en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 369 subscribers, ranking 5 619 in the Religion & Spirituality category and 2 193 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 369 subscribers.

According to the latest data from 24 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -18 over the last 30 days and by 1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 23.10%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 8.16% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 551 views. Within the first day, a publication typically gains 1 254 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 22.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 25 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 369
Subscribers
+124 hours
+477 days
-1830 days
Posts Archive
በተለያዩ ክልሎች እና የፌዴራል መንግሥት በሚመራቸው ቦታዎች ውስጥ በሚገኙ የቤተ ክርስቲያኗ አህጉረ ስብከት የሆኑትን ሥርዓተ አምልኮዋን የምትፈጽምባቸው በየመዋቅሩ የሚገኙ አስተዳደር ቢሮዎችን ከሕግ አግባብ ውጭ የቤተ ክርስቲያኗ እምነት ተከታይ ያልሆኑ ግለሰቦችን በማካተት በመንግሥት ልዩ ኃይል ድጋፍ በመውረር እና በመስበር የሕግ አግባብነት በሌላቸው እንዲሁም መብት እና ጥቅም ሳይኖራቸው በማሸግ ቤተ ክርስቲያን ላይ ወረራ እየተፈጸመባት የሚገኝ መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ ለመረዳት ችሏል፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ

በአሰበ ተፈሪ /ጭሮ/ ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን የጸጥታ ኃይሎች አስለቃሽ ጭስ ወደ ምእመናን እየወረወሩና ተኩስ መጀመራቸውን ምእመናን ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ገለጹ። ምእመናን ከጠዋት ጀምረው ቤተ ክርስቲያኗን ሲጠብቁ የነበረ ሲሆን የዞኑ የጸጥታ ኃይል "በሁለታችሁ አንገባም" በማለት ገለልተኛ ለመሆን ሞክሮ ውሏል። ነገር ግን ከመሼ ከክልል የመጣ ትእዛዝ ነው በሚል የክልሉ ልዩ ኃይልን ጨምሮ ተኩስ በመክፈት አስለቃሽ ጭስ ወደ ምእምናን እየወረወረ መሆኑን ምእምናን በስልክ ገልጸውልናል። መረጃውን ያደረሱን ምእመናን አክለውም የጸጥታ ኃይሉ ቤተ ክርስቲያኑ ከብቦ እየተኮሰና እያወከበ ቢሆንም ምእመኑ ግን ከግቢ አልወጣም ብሏል።

መንግሥት በአስቸኳይ መልስ የማይሰጥ ከሆነ የካቲት 5 ቀን 2015 ዓ.ም በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ሰላማዊ ሰልፍ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ወሰነ! ጥር 27 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እሑድ የካቲት 5 ቀን 2015 ዓ.ም በመላው ዓለም ተፈጻሚ የሚሆን የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ አደረገ። መንግስት የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ለመከፋፈል ለተነሱ ወራሪ ቡድኖች ድጋፍ እየሰጠ የሚገኝ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ቅዱስ ሲኖዶሱ ጾመ ነነዌን መላው ኦርቶዶክሳውያን ጥቁር ልብስ በመልበስ እና ወደ እግዚአብሔር በመፀለይ እንዲያሳልፉ ያዘዘ መሆኑ ይታወሳል። ሆኖም መንግስት በተከታታይ 7 ቀናት ውስጥ ተግባራዊ ምላሽ የማይሰጥ ከሆነ ከሁሉም አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት መነሻቸውን ያደረጉ እና ወደ መስቀል አደባባይ እና ወይም ወደ ባሕረ ጥምቀት ሐድረሻቸውን ያደረጉ ሰላማዊ ሰልፎች እንዲደረጉ መመሪያ ሰጥቷል።

በአሁኑ ሰዓት የጸጥታ ኃይሉ የሻሸመኔ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያንን ሙሉ በሙሉ ሰብሮ በመግባት ውስጥ በሚገኙት ምእመናን ላይ እየተኮሰ በመግደል ላይ እንደሆነ የመረጃ ምንጫችን በእንባ ጭምር ገልጸውልናል። (c)tmc

አሰላ +++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ የከተማው ህዝብ በሌለበት ከበቆጂ የሌላ እምነት ተከታዮችን በአይሱዚ በማምጣት መንበረ ጵጵስናውን ሰብረው ገብተዋል። ስድስት ፓትሮል መኪና ያጀባቸው የክልሉ ልዩ ኃይል ሲሆን ከገቡ በኋላ በተሿሚው የገዳሟን ምዷየ ምጽዋት በመሥበር ለአጃቢዎቹ የፀጥታ ሰዎች ሕገ ወጥ ተሿሚው ገንዘቡን አድለዋል። የከተማው ፖሊስ ሊቀ ጳጳሱን ብፁዕ አቡነ ያሬድን አፍኖ ምሽት ከከተማው ማስወጣቱ ይታወቃል።

#አስቸኳይ! ሻሸመኔ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ላይ በከባድ መሣሪያ የታገዘ ከፍተኛ ተኩስ ተከፍቷል። +++++++++++++++++++++++++++++++++++ (ጥር 27 ቀን 2015 ዓ.ም አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ) የጸጥታ ኃይሉ ፎቅ ላይ በመሆን በቀጥታ ቤተ ክርስቲያኑ ግቢ ውስጥ ወዳሉት ምእመናን በስናይፐር እየተኮሰ ሲሆን በዚህም አንዲት ሴት ተገድላለች ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ምእመናንና ምእመናት ቆስለዋል። ከውጪ በኩልም ሕገ ወጡ ቡድን ብር በመክፈል ያደራጃቸው ቡድኖች ድንጋይ በመወርወር ላይ ናቸው በዚህም የቤተ ክርስቲያኑን በር ሰብረውታል። ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የሲዳማ፣ጌዲዮና ምዕራብ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን እንደተናገሩት በተለያየ አቅጣጫ እየተተኮሰ እንደሆነና የጸጥታ አካላት የመከላከል ሥራ እንዳልሠሩ ገልጸዋል። የከተማዋ ነዋሪ ያልሆኑ ግለሰቦችን በመኪና ጭነው እያስገቡ ነው ሲሉም ጠቁመዋል፣ ምእመናን አሁንም በጽናት እንዲጠብቁ መልእክት አስተላልፈዋል።

አስቸኳይ! ሻሸመኔ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ላይ በስናይፐር የታገዘ ከፍተኛ ተኩስ ተከፍቷል። የጸጥታ ኃይሉ ፎቅ ላይ በመሆን በቀጥታ ቤተ ክርስቲያኑ ግቢ ውስጥ ወዳሉት ምእመናን በስናይፐር እየተኮሰ ሲሆን በዚህም አንዲት ሴት ተገድላለች ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ምእመናንና ምእመናት ቆስለዋል። ከውጪ በኩልም ሕገ ወጡ ቡድን ብር በመክፈል ያደራጃቸው ቡድኖች ድንጋይ በመወርወር ላይ ናቸው በዚህም የቤተ ክርስቲያኑን በር ሰብረውታል።

"መንግስት ቤተ ክርስቲያንን ለማፍረስ ከተሰበሰበ ወራሪ ቡድን ጋር በማበር በጠራራ ፀሐይ ሕግ ሲጥስና የሕግ አፍራሾች ተባባሪ ሆኖ ማየት እጅግ አሳፋሪ እና አንገት የሚያስደፋ ድርጊት ነው" - ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጥር 27 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ) ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል የበላይ ጠባቂ በዛሬው ዕለት በሻሸመኔ ኦርቶዶክሳውያን ላይ በመንግሥት አካላት የተፈጸመውን ግድያና ማዋከብን አስመልክቶ ጥሪ አቅርበዋል። ብፁዕነታቸው በማኅበራዊ የትሥሥር ገጻቸው ባሠፈሩት መልእክት የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በቤተ ክርስቲያን እና በክርስቲያኖችን ላይ እያደረሰ የሚገኘውን የማሳደድ ተግባር በአስቸኳይ እንዲያቆም ጠይቀዋል። በሰሜን ኢትዮጵያ ሕግ እናስከብራለን በሚል በትግራይ እንቅስቃሴ ሲያደርግ የነበረው የኢትዮጵያ መንግስት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ለማፍረስ ከተሰበሰበ ወራሪ ቡድን ጋር በማበር በጠራራ ፀሐይ ሕግ ሲጥስና የሕግ አፍራሾች ተባባሪ ሆኖ ማየት እጅግ አሳፋሪ እና አንገት የሚያስደፋ ድርጊት ነውም ሲሉ ድርጊቱን ኮንነዋል። የተፈጸመው ድርጊት ከዘር ጭፍጨፋ የሚተናነስ አይደለም ያሉት ብፁዕነታቸው የሕዝቡን ሰብዓዊ መብት ካላስከበረ መንግሥትነቱ ምን ላይ ነው ሲሉም ጠይቀዋል። ብፁዕነታቸው ለሻሸመኔ እና ምዕራብ አርሲ ኦርቶዶክሳውያን ከዘመነ ዲዮቅልጥያኖስ ያልተናነውን ይህንን ዘመን በጾም በጸሎትና በክርስቲያናዊ ጥንካሬ እንዲያልፉ ያሳሰቡ ሲሆን የፌደራልና የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የሚፈስሰውን በግፍ የኦርቶዶክሳውያን ደም እንዲያስቆሙ ጥሪያቸውን አቅርበዋል። #TMC_Addia_Ababa