uk
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Відкрити в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 369 підписників, посідаючи 5 619 місце в категорії Релігія і духовність та 2 193 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 369 підписників.

За останніми даними від 24 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на -18, а за останні 24 години на 1, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 23.10%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 8.16% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 3 551 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 254 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 22.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 25 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.

15 369
Підписники
+124 години
+477 днів
-1830 день
Архів дописів
በተለያዩ ክልሎች እና የፌዴራል መንግሥት በሚመራቸው ቦታዎች ውስጥ በሚገኙ የቤተ ክርስቲያኗ አህጉረ ስብከት የሆኑትን ሥርዓተ አምልኮዋን የምትፈጽምባቸው በየመዋቅሩ የሚገኙ አስተዳደር ቢሮዎችን ከሕግ አግባብ ውጭ የቤተ ክርስቲያኗ እምነት ተከታይ ያልሆኑ ግለሰቦችን በማካተት በመንግሥት ልዩ ኃይል ድጋፍ በመውረር እና በመስበር የሕግ አግባብነት በሌላቸው እንዲሁም መብት እና ጥቅም ሳይኖራቸው በማሸግ ቤተ ክርስቲያን ላይ ወረራ እየተፈጸመባት የሚገኝ መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ ለመረዳት ችሏል፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ

በአሰበ ተፈሪ /ጭሮ/ ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን የጸጥታ ኃይሎች አስለቃሽ ጭስ ወደ ምእመናን እየወረወሩና ተኩስ መጀመራቸውን ምእመናን ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ገለጹ። ምእመናን ከጠዋት ጀምረው ቤተ ክርስቲያኗን ሲጠብቁ የነበረ ሲሆን የዞኑ የጸጥታ ኃይል "በሁለታችሁ አንገባም" በማለት ገለልተኛ ለመሆን ሞክሮ ውሏል። ነገር ግን ከመሼ ከክልል የመጣ ትእዛዝ ነው በሚል የክልሉ ልዩ ኃይልን ጨምሮ ተኩስ በመክፈት አስለቃሽ ጭስ ወደ ምእምናን እየወረወረ መሆኑን ምእምናን በስልክ ገልጸውልናል። መረጃውን ያደረሱን ምእመናን አክለውም የጸጥታ ኃይሉ ቤተ ክርስቲያኑ ከብቦ እየተኮሰና እያወከበ ቢሆንም ምእመኑ ግን ከግቢ አልወጣም ብሏል።

መንግሥት በአስቸኳይ መልስ የማይሰጥ ከሆነ የካቲት 5 ቀን 2015 ዓ.ም በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ሰላማዊ ሰልፍ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ወሰነ! ጥር 27 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እሑድ የካቲት 5 ቀን 2015 ዓ.ም በመላው ዓለም ተፈጻሚ የሚሆን የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ አደረገ። መንግስት የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ለመከፋፈል ለተነሱ ወራሪ ቡድኖች ድጋፍ እየሰጠ የሚገኝ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ቅዱስ ሲኖዶሱ ጾመ ነነዌን መላው ኦርቶዶክሳውያን ጥቁር ልብስ በመልበስ እና ወደ እግዚአብሔር በመፀለይ እንዲያሳልፉ ያዘዘ መሆኑ ይታወሳል። ሆኖም መንግስት በተከታታይ 7 ቀናት ውስጥ ተግባራዊ ምላሽ የማይሰጥ ከሆነ ከሁሉም አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት መነሻቸውን ያደረጉ እና ወደ መስቀል አደባባይ እና ወይም ወደ ባሕረ ጥምቀት ሐድረሻቸውን ያደረጉ ሰላማዊ ሰልፎች እንዲደረጉ መመሪያ ሰጥቷል።

በአሁኑ ሰዓት የጸጥታ ኃይሉ የሻሸመኔ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያንን ሙሉ በሙሉ ሰብሮ በመግባት ውስጥ በሚገኙት ምእመናን ላይ እየተኮሰ በመግደል ላይ እንደሆነ የመረጃ ምንጫችን በእንባ ጭምር ገልጸውልናል። (c)tmc

አሰላ +++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ የከተማው ህዝብ በሌለበት ከበቆጂ የሌላ እምነት ተከታዮችን በአይሱዚ በማምጣት መንበረ ጵጵስናውን ሰብረው ገብተዋል። ስድስት ፓትሮል መኪና ያጀባቸው የክልሉ ልዩ ኃይል ሲሆን ከገቡ በኋላ በተሿሚው የገዳሟን ምዷየ ምጽዋት በመሥበር ለአጃቢዎቹ የፀጥታ ሰዎች ሕገ ወጥ ተሿሚው ገንዘቡን አድለዋል። የከተማው ፖሊስ ሊቀ ጳጳሱን ብፁዕ አቡነ ያሬድን አፍኖ ምሽት ከከተማው ማስወጣቱ ይታወቃል።

#አስቸኳይ! ሻሸመኔ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ላይ በከባድ መሣሪያ የታገዘ ከፍተኛ ተኩስ ተከፍቷል። +++++++++++++++++++++++++++++++++++ (ጥር 27 ቀን 2015 ዓ.ም አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ) የጸጥታ ኃይሉ ፎቅ ላይ በመሆን በቀጥታ ቤተ ክርስቲያኑ ግቢ ውስጥ ወዳሉት ምእመናን በስናይፐር እየተኮሰ ሲሆን በዚህም አንዲት ሴት ተገድላለች ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ምእመናንና ምእመናት ቆስለዋል። ከውጪ በኩልም ሕገ ወጡ ቡድን ብር በመክፈል ያደራጃቸው ቡድኖች ድንጋይ በመወርወር ላይ ናቸው በዚህም የቤተ ክርስቲያኑን በር ሰብረውታል። ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የሲዳማ፣ጌዲዮና ምዕራብ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን እንደተናገሩት በተለያየ አቅጣጫ እየተተኮሰ እንደሆነና የጸጥታ አካላት የመከላከል ሥራ እንዳልሠሩ ገልጸዋል። የከተማዋ ነዋሪ ያልሆኑ ግለሰቦችን በመኪና ጭነው እያስገቡ ነው ሲሉም ጠቁመዋል፣ ምእመናን አሁንም በጽናት እንዲጠብቁ መልእክት አስተላልፈዋል።

አስቸኳይ! ሻሸመኔ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ላይ በስናይፐር የታገዘ ከፍተኛ ተኩስ ተከፍቷል። የጸጥታ ኃይሉ ፎቅ ላይ በመሆን በቀጥታ ቤተ ክርስቲያኑ ግቢ ውስጥ ወዳሉት ምእመናን በስናይፐር እየተኮሰ ሲሆን በዚህም አንዲት ሴት ተገድላለች ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ምእመናንና ምእመናት ቆስለዋል። ከውጪ በኩልም ሕገ ወጡ ቡድን ብር በመክፈል ያደራጃቸው ቡድኖች ድንጋይ በመወርወር ላይ ናቸው በዚህም የቤተ ክርስቲያኑን በር ሰብረውታል።

"መንግስት ቤተ ክርስቲያንን ለማፍረስ ከተሰበሰበ ወራሪ ቡድን ጋር በማበር በጠራራ ፀሐይ ሕግ ሲጥስና የሕግ አፍራሾች ተባባሪ ሆኖ ማየት እጅግ አሳፋሪ እና አንገት የሚያስደፋ ድርጊት ነው" - ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጥር 27 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ) ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል የበላይ ጠባቂ በዛሬው ዕለት በሻሸመኔ ኦርቶዶክሳውያን ላይ በመንግሥት አካላት የተፈጸመውን ግድያና ማዋከብን አስመልክቶ ጥሪ አቅርበዋል። ብፁዕነታቸው በማኅበራዊ የትሥሥር ገጻቸው ባሠፈሩት መልእክት የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በቤተ ክርስቲያን እና በክርስቲያኖችን ላይ እያደረሰ የሚገኘውን የማሳደድ ተግባር በአስቸኳይ እንዲያቆም ጠይቀዋል። በሰሜን ኢትዮጵያ ሕግ እናስከብራለን በሚል በትግራይ እንቅስቃሴ ሲያደርግ የነበረው የኢትዮጵያ መንግስት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ለማፍረስ ከተሰበሰበ ወራሪ ቡድን ጋር በማበር በጠራራ ፀሐይ ሕግ ሲጥስና የሕግ አፍራሾች ተባባሪ ሆኖ ማየት እጅግ አሳፋሪ እና አንገት የሚያስደፋ ድርጊት ነውም ሲሉ ድርጊቱን ኮንነዋል። የተፈጸመው ድርጊት ከዘር ጭፍጨፋ የሚተናነስ አይደለም ያሉት ብፁዕነታቸው የሕዝቡን ሰብዓዊ መብት ካላስከበረ መንግሥትነቱ ምን ላይ ነው ሲሉም ጠይቀዋል። ብፁዕነታቸው ለሻሸመኔ እና ምዕራብ አርሲ ኦርቶዶክሳውያን ከዘመነ ዲዮቅልጥያኖስ ያልተናነውን ይህንን ዘመን በጾም በጸሎትና በክርስቲያናዊ ጥንካሬ እንዲያልፉ ያሳሰቡ ሲሆን የፌደራልና የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የሚፈስሰውን በግፍ የኦርቶዶክሳውያን ደም እንዲያስቆሙ ጥሪያቸውን አቅርበዋል። #TMC_Addia_Ababa