902
Subscribers
-424 hours
-77 days
-530 days
Posts Archive
የትምህርትና_ስልጠና_ተቋማት_የዕውቅናና_እድሳት_ፍቃድ_አሰጣጥ_መመሪያ_ቁጥር_02_2012.pdf2.89 KB
የተከበራችሁ በጉድኝታችን ለምትገኙ የቅድመ 1ኛ እና 1ኛ እና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤቶች ለቀጣይ ለሚኖሩን የተለያዩ ፕሮግራሞች
1. ስልጠና
2. ልምድ ልውውጥ
3. ጥያቄና መልስ
4. ሳይንስና ፈጠራ የተቀመጠዉን መዋጮ እንድታስገቡ እያልን ሁሉም መዋጮ ለታለመለት ብቻ ወጪ የሚደረግ እንደሚሆን እያሳሰብን የቅድመ 1ኛ መዋጮ ለቅድመ 1ኛ ለታቀዱ ተግባራት ብቻ የ1ኛ ደረጃም በተመሳሳይ ወጪ እንደሚደረግ እናሳስባለን። የሳይንስና ፈጠራ በቀጣይ ሳምንት በወረዳ ደረጃ ስለሚደረግ አፋጥኑት።
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+1
" የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከ9-12ኛ ክፍል ይሸፍናል " - ትምህርት ሚኒስቴር
ትምህርት ሚኒስቴር የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን በተመለከት ለሁሉም ክልሎች እና ለሁለቱ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች እንዲሁም ለትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ትናንት ጥቅምት 10/2018 ዓ.ም ደብዳቤ ልኳል፡፡
የደብዳቤውን ትክክለኝነት ቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጧል።
በሚኒስቴሩ የስርዓተ ትምህርት ማበልጸጊያ መሪ ሥራ አስፈጻማ ቴዎድሮስ ሽዋርገጥ (ዶ/ር) የተፈረመው ደብዳቤው፤ የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ከ9-12ኛ ክፍል እንደሚሸፍንና ተማሪዎች የተማሩትን ይዘቶች የሚፈተኑ መሆኑን ይገልጻል፡፡
ብሔራዊ ፈተናው ከ10ኛ እስከ 12ኛ ክፍሎች የአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ይዘቶችን መሠረት ያደረገ እንደሚሆን ተጠቁሟል፡፡
በ2015 ዓ.ም የሙከራ ትምህርት ቤቶች 9ኛ ክፍልን በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት፤ ሌሎቹ ደግሞ በቀድሞው ስርዓተ ትምህርት የተማሩ በመሆኑ ፈተናው ከሁለቱ ስርዓተ ትምህርቶች የጋራ የሆኑ ይዘቶች ተጣጥሞ የሚወጣ መሆኑ ተገልጿል፡፡
በአጠቃላይ ትምህርት ስርዓተ ትምህርት ሪፎርም መሠረት የሁለተኛ ደረጃ አዲሱ ስርዓተ ትምህርት በ2015 ዓ.ም የሙከራ ትግበራ በማካሔድ ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሙሉ ትግበራ መገባቱ ይታወቃል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
Via @tikvahuniversity
የተከበራችሁ በጉድኝት ማዕከላችን ለምትገኙ የግልና የመንግስት ተቋማት የ2018ዓ.ም የውጪ ኢንስፔክሽን ከየካቲት 3 ጀምሮ እንደሚካሄድ ይታወቃል ሰለዚህ ኢንስፔክሽን ያላችሁ ተቋማት በቂ ዝግጅት እንድታደርጉ እያልን በአካል በመገኘት ድጋፍ እስከምናደርግ በማንኛዉም ጉዳይ መረጃ እና ድጋፍ ከፈለጋችሁ በስልክ መገናኘት የምንችል መሆኑን እያሳወቅን የተለያዩ ደንቦችና መመሪያዎች በጉድኝት ቴሌግራማችን ላይ ማውረድና መጠቀም እንደምትችሉ እናሳስባለን። ለደረጃ 3 እና በላይ ወደፊት ✈️✈️✈️
የተከበራችሁ በጉድኝት ማዕከላችን ለምትገኙ የግል ትምህርት ቤቶች የ1ኛ መንፈቀ አመት የጉድኝት ፈተና በጋራ እንደምናዘጋጅ ከዚህ የተወያየን መሆኑ ይታወቃል ነገር ግን በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ፈተና በጉድኝት ደረጃ ማዘጋጀት የማንችል መሆኑን እያሳወቅን ሁሉም ት/ቤቶች የራሳችሁን ፈተና የፈተና እቅድ በተከተለ ጥያቄ አዘጋጅታችሁ ቢሮ ባወጣዉ ፕሮግራም መሠረት ተግባራዊ እንድታደርጉ እያልን በእለቱ ድጋፍና ክትትል እንደምናደርግ እናሳውቃለን።
Repost from N/a
ማስታወቂያ
ጥር 5/2018 ዓ.ም
ጉዳዩ:- የ2018 ዓ.ም ትምህርት ዘመን የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ምዝገባ ስልጠናን ይመለከታል፡፡
ከላይ በርዕሱ ለመጥቅስ እንደተሞከረው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የከተማ
አቀፍ ፈተና የተፈታኞች ምዝገባ ለማከናውን ዝግጅት አጠናቋል፡፡
በመሆኑም የአስፈታኝ ትምህርት ቤቶችን ዝርዝር በመያዝ ማለትም
1ኛ. የት/ቤቶች ዋና ር/መምህራን
2ኛ. የክ/ከተማ ፈተና ባለሙያዎች
3ኛ. በየት/ቤቱ መዝጋቢ አካለት ብዛት 1 በ6/05/2018 ዓ.ም የመንግስት ት/ቤት ከጠዋት 2፡30 -6፡00
4ኛ.በ6/05/2018 የግል ት/ቤት ከሰዓት 8፡00-10፡00 በተቀመጠው የስልጠና ፕሮግራም እና የስልጠና ቀን
መሰረት ትምህርት ቢሮ 12ኛ ፎቅ መሰብሰቢያ አዳራሽ እንዲገኙ ጥሪ እንዲተላለፍ እናሳስባለን ፡፡
ማሳሰቢያ
1.የክ/ከተማ ፈተና ባለሙያዎች ጠዋት እና ከሰዓት በሁለት ተከፍለው መምጣት አለባቸው 2.የት/ቤት ዋና ር/መ/ር ብቻ በስልጠናው ላይ መሳተፍ ይኖርበታል መወከል አይቻልምከሰላምታ ጋር #አዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር ትምህርት ቢሮ
