en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 369 subscribers, ranking 5 619 in the Religion & Spirituality category and 2 193 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 369 subscribers.

According to the latest data from 24 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -18 over the last 30 days and by 1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 23.10%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 8.16% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 551 views. Within the first day, a publication typically gains 1 254 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 22.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 25 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 369
Subscribers
+124 hours
+477 days
-1830 days
Posts Archive
"መንግስት ቤተ ክርስቲያንን ለማፍረስ ከተሰበሰበ ወራሪ ቡድን ጋር በማበር በጠራራ ፀሐይ ሕግ ሲጥስና የሕግ አፍራሾች ተባባሪ ሆኖ ማየት እጅግ አሳፋሪ እና አንገት የሚያስደፋ ድርጊት ነው" - ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጥር 27 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ) ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል የበላይ ጠባቂ በዛሬው ዕለት በሻሸመኔ ኦርቶዶክሳውያን ላይ በመንግሥት አካላት የተፈጸመውን ግድያና ማዋከብን አስመልክቶ ጥሪ አቅርበዋል። ብፁዕነታቸው በማኅበራዊ የትሥሥር ገጻቸው ባሠፈሩት መልእክት የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በቤተ ክርስቲያን እና በክርስቲያኖችን ላይ እያደረሰ የሚገኘውን የማሳደድ ተግባር በአስቸኳይ እንዲያቆም ጠይቀዋል። በሰሜን ኢትዮጵያ ሕግ እናስከብራለን በሚል በትግራይ እንቅስቃሴ ሲያደርግ የነበረው የኢትዮጵያ መንግስት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ለማፍረስ ከተሰበሰበ ወራሪ ቡድን ጋር በማበር በጠራራ ፀሐይ ሕግ ሲጥስና የሕግ አፍራሾች ተባባሪ ሆኖ ማየት እጅግ አሳፋሪ እና አንገት የሚያስደፋ ድርጊት ነውም ሲሉ ድርጊቱን ኮንነዋል። የተፈጸመው ድርጊት ከዘር ጭፍጨፋ የሚተናነስ አይደለም ያሉት ብፁዕነታቸው የሕዝቡን ሰብዓዊ መብት ካላስከበረ መንግሥትነቱ ምን ላይ ነው ሲሉም ጠይቀዋል። ብፁዕነታቸው ለሻሸመኔ እና ምዕራብ አርሲ ኦርቶዶክሳውያን ከዘመነ ዲዮቅልጥያኖስ ያልተናነውን ይህንን ዘመን በጾም በጸሎትና በክርስቲያናዊ ጥንካሬ እንዲያልፉ ያሳሰቡ ሲሆን የፌደራልና የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የሚፈስሰውን በግፍ የኦርቶዶክሳውያን ደም እንዲያስቆሙ ጥሪያቸውን አቅርበዋል። #TMC_Addia_Ababa

በሻሸመኔ ከተማ አንድ ኦርቶዶክሳዊ ወጣት ሰማዕትነትን ተቀበለ! ጥር 27 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ) በዛሬው ዕለት ሕገ ወጡ ቡድን ወደ ሻሸመኔ ይመጣል መባሉን ተከትሎ ጠዋት ሁለት ሰዓት ላይ ሥርዓተ ቅዳሴ እንደተፈጸመ ሕዝቡን ለመጥራት በከተማዋ ያሉ አድባራት ደወል ደውለዋል። ይህንን ጥሪ ሰምቶ ሁሉም ምእመን ወደ ቤተ ክርስቲያን መሔድ ይጀምራል። በዚህ ጊዜ ወደ ሻሸመኔ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን የሔዱ ምእመናን የቤተ ክርስቲያኑ በር በመዘጋቱ ከውጪ ቆመው ነበር። በእንዲህ ሁኔታ ውስጥ እያለ የከተማው ፖሊስ ሕዝቡን ለመበተን ተኩስ መክፈቱም ነው የተነገረው። እስካሁን ድረስ አንድ ኦርቶዶክሳዊ ወጣት ሰማዕትነትን መቀበሉንና በውል ያልታወቀ ሰውም በጥይት መመታቱን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ከጥቂት ዓመታት በፊት አስከፊ እልቂትና ውድመት የደረሰባት የሰማዕታት ከተማ ሻሸመኔ ዛሬም በሕገ ወጡ ቡድን ምክንያት ሞት ተደግሶላታል። ያለውን ሁኔታ ለማጣራት ወደ መልአከ ፀሐይ ቀሲስ ዮሐንስ ዘለዓለም የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ክፍል ኃላፊ የስልክ ቃለ ምልልስ አድርገን ነበር። ኃላፊውም ሁላችንም ለመሞት ተዘጋጅተናል ብለዋል። በመንግሥት በኩል ያለው ተጽዕኖም ከባድና መራር ነው ሲሉ አንስተዋል። ከጠዋት አንስቶ የአብያተ ክርስቲያናቱ በር በጸጥታ ኃይሎች ቢዘጋም ሕዝቡ አጥሩን እየገነጠለ ወደ ቤተ ክርስቲያኗ ቅጽር ጊቢ እየገባ እንደሆነም ነው የተሰማው። በሌላ በኩል በምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት በጭሮ ከተማ በሕገ ወጥ መንገድ የተሾሙት ኤጲስ ቆጶሳት ዛሬ ጥር 27 ቀን 2015 ዓ.ም እንደሚመጡ መረጃ ስለደረሳቸው የጭሮ ከተማ ሕዝበ ክርስቲያን በከተማው የሚገኙትን 4 አብያተ ክርስቲያናት በንቃት እየጠበቀ ይገኛል። ትናንት ሌሊት ሊቀ ጳጳሷ የታሠሩባትና መቆየት አይችሉምጨ ተብለው ወደ አዲስ አበባ እንዲመለሱ የተደረጉባት በአርሲ ሀገረ ስብከቷ መናገሻ አሰላ ኦርቶዶክሳውያን እየታሠሩ መሆኑንና በቤተ ክርስቲያን ቅጽር ያሉትም እንዲወጡ እየተነገራቸውና ያ የማይሆን ከሆነ የኃይል እርምጃ እንደሚወሰድባቸውም ተዝቶባቸዋል።

"ምዕመናን ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ለመጠበቅ በሚያደርጉት ጥረት ለሚፈጠረው ችግር መንግስት ኃላፊነቱን ይወስዳል" ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ ጥር 26 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) +++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ሻሸመኔ ከተማ በሕገ ወጥ የተሾመው ቡድን መንበረ ጵጵስና እና ቤተ ክርስቲያን ሰብረን እንገባለን በማለት በምእመናን ላይ ስጋት መፍጠሩን ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የሲዳማ፣ ጌዲዮ፣ አማሮ፣ ቡርጂና ምዕራብ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ማምሻውን ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን አሳወቁ። ከሰሞኑን የሀገረ ስብከቱ አገልጋዮች ያለምክንያት እየታሰሩ ነው ያሉት ብፁዕነታቸው ይህንንም ለሚመለከተው የዞን ፀጥታ አካል ለማሳወቅና ጥበቃ እንዲያደርጉ ብንደውልም፣ መልእክት ብንጽፍም ሊመልሱልን አልቻሉም ብለዋል። በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት ለኦሮምያ ክልል የሚመለከታቸው አካላት በተለይም ጥበቃና ከለላን በተመለከተ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አስቀድሞ ደብዳቤ ቢጻፍም ምንም አይነት የቃልም ሆነ የተግባር መልስ እንዳልተሰጣቸውም ተናግረዋል። ብፁዕነታቸው አክለውም መንግሥት በሕገ ወጡ ቡድን የሚደረገውን ድርጊት ማስቆም ካልቻለ ምእመናን ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ለመጠበቅ በሚያደርጉት ጥረት ለሚፈጠረው ችግር ኃላፊነቱን ይወስዳል ብለዋል። በመጨረሻም ምእመናን ቤተ ክርስቲያናቸውን እንዲጠብቁ መልእክት አስተላልፈዋል።

ብፁዕ አቡነ ያሬድ በአሰላ መቆየት አይችሉም ተብለው በዚህ ሰዓት ወደ አዲስ አበባ እንዲመለሱ ተደርገዋል።

ከአሰላ ያገኘነው መረጃ ብፁዕ አቡነ ያሬድ የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ዛሬ ምሽት 3:45 አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ከሚገኘው መንበረ ጵጵስናቸው ተወስደው መታሠራቸውን ለማወቅ ተችሏል። ሕገ ወጡ ቡድን ሾሜዋለሁ ያለው ግለሰብ በነገው ዕለት እንደሚመጣ የተነገረ ሲሆን በሌሎች ቤተእምነት ተከታዮችን በማስተባበር የአዲሱን ተሿሚ ፎቶ በባነር ለመስቀል ሲሞክሩ ተስተውሏል። በሐረር የተሐድሶ እንቅስቃሴ መሪና በይቅርታ ወደ ሥራው የተመለሰው ግለሰብ ለምዕራብ አርሲ ተሾሟል መባሉ ምእመናኑ አስቆጥቷል። EOTC TV +++++++++++++++++++++++++++++++++++

ልዩ መረጃ! ብፁዕ አቡነ ያሬድ ታሠሩ! ጥር 26 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ) ብፁዕ አቡነ ያሬድ የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ዛሬ ምሽት 3:45 አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ከሚገኘው መንበረ ጵጵስናቸው ተወስደው መታሠራቸው ተገለጸ። ብፁዕነታቸው በዛሬው ዕለት ማምሻውን ከአዲስ አበባ ወደ ሀገረ ስብከታቸው መድረሳቸውን ተ.ሚ.ማ ያገኘችው መረጃ ያመለክታል። በተጨማሪም የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኅሩያን ታምራት ወልዴ ቤትም መከበቡንና እስካሁን ያለውን ሁኔታ ማወቅ እንዳልቻሉም ነው ምንጮቻችን የገለጹት። ሕገ ወጡ ቡድን ሾሜዋለሁ ያለው ግለሰብ በነገው ዕለት እንደሚመጣ የተነገረ ቢሆንም ምእመናኑ ሕጋዊውን ቅዱስ ሲኖዶስን ብቻ እንደሚቀበሉም ገልጸዋል። #Ethiopia #Tewahedo_Media_Center #TMC_Addia_Ababa

የእነ አቶ አካለወልድ ሞገስ ሕገወጥ ቡድን የምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳምን ለመውረር ዝግጅት እያደረገ መሆኑ ተገለጸ !!! ++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ (ጥር 26 ቀን 2015 ዓ.ም አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ) ሕገወጥ ቡድኑ በፔንሲዮን መሽጉ የሰነበተ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን በተለያዩ አህጉረ ስብከት የጸጥታ ኃይሎችን ተገን በማድረግ የአህጉረ ስብከት መንበረ ጵጵስናዎችን እየሰበረ ወረራ ሲፈጽም የቆየ ሲሆን እስከ አሁን ድረስ በወለጋ የሚገኙ አራት አህጉረ ስብከት መንበረ ጵጵስናዎችን በወረራ ተቆጣጥሯቸዋል። በተመሳሳይም በነገው ዕለት አቶ አካለ ወልድ ሞገስ ቀድሞ ሊቀ ጳጳስ በነበሩበት ወቅት የበላይ ጠባቂ ሆነው ሲመሩት የነበረውን የምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳምን ለመውረር ዝግጅት ማድረጋቸውን የተ.ሚ.ማ ምንጮች ጠቁመዋል። ቅዱስ ሲኖዶስ መንግሥት የቤተ ክርስቲያኒቱን ሕግና ሥርዓት እንዲያስከብር ጥሪ ቢያቀርብም እስከ አሁን ድረስ ከመንግስት የተሰጠ ተግባራዊ ምላሽ የለም። ©ተ.ሚ.ማ