ሐሽማል ቤተ-መዘክር
Open in Telegram
👉Only for readers 👋መግቢያ👋 መግቢያ ለመግባቢያ ገታ አርገነዋል የቃላትን ግልቢያ እናም በዚህ ሀሳብ ከተስማማህበት ያንኳኳኸዉን በር የገለፅከዉን ገፅ ፈቅደናል ግባበት ምንጭ - ካልታወቀ ገጣሚ Join the group @amharicbooksforeadersgroup አድሚኑን በ ቀጥታ ለማናገር ይህንን ቦት ተጠቀሙ @Digitallibraryofhashmal_bot
Show more7 953
Subscribers
+724 hours
+347 days
+11530 days
Posts Archive
7 953
ሚስቱን የገደለው ማን እንደሆነ ሁሉም ሰው ያውቃል፤ የማያውቀው ባሏ ብቻ ነበር።
ሚስቱ በሞተች ሌሊት ማንም ሌላ ገዳይ አልፈልገም፤ ሁሉም ጣቶች ወደ እርሱ ተዘረጉ።
"እሱ ነው የገ^ደላት። ከእሱ ሌላ ማንም ሊሆን አይችልም" አሉ።
በአንድ ለሊት ባልነቱ ተሰርዞ የሚስት ገዳይ ሆነ።
ባል የእስር ቤቱን ቀዝቃዛ ግድግዳ ተደግፎ፣ "እኔ አልገ^ደልኳትም" አለ ለራሱ።
ከአንደበቱ የወጣው ቃል ከግድግዳው እየተላተመ ወደእርሱ የሚመለስ መሰለው።
"ሚስቱን እየደበደበ ሲያሰቃያት እናውቃለን" ይላሉ ጎረቤቶች
"እኔ አልገደልኳትም"
ማንም አልሰማውም። የሰሙትም ሊያምኑት አልፈለጉም።
የሟች ባል ሰካራም ነበር፣ ከነብሱ ይልቅ ቁማርን የሚያፈቅር ቆማሪ ነበር። ቁጣ ሲያሳብደው የሚስቱ ፊት ላይ ቡጢ ያሳርፋል።
ጎረቤቶቿ ከባሏ ቡጢ በየጊዜው ያድኗት ነበር።
"ለምን አትፈቺውም?" ይሏታል በዱላ የደቀቀ ሰውነቷን እያዩ
"ካልፈታሽው አንድ ቀን ይገ^ድልሻል" ይሏት ነበር።
ሚስት ሞታ ተገኘች። በማለዳ ፣ በገመድ የታነቀች ሴት ሬሳ ተገኘ፤ ፊቷ በቡጢ በልዞ ነበር።
* * *
ከመሞቷ በፊት ለባሏ ጓደኛ ስሞታ ትነግረው ነበር።
"ጓደኛህን ምከረው" ትለዋለች የባሏን ጓደኛ። የበለዘ ፊቷን እያሳየችው
"አንድ ቀን ይገድለኛል፣ ሳይገድለኝ በፊት አስቁመው" ትለው ነበር።
"ጓደኛህን ምከረው"
"ምን ማድረግ እችላለው"
"እኔን አይሰማኝም። አንተ ንገረው። ቁማር ተው በለው፣ አልኮል ቀንስ በለው"
የደፈረሰ አይኗን አስተውሎ አየው።
የሚስት ብሶት በየጊዜው የባል ጓደኛጋ ይመጣል። ሚስት ምክር ፍለጋ የባሏ ጓደኛውጋ ትሄዳለች። ስለ ባሏ በምሬት ትነግረዋለች።
ከንፈሩን እየነከሰ ያደምጣታል። አይኖቹ እንባ ያቀረሩ ይመስላል። አይኖቹ እንባ ቢያረግዙም፣ ሚስት ባሏን በማረረች ቁጥር የማይገባው ስውር ደስታ ይሰማዋል።
የገዛ ጓደኛውን ሚስቱ ስትሰድበው ፣ እያደመጠ መቀመጡ ደስታ ይሰጠው ነበር።
"አላስገደድኳትም። ራሷ በፈቃዷ ወደ እኔ መጣች እንጂ" ይላል።
ከዚያ ፥
"የጓደኛዬን ትዳር ከመፍረስ ለመታደግ እየሞከርኩ ነው" ይላል
"እሱ የማይገባውን ነገር ለምን ያገኛል?" ይላል።
የመጨረሻው ጥያቄ ፈርጠመ።
"ለምንድነው የማይገባውን መልካም ነገር ሁሉ የሚያገኘው?"
ጥያቄው በአእምሮው ውስጥ ስልጣን አገኘ። ብቻውን ሲሆን ይመላስበታል፤ ከሰዎችጋ ሲሆንም ያብሰለስለዋል።
* * *
ባል እስር ቤት ከገባ በኋላ ጓደኛው ቋሚ ጠያቂው ነው። ሁልጊዜ ይጠይቀዋል ፣ ያደምጠዋል ፥ ያፅናናዋል።
"ተስፋ አትቁረጥ"
"እኔ አልገደልኳትም"
"አውቃለሁ። ሚስትህን እንደማትገድላት አውቃለሁ"
"ማንም ሊያምነኝ አልፈልገም"
"ሰዎች የሚያውቁትን ነው የሚያምኑት"
ባል መራራ ሳቅ ሳቀ።
"ስለ እኔ የሚያውቁት ምንድነው? ሚስቱን የሚገድል አረመኔ እንደሆንኩ ነው?" ስሜት የለሽ ፈገግታ ፈገገ።
"ብዙ ስህተት ሰርቻለሁ ፤ ነገር ግን ይህን አላደረግኩትም"
ጓደኛው ዝም አለ።
"ሰዎች የሚያውቁት የሠራኋቸውን ስህተቶች ብቻ ነው" አለ የሟች ባል መሬት ላይ አንዳች ነገር እንደሚፈልግ አቀርቅሮ
ጓደኛው በሟች ባል ንግግር ስውር ደስታ ተሰማው። ባል ራሱን በጥፋተኛ ሰው ምስል ሲመለከት ደህንነቱ የተጠበቀ ይሆናል።
* * *
የፍርድ ቀን ደረሰ።
ሰዎች ተሰበሰቡ።
የባል የቀድሞ ጥቃቶቹ ተወሱ።
"በየቀኑ ይደበድባል፤ ከእሱ እጅ ብዙ ጊዜ ታድገናታል።"
ባል የጎረቤቱን ምስክርነት ሲሰማ አፉን መረረው።
"እገድልሻለሁ ብሎ ይዝትባታል"
የማያስተባብለው ምስክርነት ነው። ደጋግሞ "እገድልሻለሁ" ብሏታል።
"አልገደልኳትም" ባል አቃሰተ
በመጨረሻ ፍርዱ ተነበበ። ሃያ አምስት ዓመት ጽኑ እስራት።
ተከሳሽ ዝም አለ። ዓይኖቹ በእንባ ተሞሉ። ወደጓደኛው ዞሮ አየ። ጓደኛው አቀረቀረ።
"አልገደልኳትም"
ባል እስረኛ ሆኖ ወጣ።
* * *
"ፍትሕ ተሰጠ" ይላሉ የተሰበሰቡ ሰዎች።
"የሚገባው የሞት ፍርድ ነበር። ፍርዱ ኢፍትሐዊ ነው"
የባል ጓደኛ በልቡ ሳቀ።
ሰዎች የማያውቁትን ሁሉ እሱ ያውቃል።
በሞተች ለሊት አብሯት ነበር። የገደላት የባል ጓደኛ ነው።
የመጨረሻ እይታዋን ያስታውሰዋል። ሲያንቃት ፊቷ ላይ ያየውን ግራ መጋባት ያስታውሰዋል።
"ጓደኛህን ምከረው" ያለችውን ሴት አስታወሰ።
ስሞታ ለመንገር ቤቱ ትመላለስ ነበር። አንድ ቀን ስሞታዋን ሲሰማት ቆየ። ስታለቅስ አቀፋት። ትከሻው ላይ አስደገፋት። እንባዋን ጠረገው።
"አንተ ብቻ ነህ የምትረዳኝ"
"ይሄ ደደ^ብ ይቺን የመሰለች ሴት ያገኘው እንዴት ነው?" ብሎ አሰበ። እንባ የተራመደበትን ጉንጯን ሳማት። ዝም አለችው። ወደ ከንፈሯ ተንደረደረ ፥ ወደ ከንፈሩ ቸኮለች። አፍ ለአፍ ተሳሳሙ።
እየሳማት... እየሳመችው...
ሁሉም ነገር እንደ ህልም ነበር።...
... የነበራቸውን ተደጋጋሚ ፊትወት አሰበ።
"ጓደኛህን ምከረው" ብላው ነበር።
አሁን ምክር የምትጠይቀው ሴት የለችም። ሚስጥሩን የሚያውቅ ሰው የለም። አስወግዷታል!
... ወደ መኪናው እያዘገመ ፈገግ አለ።
"ሃያ አምስት ዓመት ፅኑ እስራት!... በቂ ነው"
የሰዎች ድምፅ ከኋላው ሰማ።
"እውነት ብትቀጥንም አትበጠስም" አሉ አንድ አዛውንት
በዝምታ ፈገግ አለ።
መኪናው ውስጥ ገባ።
የሚያስፈራው እውነት መበጠሱ አይደለም። አንድ ቀን መታወሱ እንጂ!
https://www.facebook.com/100074121486426/posts/pfbid09yZWB8KFefHZDVwfCkStWbEV2eN9zQWatcXX3WUtGwJkn2YWZ4o88bYirCvPEUZcl/?mibextid=CDWPTG
7 953
ወክ እንድናደርግ ከፈለግሽ «ወክ እናድርግ» ብቻ በይኝ። «ወክ እናድርግ እስኪ...በዛውም ባለፈው ያዬሁትን ጫማ እንገዛለን» ካልሽኝ ስለ ወኩ ማሰብ አልችልም። የጫማው ሱቅ ለመድረስ መንገዱን በሶምሶማ ነው የምሔደው።
«እስኪ ምሳ እንብላና ሀሪፍ ቡና ያለበት ቤት እወስድሀለሁ!» ካልሽኝ ምሳውን በትክክል አልመገብም። አንቺ ሁለቴ ሳትጎርሽ እኔ ጨርሼ እጄን እየታጠብኩ ነው።
በቃ አንድ ነገር አ'ዛችሁኝ ሁለተኛ ከጨመራችሁ የመጀመሪያው ትዕዛዝ ወደሁለተኛው ለመሔድ ስል የምሰራው አሰልቺ መንገድ ነው የሚመስለኝ። ይሔው ነው አመሌ!
ከልጅነቴ ጀምሮ «ቀዥቃዣው» በሚል ቅፅል ስም ነው ያደኩት። እናቴ «ስኳር ግዛና በዛውም አልማዝን ቡና ጠርተሀት ና!» ትለኛለች። አልማዝን በትክክል ስለመጥራት እያሰብኩ ጨው ገዝቼ እመለሳለሁ። «እንደው ካ'ሁንህ ልብህ የት እየሔደ ነው?» ብላ እሪሪ ትልብኛለች።
አባዬ ሀይስኩል ስገባ «ወጥረህ ተምረህ ዩንቨርስቲ እንድትገባ!» ካለኝ ቡኃላ በትክክል ተምሬ አላውቅም። ሀይስኩልን የጨረስኩት እንዲሁ ለረፍት የመጡ የዩንቨርስቲ ተማሪዎችን እየፈለኩ ስለ ካምፓስ ህይወት በመጠዬቅ ነበር።
ዩንቨርስቲ ከገባሁ ቡኃላ «ጥሩ ውጤት አምጥተህ ከተመረቅክ...ጥሩ ስራ ታገኛለህ!» አሉኝ። ትምህርቱን ለአቴንዳንስ ብቻ እየሔድኩ በጎን ስራ ጀመርኩ።
ይሔው ነው የኔ ታሪክ...በረጂሙ መንገድ ወደ መድረሻው ለመሔድ የሚደረግ ጥረት አይገባኝም። መድረሻው ከታወቀ ተንደርድሬ ልጨብጠው ነው የምሻው።
ይሔ ሁሉ ሀሳብ ውስጥ ያስገባኝ ቀን ላይ የተፈጠረው ነገር ነው። መዓዚን «የልደቴ ዋዜማ ቆንጆ የፍቅር ሰዓት እናሳልፍ?» ብዬ አቀፍኳት። እምቢ ማለት እኮ አንድ ነገር ነው። እሷ ምን ብትለኝ ጥሩ ነው?
«እሺ! ፍቅር ሰርተን እንደጨረስን ደግሞ ፊልም እናያለን!»
በአስራ አምስት ሰከንድ ጉዳዩን ፈፅሜው ቁጭ አልኩ።
«በቃ ፊልሙን ሌላ ጊዜ እናያለን።» ብላኝ አኩርፋ ሔደች።
«ቶሎ ለመጨረሴ አንቺ ነሽ ተጠያቂዋ!!» ብዬ አልከራከር ነገር ወጥታ ስትሔድ እያዬሁ ዝም አልኳት።
ከሔደች ቡኃላ ሁሉንም ነገር አሰብኩበት! አውጥቼ አውርጄ ብንለያይ ለሁለታችንም ጥሩ እንደሆነ ተሰማኝ። አንድ ነገር ካሰብኩ ደግሞ ሳላደርገው እንቅልፍ ስለማይዘኝ ሌሊት ስድስት ሰዓት ላይ ደወልኩላት።
«ምን ተፈጥሮ ነው ሚናዬ?» አለችኝ።
ለካ ቅፅል ስም ተሰጣጥተናል...ደግሞ ተመሳሳይ ነው።
«ደህና አመሸሽ ሚናዬ?»
«ደህና ነኝ! ምነው በዚህ ሰዓት?»
«እንለያይ!»
«ምንድን ነው የምታወራው?»
«እኔና አንቺ አንድ ላይ መሆን አንችልም። በጣም የተለያዬን ሰዎች ነን!»
«ተኛ እና እረፍት ውሰድ እስኪ ነገ ቁጭ ብለን እናወራበታለን።»
ስልኩን ዘጋችው። እኔ ተቃጠልኩ። «ተኛ» ብትለኝ እሺ...«ተኛ እና ነገ እናወራለን» ብላ እንቅልፌን ነሳችኝ። እሷን ስለማውራት እያሰብኩ መተኛት አቅቶኝ ስገላበጥ ነጋ።
የቀጠረችኝ ለምሳ ሰዓት ነው። ከጧት ጀምሮ ያሉኝን ቀጠሮች ሰርዤ ቤት ተቀመጥኩ። ፊልም ላይ ብዬ ከከፈትኩት ቡኃላ ከገባሁበት ሀሳብ ስባንን ምን እንደተፈጠረ ሳይገባኝ ሰላሳ ደቂቃ አልፏል። ትርፉ ድካም ነው ብዬ ዘጋሁት። ሌላም ነገር ላደርግ ሞከርኩ...ይሁን እንጂ ምሳ ሰዓት እስኪደርስ ምንም ነገር ማድረግ አቃተኝ። የቤቱን እቃ ሳነሳ ስጥል ውዬ አንድ ሰዓት ሲቀረው ሒጄ የተቀጣጠርንበት ካፌ ተቀመጥኩ። ስጠብቅ...ስጠብቅ...ስጠብቅ ኑሬ...ልክ በቀጠሯችን ሰዓት መጣች!
«ምን ነበር ያልከኝ?» አለች እንደመጣች አይን አይኔን እያዬች!
ፊትለፊት ሲሆን እንደሚከብደኝ አውቃ እንደጠራችኝ ገባኝ። ቢሆንም ከወሰንኩ ቡኃላ ብፈልግም መመለስ እንደማልችል አውቀዋለሁ።
«ይሔውልሽ ሚናዬ...እኔ እና አንቺ እንደ ግለሰብ ጥሩ ሰዎች ነን! ስንጣመር ግን ጥሩ አይደለንም! የምለው ገብቶሻላ?...»
ራሷን በአወንታ ነቀነቀች።
«ያሳለፍነው ጊዜ ለኔም ትርጉም ሳይሰጠኝ ቀርቶ አይደለም። ሁሌም እወድሻለሁ። ግን የሚሆን አይመስለኝም!»
«እሺ!»
«የምትይው ነገር የለም?»
«የለም።»
«እኔ ጋ ያሉትን እቃዎች እልክልሻለሁ።»
«እሺ።»
«እርግጠኛ ነሽ የምትይው ነገር የለም?»
«አዎ!»
ከተለያዬን ቡኃላ ንግግሯ ሲያቃጭልብኝ ዋለ!
«እሺ»...«የለም»...«እሺ»..«አዎ!» ላሳለፍነው ጊዜ ያላት ቦታ ይሔን ያህል ነው? ያሳለፍነው ጊዜ የሁለት ደቂቃ ለቅሶ ቢያንስበት እንጂ ይበዛበታል? ነው ወይስ ከኔ ጋር ለመለያዬት ቀን ስትጠብቅ ነበረ?
ልደቴ እንደሆነ ራሱ ትዝ ያለኝ ታላቅ እህቴ ደውላ ቤቷ ስትጠራኝ ነው። ሰርፕራይዝ ልታደርገኝ እንዳሰበች ገብቶኛል! ዝምብዬ እንዳልባነንኩ ሁኜ የራት ግብዣውን ተቀበልኩ። ስምንት ፎቅ ወደላይ ወጥቼ በሯ ላይ እንደደረስኩ ግን የማውቀውን ሰው ድምፅ ሰማሁ! አዎ...ራሷ መዓዚ ነበረች...ብሮጥ ብሮጥ የማላመልጥበት የሷ አለም ውስጥ ታጥሬ የምኖር መሰለኝ። ከእህቴ ጋር እያወራች ነው!
«ሲጀመር አንቺ እንለያይ ሲልሽ እንዴት ዝም ብለሽ እሽ ትይዋለሽ?» ትላለች እህቴ።
«ታውቂው የለ እሱን? አንዴ ከወሰነ ቡኃላ ሀሳቡን መቀዬር ስለማይችል እንለያይና እንዳ'ዲስ እንጀምራለን ብዬኮ ነው።»
ይሔ ንግግር ከመዓዚ አፍ መውጣቱን ማመን አቃተኝ። ይሔን ያህል ታውቀኛለች?
«ጉድ እኮ ነው! ለመሆኑ ምን ሆንኩ ብሎ ነው እንለያይ ያለሽ?»
«የተለያዬን ሰዎች ነን ነው የሚለው። እኔ ግን ሲመስለኝ በሆነ ነገር ነርቩን ነክቼዋለሁ።»
«ምን አድርገሽው ነው?»
«ትላንትና ለሰርፕራይዝ የሚሆኑ ነገሮችን እንገዛዛ ብለሽኝ ልወጣ ስል ፍቅር ካልሰራን ብሎ አስቸገረኝ። ቶሎ እንዲለቀኝ ስለፈለኩ 'ፍቅር እንስራና ፊልም እናያለን' አልኩት። ያው እሱን ደግሞ ሁለት ነገር ካዘሽው ታውቂዋለሽ...ጉዳዩን በስድስት ሰከንድ ጨርሶት ቁጭ አለ» ሳቀች! ሳቁብኝ።
ኧረ አስራ አምስት ሰከንድ ነው! ምን አይነቷ ውሸታም ናት!
«ብቻ እንደዛ በማድረጌ እኔን ጥፋተኛ ማድረግ ብቻ ሳይሆን አትረዳኝም ወደሚል አስተሳሰብ አምጥቶታል መሰለኝ። ምን ያህል እንደምወደው እና ምን ያህል እንደማውቀው እሱ ራሱ የገባው አይመስለኝም። የኔ ቀዝቃዣ!» አለችና አሁንም ሳቀች!
«በቃ ተይ አታልቅሽ እንጂ ውዴ? እኔ አስታርቃችኋለሁ!»
እየሳቀች መስሎኝ?
እንዲህ ነዋ ስረዳት የኖርኩት?
ቆይ ግን አትረዳኝም እያልኩ ከማልቀስ እረፍት ወስጄ ትንሽ እንኳን ልረዳት ሞክሬ አውቃለሁ?
እሷስ የራሷ አስተዳደግ...የራሷ አመል የለባትም እንዴ?
በየትኛው ትካሻዋ ነው የፍቅራችንን መስቀል ብቻዋን እንድትሸከም የፈረድኩባት?
«ይቅርታ የሚያደርግልኝ ይመስልሻል?»
«ኧረ ራሴ ነኝ ይቅርታ የምጠይቅሽ!» አልኩ ራሴ ብቻ በሚሰማ ድምፀት።
ለሷ ያለኝ ስሜት እንዳ'ዲስ ሲወለድ ታወቀኝ። ከሷ ሌላ ሴት አልፈልግም። እንዲያውም ከዛሬ ጀምሮ አብረን መኖር መጀመር አለብን። የወጣሁትን ደረጃ ተመልሼ ወረድኩት.....የት ነው ጥሩ ቀለበት የማገኘው?
Mikiy Azmeraw Facebook page
7 953
-ቤብ
-እ?
- እ ነው ያልከው? እኔን እ? ምን ታደርግ ልጅነቴን ቀርጥፈህ በልተህ ጥጋብ ነፍቶሀል... እኔን እ?!
-ይቅርታ እሺ... ወዬ የኔ ጨረቃ... (አቋም)
-ሂድና ብርክቲን የኔ ጨረቃ በላት
-ማናት ብርክቲ?
-እኔ ልጠይቅህ እንጂ... ብሩክ ብለህ ብለህ ሴቭ ያደረካት
-ቡራ ጉልጥምት? ወንድምሽ እኮ ነው?
-ይሁና! የኔ ወንድም ብርክቲ ለመሆን ምን ያንሰዋል ወይስ ዘረ ተባዕት እያልከኝ ነው? ዘርሽ ፍሌክሰብል አይደለም ነው?
-ኧረ እኔ አልወጣኝም... ከፈለገ ለምን በቅሎ አይሆንም... ምን አገባኝ
-ለማኛውም የደወልኩት ጊዜ እየሰጠኸኝ አይደለም... አስብበት ለማለት ነው
-እንዴ? ከነጋ ሰባቴ ተደዋወልን
-መች ኢሜል ላክ... ሲሆን ብራና ላይ የፍቅር ደብዳቤ ፅፈህ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ መላክ ነበረብህ... አንተ ግን እራት በላሽ ወይ እንኳን አትለኝም
-አብረን እኮ ነው አሁን የበላነው... በዛ ላይ አጠገቤ ሆነሽ ለምንድነው በስልክ የምናወራው... ልዘጋው ነው
-ዝጋውና የማህፀንህን በር ነው የምዘጋልህ... ስልክ ሮማንቲክ ነው አንት እንጉልፋቶ... ስኳሩን አቀብለኝ አሁን
-ይሄው ስኳር
-ሄሎ... አንተ... ከማን ጋር ነው የምታወራው? ማናት ስኳር?
-አየሽ አንቺ ደህና የተላገ እንጨት ደግመሽ መላግ ከጀመርሽ ለአንገቴም ስለማትመለሽ...
-በቃ እሺ ይቅርታ ቤብ... ስለምወድህ እኮ ነው እኔ ሌላ ሴት የመሰለችኝ... ዛሬ ማሚ ጋር የማድረው ራይድ ጥራልኝ
-የት ነው
-ሽንቁሩ በልና...
-ሽንቁሩ? መጠርጠር ነበረብኝ... ሌጎዮንን ነው ወጥሬ ስጀነጅን የከረምኩት... ወይኔ
-ኧረ ቤብ ለመፍረድ አትቸኩል... ሽንቁሩ እኮ ለአባላዘሮቹ ነው... ሰይጣኑን ስውሯ ነው የምከታተለው... ባይዜ አንተም ብትታይ ጥሩ ነው... አሁን የያዘኝ ሰይጣን ከእኔ በፊት ሜድስን ተማሪ ነበር ተከራይቶ የሚኖረው...
-እታያለው የኔ ፍቅር... እስከዛ ቢላዋን ብታስቀምጫት... ስሞትልሽ የቲክቫ ዜና አታድርጊኝ የኔ ቀንበጥ... ለአያቴ አንድ ነኝ
7 953
(ከዕድሜ እና ከዩዜን ቦልት ማን ይፈጥናል ወገን?)
ልደቴን ያለሞቴ ማሰብ አይሆንልኝም።
የጨመርኩትን ዕድሜ እንጂ ለሞት የቀረኝን አላውቀውምና።
አመት ባለፈ ቁጥር እደነቃለሁ። በየአመቱ እንደመምሞት ይሰማኛል። አመቱ ሲያልቅ እና ስኖር ሳይ "አሁንም አለህ" ብዬ በራሴ እስቃለሁ።
"አንተ ከእናቴ ሆድ አውጠተኸኛልና" እንዳለ መዝሙረኛው።
(መዝ 22 )
እንግዲህ የመኖሬን ጥቅም አስልቼው አላውቅም። እግዚአብሔር ቢወደኝ ነው የፈጠረኝ።
ሳቅንም መከራንም እስከአፍነጫቸው አውቃቸዋለሁ።
በራሴ ሀዘንና መከራ ሰዎችን አላቅሱኝ ብዬ አላውቅም። የራሴ እድር የራሴ ድንኳን አለኝ ገብቼ እቀውጠዋለሁ።
ጥቂት ያለኝን ደስታና ማግኘቴንም ሰዎችን ለማብሸቅ ማዋል አልፈልግም።
(ያጋሩት ደስታ አይሰነብትም)
ቀጣዩ አመት ህይወት ያበቃ ይሆን ወይስ ይቀጥል እንጃ?
ብቻ እስካሁን
እንደሀጠያቴ አልከፈለኝምና ጠብቆ አኑሮኛልና ከክፉ ነገር ሸሽጎኛልና ጊዜ ጨምሮልኛልና
የድንግል ማርያም ልጅ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ የተመሰገነ ይሁን! አሜን!
7 953
“እነሱ የሚያምኑትን ሳትነቅፍ የነሱ ግልባጭ ስትሆን ብቻ ጥበበኛ እና ጥሩ ሰው ነው ይላሉ። ሰዎች እራሳቸውን መሆን ከሚፈልጉ ብሎም እጣ ፈንታቸውን መቆጣጠር ከሚችሉ ሰዎች ጋር ፈጽሞ አይስማሙም። ምክንያቱም የፈጠርከው መረጋጋት እና ማስተዋል አደጋ ላይ ይጥላቸዋል። የማሰብ መብቱን የተገፈፈ ሰው መሆን በማኀበረሰቡ ያሸልማል!።”
―Jean Paul Sartre
7 953
ባለትዳር ሴት አባለግኩ፤ "አወጣሻለሁ" አልኳት። እንደተናገርኩት አደረግኩ።
እንዳሸነፍኳት ተሰምቶኝ ነበር። ከቤቴ ወጥታ በሩን ስትዘጋ የድሉ ድምፅ አብሮ ጠፋ።
ለጥቂት ቆሜ ቀረሁ። በቤቱ ውስጥ የሽቶ መዓዛ ትታ ሄዳለች።
አልጋው ላይ የተጨማደደውን ሸሚዜን አየሁ፤ ወለሉ ላይ የፀጉሯ አንድ ዘለላ ወድቋል።
አሸንፌያታለሁ።
ድሉ ደስ ሊያሰኝ ይገባ ነበር። ነገር ግን ውስጤ ባዶ ሆነ
መስታወቱ ፊት ቆምኩ።
መስታወቱን እያየሁ አባቴን አሰብኩ።
አባቴ እናቴ ከከዳችው በኋላ ሌላ ሰው ሆነ፤ አዘውትሮ መስታወት ይመለከት ጀመረ።
እናቴ ክፉ ናት!... ከአባቴ ጓደኛጋ አንሶላ በመጋፈፍ አባቴን ሰበረችው!
... ቤታችን በአንድ ቀን አልፈረሰም። በቀስታ ዘመመ፣ በዝግታ ወደቀ። ቤታችን ፈረሰ፣ የአባቴ አለም ተገንዶሶ ወደቀ።
መጀመሪያ የአባቴ ሳቅ ጠፋ። ከዚያ ድምፁ ሰለለ ፣ መናገር ጠላ። የፊቱ መስመሮች በዙ ፣ ከአይኑ በታች ጠቆረ ፣ ጉንጩ ጎረጎደ።ከንፈሩ ተሰነጠቀ።
እናቴ አባቴን በቁም ገደለችው።
ተጫዋችነቱ ከስሞ ሃዘንተኛ ሆነ ፣ አረቄና ሲጃራ መሸሸጊያው ሆኑ።
አንድ ምሽት በመስታወት ፊት ቆሞ አየሁት። ፀጉሩን እየዳሰሰ ነበር። ፊቱን ከግራ ወደ ቀኝ ይነቀንቃል። ዓይኖቹን ስር ሃዘን ተፅፏል።
"አባ?"
ደነገጠ። የገዛ ልጁ ድምጽ አስደነገጠው። ፈገግ ለማለት ሞከረ። ፈገግታወሰ ሙት ነው።
መስታወት ፊት ሲቆም በድብቅ ማየት ጀመርኩ። መስታወት ፊት ቆሞ "ከእኔ ምን አጣች? ምን ጎደለብኝ?" እያለ ራሱን ይጠይቃል።
እናቴን አልጠላኋትም። እናቴን አለመጥላቴ ይበልጥ አስከፊ ነበር።
እናቴን እወዳታለሁ ፤ እየወደድኳት አፍርባታለሁ።
ሰዎች በሹክሹክታ ያሟታል። "አመንዝራ" ይሏታል። ለአባቴ ከንፈር ይመጡለታል።
ሰዎች ሲያዩኝ "ምናልባት ከሌላ ወንድ ይሆናል የወለደችው" ይሉኛል። "ወፍ ዘራሽ ዲቃላ" ይሉኛል።
የእናቴ የሃጢያት ቀንበር ነፍሴን አጉብጧል።
ለራሴ ቃል ገባሁ። "እንደ አባቴ አልሆንም" አልኩ። ሴት ልጅ በገዛ ፍቃዷ እንድትተወኝ ላለመፍቀድ ማልኩ።
በሌላ ወንድ የምተካ መሆን የለብኝም። ራሴን በማንም እጅ አላስቀምጥም።
ከባለትዳር ሴት ጋር ተኛሁ። ሆነ ብዬ አባለግኳት።
ለመጀመሪያ ጊዜ ያየኋት ቀን ያስተዋልኩት ውበቷን አልነበረም። ቀለበቷን እንጂ!
የግራ እጇን ስታንቀሳቅስ የፀሐይ ብርሃን በቀለበቷ ላይ ይጫወት ነበር። ቀለበቷን ትነካካለች።
ሳልጠይቃት “ባለትዳር ነኝ” አለችኝ። ባል ስላላት ብቻ ልተኛት ፈለግኩ። ተኝቼ ድል ላደርጋት...
"አወጣሻለሁ" አልኳት
"ባል አለኝ" አለች
“አውቃለሁ”
ዓይኖቿ ጠበቡ።
"እንዲህ የምታየኝ ለምንድነው?"
"ራቁትሽን ምን እንደምትመስዪ እያሰብኩ"
ፊቷ ላይ የነበረውን ቁጣ አልረሳውም። ተደፈርኩኝ አለች። ተናቅኩኝ አለች።
እናቴ አባቴ ላይ ስትወሰልት ባለትዳር ነበረች።
የቀለበት ብርሃን ቤትን ከመፍረስ የሚያድን ቢሆን፣ የእኛ ቤት አይፈርስም ነበር።
“ፈተና ነህ” አለችኝ።
... ተቀራረብን። ምክንያት ፈጥራ ወደ እኔ መጣች፤ ሰበብ ፈጥሬ በሬን ከፈትኩላት።
አልጋዬ ላይ እርቃኗን ተኝታ የአባቴን ስብራት አሰብኩ፤ የአባቴን ውርደት እያሰብኩ ጋለብኳት።
ትላንት ከባሏ ሰርቄ ተኛኋት።
ዛሬም ደወልኩላት
“ነይ” አልኳት። እየጠራኋት ሳይሆን እያዘዝኳት ነበር።
“ለምን?”
ምን ልበላት ነበር?
እንደገና ምረጪኝ?
የምተው እንዳልሆንኩ አሳዪኝ?
አባቴን እንዳልሆንኩ አረጋግጪልኝ?
“ለወሲብ።” አልኳት
የማደርገውን እያሰብኩ ራሴን ጠላሁ። ድምጼ ለእርሷ የጌታ ሊመስላት ይችላል። እውነቱ ግን እንዳትመጣ የሚፈራ ሰው ድምፅ ነበር።
“እሺ” አለች።
እንድትመጣ የፈለግሁት ሰውነቷን ስለፈለግሁ ብቻ አልነበረም። ዳግመኛ እንድትመርጠኝ ፈልጌ ነበር። የምርጫዋ ባለቤት እኔ ነኝ ብዬ ለራሴ ማሳመን ፈልጌ ነበር።
ሠላሳ ደቂቃ አለፈ።
መጣች።
ባሏን አሰብኩ። በባሏ ውስጥ አባቴን አየሁት። ሚስቱን እየጠበቀ ያለው ሰው ታየኝ።
አባቴም እንደዚያ ነበር?
እናቴን ለመቅጣት እየሞከርኩ ነበር። የእናቴን ዓይነት ሴቶች በማሸነፍ ከአባቴ የተሻለ ሰው እሆናለሁ ብዬ አምኜ ነበር።
...ከአባቴ የተለየ አልሆንኩም።
አባቴ በሌላ ወንድ ተተክቶ ራሱን አጣ። እኔ ደግሞ ሌላ ወንድ የአባቴን ውድቀት እንዲወድቅ አደረግኹ።
...ወደ ውስጥ ገባች።
አባቴ ታወሰኝ፤ በመስታወት ፊት ቆሞ ራሱን የሚጠይቀው አባቴ።
ምን አጎደልኩባት? የሚለው አባቴ
ከአባቴ ምን ተሻልኩ?
"ተመለሺ" አልኳት። ድንገት አይኗ እንባ አረገዙ
"ምን አጠፋሁ?"
"ተመለሺ!"
አለቀሰች።
በሩን ዘጋሁባት።
ሕይወቴን ሙሉ ካለፈ ጦርነት ጋር እየተዋጋሁ ነበር።
ያንን ጦርነት ለማሸነፍ ስሞክር፣ ሌላ ሰው እንደ አባቴ እንዲሰበር አደረግኩ።
ምንጭ ፤ ተስፋአብ ተሾመ የፌስ ቡክ
7 953
+3
ኮርሶችን በአጭር ጊዜ ለመጨረስ እንደዚህ ባለ መልኩ የተዘጋጁ Short ኖቶች ለሁሉም ኮርስ !
አሁንም አልረፈደም ! ምዝገባው አልተጠናቀቀም ... ቶሎ ተመዝግበው ጥናቶን ያጧጡፉ !!!
📢 ለመመዝገብ 250 ብር በ Telebirr እና CBE ክፍያውን ከፈፀማችሁ በኋላ ክፍያውን መፈፀማችሁን ማረጋገጫ Screenshot በ @kelemesupport ይላኩ !
Tlebirr : 0991182353 (Danial )
CBE : 1000286598076 ( Daniel A. )
🤗 በቡድን ለምትመጡ የ 50% ቅናሽ ! ( አንድ ሰው 3 ሰዎችን ካስመዘገበ የ 50% ቅናሽ ያለው ሲሆን ከዛ በላይ ከሆነ እስከ 25% ድረስ !!! )
ሁሌ እንደምንለው ከናንተ የምንፈልገው ጥረታችሁን - ለሥኬታችሁ ነው !
7 953
ኮርሶችን በአጭር ጊዜ ለመጨረስ እንደዚህ ባለ መልኩ የተዘጋጁ Short ኖቶች ለሁሉም ኮርስ !
አሁንም አልረፈደም ! ምዝገባው አልተጠናቀቀም ... ቶሎ ተመዝግበው ጥናቶን ያጧጡፉ !!!
📢 ለመመዝገብ 250 ብር በ Telebirr እና CBE ክፍያውን ከፈፀማችሁ በኋላ ክፍያውን መፈፀማችሁን ማረጋገጫ Screenshot በ @kelemesupport ይላኩ !
Tlebirr : 0991182353 (Danial )
CBE : 1000286598076 ( Daniel A. )
🤗 በቡድን ለምትመጡ የ 50% ቅናሽ ! ( አንድ ሰው 3 ሰዎችን ካስመዘገበ የ 50% ቅናሽ ያለው ሲሆን ከዛ በላይ ከሆነ እስከ 25% ድረስ !!! )
ሁሌ እንደምንለው ከናንተ የምንፈልገው ጥረታችሁን - ለሥኬታችሁ ነው !
7 953
ስንቶቻችንነን #በትላንትናው ጠባሳችን ፍቅር እየገፋን ያለነው ? ስንቶቻችን ነን በትላንትናው ህይወታችን ምክንያት በፍርሀት ሰው ማቅረብ ማመን የተውነው??
ሰንቶቻችን ነን መልካም ሰዎች እንዳሉ ማመን ያቃተን በትላንትናችን ምክንያት ? ስንቶቻችንነን እሚወዱን እንዳሉ መቀበል ያልቻልነው ?
ሁሉም ነገር ልክ አለው እራሳቹን አክሙ ለመዳን አንድ እርምጃ ተራመዱ<<<
ላለፈው ክረምት ቤት አይሰራም ለሚመጣው እንጂ.......
✍️Gosaye
📌ማጋራት አይዘንጋ
7 953
እነሱ : ለምንድነው ሁልጊዜ የምታገኛት ?
እኔ : ምክንያቱም ለእኔ ጊዜ ለመስጠት ብላ ብዙ ሰው ርቃለች ። ብቻዋን ልተዋት አልችልም።
የ ተ ቀ ደ ደ ው ማስታወሻ
©ሶፊ
7 953
ምዝገባ ተጀመረ !!!
ለ Exit Exam ተፈታኞች
🔷Accounting & Finance
🔷Computer Science
🔷Information Technology
🔷Economics
🔷Management
🔷Nursing
በእናነተ ተደጋጋሚ ጥያቄ መሠረት ከላይ የተጠቀሱትን ዲፓርትመንቶች ኦንላይን/ Private ጥናት ጀምረናል ።
💥 በዚህ የኦንላይን ጥናት ምን ምን ያገኙበታል ?🏷 በአጭር ጊዜ ፈተናውን በሙሉ የራስ መተማመን ያለምንም ስጋት 💯 በ 💯 የሚሰሩበትን ስልቶችና ቴክኒኮችን 🏷 ለማዳረስ ወራት የሚፈጅባችሁን ብዛት ያላቸውን ኮርሶች ከእኛ ጋር በፍጥነት፣ በትኩረት እና በቅልጥፍና ከእኛ ጋር ሆናችሁ በተጠና መልኩ 🏷 በግልፅና በተብራራ መልኩ በየጊዜው የሚዘጋጁ አዳዲስ ጥያቄዎችን 💥Guys ይሄ ከ VVIP ም በላይ ነው! እንደ ሌሎች ብዙ ብር ጠይቀን ያልሆነና ጥራት የሌለውን ነገር አናቀርብም !!! ☝️☝️☝️ ከላይ የተቀሱትንና መሰል እገዛዎችን ለወራት ለናንተ ለማድረስ ስንዘጋጅ ባለው የ " Rekik Success Online Study " ያገኛሉ ! 📢 ለመመዝገብ 250 ብር በ Telebirr እና CBE ክፍያውን ከፈፀማችሁ በኋላ ክፍያውን መፈፀማችሁን ማረጋገጫ Screenshot በ @kelemesupport ይላኩ ! Tlebirr : 0991182353 CBE : 1000286598076 🤗 በቡድን ለምትመጡ የ 50% ቅናሽ ! ( አንድ ሰው 3 ሰዎችን ካስመዘገበ የ 50% ቅናሽ ያለው ሲሆን ከዛ በላይ ከሆነ እስከ 25% ድረስ !!! ) ሁሌ እንደምንለው ከናንተ የምንፈልገው ጥረታችሁን - ለሥኬታችሁ ነው ! https://t.me/kelemeakadami
7 953
መሄዷ ላይቀር እኔ እንዲህ መታገሌ
ላስቀራት ባልችል እንኳን ላዘገያት ነበር ሀሳቤ
ደቂቃም እድሜ ነው እንዲሉ
ጥቂት አብሪያት መሰንበት ብችል ብዬ....
💔
✍️Gosaye
📌ማጋራት አይዘንጋ
7 953
“ምነው አምና በሞትኩ፥ እንዲያ እንዳማረብኝ!?”
ዝምታ ይረብሸኛል።
ለዚያም ነው፥ መንገድ ስሔድ መጽሐፍ ይዤ የምዞረው፣ ሁሌም ጆሮዬ ውስጥ ‘ኤርፎን’ የምወትፈው፣ ልተኛ ስል፥ ያለችውን ፀጥታ እንኳን ላለማስተናገድ፥ የኾነ ነገር ከፍቼ ነው የምተኛው ...
በዝምታ ውስጥ ከመኾን፥ ዝም ብሎ ከሚቀደደው ቱሪናፋው ከቤ ጋር ብውል እመርጣለሁ። ዝምታ ሽሽት የማልደውልበት፣ የማላነበው፣ የማልሰማው ዜና የለም።
ዝምታ እፈራለሁ!
መንገድ ስሔድ… ስቀመጥ!
የማነበው መጽሐፍ ካልያዝኩ፣ ስራመድ የምሰማበት ኤርፎን ካልወተፍኩ…. ፖሊሶች አቻኩለው ከቤት አስወጥተውኝ ነው የሚሆነው!
ዝምታ እፈራለሁ!
አስታውሳለሁ፤ 12ኛ ክፍል ነበርኩ። ሙዚቃ ከፍቼ እያጠናሁ፥ የአጎቴን የለቅሶ ሳግ ሰምቼ ደንግጬ “ምነው አመመህ?” አልኩት፤ እሱ ሙዚቃ እየተጫወተበት ያለውን ‘ቴፕ’ ዐየት አድርጎ፥ ወደ ጣርያው አፍጥጦ፣ እምባው ቁልቁል ወረደ!
አሞት መስሎኝ ነበር… ከዚህ በፊት ሲያመው ያቃስታል፤ ሲብስበትም ማስታገሻ ይውጣል እንጂ አያለቅስም ነበር።
አጎቴ ጥቁር ነው፤ ፊቱ ክስክስ ያለ… ሲያወራ ግን እንደሚታየው ኮስተር ያለ ማንነት እንደሌለው የሚያስታውቅበት፥ ቁጥብ፣ ደስ የሚል ሰው ነው።
ልጅ እያለሁ የገዛልኝን ቼኮሌት እና ብስኩት፥ ታሞ አልጋ ሲይዝ ሲጋራ እያመጣሁ ክሼዋለሁ ።
ቤቢ፥ “ያቺን ነገር አትገዛልኝም?” ይላል፤ እገዛለታለሁ። ሲጋራውን በእጁ እያገላበጠ ካያት በኃላ፥ አፉ ላይ እንዳለ እለኩሰለታለሁ።
ዐብሮን ማንም በሌለበት ጊዜ ሁሉ፥ “አትብላ” የተባለውን፣ “አትንካ” የተባለውን ሁሉ እሰጠው ነበር።
እያጠናሁ ስለነበረ፣ ሲያለቅስ አይቼው ስለማላውቅ፣ ደንግጬ ስለነበረ፣… ዘፋኟን ባውቃትም ግጥሙን አላጤንኩትም ነበር፤ ዘፈኑ እንደረበሸው ሲገባኝ፥ ወተት እንደገነፈለበት ሰው፥ ስበር ሔጄ የቴፑን ሶኬት ነቀልኩለት ።
የማባብልበት መንገድ ስለጠፋኝ፥ “ምግብ ላምጣልህ?”፤ “ውሃ ላምጣ” አልኩት። ጣርያ ጣርያ ዕያየ ዝም ሲለኝ ከፊቱ ዞር አልኩለት።
በዚያው ሰሞን፣ ሲብስበት ሐኪም-ቤት ደግመው አስገቡት፤ አልቆየም፤ ሞተ!
የኾነ ቀን ...
አባቴ፥ ስለወንድሙ ቸርነት፣ ዘናጭነት፣ ስፖርተኛነት፣ ሰው ወዳድነት፣ አለኝታነት፣ ስለጓደኞቹ ብዛት፣… ሲተርክልኝ ያስለቀሰቺው ዘፋኝ፥ የዝና ነጋሽ ትዝ አለቺኝ።
ያስለቀሰውን የዘፈን ካሴት ከፈትኩት፤ ሆዱን ያባባው “ገዳሙ” ዘፈን ጋ ደረስኩ።
እስክስታ ሚያስመታ ‘ሪትም’ ያለው ዘፈን ነው
“.........አሆዬ እኔ ላንተ ብዬ፣ መጣሁኝ ጠቅልዬ
አዬዬ፥ እኔ ላንቺ ብዬ፥ መጣሁኝ ጠቅልዬ
“እሀሀ ገዳሙ፥ አሀሀ ገዳሙ
እሀሀ ገዳሙ፥ አሀሀ ገዳሙ
“አላስኬድ፣ አላስኬድ አለኝ፥ ይሄ ጫማ
እኔም ልበቢስ ነኝ፥ ቢመክሩኝ አልሰማ
“እሾህ ብቻ ኾኖ፥ እግሬን ብዳብሰው
እንዴት መራመጃ፥ መሔጃ ያጣል ሰው?
“ኧረግ እናናዬ፣ አረግ እናናዬ
ኧረግ እናናዬ፣ አረግ እናናዬ
“አሄ አሄ አሄ አሄ
አሄ ኡሁ
“ይወዘውዘኛል፥ ይወዝውዝ አባቱ
እህል አሸክሞኝ አርጎኝ ጎረቤቱ
አሞኝ፣ አሞኝ ውሎ፥ አሞኝ ሊያድር ነወይ?
እህል ሰርቶ መብላት፥ ጤና ላይሆን ነወይ?
“ምነው አምና በሞትኩ፥ እንዲያ እንዳማረብኝ
መለየት በሽታ፥ እንዲ ሳይጠናብኝ
“ያመኝ የነበረው፥ አያመኝም ተውኩት
ያስታማሚ ነገር ሲቸግር አየሁት
“እህህህ ገዳሙ
ጠይሙ፣ ጠይሙ..........”
ይላል
ከዛ ቀን በኋላ፥ ተረጋግቼ ሥራዬ ብዬ ሰምቼው ዐላውቅም፤ ነገር ግን ሁሉም ስንኞች ልቤ ውስጥ በአግባቡ ከመሰነድ አላዳነኝም
ድንገት ከተከፈተ፥ የሚረብሸኝ ዘፈን ኾነ ....
“ድል ስቀዳጅ፣ ደስ ብሎኝ ስጠጣ፣ እንዳማረብኝ ግደለኝ አስታማሚ ሳታሳየኝ!” ማለት ጀመርኩ። “ያደረ የዋለ በሽታ አትሰጠኝ” እለው ጀመር
“ይህ ዘፈን ምን ያህል ይረብሽሃል?” ስባል “ከዝምታ በላይ!” ማለት ጀመርኩ።
የግጥሙ ኀይል ነው፥ ወይስ የአጎቴ ኹኔታ ሕይወትን እንድፈራት ያደረገኝ?
ሕይወትን ምን ያህል ባካብዳት ነው፥ እያሸነፍኩ እንኳን “ምነው አምና በሞትኩ፥ እንዲያ እንዳማረብኝ…” የምትል ስንኝ የምታሳድደኝ?
ፈሪ ሰው እንዲህ ነው፤
ከ ጠ’መንጃ በላይ ፥ ቃል ያሳድደዋል!
© Adhanom Mitiku
7 953
Repost from Jafer Books 📚
የመጽሐፍ ፊርማ ስነስርአት
ደራሲ እሱባለው አበራ በቅርቡ ያሳተመው " ጠይም ትውስታዎች " የተሰኘው መጽሐፉን ለገሃር በሚገኘው አዲሱና ዘመናዊው መደብር በመገኘት ከተደራሲያን ጋር የትውውቅና የፊርማ ስነስርአት ሊያደርግ የፊታችን ቅዳሜ ሐምሌ 18 ተዘጋጅቷል ::
7 953
“ቀኖቹን እቆጥራለሁ ብለህ ታስባለህ? አንድ ቀን ብቻ ነው የቀረው፣ ሁልጊዜም እንደገና ይጀምራል፤ ጎህ ሲቀድ የተሰጠን ሲሆን ፀሐይ ስትጠልቅ ከእኛ ይወሰድብናል።”
— ዣን-ፖል ሳርትሬ
📌ማጋራት አይዘንጋ
7 953
በረንዳ
(በእውቀቱ ስዩም)
ባለፈው ከያሬድ ሹመቴ እና ከምኡዝ ጋራ የሆነ ምግብ ቤት በረንዳ ላይ ቁጭ ብለን ምሳ ስንበላ አንድ ጎስቆል ያሉ አዛውንት መጡና “ልጆቸ ርቦኛል “አሉን
ምኡዝ ፣ “ካለ ይስጥዎት” አላቸውና መብላቱን ቀጠለ፤
ያሬድ ምኡዝን ክፉኛ ገላመጠውና’ ‘ አባቴ ቁጭ በሉና ከኛ ጋር ይብሉ” ብሎ ጋበዛቸው፤
እኔ አዛውንቱ እንዲበሉ ፈልጊያለሁ፤ ግን አብሮ መብላቱን ልቀበለው አልቻልኩም፤
ስለዚህ “በልተን ሲበቃን የተረፈውን እንሰጣቸዋለን” የሚል ለጽድቅ የማያበቃ ለኩነኔም የማይዳርግ ሀሳብ አቀረብኩ፤
ያሬድ ግን አመረረ “ሂዱና ታጥበዎ ይምጡ አባቴ” አላቸው፤
ምኡዝ በንዴት ጨሰ፤ “ለምን ሜቄዶኒያ ቁጥር 2 ብለህ አትከፍትም?” ብሎ አንባረቀበት፤
“ምንድነው ችግርህ ? “ አለው ያሬድ;
ምኡዝ ለወሬ የማይመች ሰፊ ሀተታ አቀረበ፤ ሲጨመቅ ይህን ይመስላል፤
(አንድ ሰው ራሱን መመገብ የማይችል ከሆነ፤ ሰነፍ ነው፤ አለያም ደደብ ነው፤ አለያም አቅመቢሰ ነው፤ ወይም አመለ ቢስ ነው፤ ከሰዎች ጋር ተስማምቶ መስራት አይችልም፤ ታድያ አንዲህ ያለው ሰው ለመኖር አይመጥንም፤ ብትረዳው አታሻሽለውም፤ ስታበላው በምድሪቱ ላይ ሸክም የሚሆንበትን ጊዜ ታራዝምበታለህ እንጂ አትጠቅመውም )
ሰውየው ታጥበው መጥተው ከኛ ጋራ መብላት ጀመሩ፤ ሰማንያ ያህል የቴኒስ ኩዋስ የሚያካክሉ ጉራሾችን ወዳፋቸው ከወረወሩ በሁዋላ በረጅሙ ተንፍሰው “ ሆሆ ለዚህ ሆዴ ይጠላኛል ዘመዴ አለች እርያ” ብለው ተረቱ፤
ከዚያ ወደኔ ዞር ብለው - “ አጅሬው ለካ ይቺን እየዋጥህ ነው የጉሬዛ ሙሽራ የመሰልከው” አሉና ብቻቸውን ሳቁ፤
ከዚያ ወደ አስተናጋጁዋ ዞረው “አንቺ ቂንጥራም እስቲ አንድ ሲንግል ድራፍት ወዲህ በይ “ ብለው ጮሁ፤
‘አባቴ ስሚናገሩት ነገር ጥንቃቄ ያድርጉ፤ ደሞ እዚህ ድራፍት አይሸጥም” አለ ያሬድ፤
አዛውንቱ የያሬድን ግሳፄ ከመ ገብስ አልቆጠሩትም፤ በር ላይ ቆሞ ለውዝ ወደ ሚሸጠው ልጅ ልጅ እየጠቆሙ” ያን ጥንዚዛ ባርያ ብንለከው ከጎረቤት አያመጣልንም ?” አሉ፤
በመጨረሻ ያሬድ “ሚስት አለዎት ? ` በማለት ጠየቃቸው፤
“እሱማ አለችኝ” አሉ በታከተ ድምጥ፤
“የተረፈውን ይውሰዱላት”
አዛውንቱ ፈገግ ብለው የመለሱትን ባልፅፈው ደስ ይለኝ ነበር;
“ምሽቴማ ይሄን ተቀመሰች ጥጋብዋን አልችለውም፤ ባይሆን ለውሽማየ እቁዋጥርላታለሁ’
7 953
ልቤ እየመታ፣እግሮቼ እየተብረከረኩ፣እጆቼን እያላበኝ፣ እንደምንም እያበድኩኝ ሆስፒታል ስደርስ ፤ የጠበቀኝን ነገር ማመን ከበደኝ።
"እኔን ጥላ ሌላ ወንድ ጋር ሄዳለች።" ብዬ የፈረድኩባት ፍቅረኛዬ፣ባልዋለችበት ያዋልኳት ንፁህ ሴት...የመጨረሻው የሕይወት እስትንፋሷ ላይ ሆና ፤ ነብስ-ውጭ ፣ ነብስ-ግቢ ላይ ናት።
ለካስ...ጥላኝ የሔደችው ሌላ ወንድ አግኝታ አልነበረም።የካንሰር ህመምተኛ መሆኗን እና ቀኗ እንደደረሰ ስላወቀች፣ እኔ እሷን እያስታመምኩ እንዳልሰቃይ ፣ ወጣትነቴን እንዳላባክን እና ህመሟን እያዬሁ እንዳልታመምባት ነበር ከእኔ የራቀችው።
እኔ እዛ ከማንም ጋር ስማግጥ ፣ስረግማት እና በማንም የፌስቡክ ፅሑፍ ስመዝናት...እሷ ግን ለእኔ ስትል የብቸኝነትን ህመም ውጣ ፤ ብቻዋን ከሞት ጋር ስትታገል ነበር።
ሰማይ ምድሩ ተደፋብኝ። ስሜቱን የሚከተለው እንስሳ ፤ እኔ ሆኜ ራሴን አገኘሁት።
እጆቿን ያዝኳት። ሰውነቷ በረዶ ሆኗል። እንባዬ የአልጋውን አንሶላ እያጠበው፣ይቅር እንድትለኝ ልለምናት ቃል ስመርጥ ሳለሁ ገና ማውራት ሳልጀምር ፣ አይኖቿን ፍቅሬ ለዘላለም ጨፈነች።ሞተች።
ታዴዎስ አዲሱ
