የስንኝ ቋጠሮ
Open in Telegram
የዚህ ቻናል ዋና አላማ የተለያዩ ወጣቶች የግጥም ችሎታቸውን የሚዳብሩበት እና የሚያወጡበት ቻናል ነው። ግጥሞችን ለመላክ @mogea ይጠቀሙ መልሰን ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል!!
Show more2 046
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
2 046
"የሰው አዕምሮ በትክክል የሚዋኝበት ቢገኝ ከውቅያኖስ የጠለቀ … ከሠማይ የራቀ … ከሐሳብ የረቀቀ … በዋጋው ከሁሉ የላቀ … ተቆፍሮ ያልተደረሰበት ውድ ሐብት ነው። ግን የተቆለፈበት ቁልፍ ነውና ቁልፉን 🔑ለማግኘት ቁ ልፉ የተቆለፈበትን ደጃፍ 🚪ለመክፈት የሚያስችለውን ቁልፍ እስክናገኝ ተስፋ መቁረጥ የለብንም። ከቁልፉ ብዙ የራቅን አይመስለኝም!" @fidelMeznagna
(የተቆለፈበት ቁልፍ)
@gitmv
@gitmv
@gitmv
2 046
ተረዱልኝ
አፌን ግና ሳልከፍት ሊሰድብ ነው አሉ
ቅኔን ሳልደረድር ወርቁን ይፈታሉ
ብዬ ሳይረዱኝ ሳልል የገባቸው
ጠጉር ሰንጣቂዎች እልፍ ነው ቁጥራቸው
እማሬን ተርጉመው ፍካሬን አሰቡ
የቃላቴን ለዛ በ አረም አስዋቡ
እንደ ጅረት ሚፈስ የ ሃሳብ ልእልና
ከብዶ መታየቱ ብሂሉ ቀረና
የነገርን ሸማ ፈትል የሚፈትሉ
ቀና ሃሳቤ ላይ ቆርጠው ሚቀጥሉ
ቋጥሮ መፍታት ሱስ ላይ ሌት ከቀን ሚተጉ
አሁንም ሞልተዋል በየ ጥጋጥጉ
እኔ ግን ያልገባኝ
አንድ ጥያቄ አለኝ
ያላልኩትን ቅኔ ማስላቱ ካላቸው
ያልኩትን ማስተዋል እንዴት ተሳናቸው?
moge✍
@gitmv
@gitmv
@gitmv
2 046
የቱጋ ነኝ?
""""""""""""
"ጭለማ ውስጥ ነበርክ
አሁን ግን ነጋልህ" ብለው ያወጉኛል፤
የንጋ አይንጋ ሳላውቅ
ባሉኝ ተደምሜ እኔም ደስስ ይለኛል!
ግና ፈቀቅ የለም
ካሰመርኳት ኑሮ ከቆምኩባት ዓለም
ከኢምንቷ እርምጃ ከህይወቴ ቀለም
አብበሀል ሲሉኝ ጭራሽ ወደ መክሰም
ከከፍታ ሳይሆን ወደ ሽንቁር መክተም
እሮጬ ፈርጥጬ ካንዱ ጋ መላተም
የነፍሴ አውጪኝ አይነት ከውሀ እንደመስጠም!
ግና ፈቀቅ የለም
የእውር ድንብር
ተፈተለኩ ብዬ የምሄደው ስንዝር
የወግ እቴ ኑሮ ከማጡ መዳከር
የእንቧይ ክምር መሆን አንዱ ላይ መሽከርከር
ብል እንደበላው ጨርቅ ሲነኩኝ መተርተር
በጎሳ ቦድኞ እንደሀገር መውተርተር
ፆም ውዬ ፆም ማደር!
ግና ፈቀቅ የለም
ዘላለሙን እንባ
መች ጢም ብሎ ይሞላል የሰፈሩት ተልባ
እላይ ሲከምሩት ቁልቁል እየገባ
አውቃለሁኝ ብዬ በሸኮፍኩት ደባ
የእናት ጡት ነካሽ ዝተት የማ'ረባ
ከስንዴው እንክርዳድ ከፍሬው ገለባ!
ግና ፈቀቅ የለም
ለብሶ መድመቅ ርቆኝ በአካላቴ ልክ
ቁልቁል ወደኃላ ከእርምጃ ድክ ድክ
እንደ አልቦካ እንጀራ ሲነኩኝ መፍረክረክ
መቆም እያቃተኝ ሸብርኮኝ ብርክ ብርክ!
ግና ፈቀቅ የለም
እዪ እንግዲህ ምድሬ
አሽመድምዶኝ ጠኔ
ሰንፍጦኝ ጠረኔ
አልጎድል አልሞላ ከዝብርቅርቅ ቀኔ
ግን ነጋልህ ሲሉኝ
ተትረፈረፍክ ሲሉኝ ደስ ይለኛል እኔ!
ግና የቱጋ ነኝ?
አብርሃም ፍቅሬ
@gitmv
@gitmv
@gitmv
2 046
#መኖር_እና_ማኖር
፡
፡
አለም ሁለት መንደር ፡ ሁለት ጎዳና ናት
ሰለ አንዱ ደስታ አንዱ የሚኖርበት።
፡
ለመኖር የመጣው ሞልቶለት ሕይወቱ
በደስታ ይኖራል በሀብት እና ንብረቱ።
፡
ለማኖር የመጣም፣
በሌላ ጎዳና ያለው በምድርቱ
መከራን ሸምቶ ይኖራል በከንቱ ።
፡
፡
ሕይወት እንደዚህ ናት፣
እንደ አንዷ ሳንቲም የሁለት ገፅታ
ኑሯችን በአንድ አለም ሕይወታችን መንታ
እንደ ፀሀይ ጨረቃ ሁነናል ቀን ማታ።
፡
፡
✍በቶላዋቅ ኢተፋ
✍በ06/01/2013
፡
Share @tibebnBeMasho
@tibebnBeMasho
@tibebnBeMasho
2 046
መተናነስ
"""""""""""
ጊዜ ሲጥል ክፉ
ከሁሉ ዝቅ ዝቅ ከአፈሩ አላውሶ፤
ቀን ሲጎድል ክፉ
የእፍረትን ካባ እሬት አስቅምሶ፤
ዘመን ሲዋጅ ክፉ
ቀና ቀና አያደርግ
ዓይንን አሰብሮ ከአንገት አስጎንብሶ፤
አስቀምጦ ይገኛል
እንኳን ከአዳም ልጅ
ከግዑዝ ፍጥረቱ ቁልቁል አሳንሶ!
አብርሃም ፍቅሬ
(የቅዳስ ልጅ)
https://t.me/joinchat/AAAAAE47sVaFEmR1sP8X6A
2 046
~~~~አሳልፈኝ~~~~
በትልቁ መንገድ
እኔም አንተም ስንራመድ
ከፊቴ ብትመጣ ከፊትህ ብታየኝ
እኔ ያለፍኩትን በ'ጅህ እያሳየኸኝ
አንተ ያለፍከውን "ጀርባ" ነው አትበለኝ
.
ያለፍኩት 'ሚመስለኝ ያለፍከው 'ሚመስልህ
ጀርባዬ ፊትህ ነው ፊቴ ደሞ ጀርባህ
.
ስለዚህ ወዳጄ
.
በትልቁ መንገድ
እኔም አንተም ስንራመድ
ከፊቴ ብትመጣ ከፊትህ ብታየኝ
እኔ ያለፍኩትን በ'ጅህ እያሳየኸኝ
አንተ ያለፍከውን "ጀርባ" ነው አትበለኝ
ይልቅ ሳሳልፍህ አንተም አሳልፈኝ
✍ⒿⓄⒽⓃ
@gitmv
@gitmv
2 046
#ምንም አልል
እሺ እንግዲህ በዝምታ
የልቤን ደም ሥር ትርታ
በደቂቃ ዕድሜን ትዝታ
ትር ስትል አፍታ ለአፍታ
እያዳመጥኩ እያስታመምኩ ጊዜዬን እያሰላሰልኩ
ሳልናገር ሳልጋገር፤ እየደገምኩ እያሰለሰልኩ
ሰልሰለች እየመላለስኩ ..........
እሺ እንግዲህ በጸጥታ
የልቤን ደም ሥር ትርታ
የእስትንፋሴን ቃል ጉምጉምታ
ትር ስትል አፍታ ለአፍታ
ሳልሰለቸ እየደጋገምኩ
በእግረ ሕልና እያደቀቅኩ
እየቋጠርኩ እየቆጠርኩ
እሺ እንግዲህ አልናገርም
በአንደበቴ አልተነፍስም
በልሳኔ አልመሰክርም
አልልም፡፡ ምንም አልልም
እንዲያው ዝም እንጂ ዝም ዝም ............
የልቤ ደም ሥር ሲያቃጭል
ልሳኔን ሲያስነሳ ሲያስጥል
ቃላቴን ሲቃኝ ሲያጋግል
ትንፋሼን ሲያንር ሲያደውል
ክል ሲል ትር ድም ሲል
ማዳመጥ ማስታመም እንጅ ፤ ሌላ ምንም ምንም አልል
©✍ ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን
@gitmv
@gitmv
