en
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Open in Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Show more
2 296
Subscribers
+324 hours
+87 days
+3730 days
Posts Archive
የሁለተኛው ቀን ቅዳሴ በላይቭ ይኼው ተከታተሉ ከመንበረ ፓትሪያርክ ቅድስት ማሪያም ገዳም https://youtu.be/NLEny-zKzMs

ጸሎታችን ቶሎ መልስ እንዲያገኝ ይኼንን 3 ነገሮች አሁኑኑ አድርጉ!! እጾማለሁ የምል ሁሉ ይኼንን መስማት አለበት!! የዘርፈ የሰሞኑን አነጋጋሪው ድርግት!!https://youtu.be/pmCJ7V4Znw4?si=frl_rkyvqV_1Ghji

ቅዳሴ ላይቭ ለመከታተል በዚህ ልንክ ግቡ፡ https://www.youtube.com/live/53cxq33I4qE?si=UjercaQ8VUqgk3HU

«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!» ማቴዎስ 22:34-40 ፈሪሳውያንም ሰዱቃውያንን ምላሽ እንዳሳጣቸው በሰሙ ጊዜ በአንድነት ወደ እሱ ተሰበሰቡ። ከመካከላቸውም አንድ ሕግ ዐዋቂ ሊፈትነው ጠየቀው። “መምህር ሆይ፥ ከኦሪት ማንኛይቱ ትእዛዝ ትበልጣለች?” አለው። ጌታችን ኢየሱስም እንዲህ አለው፥ “አምላክህ እግዚአብሔርን በፍጹም ልብህ፥ በፍጹም ነፍስህ፥ በፍጹም ኀይልህ ውደደው። ታላቂቱና የመጀመሪያይቱ ትእዛዝ ይህች ናት። የምትመስላት ሁለተኛይቱም ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ የምትለው ናት። «የዕለቱ መልእክታት» - ሮሜ 12:1-17 - 2 ጴጥሮስ 1:10-16 - ሐዋ፡ሥራ 25:13-ፍጻሜ

ኑሯችሁ ላይ የምትጨምሯቸው 7ቱ መንፈሳዊ መሰላሎች!! በኑሯችንና በእምነታችን ይኼንን ከጨመራችሁ እመኑኝ ትለወጣላችሁ!! በዓብይ ጾም ይኼንን አድርጉ! #ጸሎት https://youtu.be/sA5LweuicAg?si=CGR8lhNDDxM36yn_

እንኳን ለታላቁ የዐቢይ ጾም በሰላም አደረሳችሁ!  በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ መሰረት፣ የመጀመሪያው ሳምንት "ዘወረደ" ተብሎ ይጠራል። ፩. "ዘወረደ" ማለት ምን ማለት ነው? ቃሉ የግእዝ ሲሆን ትርጉሙም "ወረደ" ማለት ነው። ይህም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳን ከሰማየ ሰማያት መውረዱን፣ ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ ሰው መሆኑን (ምስጢረ ሥጋዌን) የሚያመለክት ነው። አምላክ ለሰው ልጆች ካለው ፍቅር የተነሳ ራሱን ዝቅ አድርጎ ወደ ምድር መምጣቱን የምናስብበት ሳምንት ነው።  "ዘወረደ" አምላክ ራሱን ዝቅ ያደረገበት ነውና እኛም በዚህ ሳምንት በትሕትና እራሳችንን ዝቅ አድርገን ወደ እግዚአብሔር መቅረብ እንዳለብን የምንማርበት ሳምንት ነው። ፪. የዐቢይ ጾም ስምንቱ ሳምንታት (እሑዶች) 1), ዘወረደ (የአሁኑ ሳምንት) 2), ቅድስት (ስለ ሰንበት ቅድስና የሚነገርበት) 3), ምኩራብ (ጌታ በምኩራብ ማስተማሩ) 4), መጻጉ (የታመመው ሰው መፈወስ) 5), ደብረ ዘይት (ጌታ ዳግም እንደሚመጣ የተነገረበት) 6), ገብር ኄር (ታማኝ አገልጋይ) 7), ኒቆዲሞስ (ኒቆዲሞስ ወደ ጌታ መምጣቱ) 8), ሆሳዕና (ጌታ ወደ ኢየሩሳሌም በክብር መግባቱ) መልካም የዐቢይ ጾም !!!

ጸሎታችሁንና ስግደታችሁን እንዲህ ካደረጋችሁ የማታሸንፉት የለም!! ዲያብሎስን በማታለል እንዴት እናሸንፍ! በስግደት ወቅት የዲያብሎስ ፈተናዎች! #ስግደት #ንቁ https://youtu.be/Y8OGxkqvsgY

#_ታላቅ_የበረከት_ጥሪ_ለጎሮ_ኪዳነ_ምህረት_ቤተ_ክርስቲያን! ሼር በማድረግ የበረከቱን ጥሪ ለሌሎች አዳርሱ! ❤ የወለላይቱ እመቤት የኪዳነ ምህረት ልጆች በያላችሁበት የእመቤታችን ጸሎት እና ጸጋ በረ
#_ታላቅ_የበረከት_ጥሪ_ለጎሮ_ኪዳነ_ምህረት_ቤተ_ክርስቲያን! ሼር በማድረግ የበረከቱን ጥሪ ለሌሎች አዳርሱ! ❤ የወለላይቱ እመቤት የኪዳነ ምህረት ልጆች በያላችሁበት የእመቤታችን ጸሎት እና ጸጋ በረከት አይለያችሁ። የተአምረኛዋ እና የስዕለት ሰሚዋ የጎሮ ኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን ያልተከፈለ የመሬት 5 ሚሊዮን ብር ዕዳ አለባት። እንዲሁም ቦታዋ ጠባብ ስለሆነች 5 ሚሊዮን ብር ሊገዛ የታቀደ መሬት አለ። ❤ ስለዚህ እነዚህን ሁለቱን ታሳቢ በማድረግ ዛሬ የካቲት 7 ቅዳሜ እለት በኢትዮጲያ ሰዓት አቆጣጠር ማምሻ 12 ሰዓት በዩትዩብ፣ በፌስቡክ፣ በቲክቶክ በቀጥታ ስርጭት ወይም በ Live የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ስላለን የዚህን ታላቅ በረከት እንዳቅማችሁ ለመሳተፍ በሰዓቱ በላይቭ ጠብቁን! ❤ በተለይ ትምህርቴን የሰማችሁ፣ በትምህርቱ የተጠቀማችሁ የተለወጣችሁ፣ ጠበል ተጠምቃችሁ የተፈወሳችሁ፣ ዝክሩን በልታችሁ የቃል ኪዳኑን በረከት ያገኛችሁ ወዘተ ተማሪዎቼ እና ወዳጆቼ የኪዳነ ምህረትን የመሬት ዕዳ ለመክፈል እና መሬት ለመግዛት እንዳቅማችሁ ለመተባበር እንደማታሳፍሩኝ አውቃለሁ! ኪዳነ ምህረት ለበረከት በቀጥታ ስርጭት ታገናኘን! "ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው" የሐዋ 20፥35

እግዚኦ!! የባሰ አታምጣብኝ ነው የሚባለው ሌላ ምን ይባላል!! የመምህር ግርማ አስገራሚው ገጠመኝ!! የረሳችሁት ኃጢአት ካለ አሁኑኑ ይኼንን አድርጉ!! #ጸሎት https://youtu.be/pDhYdk6baLg?si=4LMqqU-yQBYPAcca

ጥያቄ 7፡ በዋልድባ ገዳም ውስጥ በታላቅ ተጋድሎ የኖሩትና በአንበሳ ጀርባ ላይ ተጭነው ይጓዙ እንደነበር የሚነገርላቸው ታላቁ ጻድቅ ማን ናቸው?
Anonymous voting

ጥያቄ 6፡ በመጽሐፍ ቅዱስ "የሰላም ንጉሥ" እና "የልዑል እግዚአብሔር ካህን" ተብሎ የተጠቀሰውና ለአብርሃም ኅብስትና ወይን የሰጠው ምስጢራዊ ሰው ማን ነው?
Anonymous voting

ጥያቄ 5፡ በየዓመቱ ከነሐሴ 1 እስከ 16 የምንጾመው "ጾመ ፍልሰታ" የተጀመረው በማን ጥያቄና ጸሎት ነው?
Anonymous voting

ጥያቄ 4፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት፣ አንድ ቤተ ክርስቲያን "ቤተ ክርስቲያን" ተብሎ ቅዳሴ እንዲቀደስበትና ቍርባን እንዲፈጸምበት የግድ ምን መኖር አለበት?
Anonymous voting

ጥያቄ 3፡ በጣና ባሕር ውስጥ ለ12 ዓመታት በውኃ ውስጥ ቆማ በመጸለይና ለሰው ልጅ ሁሉ ምሕረትን በመለመን የምትታወቀው ታላቋ እናት ማን ናቸው?
Anonymous voting

ጥያቄ 2፡ የቤተ ክርስቲያን መሪዎችና ሊቃውንት ተሰብስበው "የሃይማኖት ጸሎት" (ጸሎተ ሃይማኖትን) ያረቀቁበት የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ ጉባኤ የትኛው ነው?
Anonymous voting

ጥያቄ 1፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን "81 መጽሐፍ ቅዱስ" ሲባል፣ በብሉይ ኪዳንና በአዲስ ኪዳን ስንት ስንት መጻሕፍት አሉ?
Anonymous voting

ባሏ በመስተፋቅር እንዳገባት ካወቀች በኋላ ያደረገችው ነገር እጅግ ይደንቃል!! ባለትዳሮች ይኼንን ምልክት ካያችሁ መስተፋቅር ተደርጎባችኋልና ንቁበት!! #ጸሎት https://youtu.be/C8zGBm5_c08

= ይትባረክ እግዚአብሔር፡- የዚኽ ዓለም አለቃ ሰይጣን በሚገዛን ጊዜ አንድያ ልጁ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን የላከልን ኋላም መንፈሰ ጽድቅ ጰራቅሊጦስን ልኮልን በላያችን ከነበረ የኀጢአትና የበደል ርኵሰት የአነጻን እግዚአብሔር አብ ይመስገን፡፡ = ይትባረክ ወልደ አብ፡- ዳግመኛም በቅዱስ መስቀሉ ላይ ተቸንክሮ ስለ እኛ ስለ በደላችን ተሸክሞ የዘመነ ሐዲስ አማናዊ መሥዋዕት ኾኖ የተቤዠን እኛ መንጋዎቹን በድንቅ ማዳኑ የዋጀን ከእመቤታችን ከድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ የተወለደ የእግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጁ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይመስገን፡፡ = ይትባረክ መንፈስ ቅዱስ፡- ሦስተኛም እጅግ በሚደንቅ ምሥጢር የከበረ የማስተዋል ሀብተ ጸጋን በቸርነቱ የሰጠን፤ በምድር ላይ የምንኖር ሥጋውያንን ኹሉ የጐበኘን፤ ከነውረ ኀጠአት ከበደል ርስሐት የሚያነጻ ቸር እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ይመስገን፡፡ (ምንጭ፡ ተአምኆ ዘሥሉስ ቅዱስ) #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.facebook.com/hailegebrieltube2021 https://www.tiktok.com/@walkinaddistv

#አስተውሉ! "ሰይጣን ሰውን የሚያጠቃው በዝርክርክነትና በቸልተኝነት መንፈስ ነው። "ለተራ ሰው ስንሄድ ተኳኩለን፣ ለፈጣሪ ስንጸልይ ግን በቆሸሸ ማንነት" እንድንቀር በማድረግ ለጸሎታችን ያለንን ክብር ሊቀንስብን ይሞክራል። ንጽሕናችንን ስንጠብቅ ግን ለፈጣሪ ያለንን ፍቅርና ክብር እንገልጻለን። ቂም የሰይጣን መቆሚያ መሬት ነው። በልባችን ውስጥ ቂም ይዘን ብንጸልይ፣ ሰይጣን ጸሎታችን ወደ እግዚአብሔር እንዳይደርስ "ይህ ሰው የጠላቴ (የሰይጣን) ባሕርይ በውስጡ አለ" በሚል ክስ መንገድ ይዘጋል። ይቅር ስንል ግን የጠላትን ሰንሰለት እንበጥሳለን። ሰይጣን በትዕቢት የወደቀ መንፈስ በመሆኑ ስግደትንና ትሕትናን አይችልም። ስንሰግድ ሰውነታችንና ነፍሳችን ዝቅ ይላሉ፤ ይህም በውስጣችን ያለውን የትዕቢት መንፈስ ይሰብረዋል። ትሑት ልብ ደግሞ ጸሎቱ በቀጥታ ወደ እግዚአብሔር ዙፋን ይደርሳል።" #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.facebook.com/hailegebrieltube2021 https://www.tiktok.com/@walkinaddistv