en
Feedback
የስንኝ ቋጠሮ

የስንኝ ቋጠሮ

Open in Telegram

የዚህ ቻናል ዋና አላማ የተለያዩ ወጣቶች የግጥም ችሎታቸውን የሚዳብሩበት እና የሚያወጡበት ቻናል ነው። ግጥሞችን ለመላክ @mogea ይጠቀሙ መልሰን ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል!!

Show more
2 046
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
በውስጥ መስመር የተላከ ምርጥ ግጥም ጠላሁህ መሠለ ትዝ ይለኛል ያኔ ስላንተ ሲያወሩ ልቤ ይደነግጣል ለምን እንደሆነ እንጃ ዝም ብሎ ይመታል ትዝ ይለኛል ያኔ ስሜን ስትጠራኝ በደስታ ብዛት አፌን የሚይዘኝ ትዝ ይለኛል ያኔ አይኖቼን ስታየኝ አይኖቼ ደንግጠው ድንብርብር ሚሉብኝ አሁን ግን ስላንተ ቢያወሩ ስምርን ቢጠሩልኝ ስሜን ብትጠራኝ አይኖቼም ብታየኝ ጠላሁህ መሠለኝ መስሎም አይታየኝ ✍መሩ @gitmv @gitmv @gitmv

በውስጥ መስመር የተላከ ግጥም በ Jerry 🌧በዝናብ ስትቀጥረኝ🌧 🌧በዛ በክረምቱ ዝናብ በሚበዛው 🌧አዋራውም ቦክቶ ጭቃ በሚሆነው 🌧መብረቅ እንደልቡ እንዳሻው በሚጮኀው 🌧ነይ ስትል በዝናብ ጊዜውን ጠብቀህ 🌧መች መሰለኝ እኔ እንዳላየው እንባህ 🌧ለካስ ውስጥህ ጠቁሮል ለካ ውስጥህ ቆስሎል 🌧እኔን በማጣትህ አዝነሀል አሞሀል 🌧ሀዘንህን አይቼ ጤና እንደማይኖረ ኝ 🌧ይሄን ስለምታውቅ በዝናብ ቀጠርከኝ 🌧በሁለቱ ጉንጮችህ የሚፈሰው እንባ ዝናብ እንዲመስለኝ 🌧ለካ እንዳላየው ነው እንባህን በአይኔ 🌧ዶፍ ዝናብ ሲዘንብ የምጠራኝ ያኔ ገጣሚ እየሩሳሌም አሰፋ @gitmv @gitmv @gitmv

የዚህ ቻናል ዋና አላማ የተለያዩ ወጣቶች የግጥም ችሎታቸውን የሚዳብሩበት እና የሚያወጡበት ቻናል ነው። ግጥሞችን ለመላክ @mogea ፡ይጠቀሙ መልሰን ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል!!

፨ፍቅር፨ ፍቅር ደግነቱ ሊጽፋት ሲነሱ ቦታ አለመፍጀቱ ሃሳብ ሲገልጹበት ሲሉት መመቸቱ የፍቅር ክፋቱ ገላጭ መፈለጉ አድራጊ ማጣቱ ካለ መልካምነት ካለ በጎ ስራ አለመከሰቱ። @gitmv @gitmv

መንገዱን ሰው ሞላው ኑሮው ሰለጠነ ስጋችን ስብ ከቦት ነፍሳችን ቀጠነ ገበሬው ቀረና ምሁሩ ዘር ያዘ ሳያርስ እየዘራ አረም ተመዘዘ። @gitmv @gitmv @gitmv

sticker.webp0.16 KB

( ግራ ገብ ) : ያልገባኝ ሳይገባኝ…ምን አለ በገባኝ በሚል ግራ ሀሳብ… ይብስ ግራ ገባኝ! ! =============^============ ©ዳግም ሔራን Join and share……………………………👇👇 @gitmv @gitmv @gitmv ይቀላቀሉን🙏

Group: መሳም ያሣሣተው የስተ-ቀኙ ፊቴ ቡጢ አበልዞታል ቀጥቅጦኝ ጠላቴ ሸክም ያልታከተው ድንድኑ ትከሻ ዛሬ ቁልቁል ዘምሟል የለውም መካሻ ስንት ጉድ ያዘለው ጀርባዬ ቢጎብጥ ጫንበት ይላሉ ጭራሹን እስኪላጥ ዳገት ሽቅብ ወጥቶ ቢዝልም ጉልበቴ ጎመን መደለሌን መች አይተው በህይወቴ መዳፌ ሻክሮ ከአለት ቢጠጥር ደልቶኝ መሠላቸው ሌላ ጉድ ስፈጥር ጫማዬን ሣይለኩ በእኔ እግር ገብተው ሠፍቶት ነው ይላሉ በማያገባቸው ልኩም ነው ይላሉ ጭራሽ ሣይነካቸው በጫማዬ ልኬት ህይወት በሠፋችው ጠቦ እንደምሠቃይ ማን በነገራቸው ፀባዖት @gitmv @gitmv @gitmv

በውስጥ መስመር የተላከ ምርጥ ግጥም "ትመጫለሽ ወይ?" ከመጣሽ እንዳትመለሺ ብየ በሬን ከፍቼ አንችን በመጠበቅ እንቅልፌን አጥቼ ብትመጣስ እያልኩኝ መምጣትሽን እየሳልኩኝ ፎቶሽን እያገላበጥኩኝ መምጣትሽን እየጠየኩት የልቤን እያወራሁት አለሁ ስጠብቅሽ እያነገርኩት በእብርክክ ቁሜ ትመጫለሽ ወ................ይ ንገሪኝ አለ....ሜ የመሬም ልጅ ✍ @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv

ኑሮህ ቅርፁን አጥቶ ሁኔታው ቢለወጥ አለሁ እሚል ጠፍቶ ሁሉም ጀርባ ቢሰጥ ደስታህ ወደ ሀዘን እውነት ወደ ሀሰት ቢሄድ ቢገለበጥ ባይኖር ምትጠጋው ምትይዝ ምትጨብጠው ከፊትህ ቢጠፋ አይዞህ ተስፋ አትቁረጥ ከፊትህ አለ ብርሀን ከፊትህ አለ ተስፋ የምድር ከሆነው ላይ አይኖችህን አንሳ @gitmv @gitmv @gitmv

sticker.webp0.16 KB

( ግራ ገብ ) : ያልገባኝ ሳይገባኝ…ምን አለ በገባኝ በሚል ግራ ሀሳብ… ይብስ ግራ ገባኝ! ! =============^============ ©ዳግም ሔራን Join and share……………………………👇👇 @gitmv @gitmv @gitmv ይቀላቀሉን🙏

°°°ምኞት ደመና ነው! © ሲራክ የትነት ወዝ ገላ - የሰማዩ ግርግም ፥ ምኞት ደመና ነው - የጤዛ ጥርቅም። ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ @gitmv @gitmv

E-ስብራት ፨ ፨ ፨ ፨ ለተሰበረ እግር ድጋፍ ቢፈጠርም ምርኩዝን ተማምኖ እግር አይሰበርም!! ከወደዱት share ያድርጉ @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv

ውድ የስንኝ ቋጠሮ አባሎቻችን:- የዚህ ቻናል ዋና አላማ የተለያዩ ወጣቶች የግጥም ችሎታቸውን ለአንባቢያን የሚያወጡበት ቻናል ነው። ስለዚህ ግጥም የምትሞክሩ በሙሉ ግጥሞቻችሁ ላኩልን መልሰን ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል። ግጥሞችን ለመላክ @mogea ፡ይጠቀሙ @gitmv @gitmv

#ውዝግብ_2 አራሚም ታራሚሚ ባልተበየነለት እንደልቡ ዘመን ወላድ በሬው በዝቶ... እንዳገር ተዛመን ስልቻ ባነሰው ፥ የሀተታ ስብስብ በቢላዋ ምላስ እየተመተረ...... ነጭ የወሬ ስብ ግንባር ስጋ ያሉት ቁልፍልፉ ወጥቶ ..... ከማደናገሩ በጠየቁ ቁጥር.........ብዙ በቆፈሩ ጥያቄ ያጭራል ፥ የመልስ ዳር ዳሩ ። አብርሀም_ተክሉ @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv

በውስጥ መስመር የተላከ በ ዜኒት ጨለማው ቢያይልም እማይነጋ መስሎ ንዳድ ቢበረታ ውስጤን አከሳስሎ እጠብቀዋልው ደጁን እጠናለው አንድ ቀን ያልፍና እተርከዋለው ያሻገረኝ ጌታ ብዬ ዘምራለው!! Zenit D. @gitmv @gitmv

ለውጥ ነውጥ ይዞ ከመጣ በኋላ ፣ እንዴት እንተኛ? "ኢትዮጵያ" ሚል ሁሉ ፣ ይባላል "ነፍጠኛ" ፍርድ ቤት ይሾማል ፣ የኳስ ሜዳ ዳኛ ቢረግጡን ቢረግጡን ፣ ኳስ ህዝቦቹ እኛ ዳኛው ምን ሊገደው? ለሚጠልዘን ነው ፣ ግቡን የሚፈርደው። ✍በላይ በቀለ ወያ @gitmv @gitmv

የፈላስፎች ንግግር ~~~~~~ ሀብታም ይደኸያል ሀኪምም ይሞታል፣ ጎበዝ ይሸነፋል ብልህ ይሳሳታል፣ የበራውም ጠፍቶ የሠሩት ይፈርሳል፣ የቆመውም ወድቆ የሳቀ ያለቅሳል። ፍሬ መሬት ወድቆ ከዋለ ካደረ፣ ሰው ገንዘብ አግኝቶ መክበር ከጀመረ። የመጣ ነውና ቀድሞውን ከጥንት፣ ሁለቱም አይድኑም ከመበላሸት። የሰዎችን ፀባይ የተመራመረ፣ አንድ ፈላስፋ ሊቅ እንዲህ ተናገረ። በጣም በማስተዋል ከላይ እስከ ታች፣ ስመለከታቸው የሰውን ልጆች። እያጣሁባቸው ግብሩ እሚመሰገን፣ እንቃቸው ጀመር እጅግ ያለመጠን። የደንቆሮ መንፈስ ምንኛ ታደለ፣ ብልጥነት አላጣም ጅል እየመሰለ። እንኳን መፅሀፍ ማንበብ ፊደል ሳያጠና፣ ሁሉንም ያወቀ ይመስለዋልና። የሊቅ ሰው መከራ የብልኅ አባዜ፣ ሲጨነቅ መኖር ነው ባሳብ በትካዜ። አቶ ዐሳበ ቢስ ይተኛል ዝም ብሎ፣ ከትራሱ ጋራ ዐሳቡን ጠቅሎ። ከወደዱት ሼር ያድርጉ ........ ~~~~~~~~~ @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv

እንደ ክረምት ዝናብ ፣ችግሬ ይረግፋል ምስኪን ትከሻዬ ፣እሱን ይቀበላል ሰዎቹም ይላሉ ፣እንዴት ቻለው እሱ ሁሌም ብልጭ ይላል ፣ አይከደን ጥርሱ የተበደለ ሰው፣ ችግር ላላት ነፍሱ ኑሮ እንዴት ነው ቢሉት፣ ፈገግታ ነው መልሱ ይስማዕከ ወርቁ