en
Feedback
የስንኝ ቋጠሮ

የስንኝ ቋጠሮ

Open in Telegram

የዚህ ቻናል ዋና አላማ የተለያዩ ወጣቶች የግጥም ችሎታቸውን የሚዳብሩበት እና የሚያወጡበት ቻናል ነው። ግጥሞችን ለመላክ @mogea ይጠቀሙ መልሰን ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል!!

Show more
2 046
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
sticker.webp0.16 KB

የፀጥታ ጩኀት ከዝምታው ክርታስ የጩኀት ጥልቅ ወጀብ... ከልቤ ላይ ሲደርስ ዞሮ ሲያናውጠኝ ደርሶ ሲያቃጥለኝ ላዬ በድን ሆኖ ውስጤ ተበታትኖ የማይገባኝ ሀሳብ የማላቀው ሂሳብ ድንገት ሲያስጨንቀኝ የውስጤን ትኩሳት ያንጀቴን ፍም እሳት ተንፍሼው እንዳልወድቅ ወይ ነግሬ እንዳልፀድቅ መደበቂያ ዋሻ ካንገት ቃል መሸሻ ማብረጃ እንዲሆነኝ ሳቅ ነው የሚቀድመኝ ✍ሱመያ ስርሞላ @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv

"የሰው አዕምሮ በትክክል የሚዋኝበት ቢገኝ ከውቅያኖስ የጠለቀ … ከሠማይ የራቀ … ከሐሳብ የረቀቀ … በዋጋው ከሁሉ የላቀ … ተቆፍሮ ያልተደረሰበት ውድ ሐብት ነው። ግን የተቆለፈበት ቁልፍ ነውና ቁልፉን 🔑ለማግኘት ቁ ልፉ የተቆለፈበትን ደጃፍ 🚪ለመክፈት የሚያስችለውን ቁልፍ እስክናገኝ ተስፋ መቁረጥ የለብንም። ከቁልፉ ብዙ የራቅን አይመስለኝም!" @fidelMeznagna (የተቆለፈበት ቁልፍ) @gitmv @gitmv @gitmv

በማግኘት ውስጥ የኖረ : በማጣት ውስጥ ይሞታል በማግኘት ውስጥ የሞተ ግን ባጣ ቁጥር ይኖራል። @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv

ሙግት(በዕዉቀቱ ስዩም) ጊዜ በሰዉ ህይዎት ፣ ዘበት አይታክተዉ እኔም ምላሽ ባጣ ፣ መጠየቄን አልተው ኩታ ገጠም ናቸው ፣ አልፋና ኦሜጋ እንዴት ቀን ይመሻል ፣ በቅጡ ሳይነጋ ማን ዘረፈዉ ጠጉሬን? ማን አሰረዉ እግሬን? ጉልበቴን ማን በላዉ? አቅሜን ማን ወረሰዉ? ተወልዶ ሳይጨርስ እንዴት ያረጃል ሰዉ? (በዉቀቱ ስዩም) @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv

ተረዱልኝ አፌን ግና ሳልከፍት ሊሰድብ ነው አሉ ቅኔን ሳልደረድር ወርቁን ይፈታሉ ብዬ ሳይረዱኝ ሳልል የገባቸው ጠጉር ሰንጣቂዎች እልፍ ነው ቁጥራቸው እማሬን ተርጉመው ፍካሬን አሰቡ የቃላቴን ለዛ በ አረም አስዋቡ እንደ ጅረት ሚፈስ የ ሃሳብ ልእልና ከብዶ መታየቱ ብሂሉ ቀረና የነገርን ሸማ ፈትል የሚፈትሉ ቀና ሃሳቤ ላይ ቆርጠው ሚቀጥሉ ቋጥሮ መፍታት ሱስ ላይ ሌት ከቀን ሚተጉ አሁንም ሞልተዋል በየ ጥጋጥጉ እኔ ግን ያልገባኝ አንድ ጥያቄ አለኝ ያላልኩትን ቅኔ ማስላቱ ካላቸው ያልኩትን ማስተዋል እንዴት ተሳናቸው? moge✍ @gitmv @gitmv @gitmv

አተላው ይደፋ ! ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ የዘረኝነት ጉሽ ፣ . . . . . . ያሰከረው ትውልድ ፤ አንጎሉ እንደዞረ ፤ አንጀቱ እንዳረረ ፤ . . . . . . ቀኑን ከሚገፋ ፤ ጋኑን አለቅልቆ ፣ አተላውን ይድፋ ፡፡ ከወደዱት share ያድርጉ @gitmv @gitmv @gitmv

የቱጋ ነኝ? """""""""""" "ጭለማ ውስጥ ነበርክ አሁን ግን ነጋልህ" ብለው ያወጉኛል፤ የንጋ አይንጋ ሳላውቅ ባሉኝ ተደምሜ እኔም ደስስ ይለኛል! ግና ፈቀቅ የለም ካሰመርኳት ኑሮ ከቆምኩባት ዓለም ከኢምንቷ እርምጃ ከህይወቴ ቀለም አብበሀል ሲሉኝ ጭራሽ ወደ መክሰም ከከፍታ ሳይሆን ወደ ሽንቁር መክተም እሮጬ ፈርጥጬ ካንዱ ጋ መላተም የነፍሴ አውጪኝ አይነት ከውሀ እንደመስጠም! ግና ፈቀቅ የለም የእውር ድንብር ተፈተለኩ ብዬ የምሄደው ስንዝር የወግ እቴ ኑሮ ከማጡ መዳከር የእንቧይ ክምር መሆን አንዱ ላይ መሽከርከር ብል እንደበላው ጨርቅ ሲነኩኝ መተርተር በጎሳ ቦድኞ እንደሀገር መውተርተር ፆም ውዬ ፆም ማደር! ግና ፈቀቅ የለም ዘላለሙን እንባ መች ጢም ብሎ ይሞላል የሰፈሩት ተልባ እላይ ሲከምሩት ቁልቁል እየገባ አውቃለሁኝ ብዬ በሸኮፍኩት ደባ የእናት ጡት ነካሽ ዝተት የማ'ረባ ከስንዴው እንክርዳድ ከፍሬው ገለባ! ግና ፈቀቅ የለም ለብሶ መድመቅ ርቆኝ በአካላቴ ልክ ቁልቁል ወደኃላ ከእርምጃ ድክ ድክ እንደ አልቦካ እንጀራ ሲነኩኝ መፍረክረክ መቆም እያቃተኝ ሸብርኮኝ ብርክ ብርክ! ግና ፈቀቅ የለም እዪ እንግዲህ ምድሬ አሽመድምዶኝ ጠኔ ሰንፍጦኝ ጠረኔ አልጎድል አልሞላ ከዝብርቅርቅ ቀኔ ግን ነጋልህ ሲሉኝ ተትረፈረፍክ ሲሉኝ ደስ ይለኛል እኔ! ግና የቱጋ ነኝ? አብርሃም ፍቅሬ @gitmv @gitmv @gitmv

#ሁለት #ሞት ማንም ጨከነ ~ ማንም በደለ ሰው አይደለም ወይ ~ የተገደለ ? ግፍ የጣላት ነብስ ~ ዳግመኛ ላትቆም ምን ይፈይዳል ~ ጣት መጠቋቆም ? ማንም አለመ ~ ማንም ተኮሰ ሰው አይደል ወይ ~ ደሙ የፈሰሰ ? የንፁሀን ደም ~ ከንቱ ቢፈስም ገዳይ መቀየር ~ ሟች አይመለስም ===||=== @gitmv @gitmv @gitmv ከሙሉቀን ሰ•

ይሻላል እውነቱ ከኛው እጣፈንታ ላናመልጥ ነገር ወዲህ ወዲያ እያሉ ሰውን ከማስቸገር የሰውነት ወጉ ተደርሶ ቢታፈር ይቅር ይሁን ብሎ እንዲያው ከመገደር ሳይሻል አይቀርም እውነቱን ተናግሮ ካመሹበት ማደር (አቡሽ) @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv

አንዳንድ ህመም አለ እየዋለ እያደር ቆይቶ 'ሚሰማ ከራርሞ 'ሚያቆስል፣ አንዳንድ እውነት አለ ሽፋኑ ሲገለጥ አፍላነትን ሽሮ እርጅናን ሚመስል፣ እናም ይህንን ስል. . .?! ብርቱ ጉልበት ሲሰንፍ ድጋፍ የነበረው ምርኩዝ ሲያስፈልገው፣ ያየ ሰው በሙሉ በጉብዝናው ዘመን ያስብ ስለነገው። ©ምናሴ ዋቆ @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv

በተስፋ አረማመድ የጊዜን ሩጫ ፣ ውሽንፍር ቀናበት የ'ድሜን ግስጋሴ ፣ ብርሃን ተመኘ ለ'ድሜና ለጊዜ ፣ ሐሳብ አሸክሞ ተስፋ ግን ብቻውን ፣ ሲያዘግም ተገኘ ። በነጠላ ጫማ ፣ በተስፋ አረማመድ እዩት ወደ ሞቱ ፣ የብልጥ ሰው መንገድ ። መዘክር ግርማ @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv @gitmv

በበጎች መሃከል ትርምስ ተፈጥሮ ተደናብረው ሳይ ዛሬ ላይ ከወትሮ አውሬ ይሆን ብዬ በግርምት ሮጬ በ አፅንኦት ስቃኝ ብርሃኔን ገልጬ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ከበጎቼ መሃል አንደኛው ተነክሶ ወድቆ አገኘሁት በደም ተለውሶ ፨ ሁሉም በጎች ናቸው አውሬ የለም ከመሃል ምንስ ተገኝቶ ነው በጌን የሚገድል ብዬ ስደናገጥ ልቤ ተከላውሶ ተኩላን አገኘሁት የበግ ለምድ ለብሶ። ሞገስ (Moge) ✍ @gitmv @gitmv @gitmv

#መኖር_እና_ማኖር ፡ ፡ አለም ሁለት መንደር ፡ ሁለት ጎዳና ናት ሰለ አንዱ ደስታ አንዱ የሚኖርበት። ፡ ለመኖር የመጣው ሞልቶለት ሕይወቱ በደስታ ይኖራል በሀብት እና ንብረቱ። ፡ ለማኖር የመጣም፣ በሌላ ጎዳና ያለው በምድርቱ መከራን ሸምቶ ይኖራል በከንቱ ። ፡ ፡ ሕይወት እንደዚህ ናት፣ እንደ አንዷ ሳንቲም የሁለት ገፅታ ኑሯችን በአንድ አለም ሕይወታችን መንታ እንደ ፀሀይ ጨረቃ ሁነናል ቀን ማታ። ፡ ፡ ✍በቶላዋቅ ኢተፋ ✍በ06/01/2013 ፡ Share @tibebnBeMasho @tibebnBeMasho @tibebnBeMasho

መተናነስ """"""""""" ጊዜ ሲጥል ክፉ ከሁሉ ዝቅ ዝቅ ከአፈሩ አላውሶ፤ ቀን ሲጎድል ክፉ የእፍረትን ካባ እሬት አስቅምሶ፤ ዘመን ሲዋጅ ክፉ ቀና ቀና አያደርግ ዓይንን አሰብሮ ከአንገት አስጎንብሶ፤ አስቀምጦ ይገኛል እንኳን ከአዳም ልጅ ከግዑዝ ፍጥረቱ ቁልቁል አሳንሶ! አብርሃም ፍቅሬ (የቅዳስ ልጅ) https://t.me/joinchat/AAAAAE47sVaFEmR1sP8X6A

~~~~አሳልፈኝ~~~~ በትልቁ መንገድ እኔም አንተም ስንራመድ ከፊቴ ብትመጣ ከፊትህ ብታየኝ እኔ ያለፍኩትን በ'ጅህ እያሳየኸኝ አንተ ያለፍከውን "ጀርባ" ነው አትበለኝ . ያለፍኩት 'ሚመስለኝ ያለፍከው 'ሚመስልህ ጀርባዬ ፊትህ ነው ፊቴ ደሞ ጀርባህ . ስለዚህ ወዳጄ . በትልቁ መንገድ እኔም አንተም ስንራመድ ከፊቴ ብትመጣ ከፊትህ ብታየኝ እኔ ያለፍኩትን በ'ጅህ እያሳየኸኝ አንተ ያለፍከውን "ጀርባ" ነው አትበለኝ ይልቅ ሳሳልፍህ አንተም አሳልፈኝ ✍ⒿⓄⒽⓃ @gitmv @gitmv

#ምንም አልል እሺ እንግዲህ በዝምታ የልቤን ደም ሥር ትርታ በደቂቃ ዕድሜን ትዝታ ትር ስትል አፍታ ለአፍታ እያዳመጥኩ እያስታመምኩ ጊዜዬን እያሰላሰልኩ ሳልናገር ሳልጋገር፤ እየደገምኩ እያሰለሰልኩ ሰልሰለች እየመላለስኩ .......... እሺ እንግዲህ በጸጥታ የልቤን ደም ሥር ትርታ የእስትንፋሴን ቃል ጉምጉምታ ትር ስትል አፍታ ለአፍታ ሳልሰለቸ እየደጋገምኩ በእግረ ሕልና እያደቀቅኩ እየቋጠርኩ እየቆጠርኩ እሺ እንግዲህ አልናገርም በአንደበቴ አልተነፍስም በልሳኔ አልመሰክርም አልልም፡፡ ምንም አልልም እንዲያው ዝም እንጂ ዝም ዝም ............ የልቤ ደም ሥር ሲያቃጭል ልሳኔን ሲያስነሳ ሲያስጥል ቃላቴን ሲቃኝ ሲያጋግል ትንፋሼን ሲያንር ሲያደውል ክል ሲል ትር ድም ሲል ማዳመጥ ማስታመም እንጅ ፤ ሌላ ምንም ምንም አልል ©✍ ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን @gitmv @gitmv

ጣትና ቅጣት ብዕር ከወረቀት ጣትም ከቀለበት ተስማምተው እያረፉ ምነው የሚስማሙ ባለጣቶች ጠፉ ©✍ልዑል @gitmv @gitmv