"!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
Відкрити в Telegram
2 886
Підписники
-124 години
+157 днів
+10030 день
Архів дописів
Repost from Eotc Task Force
+2
መዝግባችሁ ያዙ
በሀዲያ ዞን አመካ ወረዳ ጽንፈኛ ፕሮቴስታንቶችን አሰማርተው የቡታራ ኢስጢናፋኖስ ቤተ ክርስቲያንን ያስፈረሱና ኦርቶዶክሳውያንን ያስጨፈጨፉ የብልጽግና ወንጌል(የፕሮቴስታንት ) ባለሥልጣናት፦
፩ አቶ ደገፈ ሞላንጎ (የአመካ ወረዳ አስተዳዳሪ)
2)ኢ/ር እሸቱ አዳነ አሼቦ( የአመካ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ)
3)፶ አለቃ ጡምሲዶ ሞላጎ(የወረዳው ሰላምና ጸጥታ ሀላፊ)
የጊዜ ጉዳይ ነው ሁሉም የዘራውን ነው የሚያጭደው
ቀጣዩ የፋና ዜና
"በሀገራዊ ምክክሩ ላይ ለመሳተፍ መቃብር ፈንቅለው ለመጡ ሰዎች ምክክሩ እስኪጠናቀቅ ድረስ አስፈላጊውን ድጋፎ እናደርጋለን ሲሉ ከንቲባዋ ተናገሩ"
ዳግም የድሮን ጥቃት ይፈፀምብናል በሚል የገዳሟ ተማሪዎች እየተሰደዱ መሆኑ ተነገረ!
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በደቡብ ወሎ ሐገረ ስብከት ከመካነሰላም ከተማ በቅርብ ርቀት ዓባይ ድልድይ አከባቢ በምትገኘው የዓባይ ቅድስት አርሴማ ገዳም በድሮን መደብደቧን ተከትሎ በገዳሟ ውስጥ ይማሩ የነበሩ የአብነት ተማሪዎች ገዳሟን ለቀው እየተሰደዱ መሆናቸው ታወቀ።
ፅረ ሕዝቡና ሃገር አውዳሚው የብልፅግና አገዛዝ ሐምሌ 15/2018 ዓ/ም ማርፈጃውን በገዳሟ ላይ የድሮን ድብደባ መፈፀሙ ይታወቃል።
ጥቃቱን ተከትሎ በገዳሟ ውስጥ መንፈሳዊ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ የአብነት ተማሪዎችና አንዳንድ አበው መምህራን ልባቸው እጅጉን በመሰበሩ አካባቢውን እና ገዳሟን ጥለው ለመሰደድ መገደዳቸውን መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ ችሏል።
የብልፅግናው አገዛዝ ስለ ሀገር አንድነትና ሰላም በሚፀልዩ መናንያን መነኮሳትና ገዳማት እንዲሁም አብያተክርስቲያናት ላይ በሰው አልባ አውሮፕላንና በሜካናይዝድ መሣሪያዎች ታግዞ የሚፈፀመው እልቂትና ውድመት ተባብሶ ቀጥሏል።
ሀገር እያስተዳደርኩ ነው የሚለው ይሄው ኦህዴድ መሩ የብልፅግናው አገዛዝ፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በደቡብ ወሎ ሐገረ ስብከት ከመካነሰላም ከተማ በቅርብ ርቀት ዓባይ ድልድይ አከባቢ በምትገኘው ዓባይ ቅድስት አርሴማ ገዳም ውስጥ ታቅበው ስለ ነፍሳቸው መዳን፣ ስለ ሀገር አንድነትና ሰላም፣ ስለ ሰው ልጆች ሁሉ በሚፀልዩ መናንያን መነኮሳት ላይ ሐምሌ 15 /2018 ዓ/ም በፈፀመው ዘግናኝ የድሮን ጥቃት ሁለት መናንያን መነኮሳት ለሕይወተ ሕልፈት ሲዳረጉ በርካቶች ደግሞ ለከባድ የአካል ጉዳት መጋለጣቸውን መረብ ሚዲያ በእለቱ መዘገቡ አይዘነጋም።
በጥቃቱ በመነኮሳቱ ላይ ከደረሰው እልቂት በተጨማሪ፡ የገዳማውያኑ የዓመት ቀለብ እህልና ጥራጥሬ፣ ተግባር ቤት፣ ማብሰያ እቃዎች፣ የውሃ ማጠራቀሚያ ታንከር ሙሉ በሙሉ መውደማቸው ተረጋግጧል።
በዚህም መናኒያኑ የለት ቀለባቸውና በዛ በርሃ ውስጥ የመጠጥ ውሃ የሚያጠራቅሙበት የውሃ ታንከር በመውደሙ ምክኒያት ለረሃብና ለከባድ የውሃ ጥም ተጋልጠዋል።
በዚህ ምክኒያት እና ዳግም ጥቃት ይፈፀምብናል በሚል ስጋት በገዳሟ ውስጥ ይማሩ የነበሩ የአብነት ተማሪዎችና አንዳንድ አበው መምህራን ገዳሟን ለቀው እየተሰደዱ ስለመሆናቸው ነው መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ የቻለው።
በዚኸው ሃገረ ስብከት በመኃል ሳይንት ወረዳ በታሪካዊቷ ታዕካ ነገስት አትሮንስ ማርያም ቤተክርስቲያን ላይ የካቲት 28/2018 ዓ/ም ማርፈጃውን በተፈፀመ የከባድ መሣሪያ ጥቃት፡ ሁለት ካህናትና ሦስት ዲያቆናት እንዲሁም አንዲት የቤተክርስቲያኗ አቃቢ በድምሩ ስድስት ንፁኋኖች ሲገደሉ ከ20 በላይ ንፁኋኖች ደግሞ ለከባድ የአካል ጉዳት መጋለጣቸውን በእለቱ ጣቢያችን መረብ ሚዲያ የአይን እማኞችን ዋቢ አድርጎ መዘገቡ አይዘነጋም።
በአብርሃ አፅብሃ ዘመነ መንግስት እንደተመሠረተች የሚነገርላት ታሪካዊቷ ታዕካ ነገስት አትሮንሰ ቅድስተ ማርያም ቤተክርስቲያን፡ በርካታ ነገስታት ንግስናቸውን የተቀበሉባትና ከበርካታ ነገስታት በስጦታ መልክ የተሰጠችውን ልዩ ልዩ ታሪካዊ ቅርሶችን በውስጧ የያዘች ከሐይማኖታዊ ስፍራነቷ ባሻገር በአከባቢው እንደሙዝየም የምታገለግል ደብር ናት።
በዚች ታሪካዊትና እድሜ ጠገብ ቅድስት ቤተክርስቲያን ላይ የካቲት 28/2018 ዓ/ም ማርፈጃውን በጄነራል ዘውዱ ሰጣርጌ የሚመራው የብልፅግና መከላከያ ሰራዊት ተከታታይ የመድፍ ድብደባ ተፈፅሟል።
በጥቃቱ የአትሮንስ ማርያም ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ ቆሞስ አባ ሞገስ ፍስሃ፣ የቤተክርስቲያኗ አቃቢ እማሆይ ድንቄ ታከለን ጨምሮ ሌሎች ስድስት የቤተክርስቲያኗ አገልጋይ ቀሳውስትና ዲያቆናት ሲገደሉ ከ20 ፡ብላይ ንፁኋኖች ነቁሰላቸውን ነው በእለቱ ጣቢያችን ዘግቦ የነበረው።
መረብ ሚዲያ
በዚህ ዘመን ጳጳስና የከተማ ኩብኩባ ከሆንህ ረሃብ የለ፣ጥም የለ፣ኑሮ ተወደደ የለ ፈታ ብለህ ሥጋ እየቆረጥህ ውስኪውን እየጨለጥህ መኖር ነው።ይኽ እንግዲህ ለአባ ቶማስ በዓለ ሲመት የተደገሰ ድግስ ነው። ተመልከቱት ቁርጡን፣ቅቅሉን ፣ቀይ ወጡን ።ኩብኩባዎቹ ልኩን ሊያሳዩት ዙርያውን ከበውታል😁
ኃላፊው የፕሮቴስታንት እምነት ተከተይ ስለሆኑ ከፍተኛ የኦርቶዶክስ ጥላቻ አለባቸው - የወረዳው ቤተ ክህነት
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት የአመካ ወረዳ ቤተ-ክህነት ጽሕፈት ቤት ጉዳዩን አስመልክቶ ይፋዊ አቤቱታውን ባቀረበበት ደብዳቤ ላይ በቦታው የሚኖሩ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከተዮች ለዘመናት አስከሬን ተሸክመው ከ20 ኪሎ ሜትር በላይ አቋርጠው በመጓዝ ለብዙ ዓመታት መቆየታቸውን አስታውሷል።
አሁን ግን ቁጥራቸው ከ300 በላይ የሆነ ምዕመናን በአካባቢያቸው የቤተክርስቲያን መስሪያና የመቃብር ቦታ ከግለሰብ በስጦታ ማግኘታቸውን ገልጿል።
ቦታው ከሌሎች የእምነት ተቋማት ጋር የድምጽ መረባበሽ እንዳይኖር ህጋዊና ርቀቱን ጠብቀው በስጦታ ባገኙት ቦታ ላይ የተገነባ መሆኑን ገልፆ ይሁን እንጂ የሌሎች እምነት ተከታዮች ለወረዳው ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ተቃውሟቸውን አቅርበዋል ብሏል።
ቤተክህነቱ በአካባቢው የሚኖሩ የልዩ ልዩ ሃይማኖት ተከተዮች እርስ በእርስ በመከባበርና በሰላም አብረው የሚኖሩ ቢሆንም፣ የአመካ ወረዳ የሰላምና ፀጥታ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የፕሮቴስታንት እምነት ተከተይ በመሆናቸው እና ከፍተኛ የሃይማኖት ጥላቻን በሚገልጽ መልኩ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አጥር እንድታፈርስና በአካባቢው ምንም ዓይነት ልማት እንዳይካሄድበት በማድረግ ከፍርድ ቤት አሰራር ውጪ እና ያለ አግባብ ሥልጣናቸውን በመጠቀም ፍትሕ እንዳናገኝ አድርገዋል ሲል አስታውቋል።
ይህንንም ተከትሎ ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ሰዓት ላይ የተደራጁ የፕሮቴስታንት እምነት ተከተዮች ይዞታውንና ንብረቱን ይጠብቁ በነበሩ 6 የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከተዮች ላይ ድገተኛ ጥቃት በመሰንዘር ከፍተኛ አካላዊ ድብደባ’ ፈጽመውባቸዋል ሲል ገልጿል።
በተጨማሪም ድምጽ በሌለው መሣሪያ አማካይነት ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል ያለ ሲሆን፣ በቦታው ላይ የነበረውን ሕንፃ በማፍረስና ንብረቱንም ሙሉ በሙሉ በማፍረስ ከፍተኛ ውድመት አድርሰዋል ብሏል።
በመሆኑም የወረዳው አስተዳደር ጽሕፈት ቤት በድርጊቱ ላይ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ወንጀለኞችን በፍጥነት ለሕግ እንዲያቀርብና ተገቢው አስተማሪ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ይገባል ሲል ጠይቋል።
አክሎም ጉዳት የደረሰባቸው ምዕመናን አስፈላጊውን ሕክምና እንዲያገኙና ለወደመው ንብረት ተመጣጣኝ ካሣ በሕግ አግባብ እንዲከፈላቸው እንዲሁም በፈረሰው ቤት ምትክ ሌላ ቤት ተገንብቶ ለአገልግሎት እንዲበቃ ቤተ-ክህነቱ ጠይቋል።
የሃይማኖት እኩልነትና ነፃነት እንዲረጋገጥ፣ የሕግ የበላይነት እንዲከበርና ለቤተ ክርስቲያኗና ለምዕመናን ተገቢው የሕግ ከለላ እንዲሰጥ ጥሪ ያቀረበ ሲሆን ይህ አቤቱታውንም ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ፣ ለክልሉ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ፣ ለሀዲያ ዞን ሰላም እና ጸጥታ መመሪያ፣ ለዞኑ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ እንዲሁም ለሀዲያ እና ስልጤ ሀገረስብከት ግልባጭ እንደላከ በደብዳቤው ጠቅሷል።
#ቦርከና_ዜና
#ቅዱስ_ቂርቆስና_እናቱ_ቅድስት_ኢየሉጣ (#ሐምሌ_19)
ሐምሌ ዐሥራ ዘጠኝ በዚህች ቀን ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ በሰማዕትነት መከራ ተቀበሉ። ይህም ሕፃን ዕድሜው ሦስት ዓመት ሲሆነው ከሮሜ አገር ወደሌላ ሀገር እናቱ ይዛው ሸሸች በዚያም የሸሸችውን መኰንን አገኘችው።
ሰዎችም ነገር ሠሩባት ወደርሱ አስቀረባትና ስለ አምልኮ ጠየቃት እርሷም መኰንን ሆይ ዕድሜው ሦስት ዓመት የሆነው ሕፃን አለ አማልክቶችህን ማምለክ መልካም እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ያስረዳን ዘንድ እርሱን ጠይቅ አለችው።
ሕፃኑም ወደአለበት ጭፍራውን ልኮ ወደርሱ አስመጣው ሕፃኑንም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና አንተ ደስተኛ ሕፃን ሆይ እንዴት ነህ አለው። ሕፃኑም መልሶ አዎ ለእኔ ደስታ ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ኀዘንና ልቅሶ ጥርስ ማፋጨትም ነው መጽሐፍ ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏልና አለው እግዚአብሔር ኃይልና ንግግርን ሰጥቶታልና ብዙ ተናገረ በዚያም ያሉትን እስከ አስደነገጣቸው ድረስ ንጉሡን መኳንንቱንና ጣዖታቱን ረገማቸው ከብርታቱም የተነሣ አደነቁ።
መኰንኑም በአፈረ ጊዜ በየአይነቱ በሆነ ሥቃይ ታላላቆች የማይችሉትን ታላቅና አስጨናቂ የሆነ ሥቃይን አሠቃየው እናቱንም ከርሱ ጋር እንደ እርሱ አሠቃያት እግዚአብሔርም ያለምንም ጉዳት ያነሣቸው ነበር። ብዙዎች አሕዛብም ይህን አይተው አደነቁ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም አምነው በሰማዕትነት ሞቱ የሰማዕትነትንም አክሊል ተቀበሉ።
በሕፃኑ ላይም የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት። ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶችንም አደረገ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳናቸው።
ከዚህም በኋላ መኰንኑ በታላቅ የናስ ጋን ውስጥ ውኃ ጨምረው በእሳት ያፈሉት ዘንድ አዘዘ የፍላቱም ድምጽ እንደ ክረምት ነጐድጓድ ሆነ ያን ጊዜም ፍርሀትና የሃይማኖት ጉድለት በእናቱ ላይ ደረሰባት ሕፃኑም ስለ እናቱ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ።
ያን ጊዜ ጌታችን ልቧን ወደ ሰማይ አሳርጎ ለቅዱሳን ሰማዕታት የተዘጋጁ የብርሃን ማደሪያዎችን አየች ከዚህም በኋላ ጸናች እግዚአብሔርንም አመሰገነችው ልጅዋንም ልጄ ሆይ ከእንግዲህ አንተ አባቴ ነህ እኔም ልጅህ ነኝ አለችው።
ያቺ ከኔ የተወለድክባትም ቀን የተባረከች ናት አለች ወደዚያ ወደ ጋኑ ውስጥ በገቡ ጊዜም የውኃው ፍልሐት እንደ ንጋት ጊዜ ውርጭ ቀዘቀዘ ከእግዚአብሔር የታዘዘ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ የእሳቱን ኃይል አቀዝቅዞታልና።
ከዚህም በኋላ መኰንኑ ሥጋቸው ተቆራርጦ እስከሚወድቅ ድረስ በመቃጥን ውስጥ አድርገው እንዲጐትቷቸው አዘዘ ከእግዚአብሔርም የታዘዘ መልአክ አዳናቸው መኰንኑም በታላቅ ሥቃይ ያሠቃያቸው ዘንድ አስቦ እስኪመክር ድረስ በወህኒ ቤት ዘጋባቸው።
ያን ጊዜም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሕፃኑ ቂርቆስ ወርዶ አጽናናው አረጋጋውም። ስሙን ለሚጠራና መታሰቢያውን ለሚያደርግ ቃል ኪዳን ሰጠው።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ሰማዕታት በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ሐምሌ ➛ስንክሳር ዘተዋሕዶ ፌስቡክ ገጽ የተወሰደ)
ይድረስ ለቅዱስ ፓትርያርክ አባ ማቲያስ
ቅዱስ አባታችን ሆይ፤
በመጀመሪያ በልዑል እግዚአብሔር ስም ሰላምታችንን እያቀረብን፤ ይህን መልእክት ለመላክ የተገደድነው በቤተ ክርስቲያናችን እና በልጆችዋ ላይ እየወረደ ያለው የመከራ ዶፍ ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ በመምጣቱ ምክንያት መሆኑን እንገልጻለን።
ለ ስምንት ዓመታት በየጊዜው የሚወጡ የ"እናዝናለን" መግለጫዎችን መስማትና ማንበብ ሰልችቶናል። እነዚህ መግለጫዎች የሕዝባችንን ሞት፣ ስደት እና የቤተ ክርስቲያናችንን ውድመት ሊያስቆሙልን አልቻሉም። ከቤተ ክህነት እስከ ቤተ መንግሥት ያሉትን ተፅዕኖዎች የምንረዳ ቢሆንም፣ ቅዱስነትዎ እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት እውነትን መስክረው ቤተ ክርስቲያንን የማስቀጠል እና ልጆችዎን ከጥፋት የመታደግ መንፈሳዊና አባታዊ ሀላፊነት አለብዎት።
ሥርዐቱ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ እያደረሰ ያለው ተፅዕኖ በመግለጫ እና በልምምጫ ሊቆም እንደማይችል ከእኛ ከልጆችዎ በላይ ጠንቅቀው ያውቃሉ ይረዳሉ።
ስለሆነም የልጆችዎ የጅምላ ፍጅት እና የቤተ ክርስቲያን ውድመት በእውነት የሚያሳስብዎ ከሆነ፤ ከዚህ በታች የተጠቀሱትን አማራጮች ተግባራዊ እንዲያደርጉልን በትሕትና እንጠይቃለን፦
1. ለዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ጉዳዩን ማሳወቅ፦
ሥርዐቱ በቤተ ክርስቲያናችን እና በልጆችዋ ላይ እያደረሰ ያለውን ፍጅት እና በደል በይፋ ለሚከተሉት አካላት በደብዳቤ እንዲያሳውቁልን፦
👉ለአኃት አቢያተ ክርስቲያናት
ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) እና ለሰብአዊ መብት ምክር ቤት
👉ለዓለም አቀፍ ሃይማኖቶች ፓርላማ እና ለምክር ቤቶች
👉ለዓለም ሃይማኖትና እምነት ነጻነት ሲቪል ማኅበራት ኮሚቴ
👉ለዩኔስኮ (UNESCO)
👉ለዓለም አቀፍ ፍትሕ ፍርድ ቤት (ICJ)
👉ለአፍሪካ ኅብረት
👉ለዓለም ሀገራት መሪዎች እና ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ
2. መንፈሳዊ ውሳኔ መስጠት፦
ይህን ማድረግ የማይቻል ከሆነ፤ "ልጆቼን መጠበቅም ሆነ መታደግ አልቻልሁም" በማለት መንፈሳዊ ኃላፊነትዎን በመወጣት ወደ ገዳም (ለምሳሌ አቅራቢያ ወደሚገኘው ደብረ ሊባኖስ ገዳም) በመግባት በጸሎት እንዲወሰኑ።
እነዚህን እርምጃዎች መውሰድ ከኅሊና፣ ከታሪክ እና ከእግዚአብሔር ፍርድ ነጻ የሚያወጣ እርምጃ ነው ብለን እናምናለን።
ቅዱስ አባታችን ሆይ፥አሁን ባለው ሁኔታ የ"እናዝናለን" መግለጫ ብቻ እያወጣን እንቀጥላለን ብለው የሚያስቡ ከሆነ ግን እርስዎም ኦርቶዶክሳውያንን የማጥፋት መንግሥታዊ ፕሮጄክቱን ይደግፋሉ ወደ ሚለው ድምዳሜ ለመድረስ እንገደዳለን። አዎ የ"እናዝናለን"መግለጫ መስማት ሰልችቶናል፣
አጥፊን የማይከስስ እና ተጎጂዎችን የማያስክስ የማጭበርበርና ከገዳዮች ጋር የመተባበር ተምሳሌት የሆነ ልፍስፍስ መግለጫ መስማት ሰልችቶናል፣፣ ገዳዩን ሥርዐት የማይከስና ፍትሕን የማያሰፍን መግለጫ መስማት ሰልችቶናል፣እልቂታችንን የማያቆም መግለጫ መስማት ሰልችቶናል።
Repost from Eotc Task Force
መግለጫ ለምን ይወጣል?
፩ በቤተ ክርስቲያንቱና በአማኞቿ ላይ እየደረሱ ያሉ ጥቃቶችን ለማሳወቅ
፪ መንግሥት ሀላፊነቱን እንዲወጣ ማሳሰብ እና ማስጠንቀቅ
፫ መንግሥት ሀላፊነቱን የማይወጣ ከሆነ እርምጃ ለመውሰድ ኦርቶዶክሳውያንን ከጥፋት ለመታደግ
የእኛዎቹ ግን ስምንት ዓመት ሙሉ መግለጫ ያወጣሉ አንድም ጥቅም አላስገኘም ።ሲኖዶሱ የሚሰጣቸው መግለጫዎች ፦
👉 እናዝናለን፣አዝነናል ሲሉ እንኳን ቅዱሱ የሰው ልጅ ከብት እንኳ የሞተባቸው ያክል አይሰማቸውም
👉እልቂታችንን የሚሸፍንና ቀጣይነት እንዲኖረው ያደርጋል
👉ለገዳዮች ሳይቀር ጥብቅና ይቆማል
👉ሕዝቡ ራሱን እንዲከላከል ወይም ሸሽቶ ራሱን እንዲያተርፍ አቅጣጫ አያሳይም
👉እየተነጋገርን ነው እየተወያየን ነው፣አጣሪ ኮሚቴ አቋቋመናል ወዘተ...እያለ የመንግሥትን አጀንዳ ያስፈጽማል
መፍትሔው ምንድን ነው?
👉ኦርቶዶክሱ ከአጥፊዎች የሚታደገው እረኛም ሆነ መዋቅር እንደሌለው አውቆ ራሱን በራሱ ይጠብቅ
እንዴት አድርገን ራሳችንን በራሳችን እንጠብቅ የሚለውን ከቤተሰቦቻችን ፣ከጓደኞቻችን፣ከሰን/ቤት፣ከማኅበራት ጋር መምከር።ቅር ብንለው እንኳን የማይቀር ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ መከራ ከፊትታችን ተደቅኗልና ከድንዛዜ ነጻ አዉጪ ከመጠበቅ እንውጣ ።
አንባቢው ይኽን ያስተውል
✍ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ የሚደርሰው ሁለተናዊ ጥቃት በመንግሥት እውቅና ተሰጥቶት የሚፈጸም ነው
✍ በእረኞቻችን ተክደናል ገንዘባችንን እንጂ እኛን አይፈልጉንም
✍ የራሳችንን ድርሻ ካልተወጣንና ካልሠራን አሁን ባለንበት ሁኔታ ከቀጠልን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ሆና እንዳትቀር ያሰጋል
Repost from ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)
ካልሰማችኹ ስሙት
"የማጥቃት ፕሮፓጋንዳ"
ይኽ ፕሮጀክት ከዚኽ ውጭ ነው ወይ? የተጠና በስልጠና ማንዋል ወጥቶለት ለካድሬ ለሌላውም የተሰጠ እንጂ ድንገት አይደለም። በደንብ ስሙት እኔ ከኹለት ዓመት ገደማ ጊዜ ሰጥቼ ነው ሰምቼ መረጃው ሳይጠፋ ያስቀመጥኩት።
📝የገዳማውያኑ ጥቃት ሥርዓታዊና ጥላቻን ያዘለው ስልት ቀጣይ ምዕራፍ ነው!
©በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከእናት ፓርቲ የተሰጠ የአቋም መግለጫ
👉ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ረፋድ 4:00 ላይ በአማራ ክልል፣ ደቡብ ወሎ ዞን፣ ቦረና ወረዳ የሚገኘው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የዓባይ ቅድስት አርሴማ ገዳም ላይ የድሮን ጥቃት ተፈጽሞ 2(ኹለት) መነኮሳይያት እናቶች ወዲያው ሲገደሉ፣ 14(አሥራ አራቱ) እናቶች ደግሞ ክፉኛ ቆስለው መካነ ሰላምና ደሴ ሆስፒታል ተወስደዋል። በጥላቻና ኾነ ተብሎ በሚመስል መልኩ በተፈጸመው ጥቃት የገዳማውያኑ የዓመት ቀለብ እህልና ጥራጥሬ ሙሉ በሙሉ የወደመ ሲኾን፣ ተግባር ቤት፣ ማብሰያ እቃዎች፣ የውሐ ማጠራቀሚያ የኮንክሪት ታንከር፣ የውሐ ማስተላለፊያ ቱቦዎች ሙሉ በሙሉ ወድማል። "በገዳሙ ሥርዓት የጠዋት 3:00 ፀሎት አድርሰን ኹሉም ወደተመደበበት ሥራ ሲሠማራ ድሮን የምትባለው ስትዞርና ድምጿን ሰምተናል፣ አይተናታል። እኛ ገዳማውያን ነን መቸም ቴክኖሎጂ ነው ያዩናል ምንም የሚያጠራጥርና የሚያስፈራን ነገር የለም ብለን ሥራችንን ቀጠልን" የሚሉት እማኝ "ነገር ግን እኛ እንዳስብነው አልነበረም ቆይተው ለሥራ በተሰበሰብንበት መዓት አወረዱብን፣ ያን የመሰለ ጭካኔ ለምን ማድረግ እንዳስፈለጋቸው ማሰብም ማለምም ይከብዳል። በተለይ የቆሰሉት ሲታዩ የሞቱት ይሻላል ያስብላል" ይላሉ።
👉ገዳሙ እጅግ ከባድ በረሃ ላይ ያለ ነው። በዙሪያው የሚገኝ ታጣቂም ይኹን ወታደር አናውቅም። እንግዲኽ ገዳሙ የቆመውም በእነዚኹ ወጣት መነኮሳይያት እናቶችች ድካም ነበር። ሠሪው ከተገደለ፣ አካሉ ከጎደለና የዓመት ቀለቡ ከወደመ ቀሪውንም የመግደል ያኽል ነው። ተጠንቶ የተደረገ ይመስላል ይላሉ ሌላው እማኝ።
👉እናት ፓርቲ ይኽ እብሪት የተላበሰ ድርጊት ከድግግሞሹ፣ እያስከተለ ከሚገኘው ጉዳትና በሌሎች አካባቢዎች ደግሞ በታጣቂዎች ሽፋን በእምነቱ ተከታዮች፣ አገልጋዮችና ገዳማት ላይ እየተፈጸመ ያለው ጥቃት ተራ ስህተት ሳይኾን ሥርዓታዊና ከጥላቻ የመነጨ ብሎም የአጥፍቶ መጥፋት ተግባር እንደኾነ በጽኑ ያምናል፤ ድርጊቱንም በጽኑ ያወግዛል። ለሞቱት ገዳማውያንም ሐዘኑን እንገልጻለን።
ስለኾነም፣
1. መላው ኢትዮጵያውያን ይኽን የአጥፍቶ ጠፊ የሽብር ድርጊት በአንድነት እንዲያወግዝ እንጠይቃለን።
2. መንግሥት ለድርጊቱ ሙሉ ኃላፊነቱን እንዲወስድና ድርጊቱ ሲፈጸም የሚያሳይ የፎቶና የቪዲዮ መረጃ ለሕዝብ ይፋ እንዲያደርግ አጥብቀን እንጠይቃለን፡፡
3. ሀገርን ከጥቃት ለመጠበቅ የተቋቋሙ ተቋሟት ሕዝብን ጅምላ ጨረሽ ወደመኾን መሸጋገራቸው መላው ሕዝባችንና ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ እንዲያውቀው እና አጥፊው አካል ተጠያቂ እንዲደረግ አጥብቀን እናሳስባለን፡፡
4. መላው ኢትዮጵያውያን በዚያ ሐሩር ለሀገርና ሕዝብ የሚፀልዩ ገዳማውያን ቀለባቸው እና የመጠጥ ውሐ በጥቃቱ ሙሉ በሙሉ በመውደሙ ቀሪዎቹ በረሃብና ጥም ከማለቃቸው በፊት እንዲደርስላቸው እንጠይቃለን።
ፈጣሪ አገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝባን ይጠብቅ!
©እናት ፓርቲ
ሐምሌ ፲፯ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ሥርዐቱ ገዳማውያንን በድሮን እያወደመ መነኮሳትን የሚጨፈጭፈው በ ስሕተት ወይም በግድ የለሽነት ሆኖ አይደለም ሆን ተብሎ ታስቦበት የተፈጸመ ነው።ለምን?
👉 ሥርዐቱ ኦርቶዶክስን ከምንጩ ለማድረቅ ገዳማትን ማው እንዳለበት አቅዶ እየሠራ ስለሆነ
👉 መነኮሳትን ማጥፋት ኦርቶዶክሳውያንን ተስፋ ማስቆረጥ
👉 ለወደፊት ለመፍጠር ላሰቡት አዲስ አገር እንቅፋት ይሆናሉ ብለው ያሰቡ የቤተ ክርስቲያንና ታሪኮችን ለመደምሰስ
Repost from Eotc Task Force
ወሀቢያ ምንድን ነው ? ከየት መጣ?
ወሀቢያ በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መሐመድ ኢብን አብደል ዋሂብ /1703-1792 ዓ.ም./ በተባለ ሰው የተመሠረተ የእስልምና ርእዮተ ዓለም ነው። ኢብን አብደል ዋሂብ ከ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ የብዙ እስላሞችን ቀልብ የሳበውን አዲሱን አክራሪ እስልምና መሠረት የጣለ ነው። ተከታዮቹ ራሳቸውን ዋሂዲኖች ብለው ይጠራሉ። ትርጉሙም “በተውሂድ የሚያምኑ” ማለት ነው።
መሐመድ ኢብን አብደል ዋሂብ የተወለደው በማዕከላዊው ዐረቢያ ከሪያድ በስተ ስሜን ዑያናህ በተባለ ሥፍራ ከሃንባሊ የእስልምና ት/ቤት ጋር ግኑኝነት ከነበራቸው ቤተሰቦች ነው። አብዛኞቹ ቤተዘመዶች ከዚህ ት/ቤት የወጡ መምህራን ናቸው። በልጅነቱ በወግ አጥባቂው የሱኒ እስልምና ትምህርት ተኮትኩቶ አደገ፡ ከዚያም ለበለጠ ዕውቀት ወደ መካ እና መዲና ተጓዘ። በሃራማየን ት/ቤት በዘመኑ ዋና የአክራሪ እስልምና አቀንቃኞች ከነበሩት ከመሐመድ ሐያት አል ሲንዲ ከፍተኛ ዕውቀት አግኝቷል። በዚያም በተለይም ሃዲትን በተመለከተ በቂ የሆነ ዕውቀት ለመጨበጥ ችሏል። አብደል ዋሂብ በሃዲት በተገለጠው የጥንቱ እስልምና አሁን በሚያየው እስልምና መካከል ያለው ልዩነት ያሳስበው ነበር።
በልዩ ልዩ ቦታዎች ተዘዋውሮ ዕውቀቱን ካጎለመሰ በኋላ ወደ ሀገሩ ወደ ናጅድ ከተማ ተመለሰ። በዚያም ሕዝቡ የያዘውን የተለመደ ዓይነት እስልምና በመተው ቃል በቃል ቁራዓንን በሱኒ የእስልምና መርህ መሠረት እንዲከተል ማስተማር ጀመረ። ምንም እንኳን መጀመርያ ላይ ብዙዎች ቢቃወሙትም የዳሪያው ገዥ ሙሀመድ ኢብን ሳዑድ ጥሪውን በመቀበል የሃሳቡ ደጋፊ ሆነ። በአክራሪው የእስልምና መምህርና በጦረኛው መሪ መካከል የተጀመረው ወዳጅነት ወታደራዊ የሆነ እስላማዊ መንግሥት ለመመሥረት በቃ። ይህ እስላማዊ ወታደራዊ መንግሥት በአጭር ጊዜ ውስጥ ግዛቱን ወደ ሌላው የዐረቢያ ልሳነ ምድር ማስፋፋት ቻለ።
ይህ ኃይል በ1802 ዓ.ም. በደቡብ ኢራቅ የነበሩትን የሺአቶች ቦታዎች አስለቀቀ፡ በ1803 ዓ.ም. ደግሞ መካን ተቆጣጠረ። በዚያም የመጀመርያው ጠንካራ የሳዑዲ መንግሥት ተመሠረተ። በወቅቱ የእስልምናውን ዓለም አንድ አድርገን እንገዛለን ብለው የተነሱት ኦቶማን ቱርኮች ሁኔታው ስላሰጋቸው በግብጽ የነበረውን ጦር ወደ ሳዑዲ ላኩት። በዚህ ምዕራባዊውን አሠራር ይዞ የነበረው የኦቶማን ቱርክና አዲስ በመነሳሳት ላይ በነበረው ዐረባዊው አክራሪነት መካከል በተደረገው ጦርነት የሳዑዲ ወሀቢያዎች ለጊዜው ተሸነፉ። በ1818 ዓ.ም. የመጀመሪያው የሳዑዲ መንግሥት ተጠናቀቀ።
ወሀቢዝም ማናቸውንም ዓይነት የሱፊ እስልምና አካሄዶችን አይቀበልም። የተቀደሱ ሰዎች የሚባል ነገርን አያውቅም፡ በዚህ ዓይነት አምልኮ የተስፋፉ ስዎችም ከእስልምና ያፈነገጡ በመሆናቸው ሞት ይገባቸዋል ይላል። ከቁርዓንና ከሱና በስተቀር ሌላ የእስልምና መጽሐፍ አይቀበልም። እስልምና ብቸኛ የድኅነት መንገድ ነው ይህንን ደግሞ ሰዎች በውድም ሆነ በግድ መቀበል አለባቸው፡ ስለዚህም የተቀደሰ ጦርነትን ማካሄድ አስፈላጊ ነው ይላል። /ሱረቱ 8:65/
ይህ የወሀቢዝም አስተሳሰብ በሶማልያ ከሚገኘው የአልሸባብ ቡድን እስከ አል ቃኢዳ ድረስ ያሉ የዘመናችን አሸባሪዎች የሚመሩበት አስተሳሰብ ነው። የሀገራችን እና የቤተ ክርስቲያናችን የዘመኑ ፈተናም ይህ ነው። ወሃቢዝም በየሀገሩ በተለያየ ስም ይጠራ እንጂ አሠራሩ ተመሳሳይ ነው፡ እስልምናን አክራሪ በሆነ መንገድ ኃይል ቀላቅሎ መጠቀም ነው። የወሀቢዝም መነሻም መስፋፊያውም ሳዑዲ ዐረቢያ ነው። በተለይም ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚደረገው የአክራሪ እስልምና እንቅስቃሴ ዋናው ድጋፍ የሚገኘው ከሳዑዲ ነው።
የ20 መክዘ የወሀቢያ መስፋፋት
1. የመንግሥት መመስረት (1932)
ዘመናዊ ሳዑዲ አረቢያ በIbn Saud ተመሠረተ። ከዚህ በኋላ ወሀቢዝም የመንግሥት ዋና ሀይማኖታዊ መርህ ሆነ። ይህ ማለት፦
✍የእምነት ትምህርት በመንግሥት ቁጥጥር ውስጥ ገባ
✍የእስልምናተቋማት በመንግሥት ድጋፍ ተጠናከሩ
✍የወሀቢ ትምህርት በአገር ውስጥ ተስፋፋ
2. የነዳጅ ድፍድፍ (1970ኛው ዘመን)
1970ኛው ዘመን የነዳጅ ዋጋ እየጨመረ ሲሄድ ሳዑዲ አረቢያ እጅግ ታላቅ ገቢ አገኘች። ይህ ገቢ የወሀቢ አስተሳሰብን ዓለም አቀፍ ለማስፋፋት ተጠቃሚ ሆነ።
በዚህ ምክንያት፦
✍በአፍሪካ፣ እስያ እና አውሮፓ መስጂዶች ተገነቡ
✍ኢስላማዊ ማዕከላት እና ትምህርት ቤቶች ተመሠረቱ
✍ወሀቢዝምን የሚያቀነቅኑ መጽሐፍት ታተሙ ወደ ተለያዩ ቋንቋዎች ተተረጎሙ
✍ለውጭ ተማሪዎች የትምህርት እድል (Scholarship) መስጠት
3. የትምህርትና ተቋማት መስፋፋት
✍Islamic University of Medina
✍Muslim World League
እነዚህ ተቋማት ከዓለም አቀፍ ተማሪዎችን በመቀበል የወሀቢያን አስተሳሰብ
ይዘው ወደ አገራቸው እንዲመለሱ አደረጉ።
4.
አፍጋኒስታን ጦርነት (1979–1989)በ1979 ሶቪየት ሀገር አፍጋኒስታንን በወረረች ጊዜ፣ ሳዑዲ አረቢያ ከአሜሪካ ጋር በመተባበር የሙጃሂዲን ኀይሎችን ደገፈች። ይህ ሁኔታ፦ የጂሃድ አስተሳሰብ እንዲስፋፋ አደረገ ዓለም አቀፍ እስላማዊ ኔትዎርኮች እንዲፈጠሩ በር ከፈተ። ይቀጥላል.... https://t.me/EotcTaskForce
Repost from Eotc Task Force
የእስልምና አጀማመር
ከእስልምና በፊት ያለው የአረብ ማህበረሰብ (ጃህሊያ) በጎሳ የተዋቀረ ነበር።
ብዙዎቹ ጣዖታዊ እምነት ይከተሉ ነበር።
👉መካ የንግድና የሃይማኖት ማዕከል ነበረች።
👉እስልምና በ Muhammad (570–632) ተጀመረ።
👉610 ቁራን ወርዶ የተጠቃለለበት ነው ብለው ያምናሉ
👉ከእስልምና በፊት የነበረው የአረብ ማህበረሰብ (ጃህሊያ) በጎሳ የተዋቀረ ነበር።
👉ብዙዎቹ ጣዖታዊ እምነት ይከተሉ ነበር
👉ሙሐመድ ሲመጣ ግን ወደ እስልምናው ተጠቃቀሉ
👉622 ዓ.ም (ሂጅራ) በመዲና የመጀመሪያው እስላማዊ ማህበረሰብ ተቋቋመ። ይህ የፖለቲካ እና የሀይማኖት አንድነት መሠረት ሆነ።
👉ከዚያን ጊዜ በኋላ ባሉት ዓመታት እስልምና ባሳየው መስፋፋፋት የዓለምን ፖለቲካዊ፣ኢኮኖሚያዊና ወታደራዊ ይዞታ ለውጦታል።በሳዑዲ ዓረቢያ የተጀመረው ኢስላማዊ መንግሥት በአንድ ክፍለ ዘመን ውስጥ ይዞታውን በማስፋፋት በምዕራብ ከአትላንቲክ ጀምሮ በምሥራቅ እስከ መካከለኛው እስያ ደርሷል።
ሙሐመድ እምነቱን ይጀምሩት እንጂ ያስፋፉት ተከታዮቻቸው ናቸው።መሐመድ ከሞቱ በኋላ እስልምና እንዴት ይመራ በሚለው ጥያቄ ክርክር ተነሳ። ከእርሱ በኋላ ተከታዮቹ መሪነትን ማን እንደሚወስድ በሚለው ጉዳይ ልዩነት ተፈጠረ። በዚህ ምክንያት በእስልምና ታሪክ “ፍትና (Fitna)” ተብሎ የሚጠራ የውስጥ ግጭት ተከሰተ።
ከዚያ በኋላ የኡማያድ መንግሥት ተመሠረተ፤ በኋላም የአባሲድ መንግሥት ተተካ። የኡማያድ መንግሥት እስልምናን በሰፊው አስፋፋ፤ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ ድረስ ብዙ አገሮች ተካተቱ።
በአባሲድ ዘመን ደግሞ ባግዳድ የእውቀት እና የሳይንስ ማዕከል ሆነች። ብዙ መጻሕፍት ተተርጎሙ፤ ፍልስፍና፣ ሕክምና፣ ሳይንስ እና ሌሎች ዕውቀቶች ተስፋፉ።እንዲያና እንዲህ እያ እስልምና እስልምና እየተስፋፋ ሄደ።
እስልምና ወደ ኢትዮጵያ መቼ እና እንዴት ገባ?
✍እስልምና ወደ ኢትዮጵያ በ7ኛው ክፍለ ዘመን ገባ።
✍በ615 ዓ.ም በመካ ላይ የነበረው እስላሞችና የማሳደድ ዘመቻ እየጠነከረ ሲመጣ ነቢዩ Muhammad ተከታዮቹን ወደ አቢሲኒያ (የዚህ ዘመን ኢትዮጵያ) እንዲሄዱ አደረገ።
✍በዚያን ጊዜ ኢትዮጵያን ይመራ የነበረው ንጉሥ አርማሕ ነበር። እርሱ ሙስሊሞቹን በእንግድነት ተቀበላቸው። ይህ ክስተት በእስላማዊ ታሪክ “የመጀመሪያው ሂጅራ” ተብሎ ይጠራል።
✍ ይህ እስልምናና ኢትዮጵያ መካከል ያለው የመጀመሪያ ሰላማዊ ግንኙነት ነበር።
እስልምና በኢትዮጵያእንዴት ተስፋፋ?
1) በንግድ መንገድ (8ኛ–12ኛ ክፍለ ዘመን)
የቀይ ባሕር እና የህንድ ውቅያኖስ ንግድ መንገዶች እስልምናን ወደ ምሥራቅ ኢትዮጵያ አስገቡ።
©ዘይላ
©ባርበራ
©ሐረር
ነጋዴዎች በሰላማዊ መንገድ እስልምናን አስፋፉ። ይህ ስፋት በተለይ በአፋር፣ በሶማሌ እና በሐረርጌ ክልሎች ታይቷል።
2 የእስላማዊ ስልጣናት (12ኛ–16ኛ ክፍለ ዘመን)
1✍ የኢፋት ስልጣን(Ifat Sultanate)
2✍የአዳል ስልጣናት(Adal Sultanate)
ይቀጥላል....
