es
Feedback
ፋአድ 𝐅𝐔𝐀𝐃 𝙰𝚋𝚞 𝚕𝚀𝚖𝚊𝚗𝚎

ፋአድ 𝐅𝐔𝐀𝐃 𝙰𝚋𝚞 𝚕𝚀𝚖𝚊𝚗𝚎

Ir al canal en Telegram
1 552
Suscriptores
-124 horas
Sin datos7 días
-1230 días
Archivo de publicaciones
ﺃَﺳْﻠَﻢَ) ﻓﻲ ﺍﻵﻳﺘﻴﻦ ﺃﻱ : ﺍﻧﻘﺎﺩ《እርሱ መልካም ሠሪ ኾኖ ፊቱን ለአላህ ከሰጠና የኢብራሂምንም መንገድ ቀጥተኛ ሲኾን ከተከተለ ሰው ይበልጥ ሃይማኖቱ ያማረ ማን ነው አላህም ኢብራሂምን ፍጹም ወዳጅ አድርጐ ያዘው፡፡》  (📚አል ኒሳእ) ﻭﻣﻌﻨﻰ (ﺃَﺳْﻠِﻤُﻮﺍ) ﻭ ( ﻭﺃﺫﻋﻦ . 👆 ከላይ ባሉት አንቀፆች ላይ እጅ ስጡ እና ፊቱን ወደ አላህ ያዞረ በመባል የተጠቀሱት ለአላህ ታዘዙ ዝቅ በሉ ለማለት ነው!! ******                   ▪️👉 7ኛ ﺍﻟﻘﺒﻮﻝ ﺍﻟﻤﻨﺎﻓﻲ ﻟﻠﺮﺩ ؛ ﻓﻼﺑﺪ ﻣﻦ ﻗﺒﻮﻝ ﻫﺬﻩ ﺍﻟﻜﻠﻤﺔ ﻗﺒﻮﻻً ﺣﻘﺎً ﺑﺎﻟﻘﻠﺐ ﻭﺍﻟﻠﺴﺎﻥ ، ﻭﻗﺪ ﻗﺺَّ ﺍﻟﻠﻪ ﻓﻲ ﺍﻟﻘﺮﺁﻥ ﺍﻟﻜﺮﻳﻢ ﻋﻠﻴﻨﺎ ﺃﻧﺒﺎﺀ ﻣﻦ ﻗﺪ ﺳﺒﻖ ﻣﻤﻦ ﺃﻧﺠﺎﻫﻢ ﺍﻟﻠﻪ ﻟﻘﺒﻮﻟﻬﻢ ﻟـ ‏« ﻻ ﺇﻟﻪ ﺇﻻ ﺍﻟﻠﻪ ‏» ، ﻭﺍﻧﺘﻘﺎﻣﻪ ﻭﺇﻫﻼﻛﻪ ﻟﻤﻦ ﺭﺩﻫﺎ ﻭﻟﻢ ﻳﻘﺒﻠﻬﺎ·  ☂ ሰባተኛውና የመጨረሻው ሸርጥ ይቺን ንግግር እንቢተኝነትን በማስወገድ መቀበል ሲሆን አላህ በቁርአኑ ይቺን ላ ኢላሀ ኢለላህን ከልቡና በምላሱ በሙሉ ተቀባይነት የተቀበለን እንዳዳነና እንቢ ብለው ያፈነገጡትን ደግሞ እንዳጠፋ የበፊት ሰዎችን ታሪክ ነግሮናል!!  💥 አላህም እንዲህ ይላል፦  ﺛُﻢَّ ﻧُﻨَﺠِّﻲ ﺭُﺳُﻠَﻨَﺎ ﻭَﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺁﻣَﻨُﻮﺍ ﻛَﺬَﻟِﻚَ ﺣَﻘًّﺎ ﻋَﻠَﻴْﻨَﺎ ﻧُﻨْﺞِ ﺍﻟْﻤُﺆْﻣِﻨِﻴﻦَ ‏[ﻳﻮﻧﺲ 103‏] 《ከዚያም መልክተኞቻችንን እነዚያንም ያመኑትን እናድናለን፡፡ እንደዚሁም ምእምናንን (ከጭንቅ ሁሉ) እናድናለን፡፡ (ይህ) በእኛ ላይ ተረጋገጠ፡፡》 (📚ዩኑስ)  ﺇِﻧَّﻬُﻢْ ﻛَﺎﻧُﻮﺍ ﺇِﺫَﺍ ﻗِﻴﻞَ ﻟَﻬُﻢْ ﻟَﺎ ﺇِﻟَﻪَ ﺇِﻟَّﺎ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﻳَﺴْﺘَﻜْﺒِﺮُﻭﻥ★َ ‏ﻭَﻳَﻘُﻮﻟُﻮﻥَ ﺃَﺋِﻨَّﺎ ﻟَﺘَﺎﺭِﻛُﻮ ﺁﻟِﻬَﺘِﻨَﺎ ﻟِﺸَﺎﻋِﺮٍ ﻣَﺠْﻨُﻮﻥٍ‏ [ﺍﻟﺼﺎﻓﺎﺕ36-35]  《እነርሱ ከአላህ ሌላ አምላክ የለም በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ፡፡★እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን? ይሉም ነበር፡፡》 (📚አል ሷፋት)        ★ እንግዲህ አንተ ሀቅን ፈላጊ የሆንክ ባሪያ ሆይ የ "ላ ኢላሀ ኢለላህ" መስፈርቶች ከአጭር ማብራሪያ ጋር ይሄን ይመስላል። በስተመጨረሻም በዚህ ርእስ ዙሪያ ላይ የአንድን ዑለማ ንግግር እየጋበዝኳቹህ ይህን መስፈርት ያላሟል ከእስልምና ክልል በምኑም እንደሌለበት በማስታወስ ፅሁፌን እጨርሳለሁ!!  ✍ {[ውዱ የመሀመድ አብዱልወሀብ የልጅ ልጅ ሸይኽ *አብዱረህማን ኢብኑ ሀሰን* እንዲህ ይላል፦ ]} لا بد فى شهادة أن لا إله إلا الله من سبعة شروط ، لا تنفع قائلها إلا باجتماعها ، أحدها : _العلم المنافي للجهل . الثانى : اليقين المنافي للشك . الثالث : القبول المنافي للرد . الرابع : الانقياد المنافي للترك . الخامس : الإخلاص المنافي للشرك. السادس: الصدق المنافي للكذب . السابع : المحبة المنافي لضدها_ . ላ ኢላሀ ኢለሏህ ሰባት ሸርጥ(መስፈርት) እንዳላት ጥርጥር የለውም፤ ላ ኢላሀ ኢለሏህ የሚልም ሰው እኒህን ሸርጦች በመሰበሰብ ቢሆን እንጂ አይጠቅመውም፦ 1ኛ ጅህልናን ያስወገደ እውቀት፣  2ኛ ጥርጣሬን ያስወገደ እርግጠኝነት፣ 3ኛ እምቢተኝነትን ያስወገደ ተቀባይነት፣  4ኛ መተውን ያስወገደ ታዛዥነት፣  5ኛ ሽርክን ያስወገደ ኢኽላስ፣  6ኛ ውሸትን ያስወገድ እውነተኝነት፣ 7ኛ የቃሏን ተቃራኒ ያስወገደ የሆነ ውዴታ!  _ﺍﻟﻠﻪ ﻳﻮﻓﻘﻨﺎ ﺟﻤﻴﻌﺎً ﻟﺘﺤﻘﻴﻖ ﻛﻠﻤﺔ ﺍﻟﺘﻮﺣﻴﺪ ‏« ﻻ ﺇﻟﻪ ﺇﻻ ﺍﻟﻠﻪ ‏» ﻗﻮﻻً ﻭﻋﻤﻼً ﻭﺍﻋﺘﻘﺎﺩﺍً ، ﻭﻫﻮ ﺍﻟﻤﻮﻓﻖ ﻭﺣﺪﻩ ﻭﺍﻟﻬﺎﺩﻱ ﺇﻟﻰ ﺳﻮﺍﺀ ﺍﻟﺴﺒﻴﻞ· ﻭﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻭﺳﻠﻢ ﻭﺑﺎﺭﻙ ﻭﺃﻧﻌﻢ ﻋﻠﻰ ﻋﺒﺪ_ _ﺍﻟﻠﻪ ﻭﺭﺳﻮﻟﻪ ﻧﺒﻴﻨﺎ ﻣﺤﻤﺪ ﻭﻋﻠﻰ ﺁﻟﻪ ﻭﺻﺤﺒﻪ ﺃﺟﻤﻌﻴﻦ· https://t.me/AbulQmane

 💥 አላህም በዚህ ጉደይ ላይ የሚከተለውን ይላል፦  ﺃَﻟَﺎ ﻟِﻠَّﻪِ ﺍﻟﺪِّﻳﻦُ ﺍﻟْﺨَﺎﻟِﺺُ ‏[ﺍﻟﺰﻣﺮ 3] ﻣُﺨْﻠِﺼِﻴﻦَ ﻟَﻪُ ﺍﻟﺪِّﻳﻦَ [ﺍﻟﺒﻴﻨﺔ 5]  《አላህን ሃይማኖትን ለእርሱ ብቻ አጥሪዎች፣ ቀጥተኞች ኾነው ሊግገዙት፣(አንጂ አልታዘዙም)》  (📚አል በይነህ)  📜 በሀዲስ በመጣ ዘገባ ላይ ደግሞ፦ ﻋﻦ ﺃﺑﻲ ﻫﺮﻳﺮﺓ ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻪ ﻋﻦ ﺍﻟﻨﺒﻲ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ : ))ﺃَﺳْﻌَﺪُ ﺍﻟﻨَّﺎﺱِ ﺑِﺸَﻔَﺎﻋَﺘِﻲ ﻳَﻮْﻡَ ﺍﻟﻘِﻴَﺎﻣَﺔِ، ﻣَﻦْ ﻗَﺎﻝَ ﻻَ ﺇِﻟَﻪَ ﺇِﻟَّﺎ ﺍﻟﻠَّﻪُ، ﺧَﺎﻟِﺼًﺎ ﻣِﻦْ ﻗَﻠْﺒِﻪ 🎤 አቡ ሁረይራ(ረ·ዐ) ከረሱል ﷺ ይዞ እንደዘገበልን፦ ረሱል እንዲህ አሉ፤ «በትንሳኤ ቀን በእኔ ሸፍዐ(ማማለድ) እድለኛው ከልቡ ጥርት አድርጎ ላ ኢላሀ ኢለሏህ ያለ ነው።ِ» *******                        ▪️👉 4ኛ ﺍﻟﺼﺪﻕ ﺍﻟﻤﻨﺎﻓﻲ ﻟﻠﻜﺬﺏ ؛ ﻭﺫﻟﻚ ﺑﺄﻥ ﻳﻘﻮﻝ ﻫﺬﻩ ﺍﻟﻜﻠﻤﺔ ﺻﺎﺩﻗﺎً ﻣﻦ ﻗﻠﺒﻪ ﻳﻮﺍﻃﺊ ﻗﻠﺒﻪ ﻟﺴﺎﻧﻪ ☂ አራተኛው መስፈርት ውሸትን ያስወገደ እውነተኝነት ሲሆን ይህም ማለት ይቺን ንግግር ሲናገር ልቡ እውነተኛ ሁኖ እንደውም ልቡ ከምላሱ ጋር የተመሳሰለሽ ወይም የገጠመች ሁኖ ማለት ነው። 💥 አላህም ሙናፊቆችን ሲወቅስ የሚከተለውን ይላል፦ ﺇِﺫَﺍ ﺟَﺎﺀَﻙَ ﺍﻟْﻤُﻨَﺎﻓِﻘُﻮﻥَ ﻗَﺎﻟُﻮﺍ ﻧَﺸْﻬَﺪُ ﺇِﻧَّﻚَ ﻟَﺮَﺳُﻮﻝُ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻭَﺍﻟﻠَّﻪُ ﻳَﻌْﻠَﻢُ ﺇِﻧَّﻚَ ﻟَﺮَﺳُﻮﻟُﻪُ ﻭَﺍﻟﻠَّﻪُ ﻳَﺸْﻬَﺪُ ﺇِﻥَّ ﺍﻟْﻤُﻨَﺎﻓِﻘِﻴﻦَ ﻟَﻜَﺎﺫِﺑُﻮﻥَ ‏[ﺍﻟﻤﻨﺎﻓﻘﻮﻥ 1] 《መናፍቃን በመጡህ ጊዜ «አንተ የአላህ መልክተኛ መኾንህን በእርግጥ (ምለን) እንመሰክራለን» ይላሉ፡፡ አላህም አንተ በእርግጥ መልክተኛው መኾንህን ያውቃል፡፡ አላህም መናፍቃን (ከልብ እንመሰክራለን በማለታቸው) ውሸታሞች መኾናቸውን ይመሰክራል፡፡》  (📚አል ሙናፊቁን) ﺍﻟﻢ★ﺃَﺣَﺴِﺐَ ﺍﻟﻨَّﺎﺱُ ﺃَﻥْ ﻳُﺘْﺮَﻛُﻮﺍ ﺃَﻥْ ﻳَﻘُﻮﻟُﻮﺍ ﺁﻣَﻨَّﺎ ﻭَﻫُﻢْ ﻟَﺎ ﻳُﻔْﺘَﻨُﻮﻥَ★ﻭَﻟَﻘَﺪْ ﻓَﺘَﻨَّﺎ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﻣِﻦْ ﻗَﺒْﻠِﻬِﻢْ ﻓَﻠَﻴَﻌْﻠَﻤَﻦَّ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺻَﺪَﻗُﻮﺍ ﻭَﻟَﻴَﻌْﻠَﻤَﻦَّ ﺍﻟْﻜَﺎﺫِﺑِﻴﻦَ ‏[ﺍﻟﻌﻨﻜﺒﻮﺕ 3-1: ‏] 《አ.ለ.መ (አሊፍ ላም ሚም)★ሰዎቹ አምነናል በማለታቸው ብቻ እነሱ ሳይፈተኑ የሚተው መኾናቸውን ጠረጠሩን★ እነዚያንም ከእነሱ በፊት የነበሩትን በእርግጥ ፈትነናል፡፡ እነዚያንም እውነት የተናገሩትን አላህ በእርግጥ ያውቃል፡፡ ውሸታሞቹንም ያውቃል፡፡》  (📚አል አንከቡት) ★ ከላይኛው አንቀፅ ውሸት ያልተወገደበት የምስክርነት ቃል ሙናፊቅነትን(አስመሳይነትን) እንጂ ሌላን እንደማይገልፅ ግልፅ ነው።  በተጨማሪም በሀዲስ ዘገባ የተጠቀሰው የሚከተለውን ይመስላል፦  ﻋﻦ ﻣﻌﺎﺫ ﺑﻦ ﺟﺒﻞ ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻪ ﻋﻦ ﺍﻟﻨﺒﻲ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ ﻣَﺎ ﻣِﻦْ ﺃَﺣَﺪٍ ﻳَﺸْﻬَﺪُ ﺃَﻥْ ﻻَ ﺇِﻟَﻪَ ﺇِﻟَّﺎ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﻭَﺃَﻥَّ ﻣُﺤَﻤَّﺪًﺍ ﺭَﺳُﻮﻝُ ﺍﻟﻠَّﻪِ، ﺻِﺪْﻗًﺎ ﻣِﻦْ ﻗَﻠْﺒِﻪِ، ﺇِﻟَّﺎ ﺣَﺮَّﻣَﻪُ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﻋَﻠَﻰ ﺍﻟﻨَّﺎﺭ 🎤 ሙዐዝ ኢብኑ ጀበል(ረ·ዐ) ከረሱል ﷺ ይዞ እንደዘገበልን ረሱል እንዲህ አሉ፦ «ከመካከላችሁ "ከልቡ እውነተኛ ሁኖ" ላ ኢላሀ ኢለላህ ሙሀመድ ረሱሉላህ ብሎ አንዳችሁም አይመሰክርም አላህ ከእሳት እርም(ሀራም) ያደረገው ቢሆን እንጂ!!» *****  ▪️👉 5ኛ ﺍﻟﻤﺤﺒﺔ ﺍﻟﻤﻨﺎﻓﻴﺔ ﻟﻠﺒﻐﺾ ﻭﺍﻟﻜﺮﻩ ؛ ﻭﺫﻟﻚ ﺑﺄﻥ ﻳﺤﺐ ﻗﺎﺋﻠﻬﺎ ﺍﻟﻠﻪ ﻭﺭﺳﻮﻟﻪ ﻭﺩﻳﻦ ﺍﻹﺳﻼﻡ ﻭﺍﻟﻤﺴﻠﻤﻴﻦ ﺍﻟﻘﺎﺋﻤﻴﻦ ﺑﺄﻭﺍﻣﺮ ﺍﻟﻠﻪ ﺍﻟﻮﺍﻗﻔﻴﻦ ﻋﻨﺪ ﺣﺪﻭﺩﻩ ، ﻭﺃﻥ ﻳﺒﻐﺾ ﻣﻦ ﺧﺎﻟﻒ ‏« ﻻ ﺇﻟﻪ ﺇﻻ ﺍﻟﻠﻪ ‏» ﻭﺃﺗﻰ ﺑﻤﺎ ﻳﻨﺎﻗﻀﻬﺎ ﻣﻦ ﺷﺮﻙ ﺃﻭ ﻛﻔﺮ ﺃﻭ ﻳﻨﺎﻗﺾ ﻛﻤﺎﻟﻬﺎ ﻣﻦ ﺑﺪﻉ ﻭﻣﻌﺎﺻﻲ ☂ አምስተኛው መስፈርት ደግሞ ጥላቻን ያስወገደ ውዴታ ሲሆን ይህም ማለት በላ ኢላሀ ኢለሏህ የሚናገረው ሰው አላህን፣ መልእክተኛውን፣ እስልምናንና በአላህ ትእዛዝ ላይ ያሉትንና ድንበሩን የማያልፉትን መውደድ እንዲሁም ላ ኢላሀ ኢለላህን በሚንድ በሆነ ሽርክና ኩፍር ወይም ቢድዐና አመፅ ላይ ያለን ተቃራኒ አካል መጥላት ማለት ነው!! 💥 አላህም በዚህ ዙሪያ እንዲህ ይላል፦ ﻭَﻣِﻦَ ﺍﻟﻨَّﺎﺱِ ﻣَﻦْ ﻳَﺘَّﺨِﺬُ ﻣِﻦْ ﺩُﻭﻥِ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺃَﻧْﺪَﺍﺩًﺍ ﻳُﺤِﺒُّﻮﻧَﻬُﻢْ ﻛَﺤُﺐِّ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻭَﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺁﻣَﻨُﻮﺍ ﺃَﺷَﺪُّ ﺣُﺒًّﺎ ﻟِﻠَّﻪِ ‏[ﺍﻟﺒﻘﺮﺓ 165]  《ከሰዎችም ከአላህ ሌላ ባለንጣዎችን (ጣዖታትን) አላህን እንደሚወዱ የሚወዷቸው ኾነው የሚይዙ አሉ፡፡ እነዚያ ያመኑትም አላህን በመውደድ (ከነርሱ) ይበልጥ የበረቱ ናቸው፡፡》 (📚አል በቀራህ) 📜 በሀዲስ በመጣ ዘገባ ደግሞ፦  ﻋﻦ ﺃﻧﺲ ﺑﻦ ﻣﺎﻟﻚ ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻪ ﻗﺎﻝ : ﻗﺎﻝ ﺭﺳﻮﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ ﺛَﻠَﺎﺙٌ ﻣَﻦْ ﻛُﻦَّ ﻓِﻴﻪِ ﻭَﺟَﺪَ ﺣَﻠَﺎﻭَﺓَ ﺍﻟْﺈِﻳﻤَﺎﻥِ : ﺃَﻥْ ﻳَﻜُﻮﻥَ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﻭَﺭَﺳُﻮﻟُﻪُ ﺃَﺣَﺐَّ ﺇِﻟَﻴْﻪِ ﻣِﻤَّﺎ ﺳِﻮَﺍﻫُﻤَﺎ ، ﻭَﺃَﻥْ ﻳُﺤِﺐَّ ﺍﻟْﻤَﺮْﺀَ ﻟَﺎ ﻳُﺤِﺒُّﻪُ ﺇِﻟَّﺎ ﻟِﻠَّﻪِ ، ﻭَﺃَﻥْ ﻳَﻜْﺮَﻩَ ﺃَﻥْ ﻳَﻌُﻮﺩَ ﻓِﻲ ﺍﻟْﻜُﻔْﺮِ ﻛَﻤَﺎ ﻳَﻜْﺮَﻩُ ﺃَﻥْ ﻳُﻘْﺬَﻑَ ﻓِﻲ ﺍﻟﻨَّﺎﺭ· 🎤 አነስ ኢብኑ ማለኪ(ረ·ዐ) ከረሱል ﷺ ይዞ እንደዘገበልን ረሱል እንዲህ አሉ፦ «ሶስት ነገሮች በውስጡ ያሉት ሰው የኢማንን ጥፍጥና አግኝቷል፤ ከሌሎቹ ነገሮች የበለጠ አላህና መልእክተኛው እርሱ ዘንድ ተወዳጅ ሲሆኑ፣ አንድን ሰው ሲወድ ለአላህ ብሎ እንጂ ለሌላ ሳይወደው ሲቀር ፣እሳት ውስጥ መወርወርን እንደሚጠላው ሁሉ ወደ ኩፍር መመለስን የሚጠላ ሲሆን!!» 🎤 በተጨማሪም፦  يقول ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ : ﺃﻭﺛﻖ ﻋﺮﻯ ﺍﻹﻳﻤﺎﻥ ﺍﻟﺤﺐ ﻓﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻭﺍﻟﺒﻐﺾ ﻓﻲ ﺍﻟﻠﻪ  «የእምነት አስተማማኙ ገመድ ለአላህ ብሎ መውደድ ለአላህ ብሎ መጥላት ነው።» (ረሱል ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ****** ▪️👉 6ኛ ﺍﻻﻧﻘﻴﺎﺩ ﺍﻟﻤﻨﺎﻓﻲ ﻟﻠﺘﺮﻙ ؛ ﻓﻼﺑﺪ ﻟﻘﺎﺋﻞ ‏« ﻻ ﺇﻟﻪ ﺇﻻ ﺍﻟﻠﻪ ‏» ﺃﻥ ﻳﻨﻘﺎﺩ ﻟﺸﺮﻉ ﺍﻟﻠﻪ ﻭﻳﺬﻋﻦ ﻟﺤﻜﻤﻪ ﻭﻳﺴﻠﻢ ﻭﺟﻬﻪ ﻟﻠﻪ ☂ ለአላህ ትእዛዝ መተውን በማስወገድ መጎተት(መታዘዝ) ስድስተኛው ሸርጥ ነው። በርግጥም አንድ በላ ኢላሀ ኢለላህ የሚናገር ሰው ለአላህ ሸሪዐ ሊታዘዝ፣ ለፍርዱ ሊተናነስና ለአላህም እጅ ሊሰጥ ግዴታ በመሆኑ ላይ ጥርጥር የለውም!! 💥 አላህም አንዲህ ይላል፦  ﻭَﺃَﻧِﻴﺒُﻮﺍ ﺇِﻟَﻰ ﺭَﺑِّﻜُﻢْ ﻭَﺃَﺳْﻠِﻤُﻮﺍ ﻟَﻪُ ‏[ﺍﻟﺰﻣﺮ 54] 《ወደ ጌታችሁ (በመጸጸት) ተመለሱ፡፡ ለእርሱም ታዘዙ፡፡》 (📚አል ዙመር) وَمَنْ أَحْسَنُ دِينًا مِمَّنْ أَسْلَمَ وَجْهَهُ لِلَّهِ وَهُوَ مُحْسِنٌ وَاتَّبَعَ مِلَّةَ إِبْرَاهِيمَ حَنِيفًا ۗ وَاتَّخَذَ اللَّهُ إِبْرَاهِيمَ خَلِيلًا ‏[ﺍﻟﻨﺴﺎﺀ 125]

🔺የ "ላ ኢላሀ ኢለሏህ መስፈርቶች" ~~~ የ "ላ ኢላሀ ኢለሏህ መስፈርቶች" ከቁርዓንና ከሀዲስ بسم الله الرحمان الرحيم  አላህ ለኛ ከዋለልን ፀጋዎች ውስጥ ዋናውና አንዱ መልእክተኛን ልኮልን የተውሂድንና የዚችን የ" *ላ ኢላሀ ኢለሏህ* " ጉደይ እንዲብራራልንና እንድንገነዘበው ማድረጉ ተጠቃሽ ነው።    ሁሉም መልእክተኞች ወደ ህዝቦቻቸው ሲመጡ ይችን የተውሂድ ንግግር የሆነችውን *ላ ኢላሀ ኢለሏህ* ለማስጨበጥ ነው። አላህም ስለነርሱ የሚከተለውን ይላል፦  【ﻭَﻣَﺎ ﺃَﺭْﺳَﻠْﻨَﺎ ﻣِﻦْ ﻗَﺒْﻠِﻚَ ﻣِﻦْ ﺭَﺳُﻮﻝٍ ﺇِﻻ ﻧُﻮﺣِﻲ ﺇِﻟَﻴْﻪِ ﺃَﻧَّﻪُ ﻻ ﺇِﻟَﻪَ ﺇِﻻ ﺃَﻧَﺎ ﻓَﺎﻋْﺒُﺪُﻭﻥِ 】《ከአንተ በፊትም እነሆ ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና ተገዙኝ በማለት ወደርሱ የምናወርድለት ቢኾን እንጅ ከመልክተኛ አንድንም አላክንም።》📚አል አንቢያእ) በሌላ አንቀፅ ላይ ሁሉም መልእክተኞች ለህዝቦቻቸው የሚከተለው ንግግር እንዳሉም አላህ ሲነግረን እንዲህ ይላል፦ ﺍﻋْﺒُﺪُﻭﺍ ﺍﻟﻠَّﻪَ ﻣَﺎ ﻟَﻜُﻢْ ﻣِﻦْ ﺇِﻟَﻪٍ ﻏَﻴْﺮُﻩُ  ወገኖቼ ሆይ! አላህን ተገዙ፡፡ ከእርሱ ሌላ ምንም አምላክ የላችሁም፡፡  ★ እንግዲህ ይቺ "ላ ኢላሀ ኢለሏህ"የመልእክተኞች ሁሉ አላማ ከሆነች ልንከተላትና ልንማራት ግድ ይላል!! ማንኛውም የዲነል ኢስላምን መንገድ የፈለገ በሙሉ በቁርዓንና በሀዲስ የተጠቀሱትን የዚችን ንግግር መስፈርቶች በሙሉ ሊያሟላ ግድ ለመሆኑ ጥርጥር የሌለበት ነጥብ ነው!! *******                    ለዚህም ነው አንድ ሰው ወደ እስልምና መግባት ከፈለገ ይቺን ወደ እስልምና መግቢያ የሆነችውን ቃል ከነ መስፈርቶቿ ሊላት ግድ ነው የምንለው። *ከዚህ በመቀጠል የ ላኢላሀ ኢለላህን ሸርጦች(መስፈርት) ከቁርአንና ከሀዲስ በአጭሩ የምንገልፀው ይሆናል።   ላ ኢላሀ ኢለሏህ ሰባት*(7) ሸርጦች አሏት ▪ 1ኛ= ﺍﻟﻌﻠﻢ ﺑﻤﻌﻨﺎﻫﺎ ﺍﻟﻤﺮﺍﺩ ﻣﻨﻬﺎ ﻧﻔﻴﺎً ﻭﺇﺛﺒﺎﺗﺎً ؛ ﻭﺫﻟﻚ ﺑﺄﻥ ﺗﻨﻔﻲ ﺟﻤﻴﻊ ﺃﻧﻮﺍﻉ ﺍﻟﻌﺒﺎﺩﺓ ﻋﻦ ﻛﻞ ﻣﻦ ﺳﻮﻯ ﺍﻟﻠﻪ ﻭﺗﺜﺒﺖ ﺫﻟﻚ ﻟﻠﻪ ﻭﺣﺪﻩ የመጀመሪያ የላ ኢላሀ ኢለሏህ መስፈርት ትርጉሞቿን ማወቅ ሲሆን ይህም ማለት ከአላህ ውጭ ያሉ አምልኮቶችን በሙሉ ውድቅ በማድረግ አምልኮትን ለአላህ ብቻ ማፅደቅን የሚመለከት ይሆናል።     👉 በዚህም ዙሪያ ላይ የመጡ መረጃዎች ብዙ ናቸው፦ሁል ጊዜ በምናነባት በሱረቱል ፋቲሀህ ላይ ጌታችን አላህ እንዲህ ይላል፦  【ﺇِﻳَّﺎﻙَ ﻧَﻌْﺒُﺪُ ﻭَﺇِﻳَّﺎﻙَ ﻧَﺴْﺘَﻌِﻴﻦ】ُ ‏[📚ﺍﻟﻔﺎﺗﺤﺔ] 《አንተን ብቻ እንግገዛለን፤ አንተንም ብቻ እገዛ እንጠይቃለን።》 (📚አል ፋቲሀህ) ﻓَﺎﻋْﻠَﻢْ ﺃَﻧَّﻪُ ﻟَﺎ ﺇِﻟَﻪَ ﺇِﻟَّﺎ ﺍﻟﻠَّﻪُ ‏[📚ﻣﺤﻤﺪ 19:‏]  《እነሆ ከአላህ ሌላ በእውነት የሚመለክ አምላክ አለመኖሩንም ዕወቅ፡፡》 (📚ሱረቱል ሙሀመድ) ﺇِﻟَّﺎ ﻣَﻦْ ﺷَﻬِﺪَ ﺑِﺎﻟْﺤَﻖِّ ﻭَﻫُﻢْ ﻳَﻌْﻠَﻤُﻮﻥَ ‏[📚ﺍﻟﺰﺧﺮﻑ 86:‏]  《የሚያውቁ ኾነው በእውነት ከመሰከሩት በስተቀር…》 (📚አል ዙኽሩፍ)  👆ይቺን አንቀፅ የተፍሲር ሙሁራን ሲያብራሩ እንዲህ ይላሉ፦  ﺃﻱ ﺇﻻ ﻣﻦ ﺷﻬﺪ ﺑـ ‏« ﻻ ﺇﻟﻪ ﺇﻻ ﺍﻟﻠﻪ ‏» ﻭَﻫُﻢْ ﻳَﻌْﻠَﻤُﻮﻥَ ﺃﻱ ﻣﺎ ﺷﻬﺪﻭﺍ ﺑﻪ ﻓﻲ ﻗﻠﻮﺑﻬﻢ ﻭﺃﻟﺴﻨﺘﻬﻢ . «በ ላኢላሀ ኢለላህ እያወቀ ማለትም በልቡና በምላሱ የመሰከረው እያወቅ ሲቀር ለማለት ነው ይላሉ!!» ★ እንግዲህ የ ላኢላሀ ኢለሏህ ባለቤቶች አምልኮትን ለአላህ ብቻ የሰጡ መሆንና በ ላኢላሀ ኢለላህ ላይ ሙሉ እውቀት እንደሚያስፈልግም ከላይ ያሉት ሶስት አንቀፆች ያስገነዝቡናል።በሀዲስ በመጣ ዘገባ ላይ ደግሞ፦  ﻭﻋﻦ ﻋﺜﻤﺎﻥ ﺑﻦ ﻋﻔﺎﻥ ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻪ ﻗﺎﻝ : ﻗﺎﻝ ﺭﺳﻮﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ ﻗﺎﻝ : ﻣَﻦْ ﻣَﺎﺕَ ﻭَﻫُﻮَ ﻳَﻌْﻠَﻢُ ﺃَﻧَّﻪُ ﻟَﺎ ﺇِﻟَﻪَ ﺇِﻟَّﺎ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﺩَﺧَﻞَ ﺍﻟْﺠَﻨَّﺔ ዑስማን ኢብኑ አፋን(ረ·ዐ) ከረሱል ﷺ ይዞ እንደዘገበልን፦ «ከአላህ ውጭ በእውነት የሚመለክ አምላክ አለመኖሩን እያወቀ የሞተ ሰው በርግጥ ጀነት ገባ!!» እንግዲህ በመጀመሪያው መስፈርት ዙሪያ ላይ ካሉት መረጃዎች መካከል የቁርዐንና የሀዲስን ቃኝተናል፣ በመሆኑም ማንኛውም የ ላ ኢላሀ ኢለላህ ተናጋሪ ይህን የመጀመሪያ መስፈርት ቃሏን ከማለቱ በፊት ማስገኘት ግዴታ ይሆንበታል። ******                         ▪️👉 2ኛ   ﺍﻟﻴﻘﻴﻦ ﺍﻟﻤﻨﺎﻓﻲ ﻟﻠﺸﻚ ﻭﺍﻟﺮﻳﺐ ؛ ﻭﻣﻌﻨﺎﻩ ﺃﻥ ﻳﻜﻮﻥ ﻣﻮﻗﻨﺎً ﺑﻬﺬﻩ ﺍﻟﻜﻠﻤﺔ ﻳﻘﻴﻨﺎً ﺟﺎﺯﻣﺎً ﻻ ﺷﻚ ﻓﻴﻪ ﻭﻻ ﺭﻳﺐ  የ ላ ኢላሀ ኢለላህ ሁለተኛ መስፈርት ሁኖ የምናገኘው ከጥርጣሬ የራቀን ፍፁም እርግጠኛነትን ይሆናል። ይህም ማለት በዚች ቃል መስካሪ የሆነው ሰው በቃሏ ላይ ሙሉ የሆነ እርግጠኛነት፣ ቆራጥነት እንዲሁም ከጥርጣሬ የራቀ እምነት ሊኖረው ማለት ነው። 💥 አላህ አማኞችን ሲሰይም እንደከሚከተለው ይላል፦  ﺇِﻧَّﻤَﺎ ﺍﻟْﻤُﺆْﻣِﻨُﻮﻥَ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﺁﻣَﻨُﻮﺍ ﺑِﺎﻟﻠَّﻪِ ﻭَﺭَﺳُﻮﻟِﻪِ ﺛُﻢَّ ﻟَﻢْ ﻳَﺮْﺗَﺎﺑُﻮﺍ ﻭَﺟَﺎﻫَﺪُﻭﺍ ﺑِﺄَﻣْﻮَﺍﻟِﻬِﻢْ ﻭَﺃَﻧْﻔُﺴِﻬِﻢْ ﻓِﻲ ﺳَﺒِﻴﻞِ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺃُﻭﻟَﺌِﻚَ ﻫُﻢُ ﺍﻟﺼَّﺎﺩِﻗُﻮﻥَ { ‏[ ﺍﻟﺤﺠﺮﺍﺕ 15 ‏]  《እውነተኛዎቹ) ምእምናን እነዚያ በአላህና በመልእከተኛው ያመኑት ከዚያም ያልተጠራጠሩት በገንዘቦቻቸውና በነፍሶ ቻቸውም በአላህ መንገድ የታገሉት ብቻ ናቸው፡፡ እነዚያ እነሱ እውነተኞቹ ናቸው፡፡》📚አል ሁጁራት) ﻭﻣﻌﻨﻰ ﻟَﻢْ ﻳَﺮْﺗَﺎﺑُﻮﺍ ﺃﻱ ﺃﻳﻘﻨﻮﺍ ﻭﻟﻢ ﻳﺸﻜُّﻮﺍ . 《በአንቀፁ ውስጥ ያልተጠራጠሩ በማለት የተገለፀው እርግጠኛ የሆኑ ለማለት ነው!!》 📜 በሀዲስ ከመጣ ዘገባ ደግሞ፦ ﻋﻦ ﺃﺑﻲ ﻫﺮﻳﺮﺓ ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻪ ﻗﺎﻝ : ﻗﺎﻝ ﺭﺳﻮﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ : ﺃَﺷْﻬَﺪُ ﺃَﻥْ ﻟَﺎ ﺇِﻟَﻪَ ﺇِﻟَّﺎ ﺍﻟﻠﻪُ، ﻭَﺃَﻧِّﻲ ﺭَﺳُﻮﻝُ ﺍﻟﻠﻪِ، ﻟَﺎ ﻳَﻠْﻘَﻰ ﺍﻟﻠﻪَ ﺑِﻬِﻤَﺎ ﻋَﺒْﺪٌ ﻏَﻴْﺮَ ﺷَﺎﻙٍّ ﻓِﻴﻬِﻤَﺎ ﺇِﻟَّﺎ ﺩَﺧَﻞَ ﺍﻟْﺠَﻨَّﺔَ  🎤 አቡ ሁረይራ(ረ·ዐ) ከረሱል ﷺ ይዞ እንደዘገበልን፦ ረሱል እንዲህ አሉ «ከአላህ ሌላ በእውነት የሚመለክ አምላክ እንደሌለና እኔም የአላህ መልእክተኛ መሆኔን እመሰክራለሁ፣ በነዚህ ሁለት የምስክርነት ቃሎች አንድ ባሪያ ጌታውን ከጥርጣሬ ውጭ ሁኖ አይገናኘውም ጀነት የገባ ቢሆን እንጂ!!»  *****                   ▪️👉 3ኛ= ﺍﻹﺧﻼﺹ ﺍﻟﻤﻨﺎﻓﻲ ﻟﻠﺸﺮﻙ ሶስተኛው ሸርጥ ደግሞ ከሽርክ በራቀ መልኩ ኢኽላስን የተላበሰ መሆን ነው። ኢኽላስ ስንል አላህን ከርሱ ውጭ ካሉ አምልኮቶች ሁሉ አርቆ በብቸኝነት ማምለክ ማለት ነው።

أذكار الصباح | أحمد النفيس

أذكار الصباح | أحمد النفيس

qsyd_mw_thr_twqz_lqlwb_y_yh_lnsn_mhl_ntbh_gmcsk7f7mas_71d8cff7.mp35.71 MB

قصيدة_مؤثرة_عن_القبر_و_الموت_لقد_فنوا_و_ما_بقى_منهم_خبر_48k.mp32.49 MB

y_yh_lnsn_mhl_ntbh_aabdlkrym_mhywb_lqd_fnw_wm_bq_mnhm_hd_ya_ayo.mp35.52 MB

وَوَصَّيْنَا الْإِنسَانَ.mp314.80 MB

የአሹራ ፆም ቱሩፋቶች.mp32.53 MB

📚 كتاب صوتي: العلم النافع.mp320.14 MB

ከተፃፉ ቆየት ቢሉም ይነበብ

“በመጨረሻይቱም (አለም) እነርሱ የሚያረጋግጡ ከሆኑት (መሪ ነው)። (አል' በቀራህ፡ 4) በዚህ የቁርኣን አንቀጽ የተፈለገው ሲቀጠሩት የነበረው ነገር እንደመጣቸው እርሱም የቂን (ሞት) እንደሆነ ይገልጻል፡፡)) ይህ አንቀጽ ፣ ዓቅለኛ ሆኖ ለአካለ መጠን ከደረሰበት ጊዜ ጀምሮ _ እስኪሞት ድረስ ዒባዳ ዋጅብ እንደሆነ ፣ ሱፍያዎች እንደሚሉት ከሞት በፊት ግዴታ የሚቆምበት “ሀል” የሚባል እንደሌለ ይጠቁማል፡፡ ይህ ፣ ድሮም ይሁን አሁን የሱፍያ ዲን ነው፡፡ ዒባዳን አስመልክቶ የሱፍያ አቋም ይህ ነው፡፡ ከሱፍያዎች ኪታብ የነቀልነው ጥቂቱን ብቻ ነው… እኔ በጥናቴ ላይ ትኩረት ያደረኩት የዒባዳውን እና በዒባዳ ላይ ያላቸውን አቋም ብቻ ነው፡፡ ሌሎችም ልክበተውሂድ ፣ በሩሡሎች መልእክተኛነት ፣ በሸሪዓው እና በቀደር ዙሪያ አቋም እንዳላቸው ሁሉ ባልተጠቀሱ የቀሩ ጉዳዮችም የተለዩ አቋሞች ያሏቸው ሲሆን ይህን ለማብራራት ተከታታይና  በጣም ሰፋ ያሉ ማብራሪያዎች ይሻል በዚህ እርስ ግን ለቅምሻ ያክል የስኳሁኑ ይበቃናል ሀቅን በሀቅነቱ እንዲያሳየን እና መከተልንም እንዲለግሰን ፤ ባጢልንም በባጢልነት እንዲያሳየን እና መራቅን እንዲቸረን ፤ ከመራን በኋላ ልቦቻችንንም እንዳያጠምብን አላህን እለምነዋለሁ፡፡ #ክፍል1 https://t.me/AbulQmane/2148 ክፍል2 https://t.me/AbulQmane/2149 ክፍል3 https://t.me/AbulQmane/2150 ክፍል4 https://t.me/AbulQmane/2172 ክፍል5 https://t.me/AbulQmane/2176 ክፍል6 https://t.me/AbulQmane/2219

🔺ሱፊያዎች በዲንና በዒባዳ መሰረቶቸ ላይ ያአላቸው ስህቱ አቋም #ክፍል6 ~~~ وموقف الصوفية من أصول العبادة والدين ስድስተኛ፡- ባጢል (ስህተት) ከሆነው የሱፍያ ዲን መካከል ፡ አንድ ሰው ከሸሪዓዊ ሀላፊነት የሚወጣበት ደረጃ አለ ማለታቸው ነው ይህ የተሶውፍ አመለካከት ድንበር አልፎ የጥመትን ጫፍ የመድረሱ ውጤት ነው፡፡ የተሶውፍ መሰረቱ ኢብን አልጀውዝይ እንደተናገረው ነበር፡-ወራዳ የሆነን ስነምግባር ታግሎ መመለስ፣ ነፍስን አሰልጥኖ ወደጥሩ ስነምግባርመውሰድ፡፡ ዙህድ ፣ ችሎታ ፣ ትዕግስት ፣ ኢኽላስ እና እውነተኛነት፡፡)) በተጨማሪ የሚከተለውን ተናግሯል፡- ((የመጀመሪያዎቹ (ሱፍዮች) ባህሪ ይህ ነበር ፤ አንዳንድ ነገሮችን ኢብሊስ እነርሱን ከዚያም ተከታዮቻቸውን ቀላቀለባቸው፡፡ አንድ ክፍለ ዘመን ባለፈ ቁጥር በሁለተኛው ክፍለ ዘመን (ሰይጣን) ወደኋላ ላሉት የበለጠ የተመቻቸ እስኪሆንለት ድረስ በሰዎች ላይ ዲናቸውን ይቀላቅልባቸዋል፡፡ ዋናው የመቀላቀል መሰረቱ ከእውቀት ማገዱ ፣ ተፈላጊው አላማ እውቀት ሳይሆን ተግባር ነው ብሎ ማሳየቱ ነው፡፡ የሰይጣን ዋና አላማ የእውቀትን መብራት በእነርሱ ላይ ካጠፋ በኋላ በጨለማ እንዲደናበሩ ማድረግ ነው፡፡ ይህ ብቻ አይደለም ዱንያን በአጠቃላይመተው አስፈላጊ እንደሆነ ያሳያቸዋል፡፡ አካላቸውን የሚያስተካክሉበትን ዱንያ እንዲተው ያደርጋቸዋል፡፡ ገንዘብን ከጊንጥ ጋር ያመሳስሉታል … ነፍስን ከአቅም በላይእንድትሸከም ያደርጓታል፡፡ ጭራሽ ከአልጋ ላይ መጋደምን አያስፈልግም እስከማለት ይደርሳሉ … ከእነርሱ መካከል እውቀት ካለመኖሩ የተነሳ ሳያውቅ በረሡል ላይበተዋሹ ሐዲሶች ለመተግበር ይሞክራል፡፡ ከዚያም ሰዎች መራብ ፣ መደህየት እንዳለባቸው በወስዋስ (በብዥታ) ላይ የሚቀሰቅሱ መጽሐፎችን የጻፉ ሰዎች መጡ፡፡ ልክ እንደ ሀሪስ አልሙሀሲቢ ማለት ነው፡፡ ሌላው ደግሞ መጣ የሱፍያን መዝሀብ ማጣራት ጀመረ ፣ እነርሱ የሚለዩበትን ባህሪዎች ነጥሎ አስቀመጠ፡፡ የሱፍያ ባህሪ በማጨብጨብ ፣ በመወዛወዝ ፣ በዜማ የተለየ እንደሆነ ግልጽ አደረገ፡፡ አሁንም ነገሩ በዚህ አላቆመም እየጨመረ ሄደ፡፡ መሻይኾቻቸው …. ከዑለማ ራቁ እነርሱ ያሉበትን “ኢልመል ባጢን”(ስውር እውቀት)በማለት ሰየሙ ፣ የሸሪዓውን እውቀት ደግሞ “ኢልመ ዟሂር” (ግልጽ እውቀት) በማለት ሰየሙ፡፡ ከእነርሱ መካከል ከረሐብ የተነሳ ብዥታ ውስጥ የወደቀውን ፣ በቃ ይህ ግለሰብ የአላህ ከፍተኛ ወዳጅ እንደሆነ አድርገው ቆጠሩ…እነዚህ ሰዎች በክህደትና በቢድዓ መካከል ሆኑ፡፡ ከዚያም ጦሪቃዎች በርካታ ሆኑ (1) ፣ ዓቂዳቸውም በዚህ ምክንያት ተበላሸ፡፡ ከእነርሱ መካከል የ “ሁሉል” ዓቂዳ ያለው አለ፡፡ ከእነርሱ መካከል የኢቲሃድ ዓቂዳ ያለው አለ፡፡ ኢብሊስ በቢድዓ የእውቀት አይነቶች እንዲዋዥቁ ከማድረግ አልተወገደም …)) ( 📕ተልቢስ አል'ኢብሊስ 157-158) ሸይኹል ኢስላም ብን ተይሚያ - ረሂመሁሏህ - የሚከተለውን ጥያቄ ተጠየቁ፡- ((አንዳንድ ሰዎች አሉ ነፍስን በማለማመድ የዘወተሩ ፣ ከዚያም እራሳቸውን ጀውሐር (በራሳቸው የተብቃቁ) ነን ብለው ያሰቡ ፤ “… ፣ ትዕዛዝ ክልከላ የተራው ማህበረሰብ መንገድ ነው ፣ እነርሱም ጀውሐር ደረጃ ቢደርሱ ሁሉም ነገር ከእነርሱ ላይይነሳላቸው ነበር፡፡ ነብይነት ተራውን ማህበረሰብ በህግ ለመዳኘት እና ስርዓት የማስያዝ ጥበብ ነው፡፡ እኛ ደግሞ ከተራው ማህበረሰብ አይደለንም፡፡ በተክሊፍ (በህግ) ጓዳ የምንገባ አይደለንም፡፡ እኛ ጀውሀር ሆነናል ጥበብን አውቀናል ይላሉ፡፡” መልስ፡- ይህ ንግግር ከአይሁድና ነሷራ ንግግር የከፋ ትልቅና ከባድ ክህደት እንደሆነ ከኢማን እና ዒልም ባለቤቶች ዘንድ ጥርጥር የለውም፡፡ አይሁድና ነሷራ በተወሰኑ ኪታቦች አመኑ በከፊሉ ካዱ፡፡ እነዚህ ከሐዲ ከመሆናቸው ጋር ለአላህ ትዕዛዝን ፣ ክልከላን ፣ ዛቻ ፣ ቀጠሮ እንዳለ ያምናሉ ይህም የተሰረዘረውን የተቀየረውን አይሁድነትን እና ነሷራነትን አጥብቀው እስከያዙ ድረስ ነው፡፡ከእነርሱ አማኞች ውስጥ ሙናፊቆቻቸው ማለትም ፈላስፎቻቸው ከዚህ ኡመት ሙናፊቆች በጣም የከፉ ናቸው፡፡ ምክንያቱም ክህደትን ይፋ አድርገው ፣ ኒፋቅን ድብቅ አደረጉ፡፡ ኢማንን ይፋ አድርጎ ንፍቅናን ከደበቀው የከፋ ሆነ፡፡ የተፈለገው አላማ ፣ በተሰረዘው ጥቅል ህግ አጥብቀው ከያዙት ነሷራ እና አይሁድ በአጠቃላይ ትዕዛዝ ክልከላ ከእኔ ላይ ወድቆልኛል ከሚለው ሱፍያ የተሻለ ነው ። እነዚህ ከማንኛውም መጽሓፍ ፣ ሸሪዓዎች እና ሚለሎች ሁሉ አፈንግጠዋል፡፡ ምክንያቱም ለአላህ መታዘዝና መከልከል የሚባል ነገር ከእነርሱ ዘንድ የለም፡፡ እንደውም ከዚህ በፊት ከኢብራሂም ቅሪት መጽሓፍትን አጥብቀው ከያዙት የአረብ ሙሽሪኮችም ይከፋሉ፡፡ እነዚህ ሙሽሪክ ከመሆናቸው ጋር እነርሱ የያዙት የተወሰነ ሐቅ አለ፡፡ እነዚህ ግን ፣ ከሐቅ የወጡ ናቸው ፤ ከሐቅ አንድም የያዙት የለም፡፡ እነርሱ ፣ ትዕዛዝንም ክልክልንም ሙሉ በሙሉ ዝግ አድርገዋል፡፡)) በመቀጠል እንዲህ ይላል፡- ((ከእነርሱ መካከል በሚከተለው ቁርኣን ማስረጃ የሚያደርግ አለ፡- وَاعْبُدْ رَبَّكَ حَتَّىٰ يَأْتِيَكَ الْيَقِينُ እውነቱም (ሞት) እስኪመጣህ ድረስ ጌታህን ተገዛ፡፡ Surah: Al-Hijr, Ayat: 99 የዚህ ትርጉሙ፡ “ጌታህን ተገዛ እውቀት እና ግንዛቤ እስክትደርስ” ማለት ነው ይላሉ፡፡ ከዚህ ደረጃ ከደረስክ ዒባዳ ከአንተ ላይ ይነሳልሃል፡፡ አንዳንዶች ደግሞ ፡ “የሆነ ባህሪ ላይ እስክትደርስ ድረስ ስራ” ይላሉ፡፡ የሱፍያ ባህሪ ላይ ከደረስክ ዒባዳ ከአንተ ላይ ይነሳልሃል፡፡ እውቀትና ግንዛቤ ላይ ከደረሱ ፈርድ ይተዋሉ ፤ ሀራም ይሰራሉ፡፡ ይህ ከዚህ በፊት እንዳስቀደምነው ግልጽ የሆነ ክህደት ነው፡፡በእነርሱ ላይ እንጅ ለእነርሱ ማስረጃ ሆኖ የሚያገለግል አይደለም፡፡ ሀሰን አልበስርይ - ረሂመሁሏህ - የሚከተለውን ተናግረዋል፡- " إن الله لم يجعل لعمل المؤمنين أجلا دون الموت" “ለሙእሚን ከሞት በፊት (ስራን የሚያቆምበት) የጊዜ (ገደብ) አላህ አላደረገም” ከዚያም የሚከተለውን ቁርኣን አነበበ፡- وَاعْبُدْ رَبَّكَ حَتَّىٰ يَأْتِيَكَ الْيَقِينُ እውነቱም (ሞት) እስኪመጣህ ድረስ ጌታህን ተገዛ፡፡ “የቂን” ማለት ሞት እና ከሞት በኋላ መሆኑን ዑለሞች በአጠቃላይ ተስማምተዋል፡፡ ለዚህ ተመሳሳይ የሚከተለው ቁርኣን ማስረጃ ይሆናል፡፡ مَا سَلَكَكُمۡ فِي سَقَرَ (ይሏቸዋልም) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?» وَلَمْ نَكُ نُطْعِمُ الْمِسْكِينَ "ምስኪኖችንም አንመግብም ነበር።" وَكُنَّا نَخُوضُ مَعَ الْخَائِضِينَ "ከከንቱ ንግግርና ከሐሰት ጋር ከሚገቡ ሰዎች ጋር እንገባ ነበር።" وَكُنَّا نُكَذِّبُ بِيَوْمِ الدِّينِ "የፍርድ ቀንንም እናስተባብል ነበር።" حَتَّىٰ أَتَانَا الْيَقِينُ "እርግጠኛው ነገር (ሞት) እስከ መጣብን ድረስ።" ሱረቱ አል ሙደሲር42-47 ይህን ቃል ሶላትንና ዘካን እንደተው ፣ በትንሳኤ ቀን መዋሸታቸውን ፣ ሞት እስኪመጣቸው ድረስ ከሚዘባርቁት ጋር መዘባረቃቸውን የተናገሩት በጀሀነም ውስጥ ሆነው ነው፡፡ እነርሱ በዚህ ባህሪ ላይ ሆነው በዱንያ ላይ አማኝ ያልነበሩ መሆናቸው የታወቀ ጉዳይ ነው፡፡ አላህ በሚከተለው ቃል ከተናገረላቸው ሰዎችም አይደለም፡፡ وَبِالْآخِرَةِ هُمْ يُوقِنُونَ

🔺ስንወለድ ሙስሊም ነን ሲባል ? ~~~~ «ፊጥራ» الْفِطْرَةِ ማለት 'ተፈጥሯዊ ዝንባሌ' natural inclination ማለት ሲሆን፥ ይህም አምላክ አጠቃላይ የሰው ልጆችን ሁሉ እኩል አድርጎ የፈጠረውን ንጹሕ ማንነታችንን የሚገልጽ ቃል ነው። በእስልምና አስተምህሮ ድቀተ-ባሕርይ ወይም ጥንተ-አብሶ 'original sin' እየተባለ ከውልደታችን ጀምረን በውርስ ያመጣነው አንድም ነገር ባለመኖሩ ሁሉም ሰው ሲወለድ ያልተበከለ እና ኃጢአት አልባ የሆነውን አዲስ ማንነት ይዞ ነው። ይህ በተፈጠሮ ንጹሕ የሆነው ማንነት 'ፊጥራ' ተብሎ ይጠራል። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رضى الله عنه قَالَ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم ‏كُلُّ مَوْلُودٍ يُولَدُ عَلَى الْفِطْرَةِ، فَأَبَوَاهُ يُهَوِّدَانِهِ أَوْ يُنَصِّرَانِهِ أَوْ يُمَجِّسَانِهِ،  የአላህ መልዕክተኛ ❲ﷺ❳ እንዲህ ብለዋል:- "ሁሉም የሚወለደው ሰው በፊጥራ ላይ ነው። ወላጆቹ ግን አይሁድ፣ ክርስቲያን ወይም ዞርስቲያን ያደርጉታል።" (📚Sahih al-Bukhari 1385: Book 23, Hadith 137) ከዚህ ሐዲስ በግልጽ የምንረዳው፥ አንድ ህጻን በወላጆቹ ጫና ወደ ኩፍር ከመግባቱ በፊት ያልተበረዘ ማንነት (ፊጥራ) ላይ መሆኑን ነው። ቡኋለ ላይ የተለያዩ ክህደቶችን በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ይፈፅማል። ያኔ ያ ንጹሕ ተፈጥሯዊ ዝንባሌው ጠፍቶ ካፊር ይሆናል። አምላካችን አላህ በቅዱስ  ቃሉ ይህን 'ንጹሕ ፈለግ' ያዙ፣ ከዚያም አትውጡ በማለት ያዘናል፥ ❲ምዕራፍ 30፥30❳...ይህን ስንል ግን አንድ ሰው ሲፈጠር (ሲወለድ) የእስልምናን ሃይማኖት ሕግ እና ስርዓት አውቆ ይመጣል ማለታችን አይደለም። የትኛውም ሰው ሃይማኖተኛ ሆኖ ወደዚህ ምድር አይመጣም። ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያህ እንዲህ ይላሉ:- ولا يلزم من كونهم مولودين على الفطرة أن يكونوا حين الولادة معتقدين للإسلام بالفعل فإن الله أخرجنا من بطون أمهاتنا لا نعلم شيئا ولكن سلامة القلب وقبوله وإرادته للحق : الذي هو الإسلام بحيث لو ترك من غير مغير لما كان إلا مسلما «በፊጥራ (ተፈጥሯዊ ዝንባሌ) ላይ ተወለዱ ሲባል በተወለዱበት ወቅት እስልምናን በተግባር ይፈፅሙታል (ያውቁታል) ማለት አይደለም። ምክንያቱም አላህ ከእናቶቻችን ሆድ ሲያወጣን ምንም የማናውቅ አድርጎን ነውና። ስለዚህ እውነትን ይፈልግ ዘንድ የልብን ንጽሕና ሰጥቶታል። አንዳች በካይ ባይቀይረው ኖሮ ከሙስሊም ውጪ ሌላ አይሆንም። ❲መጅሙዕ አል-ፈታዋ ቅፅ 4/247❳ ሸይኹ አክሎም እንዲህ ይላሉ:- ‟ይህ ተፈጥሯዊ ዝንባሌ በራሱ የአምላክን መኖር ያረጋግጣል፣ እርሱን መውደድና ብቻውን ልናመልከው እንደሚገባ ይጠቁማል።” አዎ ተፈጥሮ አንድ አምላክ መኖሩን ያሳያል፣ ያ አምላክ ሁሉን ቻይ፣ ፍቅር (ወዳድ)፣ ከእኛ ጋር የሆነ ገዢ ኃይል መኖሩን ገና ከልጅነታችን ጀምሮ እንድናውቅ ያደርገናል። አንዳች አደጋ ሲደርስብን ልባችን ቶሎ ያድናት ዘንድ የምትማፀነው ያ የማይታየው አካል እርሱ አምላክ ነው። ይህ በተፈጥሮ የምናውቀው የኃያል አምላክ ባህሪ ነው። ይህን ታላቅ አምላክ በትክክል ማወቅ ግዴታ ስለሆነ አምላክ በነቢያቱ በኩል እራሱን ለእኛ ግልጽ አድርጓል። ስናጠቃልል:- ሰው ሲወለድ ሃይማኖተኛ ሆኖ አይደለም፣ በተፈጥሮ ለአምላክ ታዛዥ ከመሆኑ አንጻር ሙስሊም መባሉ እውነት ቢሆንም ከTheological perspective በኩል ከሆነ ግን ትክክል አይደለም። ያን እስልምና የምናገኘው በነቢያት ትምህርት ብቻ ነው። https://t.me/AbulQmane

ኢንሻ አላህ ይቀጥላል