደዘገበልን ረሱል እንዲህ አሉ፦ «ሶስት ነገሮች በውስጡ ያሉት ሰው የኢማንን ጥፍጥና አግኝቷል፤ ከሌሎቹ ነገሮች የበለጠ አላህና መልእክተኛው እርሱ ዘንድ ተወዳጅ ሲሆኑ፣ አንድን ሰው ሲወድ ለአላህ ብሎ እንጂ ለሌላ ሳይወደው ሲቀር ፣እሳት ውስጥ መወርወርን እንደሚጠላው ሁሉ ወደ ኩፍር መመለስን የሚጠላ ሲሆን!!» 🎤 በተጨማሪም፦  يقول ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ : ﺃﻭﺛﻖ ﻋﺮﻯ ﺍﻹﻳﻤﺎﻥ ﺍﻟﺤﺐ ﻓﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻭﺍﻟﺒﻐﺾ ﻓﻲ ﺍﻟﻠﻪ  «የእምነት አስተማማኙ ገመድ ለአላህ ብሎ መውደድ ለአላህ ብሎ መጥላት ነው።» (ረሱል ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ****** ▪️👉 6ኛ ﺍﻻﻧﻘﻴﺎﺩ ﺍﻟﻤﻨﺎﻓﻲ ﻟﻠﺘﺮﻙ ؛ ﻓﻼﺑﺪ ﻟﻘﺎﺋﻞ ‏« ﻻ ﺇﻟﻪ ﺇﻻ ﺍﻟﻠﻪ ‏» ﺃﻥ ﻳﻨﻘﺎﺩ ﻟﺸﺮﻉ ﺍﻟﻠﻪ ﻭﻳﺬﻋﻦ ﻟﺤﻜﻤﻪ ﻭﻳﺴﻠﻢ ﻭﺟﻬﻪ ﻟﻠﻪ ☂ ለአላህ ትእዛዝ መተውን በማስወገድ መጎተት(መታዘዝ) ስድስተኛው ሸርጥ ነው። በርግጥም አንድ በላ ኢላሀ ኢለላህ የሚናገር ሰው ለአላህ ሸሪዐ ሊታዘዝ፣ ለፍርዱ ሊተናነስና ለአላህም እጅ ሊሰጥ ግዴታ በመሆኑ ላይ ጥርጥር የለውም!! 💥 አላህም አንዲህ ይላል፦  ﻭَﺃَﻧِﻴﺒُﻮﺍ ﺇِﻟَﻰ ﺭَﺑِّﻜُﻢْ ﻭَﺃَﺳْﻠِﻤُﻮﺍ ﻟَﻪُ ‏[ﺍﻟﺰﻣﺮ 54] 《ወደ ጌታችሁ (በመጸጸት) ተመለሱ፡፡ ለእርሱም ታዘዙ፡፡》 (📚አል ዙመር) وَمَنْ أَحْسَنُ دِينًا مِمَّنْ أَسْلَمَ وَجْهَهُ لِلَّهِ وَهُوَ مُحْسِنٌ وَاتَّبَعَ مِلَّةَ إِبْرَاهِيمَ حَنِيفًا ۗ وَاتَّخَذَ اللَّهُ إِبْرَاهِيمَ خَلِيلًا ‏[ﺍﻟﻨﺴﺎﺀ 125]

🔺የ "ላ ኢላሀ ኢለሏህ መስፈርቶች" ~~~ የ "ላ ኢላሀ ኢለሏህ መስፈርቶች" ከቁርዓንና ከሀዲስ بسم الله الرحمان الرحيم  አላህ ለኛ ከዋለልን ፀጋዎች ውስጥ ዋናውና አንዱ መልእክተኛን ልኮልን የተውሂድንና የዚችን የ" *ላ ኢላሀ ኢለሏህ* " ጉደይ እንዲብራራልንና እንድንገነዘበው ማድረጉ ተጠቃሽ ነው።    ሁሉም መልእክተኞች ወደ ህዝቦቻቸው ሲመጡ ይችን የተውሂድ ንግግር የሆነችውን *ላ ኢላሀ ኢለሏህ* ለማስጨበጥ ነው። አላህም ስለነርሱ የሚከተለውን ይላል፦  【ﻭَﻣَﺎ ﺃَﺭْﺳَﻠْﻨَﺎ ﻣِﻦْ ﻗَﺒْﻠِﻚَ ﻣِﻦْ ﺭَﺳُﻮﻝٍ ﺇِﻻ ﻧُﻮﺣِﻲ ﺇِﻟَﻴْﻪِ ﺃَﻧَّﻪُ ﻻ ﺇِﻟَﻪَ ﺇِﻻ ﺃَﻧَﺎ ﻓَﺎﻋْﺒُﺪُﻭﻥِ 】《ከአንተ በፊትም እነሆ ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና ተገዙኝ በማለት ወደርሱ የምናወርድለት ቢኾን እንጅ ከመልክተኛ አንድንም አላክንም።》📚አል አንቢያእ) በሌላ አንቀፅ ላይ ሁሉም መልእክተኞች ለህዝቦቻቸው የሚከተለው ንግግር እንዳሉም አላህ ሲነግረን እንዲህ ይላል፦ ﺍﻋْﺒُﺪُﻭﺍ ﺍﻟﻠَّﻪَ ﻣَﺎ ﻟَﻜُﻢْ ﻣِﻦْ ﺇِﻟَﻪٍ ﻏَﻴْﺮُﻩُ  ወገኖቼ ሆይ! አላህን ተገዙ፡፡ ከእርሱ ሌላ ምንም አምላክ የላችሁም፡፡  ★ እንግዲህ ይቺ "ላ ኢላሀ ኢለሏህ"የመልእክተኞች ሁሉ አላማ ከሆነች ልንከተላትና ልንማራት ግድ ይላል!! ማንኛውም የዲነል ኢስላምን መንገድ የፈለገ በሙሉ በቁርዓንና በሀዲስ የተጠቀሱትን የዚችን ንግግር መስፈርቶች በሙሉ ሊያሟላ ግድ ለመሆኑ ጥርጥር የሌለበት ነጥብ ነው!! *******                    ለዚህም ነው አንድ ሰው ወደ እስልምና መግባት ከፈለገ ይቺን ወደ እስልምና መግቢያ የሆነችውን ቃል ከነ መስፈርቶቿ ሊላት ግድ ነው የምንለው። *ከዚህ በመቀጠል የ ላኢላሀ ኢለላህን ሸርጦች(መስፈርት) ከቁርአንና ከሀዲስ በአጭሩ የምንገልፀው ይሆናል።   ላ ኢላሀ ኢለሏህ ሰባት*(7) ሸርጦች አሏት ▪ 1ኛ= ﺍﻟﻌﻠﻢ ﺑﻤﻌﻨﺎﻫﺎ ﺍﻟﻤﺮﺍﺩ ﻣﻨﻬﺎ ﻧﻔﻴﺎً ﻭﺇﺛﺒﺎﺗﺎً ؛ ﻭﺫﻟﻚ ﺑﺄﻥ ﺗﻨﻔﻲ ﺟﻤﻴﻊ ﺃﻧﻮﺍﻉ ﺍﻟﻌﺒﺎﺩﺓ ﻋﻦ ﻛﻞ ﻣﻦ ﺳﻮﻯ ﺍﻟﻠﻪ ﻭﺗﺜﺒﺖ ﺫﻟﻚ ﻟﻠﻪ ﻭﺣﺪﻩ የመጀመሪያ የላ ኢላሀ ኢለሏህ መስፈርት ትርጉሞቿን ማወቅ ሲሆን ይህም ማለት ከአላህ ውጭ ያሉ አምልኮቶችን በሙሉ ውድቅ በማድረግ አምልኮትን ለአላህ ብቻ ማፅደቅን የሚመለከት ይሆናል።     👉 በዚህም ዙሪያ ላይ የመጡ መረጃዎች ብዙ ናቸው፦ሁል ጊዜ በምናነባት በሱረቱል ፋቲሀህ ላይ ጌታችን አላህ እንዲህ ይላል፦  【ﺇِﻳَّﺎﻙَ ﻧَﻌْﺒُﺪُ ﻭَﺇِﻳَّﺎﻙَ ﻧَﺴْﺘَﻌِﻴﻦ】ُ ‏[📚ﺍﻟﻔﺎﺗﺤﺔ] 《አንተን ብቻ እንግገዛለን፤ አንተንም ብቻ እገዛ እንጠይቃለን።》 (📚አል ፋቲሀህ) ﻓَﺎﻋْﻠَﻢْ ﺃَﻧَّﻪُ ﻟَﺎ ﺇِﻟَﻪَ ﺇِﻟَّﺎ ﺍﻟﻠَّﻪُ ‏[📚ﻣﺤﻤﺪ 19:‏]  《እነሆ ከአላህ ሌላ በእውነት የሚመለክ አምላክ አለመኖሩንም ዕወቅ፡፡》 (📚ሱረቱል ሙሀመድ) ﺇِﻟَّﺎ ﻣَﻦْ ﺷَﻬِﺪَ ﺑِﺎﻟْﺤَﻖِّ ﻭَﻫُﻢْ ﻳَﻌْﻠَﻤُﻮﻥَ ‏[📚ﺍﻟﺰﺧﺮﻑ 86:‏]  《የሚያውቁ ኾነው በእውነት ከመሰከሩት በስተቀር…》 (📚አል ዙኽሩፍ)  👆ይቺን አንቀፅ የተፍሲር ሙሁራን ሲያብራሩ እንዲህ ይላሉ፦  ﺃﻱ ﺇﻻ ﻣﻦ ﺷﻬﺪ ﺑـ ‏« ﻻ ﺇﻟﻪ ﺇﻻ ﺍﻟﻠﻪ ‏» ﻭَﻫُﻢْ ﻳَﻌْﻠَﻤُﻮﻥَ ﺃﻱ ﻣﺎ ﺷﻬﺪﻭﺍ ﺑﻪ ﻓﻲ ﻗﻠﻮﺑﻬﻢ ﻭﺃﻟﺴﻨﺘﻬﻢ . «በ ላኢላሀ ኢለላህ እያወቀ ማለትም በልቡና በምላሱ የመሰከረው እያወቅ ሲቀር ለማለት ነው ይላሉ!!» ★ እንግዲህ የ ላኢላሀ ኢለሏህ ባለቤቶች አምልኮትን ለአላህ ብቻ የሰጡ መሆንና በ ላኢላሀ ኢለላህ ላይ ሙሉ እውቀት እንደሚያስፈልግም ከላይ ያሉት ሶስት አንቀፆች ያስገነዝቡናል።በሀዲስ በመጣ ዘገባ ላይ ደግሞ፦  ﻭﻋﻦ ﻋﺜﻤﺎﻥ ﺑﻦ ﻋﻔﺎﻥ ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻪ ﻗﺎﻝ : ﻗﺎﻝ ﺭﺳﻮﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ ﻗﺎﻝ : ﻣَﻦْ ﻣَﺎﺕَ ﻭَﻫُﻮَ ﻳَﻌْﻠَﻢُ ﺃَﻧَّﻪُ ﻟَﺎ ﺇِﻟَﻪَ ﺇِﻟَّﺎ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﺩَﺧَﻞَ ﺍﻟْﺠَﻨَّﺔ ዑስማን ኢብኑ አፋን(ረ·ዐ) ከረሱል ﷺ ይዞ እንደዘገበልን፦ «ከአላህ ውጭ በእውነት የሚመለክ አምላክ አለመኖሩን እያወቀ የሞተ ሰው በርግጥ ጀነት ገባ!!» እንግዲህ በመጀመሪያው መስፈርት ዙሪያ ላይ ካሉት መረጃዎች መካከል የቁርዐንና የሀዲስን ቃኝተናል፣ በመሆኑም ማንኛውም የ ላ ኢላሀ ኢለላህ ተናጋሪ ይህን የመጀመሪያ መስፈርት ቃሏን ከማለቱ በፊት ማስገኘት ግዴታ ይሆንበታል። ******                         ▪️👉 2ኛ   ﺍﻟﻴﻘﻴﻦ ﺍﻟﻤﻨﺎﻓﻲ ﻟﻠﺸﻚ ﻭﺍﻟﺮﻳﺐ ؛ ﻭﻣﻌﻨﺎﻩ ﺃﻥ ﻳﻜﻮﻥ ﻣﻮﻗﻨﺎً ﺑﻬﺬﻩ ﺍﻟﻜﻠﻤﺔ ﻳﻘﻴﻨﺎً ﺟﺎﺯﻣﺎً ﻻ ﺷﻚ ﻓﻴﻪ ﻭﻻ ﺭﻳﺐ  የ ላ ኢላሀ ኢለላህ ሁለተኛ መስፈርት ሁኖ የምናገኘው ከጥርጣሬ የራቀን ፍፁም እርግጠኛነትን ይሆናል። ይህም ማለት በዚች ቃል መስካሪ የሆነው ሰው በቃሏ ላይ ሙሉ የሆነ እርግጠኛነት፣ ቆራጥነት እንዲሁም ከጥርጣሬ የራቀ እምነት ሊኖረው ማለት ነው። 💥 አላህ አማኞችን ሲሰይም እንደከሚከተለው ይላል፦  ﺇِﻧَّﻤَﺎ ﺍﻟْﻤُﺆْﻣِﻨُﻮﻥَ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺁﻣَﻨُﻮﺍ ﺑِﺎﻟﻠَّﻪِ ﻭَﺭَﺳُﻮﻟِﻪِ ﺛُﻢَّ ﻟَﻢْ ﻳَﺮْﺗَﺎﺑُﻮﺍ ﻭَﺟَﺎﻫَﺪُﻭﺍ ﺑِﺄَﻣْﻮَﺍﻟِﻬِﻢْ ﻭَﺃَﻧْﻔُﺴِﻬِﻢْ ﻓِﻲ ﺳَﺒِﻴﻞِ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺃُﻭﻟَﺌِﻚَ ﻫُﻢُ ﺍﻟﺼَّﺎﺩِﻗُﻮﻥَ { ‏[ ﺍﻟﺤﺠﺮﺍﺕ 15 ‏]  《እውነተኛዎቹ) ምእምናን እነዚያ በአላህና በመልእከተኛው ያመኑት ከዚያም ያልተጠራጠሩት በገንዘቦቻቸውና በነፍሶ ቻቸውም በአላህ መንገድ የታገሉት ብቻ ናቸው፡፡ እነዚያ እነሱ እውነተኞቹ ናቸው፡፡》📚አል ሁጁራት) ﻭﻣﻌﻨﻰ ﻟَﻢْ ﻳَﺮْﺗَﺎﺑُﻮﺍ ﺃﻱ ﺃﻳﻘﻨﻮﺍ ﻭﻟﻢ ﻳﺸﻜُّﻮﺍ . 《በአንቀፁ ውስጥ ያልተጠራጠሩ በማለት የተገለፀው እርግጠኛ የሆኑ ለማለት ነው!!》 📜 በሀዲስ ከመጣ ዘገባ ደግሞ፦ ﻋﻦ ﺃﺑﻲ ﻫﺮﻳﺮﺓ ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻪ ﻗﺎﻝ : ﻗﺎﻝ ﺭﺳﻮﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ : ﺃَﺷْﻬَﺪُ ﺃَﻥْ ﻟَﺎ ﺇِﻟَﻪَ ﺇِﻟَّﺎ ﺍﻟﻠﻪُ، ﻭَﺃَﻧِّﻲ ﺭَﺳُﻮﻝُ ﺍﻟﻠﻪِ، ﻟَﺎ ﻳَﻠْﻘَﻰ ﺍﻟﻠﻪَ ﺑِﻬِﻤَﺎ ﻋَﺒْﺪٌ ﻏَﻴْﺮَ ﺷَﺎﻙٍّ ﻓِﻴﻬِﻤَﺎ ﺇِﻟَّﺎ ﺩَﺧَﻞَ ﺍﻟْﺠَﻨَّﺔَ  🎤 አቡ ሁረይራ(ረ·ዐ) ከረሱል ﷺ ይዞ እንደዘገበልን፦ ረሱል እንዲህ አሉ «ከአላህ ሌላ በእውነት የሚመለክ አምላክ እንደሌለና እኔም የአላህ መልእክተኛ መሆኔን እመሰክራለሁ፣ በነዚህ ሁለት የምስክርነት ቃሎች አንድ ባሪያ ጌታውን ከጥርጣሬ ውጭ ሁኖ አይገናኘውም ጀነት የገባ ቢሆን እንጂ!!»  *****                   ▪️👉 3ኛ= ﺍﻹﺧﻼﺹ ﺍﻟﻤﻨﺎﻓﻲ ﻟﻠﺸﺮﻙ ሶስተኛው ሸርጥ ደግሞ ከሽርክ በራቀ መልኩ ኢኽላስን የተላበሰ መሆን ነው። ኢኽላስ ስንል አላህን ከርሱ ውጭ ካሉ አምልኮቶች ሁሉ አርቆ በብቸኝነት ማምለክ ማለት ነው።

أذكار الصباح | أحمد النفيس

أذكار الصباح | أحمد النفيس

qsyd_mw_thr_twqz_lqlwb_y_yh_lnsn_mhl_ntbh_gmcsk7f7mas_71d8cff7.mp35.71 MB

قصيدة_مؤثرة_عن_القبر_و_الموت_لقد_فنوا_و_ما_بقى_منهم_خبر_48k.mp32.49 MB

y_yh_lnsn_mhl_ntbh_aabdlkrym_mhywb_lqd_fnw_wm_bq_mnhm_hd_ya_ayo.mp35.52 MB

وَوَصَّيْنَا الْإِنسَانَ.mp314.80 MB

የአሹራ ፆም ቱሩፋቶች.mp32.53 MB

📚 كتاب صوتي: العلم النافع.mp320.14 MB

ከተፃፉ ቆየት ቢሉም ይነበብ

“በመጨረሻይቱም (አለም) እነርሱ የሚያረጋግጡ ከሆኑት (መሪ ነው)። (አል' በቀራህ፡ 4) በዚህ የቁርኣን አንቀጽ የተፈለገው ሲቀጠሩት የነበረው ነገር እንደመጣቸው እርሱም የቂን (ሞት) እንደሆነ ይገልጻል፡፡)) ይህ አንቀጽ ፣ ዓቅለኛ ሆኖ ለአካለ መጠን ከደረሰበት ጊዜ ጀምሮ _ እስኪሞት ድረስ ዒባዳ ዋጅብ እንደሆነ ፣ ሱፍያዎች እንደሚሉት ከሞት በፊት ግዴታ የሚቆምበት “ሀል” የሚባል እንደሌለ ይጠቁማል፡፡ ይህ ፣ ድሮም ይሁን አሁን የሱፍያ ዲን ነው፡፡ ዒባዳን አስመልክቶ የሱፍያ አቋም ይህ ነው፡፡ ከሱፍያዎች ኪታብ የነቀልነው ጥቂቱን ብቻ ነው… እኔ በጥናቴ ላይ ትኩረት ያደረኩት የዒባዳውን እና በዒባዳ ላይ ያላቸውን አቋም ብቻ ነው፡፡ ሌሎችም ልክበተውሂድ ፣ በሩሡሎች መልእክተኛነት ፣ በሸሪዓው እና በቀደር ዙሪያ አቋም እንዳላቸው ሁሉ ባልተጠቀሱ የቀሩ ጉዳዮችም የተለዩ አቋሞች ያሏቸው ሲሆን ይህን ለማብራራት ተከታታይና  በጣም ሰፋ ያሉ ማብራሪያዎች ይሻል በዚህ እርስ ግን ለቅምሻ ያክል የስኳሁኑ ይበቃናል ሀቅን በሀቅነቱ እንዲያሳየን እና መከተልንም እንዲለግሰን ፤ ባጢልንም በባጢልነት እንዲያሳየን እና መራቅን እንዲቸረን ፤ ከመራን በኋላ ልቦቻችንንም እንዳያጠምብን አላህን እለምነዋለሁ፡፡ #ክፍል1 https://t.me/AbulQmane/2148 ክፍል2 https://t.me/AbulQmane/2149 ክፍል3 https://t.me/AbulQmane/2150 ክፍል4 https://t.me/AbulQmane/2172 ክፍል5 https://t.me/AbulQmane/2176 ክፍል6 https://t.me/AbulQmane/2219