en
Feedback
"!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"

"!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"

Open in Telegram

ወቅታዊ ሃይማኖታዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ይዳሰሱበታል!

Show more
2 886
Subscribers
+124 hours
+37 days
+1530 days
Posts Archive
ዓመቱ በሙሉ በማውራት አለቀ። አሁንም ማውራት ከዚያም ማውራት ማውራት... ነጥብ ያለው ተግባር ካልተፈጸመበት ዓመቱ በሙሉ በፍሬ የተሞላ አይሆንም። ከማውራት ዓመት ወደ መልካም የወሬ ዓመት ልንል ትንሽ ቀርቶናል።

የጀርመን ክርስትና” አቀንቃኞች የዘር ሕጎችን በእምነታቸው ውስጥ ከፍ አድርጎ መደገፍ ከእግዚአብሔር የተጣለባቸው የመገለጥ አደራ እንደሆነ ይሰማቸዋል። በጀርመን ክርስትና ቸርች 10 ነጥቦች ያለው መመሪያ ሲያሳትሙ ማዕከል ያደረገው ዘረኝነትን ነበር። ሰባተኛው ነጥብ እንዲህ ይል ነበር፡- “እግዚአብሔር ዝርያን፣ አገርን፣ ብሔራዊ ሕጎችን እንድንጠብቅ አደራ ሰጥቶናል። . .ስለዚህ የዝርያ መቀላቀልን አጥብቀን መቃወም አለብን።”  እንዲሁም ነጥብ ዘጠኝ፡- “አይሁድ ለዝርያችን ጥራት ከፍተኛ አደጋ ሆነው ይገኛሉ። ተልዕኳችን እንግዳና ባዕድ የሆነ ደም ወደ ዘራችን እንዳይገባ መጠንቀቅና መጠበቅ ግዴታችን ነው። መዳቀል ደማችንን የመበከል እድል ስለሚፈጥር የአይሁድን የጀርመን ዜግነት የሚፈቅድ ሕግን እንቃወማለን። በጀርመንና በተለይ በአይሁድ መካከል የሚደረግ ጋብቻ ፈጽሞ ሊከለከል ይገባል” ይላል፡፡  በ1933 በታተመው The Handbook of the German Christians በሚል  የጀርመን ክርስትናን አቋም በሚገልጥ ዐረፍተ ነገር ላይም “የጀርመን ዜጋ ከሌላ ጋር መጋባት ከእግዚአብሔር ፈቃድ የሚቃረን ነው” ሲል ያውጃል። 

"የትናንት ለዘብተኝንትና አድርባይነት ዛሬ በቅሎ ሞት አሳጭዶናል። የዛሬ እንቅልፍና ስንፍና ነገ ባዶ ያስቀረናል።" ንዋይ ካሳሁን

Repost from Eotc Task Force
የመከራውን  ጥልቃት የማይረዳ ሕዝብ ሁሌም የጥቃት ዒላማ እንደሆነ ነው የሚቀጥለው።ትግል ቢጀምር እንኳ፦ 👉ለምን  እንደሚታገል በአግባቡ አይረዳም 👉ትግሉ በሐሰተኞች ተጠልፎ የ እንጀራ መብያ ይሆናል፣እንደ አንድ የሥራ መስክ ይቆጠራል 👉  የገዳዮች አገልጋይ ይሆናል

ክራውስ የጀርመን ክርስትናን ለማስተዋወቅ ባደረገው ጥረት ጥቃቱ በብሉይ ኪዳን ብቻ ሳይገደብ “ኢየሱስም ቢሆን” [አምላካችን ክብር ምስጋና ይድረሰውና] አለ፡- “ኢየሱስም ቢሆን ሊገለጽና ሊቀርብ የሚገባው ከብሔራዊ ሶሻሊስት ፓርቲ ፍላጎት አንፃር ነው” አለ።  የኒዮርክ ታይምስ ጋዜጣ ክራዑስ “ወደ ጀግናው አርያናዊው ኢየሱስ መመለስ አለብን፣ ጀርመኖች ኢየሱስን ተዋጊ መሪ አድርገው መሳል ይገባቸዋል” ብሎ መናገሩን ጽፏል።  በንግግሮቹ “የጀርመን ክርስትና” አራማጆች የሞቀ ጭብጨባ ይለግሱት ነበር።  ክርስትና ዘረኞች ለክፉ ዓላማቸው መጠቀሚያ ሊያደርጉት ሲሞክሩ ምን ሊመስል እንደሚችል የክራዑስ ገለጻ አሳይቷል።  የተመረጡት አዳዲሶቹ “የጀርመን ክርስትና” መሪዎች አርያን ያልሆኑ ዝርያዎችን ከየመሥሪያ ቤቶች የማስወገዱን አሠራር በቤተ ክርስቲያንም ተገበሩት።  የመጀመሪያው የአርያን አንቀጽ “ዝርያው አርያን ያልሆነ ወይንም አርያን ካልሆነ ሰው ጋር የተጋባ ሰው ካህን አይባልም”  ይላል። ከዚያም ስዋስቲካን አንግበው የናዚን ፍላጎት የሚያስፈጽሙ “የጀርመን ክርስቲያኖች” የፕሮቴስታንት ቸርች ውስጥ ተልእኮ ይዘው በመግባት የናዚ ርእዮት መምህራን ሆነው በመስቀሉ ጀርባ ተደብቅው በክርስቶስ ፈንታ ለሂትለር ታማኝ ስለ መሆንና ለጀርመን ዝርያ ልዩነት ስለ መቆም፣ ዘረኝነትንና ጥላቻን አበክረው እንዲሰብኩ ይደረጉ ነበር። የጀርመን ብሔራዊ ሶሻሊስት ፓርቲን ክርስትናን የማጥፋት እቅድ ፊት ለፊት ቆመው የሚዋጉ አያሌ ጀርመናዊ ክርስቲያኖች ነበሩ። የጀርመን ፓስተሮችና ክርስቲያኖች ቡድን በአንድነት ሆነው በዘርና በብሔር ላይ ያተኮረውን “የጀርመን ክርስትና” ንቅናቄ ተቃውመዋል። ከእነዚህ ተቃዋሚዎች መካከል አንዱ ዲይትሪች ቦንሆፈር ነው። የናዚን ሥርዓት የተቃወሙ ብዙዎች ሰዎች ቢኖሩም ቦንሆፈር የተቃውሞው ምልክት ሆኖ ወጣ። ቦንሆፈር የአርያን አንቀጽን የሚቀበል ክርስቲያን ሁሉ ከእውነተኛ ክርስትና የተለየና የሐሰት ክርስትና የሚከተል መሆኑን በኃይልና በቁጣ ያስተምር ነበር። በእንዲህ ዓይነት ጊዜ እውነተኛውን ክርስትና ለመጠበቅ ሲባል መሰደድና ከእነዚህ መናፍቃን መለየት እንደሚገባም በአጽንኦት አስተምሯል።    ለአርያን አንቀጽ መታወጅን ምላሽ የፓስተሮች የአደጋ ጊዜ ሊግ (Pastor’s Emergency League) ተመሠረተ።  የንቅናቄው መሪ የነበረ ፓስተር ማርቲን ኒሞለር (Martin Niemoller) የጀርመን ቤተ ክርስቲያንን ናዚፊኬሽን ይቃወም ነበር። ከዚህ ንቅናቄ ውስጥ የኮንፌሲንግ ቸርች ተወለደ። ቢያንስ ግማሽ ያህሉ የጀርመን ቸርች የናዚን መስመር የማስገባት (Gleichschaltung) ዶክትሪን ተቃውመዋል። ሰነዱ ሲነበብ የተቃውሞው መንፈስ በቃላቶቹ ግልጽ ይሆናል።  ቦንሆፈር የጀርመን አዋጅን “የደቀ መዛሙርትነት ዋጋ” (The Cost of Discipleship) በሚለው መጽሐፉ ውስጥ ሲገልጸው “ቤተ ክርስቲያን እንደ ብሉይ ኪዳን እስራኤል ብሔራዊ አንድነት ልትፈጥር የተሠራች ሳትሆን ከፖለቲካና አገር አጥር ውጭ የሆነች የአማኞች አንድነት ናት” ብሏል፡፡   በመጨረሻም ቦንሆፈርና ሌሎች ናዚን የተቃወሙ ሕይወታቸውን በመሥዋዕትነት ከፍለዋል።ከ1933-1945 ናዚዎች የፈጠሩት “የጀርመን ክርስትና” በአንድ በኩል፣ ነባሩ ፕሮቴስታንት ክርስትና (ኮንፌሲንግ ቸርች) ደግሞ በሌላ በኩል ያደረጉት ትግል ከባድና መራር ነበር፡፡ በ1945 ጀርመን በጦርነት ስትሸነፍ ፋሺዝም ፈጥሮት የነበረው “የጀርመን ክርስትናም” አብሮ ተሸነፈ፡፡ ኮንፌሲንግ ቸርች ደግሞ አሸናፊ ሆነ። ለኑፋቄው ንቅናቄ የሕጋዊነት ሽፋንና ሁለገብ ድጋፍ ሲሰጥ የነበረው የናዚ ፓርቲ ሲወድቅ አጋፋሪዎቹ አፋቸው ተዘጋ፣ ተበተኑም።  “የጀርመን ክርስትና” ንቅናቄ እምነት በመንግሥታት ተስፋ ሰጭነት፣ በዘረኝነትና በብሔርተኝነት ጉዳይ ሲታወር ምን እንደሚከተል ጥሩ ማስተማሪያ ሆኖ  አልፏል። ይህን የኑፋቄ ጠባሳ የጀርመን ክርስቲያኖች የሚዘክሩት የክህደት ሁሉ ቁንጮ አድርገው ነው። “የጀርመን ክርስትና” ንቅናቄ ክርስቲያኑን ከድባቴ በመቀስቀስ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል። የአገራችን አሁናዊ ሁኔታ በጀርመን ከተፈጸመው አንጻር ሲቃኝ ምን ይመስላል?  አሁን በአገራችን ያለው ሁኔታ በጀርመን አገር በናዚ ፓርቲ የተደረገውን የሚመስል ሆኖ ይታያል፡፡ አሁን በአገራችን በበተለይም ደግሞ ሁሉም የፓለቲካ ፓርቲና ነጻ አውጪ የራሱን ክርስትና እየፈጠረ ነው። የኦፒዲኦ እና የህወሀት በኦሮሚያና በትግራይ ቤተ ክህነት አቀንቃኞች ዝንባሌ ውስጥ ልዩ ኑፋቄ ተወልዷል። ክርስትናውን ለዘረኛ ፖለቲካ መገልገያነት የማመቻቸት ግብ ይዞ በመነሣት፣ የናዚ ጀርመን የፈጠረውን “የጀርመን ክርስትና” ዓይነት የብሔር ክርስትና (የኦሮሞ፣ የትግሬ፣ የሲዳማ ወዘተ) በሚል ለንዑስ ፖለቲካ-ወለድ ማንነት የሚመች ኑፋቄያዊ “ክርስትና” ለመፍጠር እየተሠራ ነው፡፡ ኦርቶዶክስን ለየብሔረሰቡ ፖለቲካ ለማስማማት ጥረት እየተደረገ ነው። መምህር ፋንታሁን ዋቄ

👆ከላይኛው የቀጠለ👇 ከቤተ ክርስቲያን የአይሁድ ዝርያ ያላቸውን ክርስቲያኖች የማግለሉ ሂደት ከናዚ እርምጃ ጋር እየተናበበ እርምጃ በእርምጃ እየተጠናከረ ሄደ። በ1935 ናዚ በኑረንበርግ አዋጁ አይሁድነትን የተለየ ዝርያ ተብሎ እንዲታወቅ አሳወጀ። ከኑረንበርጉ ሕግ በኋላ ብዙ “የጀርመን ክርስቲያኖች” የተጠመቁ አይሁዶች የሚያመልኩበት ቦታ የተለየ እንዲሆን መጠየቅ ጀመሩ።  የኑረንበርጉ ሕግ አይሁዶች በሕግ ከጀርመን ማኅበረሰብ የተገለሉ አደረጋቸው፡፡ በቤተ ክርስቲያን ውስጥም ተግባራዊ መደረግ ጀመረ።   ከ1935ቱ የኑረንበርግ ሕግ በኋላ “የጀርመን ክርስትናን” ለተፈለገው አዲስ ንቅናቄያቸው እንዲስማማ አድርገው የራሳቸው ኢየሱስ ለመሣል ሞከሩ።  ለዚህም “ኢየሱስ የአይሁድ ደም የለውም፣ ኢየሱስ አርያን (ጀርመናዊ) ነው” ብለው ደመደሙ። ንቅናቄው ትምህርቱ ተቀባይነት ያገኝ ዘንድ “ኢየሱስ በገሊላ ከሚኖሩ አርያን ጎሣ የተወለደ ነው” እያሉ እንደ ኢማኑኤል ሂንሪሽ (Emanuel Hirsch) እና ሁስተን እስቲዋርት (Houston Stewart) ያሉ ምሁራን ማስተጋባት ጀመሩ፡፡ የጀርመን ክርስትና የነገረ ክርስቶስ ማዕከሉን “ኢየሱስ ሴማዊ አይደለም” በማለት ብቻ ሳይገደብ “ኢየሱስ ዋናው ጸረ-ሴማዊ ነው” በሚል እሳቤ ላይ አደረገ።  በንቅናቄው ውስጥ የሚሳተፉት ብዙዎች የሂትለር ርእዮት ፕሮፓጋንዳ አባት የሆነውን የዮሴፍ ጎቤልስን (Joseph Goebbels) “ኢየሱስ የመጀመሪያው የአይሁድ ጠላት ነው” የሚለውን ጥሪ የተቀበሉ ነበሩ።  ዘረኝነትን ከእምነታቸው ጋር ለማስማማት ሲባል “የጀርመን ክርስትና” ንቅናቄ አይሁዳዊ የሆነውን የመጽሐፍና የአስተምህሮ ይዘት ሁሉ ከክርስትናቸው ለማጽዳት ሞከሩ። ከዚህ የተነሣም አንዳንዶቹ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን ኢቀኖናዊ ናቸው ብለው ሲክዱ  ሌሎቹ ደግሞ የብሉይ ኪዳንን ቀኖናዊት ሳይክዱ ጸረ-ሴማዊነታቸውን እንዲደግፍላቸው በማድረግ በራሳቸው መንገድ አመሰቃቅለው ይጽፉትና ይተረጉሙት ነበር። ሌሎች ደግሞ ጸረ-ሴማዊ አቋማቸውን ለማጠናከር ብሉይ ኪዳንን የሚጠቅስ ጌታ ለአይሁድ እውቅና የሰጠባቸውን የሐዲስ ኪዳንን ጥቅስ ሁሉ እያስወገዱ ወንጌልን እንደ አዲስ ጽፈዋል።        ሴማዊነትን መጥላትንና መጸየፍን ሁሉንም ጀርመናዊ በአንድነት የሚያሰባስብ የጋራ አጀንዳ አደረጉት፡፡ ኦቶ ብሮክልሸን (Otto Brokelschen) ይህን “የጀርመን ክርስቲያን” አቋም እንዲህ ሲል ይገልጸዋል፡- “የጀርመን ብሔራዊ የክርስቲያኖች አንድነት ለጀርመን ቤተ ክርስቲያን ባዕድ ናቸው ተብለው የሚታመንባቸውን ማንኛውንም ትምህርትና የአይሁድ የሚመስሉትን ነገሮች ሁሉ ከቤተ ክርስቲያን ጠራርጎ ማጽዳት አንድነትን የሚፈጥር ድል አድርገው ወስደውት ነበር።”  ጀርመናዊ አንድነት መፍጠር በሚል ስም ማንኛውንም ዶግማና አስተምህሮ ሙሉ በሙሉ ተካደ።    “የጀርመን ክርስቲያኖች” በአይሁድ ላይ ሉተር የነበረውን ጥላቻ በሁሉም ክርስቲያኖች ላይ እንዲኖር እጅግ ከመናፈቃቸው የተነሳ በ1940 ሉተርን ጠቅሰው እንዲህ ሲሉ በእምነት መጻሕፍት ደረጃ አቅጣጫ ይሰጡ ነበር፡- “የአይሁድን ምኩራቦች በያሉበት አቃጥሏቸው፣ በእሳት ለማቃጠል አስቸጋሪ የሆኑትን ደግሞ ቆሻሻ ከምሩባቸው።”  ያለዚህ ረዥም ታሪካዊ መሠረት “የጀርመን ክርስትና” ንቅናቄ መቆምም መኖርም አይችልም ይሉ ነበር።    በሌላ በኩል ሂትለር የጥላቻና ዘር የማጥፋት ዝንባሌ መነሻው የፐሮትስታንት መሥራች የሉተር አስተምህሮና ድርጊቶች ነበሩ። ሉተር በዘመኑ ለሕዝቡ አቅጣጫ ሲሰጥ “አይሁዶችና ውሸቶቻቸው /"On the Jews and Their Lies" በሚል ርዕስ በ1543 እ.አ አ ጸረ አይሁድና  እና ጸረ ሴመቲክ ጽሑፍ ጽፏል።  ሉተር በጽሑፉ አንዲህ ይላል “የአይሁድ ትምህርት ቤቶቻቸው፥ ምኩራቦቻቸውና የንግድብ ቦታቸው በእሣት መቃጠል አለበት”፥ የፈሎት መጽሐፍቶቻቸው መውደም ይገባቸዋል፥ ቤቶቻቸውና ያለቸው ሀብት ሁሉ መወረስ አለበት። ሉተር ለአይሁድ ምንም አይነት ሐዘኔታ፥ የሕግ ከለላና ርኅራኄ ማድረግ አይገባም። እነዚህ መርዞች አካባቢውን ሁሉ ስለበከሉት  ("these poisonous en”venomed worms" ) ተጭነው ወደ አስገዳጅ የጉልበት ሥራ ስፍራ መታቀብ ወይንም ለዘላለም ከዚህ አገር ተጠርገው መባረር አለባቸው።    እንዲሁም በአይሁዳውያን ላይ አልቂት እንዲታወጅ ጥሪሳያቀርብ “እንዚህን በጅምላ መርዞ አለመጨረሳችን የእኛ ስህተት ነው/  "[W]e are at fault in not slaying them" ይላል . ይህ ጽሑፍ  ከ500 ዓመታት በኋላ ለተነሳው ሂትለርና ሌሎች የጸረ አይሁድና ጸረ ሱሜቲክ ንቅናቄዎችን መሠረት ሆኗል።  ሂትለር በተነሳበት ዘመን መጽሐፉ በአስተሳሰቡ ደጋፊዎችና በፓርቲው  ዘንድ በብዛት ተሰራጭቶ ይነበብ ነበር።  በ2ኛው ዓለም ጦርነት መጽሐፉ በሰልፈኞች እጅ ተይዞ ይታይ ነበር፥ ምናልባተም ለአይሁድ እልቂት ዋና ሞተር የሆነው የዚህ የሉተር አስተምህሮ እንደሆነ ይታመናል።   ለተጨማሪ ጥናትና ንባብ ---  “የጀርመን ክርስትና” ኑፋቄያዊ ንቅናቄ ለናዚ ፓርቲ የፕሮቴስታንት ቸርችን ሰብሮ “ናዚያዊ ፕሮቴስታት” በመፍጠር የራሱ ዓላማ ማስፈጸሚያ ማድረጉ መንገዱን ቀላል አደረገለት። በዚህ ሂደት ራሳቸው ቸርቾቹ ወንጌላውያንና መምህራን ከናዚ ፕሮፓጋንዲስቶች ባልተናነሰ አገልጋይ ሆነው ተገኙ። ስለዚህ ለናዚዎች ቤተ ክርስቲያንን ለማጥፋት ከመታገል ይልቅ በመቀየር (ውስጧ ገብቶ በመቆጣጠርና ሪፎርም በማድረግ) መጠቀሙ ትርፋማነቱ ልቆ ተገኘ።  በዚህ ስሌት መሠረትነት ሂትለር የቻንሰለርነት ሥልጣኑን ባገኘ በሰባት ወር ውስጥ ሐምሌ 23፣ 1933 በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ምርጫ እንዲካሄድ ጥሪ አደረገ። ምርጫው የተፈለገው ለናዚ ፓርቲ ምቹ የሆነች ጀርመናዊት የሬይክ ቸርች (Reichskirche - Reich Church) ለመመሥረት ነበር። በጥንቃቄ በታቀደ ስልት ምርጫው ለሂትለር ግብ እንዲያገለግል ተደርጎ ተከናወነ። የቦንሆፈር ግለ ታሪክ ጸሐፊ ኤሪክ ሜታክሳስ (Eric Metaxas) የሂትለርን የቸርች ምርጫ እንደሚከተለው ያጠቃልለዋል፡- “በምርጫው ሂደት ላይ ምንም አይነት አሉታዊ ተጽእኖ ለማሳደር የሚሞክር ሁሉ በጀርመን ክርስትና ንቅናቄ “በአገር ክህደት” ይከሰሳል። ትርጉም ያለው ተቃውሞ እንዳይደራጅ የምርጫ ጥሪው በተላለፈበት ቀን እና በምርጫው ዕለት መካከል የነበረው ጊዜ አንድ ሳምንት ብቻ ነበር።”  በሂትለር በተመረጡ ሰዎች አማካይነት ከ28ቱ የፕሮቴስታንት አህጉረ ስብከቶች ከሦስቱ በስተቀር ሁሉም ቸርቾች ከምርጫው በኋላ በናዚ ርእዮትና መርሆዎች መስመር ገቡ።    እዚህ ላይ በአገራችን “ሃይማኖቶቹ ሁሉ ከኦሮሙማ በታች ናቸው”   በሚል የብልጽግና መንግሥት አሠራር የኦሮሞ፥ የትግራይ ወዘተ የዘር ሲኖዶስ ለመፍጠር ብያኔ ተሰጥቶ ሰው እስኪጨፈጨፍለት የደረሰ ተመሳሳይ ጉዞ መኖሩና ማስታወስ ለማገናዘብ ይጠቅማል።  የሂትለር እቅድ እንደታሰበው ተሳካ። የጀርመን ቸርቾች የተዋረዳዊ መዋቅራት አመራር አዲስ በተመረጠው “የጀርመን ክርስትና” መሪዎች እጅ ወደቀ። ከዚያም ዋና ሥራቸው የናዚን ርእዮተ ዓለም ማስተማር ሆነ። የተለያዩ ሰልፎችና ንግግሮችም ይደረጉ ጀመር፡፡ ከራውስ የተባለ ተናጋሪ “በክርስትና ውስጥ ያለው የአይሁድ ተጽእኖ ተቀባይነት የለውም”፣ “ብሉይ ኪዳን፣ ሐዋርያ ጳውሎስ፣ የመስቀል ምልክት ሁሉ በናዚ ርእዮት መሠረት ተቀባይነት የላቸውም”  ሲል ሃያ በሺህ ሰዎች ፊት በአደባባይ ተናገረ።

በኢትዮጵያ ምድር እየተፈጸመ ያለው የዘር ማጥፋት ወንጀል እስከ የዘር ቤተ ክህነትና ዘር ቸርች ምሥረታ ከ የ6ሚሊየን አይሁዶችን ዘር ካጠፋው ከናዚ ጀርመን ፓርቲ የተቀዳ ነው ።

ይኽን ጉዳይ እንዳትረሱት?

አንተስ? አንቺስ?
አንተስ? አንቺስ?

ቀድሶ የሚያቆርበኝን ካህኔን፣ለመንግሥተ ሰማያት እንድዘጋጅ ቃሉን የሚያስተምረኝ መምህሬን፣በጥምቀት ወንድሞቼና እህቶቼ ሆኑትን ኦርቶዶክሳውያን በጅምላ ከሚጨፈጭፉ ቤተ ክሮስቲያኔን ከሚያቃጥሉና ከሚያፈራርሱ አጥፊዎች ጋር የሚተባበር፦ 👉መዋቅር፦ አይወክለኝም 👉ጳጳስ ፦አባቴ አይደለም 👉 ሰባኪ፦ መምህሬ አይደለም 👉 ምዕመን፦ ወንድሜ አይደለም/እህቴ አይደለችም

Repost from Eotc Task Force
ኦርቶዶክሳዊነትን ማስቀጠልየምንችለው እንደ ቀደምት አባቶቻችን ኦርቶዶክሳዊ ልቡና፣ኦርቶዶክሳዊ ማያ፣ኦርቶዶክሳዊ መለኪያ፣ኦርቶዶክሳዊ ኅብረት ሲኖረን ብቻ ነው።ሰፈርተኛኛ መንደርተኛ ያዳክማታል እንጂ አያሻግራትም

Repost from Eotc Task Force
ይኽን ስንል በጥላቻ ተነሳስተን የምንጽፍ የሚመስለው አይጠፋም እኮ ።ከነቃህ ንቃ ራስህን አድን።አሊያ ግን ትሰለቀጣለህ።
ይኽን ስንል በጥላቻ ተነሳስተን የምንጽፍ የሚመስለው አይጠፋም እኮ ።ከነቃህ ንቃ ራስህን አድን።አሊያ ግን ትሰለቀጣለህ።

ዉድ የቻናሌ አባላት ሰላመ እግዚአብሔር ይብዛላችሁ።ፈቃደኛ ለሆናችሁ ብቻ አንድ አሳብ ላጋራችሁ።በአርሲ ምድር እየተፈጸመ ባለው ኦርቶዶክስ ተኮር ጭፍጨፋ አንዲት የካህን ሚስት አክራሪ የኦሮሞ እስላም
ዉድ የቻናሌ አባላት ሰላመ እግዚአብሔር ይብዛላችሁ።ፈቃደኛ ለሆናችሁ ብቻ አንድ አሳብ ላጋራችሁ።በአርሲ ምድር እየተፈጸመ ባለው ኦርቶዶክስ ተኮር ጭፍጨፋ አንዲት የካህን ሚስት አክራሪ የኦሮሞ እስላም ታጣቂዎች በ16 ጥይት ደብድበው ገደልናት ብለው ጥለዋት ይሄዳሉ።በእግዚአብሔር ቸርነት ከሞት ተረፈች  ነገር ግን እጅዋ ተቆርጧል። ይኽ ብቻ አይደለም ካህኑን ከእነ ወንድ ልጃቸው የትኩስ እሩምታ ከፍተባቸው እግዚአብሔር አትርፎአቸዋል።ሀብት ንብረታቸው ሙሉ በሙሉ ወድሟል ከብቶቻቸው ተዘርፈዋል።እነርሱም ሸሽተው ወደ አዳማ ገቡ።እዚያም ሊያገድሏቸው ሲሉ ወደ አዲስ አበባ መጡ። ይኽ ድርጊት የተፈጸመው በመርቲ ወረዳ ነው።ካህኑ አሁን የቀን ሥራ እየሠሩ ነው ከራሳቸው ጋር ስምንት(8) ቤተሰብ እያስተዳደሩ ያሉት።በዚህ ላይ ሚስታቸውን በየጊዜው ያሳክማሉ። የማገዝ  ፈቃደኛ የሆናችሁ በውስጥ መስመር አውሩኝ ከእነርሱ ጋር ላገናችሁ።በአካል ሄዶ ማግኘት የሚፈልግ ካለም አድራሻውን መጠቆም ችላለሁ።

Repost from Eotc Task Force
( Maryamawit Henok Lemessa 2017ዓ.ም እንደጻፈችው) ጾመ ፍልሰታን ያሳለፍኩት ኢትዮጵያ ነበር። ከአዲስ አበባ በስተ ሰሜን ያለ ቦታ ላይ ነው የሰነበትነው። ሰዓታት በ14 ፈጽመን የምንሸክፈውን ሸካክፈን ከሰዓት ወደ አዲስ አበባ ስንመለስ የተለያዩ የኦሮሚያ ከተሞች አቋርጠን ነውና የምናልፈው ባለፍንባቸው ከተሞች ደመራ ተደምሮ፣ የከብት እርድ ተፈጽሞ፣ የሆኑ የተደራጁ  ወጣቶች ተመሳሳይ አርማ ያለው ቲሸርትና ሴቶቹ የባህል ልብስ ለብሰው፣ ''ቢራን በርዬ'' እያሉ ሲጨፍሩ እያየን ግራ ገብቶን፣ ሁለት ሶስት ትንንሽ ከተሞችን አልፈን፣ ሁኔታው በሌለቹም ከተሞች ተመሳሳይ በሆነ ሁኔታ ሲደጋመገም መኪናችንን አቁመን ምን እየሆነ እንዳለ ለማጣራት ሞከርን። ልብ በሉ የፍልሰታ ጾሞ ውስጥ ነን ገና። ነገር ግን በየቦታው ደመራ እየተደመረ፣ ከብት እየታረደ፣ የሆነ ምንነቱ ያልታወቀ አዲስ በዓል በደመቀ ሁኔታ እየተከበረ ነበር። እዛ ካሉት መካከል "ማሊኒሞ ኩን?' አያና ማሊ ከበጃ ጅሩ?" (ምንድነው ይሄ ደግሞ? ምን በዓል ነው?) ብለን ስጠይቅ፣ "የኦሮሞ መስቀል ነው" የሚል ምላሽ አገኘን። ከመቼ ጀምሮ ነው ኦሮሞ በፍልሰታ ''ቢራን በርዬ'' እያለ ደመራ የሚደምረው? ቤተ ክርስቲያንስ የማታውቀው ደመራ ከየት መጣ? ያውም እርድ በጾመ ፍልሰታ ይፈጽማሉ? የበዓሉ ፈጻሚዎችም አስፈጻሚዎችም ኦርቶዶክሶች አይደሉም። በገንዘብ የሚደገፉ በየከተማው በመንግስት በጀት ''ገልማ'' እየተሠራላቸው ያሉ የዋቄፈና አማኞች ነን የሚሉ ናቸው። በመንግሥት sponsor የተደረገ መሆኑን የምታውቁት ባለፍኩባቸው ከተሞች ሁሉ ተመሳሳይ ዝግጅት፣ ሰፊ የሆነ ገንዘብ የፈሰሰበት ትልልቅ ድግስ እየተደረገ መሆኑን ስትመለከቱ ነው። ለወጣቶቹ ተመሳሳይ አርማ ያለው ልብስ ተዘጋጅቶ እንዲለብሱ ተደርጓል። ሕዝቡ ከአስፋልቱ ግራና ቀኝ ቆሞ ግራ በገባው ስሜት ይታዘባል። ከቅዳሴ መውጫ ሰዓት ነውና ነጠላ የለበሱ ብዙ ምዕመናን ራቅ ራቅ ብለው ቆመው ያታያሉ። የበዓሉ ባለቤቶችም ተሳታፊዎችም እነዚህ ቲሸርት ታትሞ እንዲለብሱ የተደረጉና ደመራውን ከበው እየበሉ እየጠጡ ያሉ ወጣቶች ናቸው። ይህ ድርጊት ምን እንደሆነ ለመገመት ብዙም አላሰብኩም። መንግሥት የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንን ማሕበራዊ መሠረት ከሕዝቡ ለማራቅ እየሠራ እንደሆነ ግልጽ ነው። ሁላችንም እንደምናውቀው፣ የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የመስቀል ደመራን በትውፊት መስከረም 17 እንዲከበር ታደርጋለች። የኦሮሞ ማሕበረሰብም በተለይ የሸዋ (የቱለማ) ኦሮሞ ጽኑ ኦርቶዶክሳዊና ከኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን በዓላት ጋር ሕይወቱ የተሳሰረ ነው። ይበልጡኑ ከመስቀልና ከደመራ ጋር የማይነጣጠል ትስስር አለው። ይህንንም ደመራ በመስከረም 16 ማታ እና በመስከረም 17 ማለዳ ላይ ያከብራል። "ቢራን በርዬ"ም(መስከረም ጠባ) የሚለው ያኔ ነው። ከጨለማ ወደ ብርሃን ወጥቻለሁ ሲል። ይህን የሕዝብና የቤተ ክርስቲያን ግንኙነት ለመበጣጠስ በተለያዩ ጊዜያት ብዙ ሙከራዎች ተደርገዋል። ነገር ግን በነሱ ግምት ያሰቡትን ያህል አልሄደላቸውም። አሁን ደግሞ እየተሄደበት ያለው መንገድ፣ ሕብረተሰቡ ከቤተ ክርስቲያን የወረሳቸውን በዓላት በመንጠቅና ከቤተ ክርስቲያን ጋር በሚጋጩ ቀናት እንዲከበሩ ማድረግ ነው። የዚህ በዓል ባለቤትነትም በአባቶቻችን በጾምና በጸሎት ለተደመሰሰው ለዋቄፈና አምልኮት (አምልኮተ ቦረንቲቻ) እየተሰጠ ነው። ይህ ተመሳሳይ ድርጊት በታላቁ የጌታ ጾም (ዐቢይ ጾም) ጊዜም  እየተጠበቀ ላለፉት ዓመታት ተፈጽሟል። በመንግሥት ስፖንሰር አድራጊነት በከተማ አደባባዮች በሰሙነ ሕማማት ከብቶች ታርደው ወጣት ሰብስበው ያበላሉ፣ "ኢሬቻ አርፋሳ ቱሉ"' እየተባለ ይከበራል። ይህ ሁሉ የሚደረገው፣ በኦርቶዶክስ እምነቱ ጠንካራ የሆነው የቱለማ ኦሮሞ ከቤተ ክርስቲያን ጋር ያለውን ጥብቅ ትስስር እንዲያጣ ለማድረግ ነው። አቡነ ሳዊሮስና ሌሎች አባቶች ይህን ሁሉ እያዩ ዝም ብለዋል። ሸገር ሲቲ የሳቸው ሀገረ ስብከት ነው። ደቡብ ምዕራብ ሸዋም የሳቸው ነው። ምዕራብ ሸዋ የአባ ገብርኤል ነው። ኦርቶዶክሳዊነት ሰፊ መሠረት ያለው በነዚህ አካባቢዎች ነው። "የቤተ ክርስቲያን በዓላትንና መገለጫዎችን ለዋቄፈና አሳልፋችሁ አትስጡ!" ወይም "ይህ በመንግሥት የሚደረግ ቤተ ክርስቲያንን የመገዳደር ተግባር ነው!" ብለው እንኳን ለመናገር አልደፈሩም። አይደፍሩምም! ... ከስር ያለውን ፎቶ ያነሳሁት በአንዲት ትንሽ ከተማ ውስጥ በቀን ነሐሴ 14/2017 ነው። አዲስ አበባ ከገባሁ በዃላም እንዳጣራሁት በምስራቅ ሸዋ ዞን ብቻ ሳይሆን በሸገር ሲቲ፣ በምዕራብ ሸዋ ባሉም ከተሞችም በነሐሴ 14  እና 15 የከተማ አስተዳደሮቹ ሙሉ ወጪውን ሸፍነው ንሄንን ምንነቱ ያልታወቀ የነጠቃ በአል ሲከበር እንደነበር አረጋግጫለው። https://t.me/EotcTaskForce

ምንድን ነው እየሆነ ያለው? በዚህ በስምንት ዓመት በእኛ ላይ ያልደደረሰ የግፍ ዓይነት የለም።ብዙዎቻችን አካላዊ ጥቃቱን ብቻ ነው የምንረዳው ነገር ግን ዘርፈ ብዙ ጥቃቶች ናቸው የከተፈቱብን።እስኪ በጥቂቱም እንመልከት፦ ፩ ኦርቶዶክሳዊነት ራሱ የአማራ  የምንሊክ ሃይማኖት ነው  እየተባለ እንዲዳከም እየተከረገ ነው ፪ ከታሪክ መዝገብ እየተፋቅን ነው።የሦስት ሺህ የታሪክ ልዕልናችን በ 150 ዓመት እየተተካ ነው።ከመጽሐፍ ቅዱስ ሳይቀር እየፋቁን ነው። ፫ ኦርቶዶክሳዊ አሻራዎችና ምልክቶች እየወደሙ ይገኛሉ ፬  ኦርቶዶክሳዊ እሴቶች እየጠፉ ነው ፭  ሀገርን ያቆሙ ትውልድን የቀረጹ ኦርቶዶክሳዊ ባህሎቻችን እንዲጠፉ እየተደረገ ነው ፮ ኦርቶዶክሳዊ በዓሎቻችን  ሴኩላር እንዲሆኑ፣ እንዲደቡዝዙ እና በሌሎች እንዲተኩ እየተደረገ ነው። 👉የአደባባይ በዓላት ፖለቲከኞች የሐሰት ፕሮፓጋንዳ የሚነዙበት ሆኑአል 👉የአደባባይ በዓላት ሕዝቡ በነጻነት እንዳያከብር ከፍተኛ የታጠቀ ኀይል ተሰማርቶ እንዲረብሽ እየተደረገ ነው 👉 ሆን ተብሎ ታስቦበትና ታቅዶበት የመስቀል በዓልን በኢሬቻ፣ደብረ ታቦርን እና የካቲት 16 በ መስቀላ ኦሮሞ(የኦሮሞ መስቀል)፣የዘመን መለወጫ (ቅዱስ ዮሐንስን) በአያና ቃሜ፣ሰሙነ ሕማማትንና ትንሳኤን "ኢሬቻ አርፋሳ ቱሉ" እየተተኩ ነው።ኦርቶዶክሳዊ በዓላትን በሌሎች የመተካት ሥራው እየተሠራ ያለው ደግሞ በሸዋ ኦሮሞ ኦርቶዶክሱ ላይ ነው። ለዚህ በአል sponsor የሚያደርገው ለወጣቶቹ ሳይቀር ተመሳሳይ ልብስ የሚያሰፋው በጾም ወቅት በሬ እያረደ የሚያበላው መንግሥት ነው። በርግጥ ይኽን ስል  ጭንቅላታቸው በዘረኝነት የጠበበ ሰዎች ይሳደቡ ይሆናል እውነታው ግን ይኽ ነው።ከዚህ የምንረዳው ሥርዐቱ ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ከስሯ ነቅሎ ለማጥፋት እየሠራ መሆኑን ነው። በአዲስ አበባ ከተማ ሳይቀር በየአደባባይ እየተደረጉ ያሉ እንቅስቃሴዎች የፕሮጄክቱ አካል ናቸው።ሊመርህ ይችላል ዋጠው።     ኢዮሳፍጥ ጌታቸው          01/13/2018 ዓ.ም

አንወሻሽ ከእግዚአብሔር ቃል ይልቅ የህወሕትና የኦነግ የጥላቻና የሐሰት ትርክት ነግሦብናል።አብዛኞቻችን ዘረኞች ነን።ታዲያ ከእኛ በላይ የቤተ ክርስቲያን ጠላት አለ እንዴ?

+1
መርካቶ በዚህ መልኩ እየነደደች ነው እ

የቤተ ክርስቲያን መዋቅር በኢአማኒ፣ በጠላት ተላላኪዎች፣በስሑታን ፖለቲከኞች፣በዘረኞች፣በሆዳሞችና ድሎት ፈላጊዎች፣በአቅመ ቢሶች፣በጨካኞችና  በምንደኞች እጅ ላይ በመውደቁ የኦርቶዶክሳውያን ፍጅት ሊቆም አልቻለም በ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ስለ ሞታችን እንኳ ማውራት እንደ ወንጀል ተቆጠረብን።በየቀኑ የሞት ዜና እየነገሩ መኖር ሰለቸን።ዝም ብንልም ሕመም ብንናገርም ሕመም።