904
Subscribers
-124 hours
-37 days
No data30 days
Posts Archive
Repost from T Educational info 🌿🌿🌿🌿🌿
ለሁሉም የመንግስትና የግል 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች
ከላይ በርዕሱ ለመግለጽ እንደተሞከረው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በ2017 ዓ.ም የሂሳብ እና እንግሊዝኛ ትምህርቶችን ውጤት ለማሻሻል የተለያዩ ስትራቴጂክ እቅዶችን አዘጋጅቶ ተግባራዊ እያደረገ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ከነዚህ ስትራቴጂክ እቅዶች መካከል አንዱ የሂሳብ እና እንግሊዝኛ ቤተ ሙከራ ስታንዳርድ ማኑዋል ተግባራዊ ማድረግ መሆኑን በመግለጽ በቁጥር አ22/14.933/አ28-40/35 በቀን 29/05/2017 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ አሳውቆናል፡፡
ስለሆነም በሁሉም 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች የሂሳብ እና እንግሊዝኛ ቤተ ሙከራ ስታንዳርድ ማኑዋል መሠረት በማድረግ ተግባራዊ እንዲደረግ ከዚህ ሸኚ ደብዳቤ ጋር 32 ገጽ አባሪ በማድረግ የላክን መሆኑን እንገልጻለን፡፡
Repost from N/a
አንድ የሂሳብ መምህር በክፍለ ጊዜው ለማስተማር ወደ ክፍል ሲገባ ያጋጠመው ነገር እጅግ አስገራሚ ነበር። ተማሪዎቹ ተረባርበው የመምህሩን መቀመጫ ወንበር ጣሪያ ላይ አንጠልጥለውታል።
መምህሩ ወደ ክፍሉ ሲገባ ተማሪዎቹ "ምን ሊለን ይሆን?" በሚል ጉጉት በዝምታ ይጠባበቁት ጀመር።
መምህሩ ሁኔታውን ተመልክቶ
"ይህንን ያደረገው ማን ነው?" ሲል ጠየቀ።
ክፍሉ በጸጥታ ተዋጠ። ማንም ሊናገርና ሊተነፍስ አልደፈረም።
በዚህ ጊዜ መምህሩ በቁጣ መጮህ ወይም ተማሪዎቹን ማንገላታት አልመረጠም።
ይልቁንም በልቡ እንዲህ አለ፡
"የተማርኩት እውቀት እንዲህ ላለ ቀላል ችግር መፍትሄ ካላስገኘልኝማ ምኑን ተማርኩት?"
ፈገግ ብሎ ምንም እንዳልተፈጠረ በማስመሰል ወደ ጥቁር ሰሌዳው አመራና እንዲህ አለ፦
"ተማሪዎች፣ ዛሬ አስገራሚ የፈተና ቀን ነው። ከ60 ነጥብ የሚታሰብ ፈተና አዘጋጅቻለሁ። ወረቀት አውጡና የሚከተሉትን ሶስት ጥያቄዎች በ30 ደቂቃ ውስጥ መልሱ።"
ሰሌዳው ላይ የተፃፉት ጥያቄዎች እነዚህ ነበሩ፦
ጥያቄ 1፡ በወንበሩና በወለሉ መካከል ያለውን ርቀት በሜትር አስሉ? (2 ነጥብ)
ጥያቄ 2፡ በወንበሩና በጣሪያው መካከል ያለውን የጂኦሜትሪ ግንኙነት አብራሩ? (2 ነጥብ)
ጥያቄ 3፡ ወንበሩን ጣሪያው ላይ የሰቀለውን ተማሪ እና የተባባሪዎቹን ስም ዝርዝር ጻፉ? (56 ነጥብ)
ተማሪዎቹ የ3ኛው ጥያቄ ነጥብ እጅግ ከፍተኛ መሆኑን ሲመለከቱ ተደናገጡ። ለአንደኛውና ለሁለተኛው ጥያቄ ሳይጨነቁ፣ 56 ነጥቡን ላለማጣት ሲሉ የወንጀሉን ፈፃሚ ስም ከነአባቱ ዘርዝረው አስረከቡ።
መምህሩም በፈገግታ ወረቀቱን ተቀብሎ ውጤቱን ካረጋገጠ በኋላ፣ ዋናውን ጥፋተኛ ጆሮውን ይዞ ከክፍል አስወጣው።
ከመውጣቱም በፊት ለተማሪዎቹ አንድ ትልቅ መልዕክት አስተላለፈ፡-
"#መምህር የሆንኩት ተምሬ እንጂ በዕድል አይደለም!"
#መምህራን ተመሳሳይ ገጠመኞች አጋጥመዋችሁ ያውቃል? ካላችሁ ልምድ ወይም #ከሰማችሁት ገጠመኝ #አጋሩን
