en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 383 subscribers, ranking 5 582 in the Religion & Spirituality category and 2 194 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 383 subscribers.

According to the latest data from 09 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 38 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 21.91%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 9.42% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 370 views. Within the first day, a publication typically gains 1 449 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 25.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 10 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 383
Subscribers
-124 hours
-67 days
+3830 days
Posts Archive
#አቡነ_አብሳዲ_ዘደብረ_መጒና_፤ #ታኅሣሥ 29 ልደታቸው ከጌታችን ልደት ጋር ከተባበረላቸው ቅዱሳን መካከል አንዱ ናቸው፡፡ ፠ #የበረሃው_ዕንቊ_ገዳም_መንበረ_ልዑል_ጽርሐ_አርያም_ደብረ_መጕናን_የመሠረቱ፡፡ ፠ አብርሃም ቅድስት ሥላሴን እንዳስተናገደ፤ #አቡነ_አብሳዲ_ደግሞ_ጌታችንን_ተቀብለው_እግሩን_ያጠቡ_ናቸው፡፡ (ፎቶውን ይመልከቱ) ፠ #ደቀ_መዛሙርቶቻቸው_በተሰየፉበት_አንገረብ_ወንዝ_ላይ_ #44ት #የፍል_ውኃ_ፈዋሽ_ጠበል_አንገረብ_የሚባል_ያላቸው፤ በሃገራችን ብዙሃን ሕዝብ ከሚጠመቅባቸው ጠበሎች ዋነኛው ከተጠማቂው ሕዝብ ብዛት የተነሣ #ቀንና_ሌሊት_ጥምቀት_የሚካሄድበት፡፡ (ፎቶውን ይመልከቱ) ፠ ከብቃታቸው የተነሣ ወደ ላይ ጽርሐ አርያምን ወደ ታች በርባሮስ ድረስ የሚደረገውን የሚመለከቱ፤ ፠ #ወላዴ_አእላፍ ፥ #ወላዴ_ቅዱሳን_ሊቃውንት፥ #አበ_ብዙኃን፥ #ወላዴ_ሰማዕታት የሆኑ፤ ፠ በፀሐይ ሰረገላ፥ በብርሃን መንኰራኵር እየተጫኑ እንደ ሐዋርያት የሚያስተምሩት፤ ፠ 470 ዓመታትን የኖሩት፡፡ ፠ ታኅሣሥ 29 የጌታችንና,ን የጻድቁን የልደት በዓል፤ ሙሉ አርማጭሆ እንዲሁም የትክል ድንጋይ፣ የዳንሻና አካባቢው ምዕመናን በ10ሺዎች የሚቈጠር ሕዝብ የሚያከብርላቸው፡፡ * ምንኵስናን የተቀበሉት ከአቡነ ዮሐንስ ከማ ነው፡፡ * በማንዳባ ገዳም ከ7ቱ ከዋክብትና ከ7ቱ ከዋክብተ ጣና አንዱ ከኾኑትና ደንጊያን እንደ ጀልባ ከሚጠቀሙት ከአቡነ ያሳይ ጋር ብዙ የጽድቅ ሥራና የትሩፋት ተጋድሎን ፈጽመዋል፡፡ * ቀድሞ በኤርታ ደብረ ማርያም ነበር የሚኖሩት፤ ኋላ ታቦተ ማኅበረ በኵርንና ታቦተ ኪዳነ ምሕረትን ይዘው ብዙ ቅዱሳንን ወዳፈለቁበት መሥዋዕተ ኦሪት ይሠዋበት ወደነበረው ገዳመ መጕና መጡ፤ ገዳሙ የሚገኘውም በጎንደር ታች አርማጭሆ ነው፡፡ ‹‹በሬ ሜዳ›› የሚባለው ቦታ ላይ የጌታችን ልደትና የጻድቁ ልደት ዝክር የሚዘከርበት ምርፋቅ ነው፡፡ ጻድቁ የተጓዙባቸው ምዕራፋት ከቁርባኔ ወንዝ እስከ መታጠቂያ በር 13ት ሲሆኑ የ13ቱ ሕማማት ምሳሌ ሲሆኑ፤ የመታጠቂያ በር ደግሞ የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው፡፡ በ1407 ዓ.ም. በአፄ ይስሐቅ ዘመን ‹‹ዳሩ እሳት ፥ መሐሉ ገነት፡፡›› ተብሎ ተገድሟል፡፡ ወላዴ አእላፍ አበ ብዙኃን ዐምዳ ወብርሃና ለደብረ መጒና በቆብ የወለዷቸው በርካታ ቅዱሳን ቢኖርም፤ #ገዳማትን_የመሠረቱ_ለአብነት_ዋናዎቹ_፤ ፠ #አቡነ_ስነ_ኢየሱስ_ (ቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ ገዳምን የመሠረቱ) ፠ አቡነ ሥልጣነ ክርስቶስ (አመራ ቊስቋም ገዳምን የመሠረቱ) ፠ #አቡነ_ልብሰ_ክርስቶስ_ (ዳውጨና አማኑኤል ገዳምን የመሠረቱ) ፠ አቡነ ማቴዎስ (ያይራ ተክለ ሃይማኖት ገዳምን የመሠቱ) ፠ #አቡነ_ዮሐንስ_ዘመረባ (ጊዮርጊስ ገዳምን የመሠረቱ) ፠ ሰማዕቱ አቡነ ጽጌ ድንግል (እንኮ ድብ ገዳምን የመሠረቱ) ፠ #አቡነ_ዘወልደ_ዳዊት (ጐረፍ ተክለ ሃይማኖትን የመሠረቱ) ፠ አቡነ መቅደሰ ክርስቶስ (ሳይኮ ኪዳነ ምሕረትን የመሠረቱ) ፠ #አቡነ_ህላዌ_ክርስቶስ (አምስትያ ገዳምን የመሠረቱ) ፠ አቡነ ተላዌ ክርስቶስ ( ገዳምን የመሠረቱ) ፠ #አቡነ_ከናፍረ_ክርስቶስ (ገዳምን የመሠረቱ) ፠ አቡነ የማነ ክርስቶስ (ገው ጊዮርጊስን የመሠረቱ) ፠ #አቡነ_ዕደ_ክርሰቶስ (የኢትዮጵያና የግብፅ ሐዋርያ ፥ የደብረ መጕና 3ኛ መምህር /አበምኔት/) ፠ አቡነ መዝራዕተ ክርስቶስ (በትግራይ ገዳምን የመሠረቱ፤ ልደታቸው ከአባታቸው ጋር በታኅሣሥ 29 የተባበረላቸው) ፠ #ሰማዕቱና_በአባታቸው_ወንበር_የተተኩት_አቡነ_አምኀ_ጊዮርጊስ፡፡ (የደብረ መጕና 2ኛው መምህረ /አበምኔት/) ሲሆኑ፤ #ቅዱሳን_ደራስያን_ሊቃውንት_ከሆኑት_መካከል_ለአብነት_፤ ፠ #አባ_ገብረ_ኢየሱስ_ (የሰቈቃወ ድንግል ደራሲ) ፠ #እጨጌ_በትረ_ጊዮርጊስ_ (በአፄ ፋሲል ዘመን የኢትዮጵያ ሊቃውንት አፈ ጕባኤ የነበሩና የቅባት ሃይማኖት መሪዎች እነ አልፎንሱ ሜንዴዝን የረቱ …. በዚህም ሊቃነታቸው በዐይኑ ያየ ባለቅኔ፤ ‹‹ወረከብናሁ ለበትር ዘያደክማ ለሮሜ፤ ቅሩጸ በንባብ ወጽሩበ በትርጓሜ፡፡›› ብሎ የተቀኘላቸው የሊቃውንት ዋልታ፡፡ ፠ #አባ_ስብሐት_ለአብ_ (የመልክ ሥላሴ፣ ሰይፈ ሥላሴ፣ ዘይነግሥን የደረሱና 14ቱን ቅዳሴ ያመሠጠሩና በአንድምታ የተረጐሙ፣ በጎንደር ደብረ ብርሃን ሥላሴ ከብዙ ሊቃወንት ጋር በመሆን የቅኔና የመጻሕፍትን ምሥጢር ከነሙሉ አገባቡና እርባ ቅምሩን እንዲሁም የአቡሻኽርን ሁሉ የቀመሩ፤ የንጉሡ የአድያም ሰገድ ኢያሱ መምህረ ንስሐ የነበሩ) ፠ #አባ_ዳንኤል_፤ (ብዙ መጻሕፍትን ያሰባሰቡና የጻፉ፤ ንዋያተ ቅድሳትን የሚሠርቅ ‹‹ቢዘራ ለበረድ ፥ ቢወልድ ልጁን ለጕጓድ፡፡›› ብለው ከ8000 በላይ ሊቃውንትን በማሰባሰብ እንዲወሰን ያደረጉ፡፡ #ከላይ_ያሉትን_ለአብነት_የጠቀስናቸውን_ቅሳንና_ሊቃውንት_አስተምረውና_ወልደው_፤ ለ90 ዓመታት ፍሬና ቅጠላ ቅጠል ተመግበው፤ ራቁታቸውን በጋ ከክረምት በበረሃው መንነው፤ ሳማ (አበርባራን) ለትሩፋትና ለተጋድሎ ለብሰው፤ በፀሐይ ሰረገላ፥ በብርሃን መንኰራኵር እየተጫኑ እንደ ሐዋርያት በማስተማራቸው፤ የጸጋና የቅብዐት ተካተዮችን እያስተማሩ ወደ እናት ቤ/ክ በመመለሳቸው፤ ** የሚያምረውን ሥጋዊ ደም ግባታቸውንና ሰውነታቸው እንደ ጻድቁ ቅዱስ ኢዮብና እንደ ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ወደ ቁስል በመቀየራቸውና ሥስቃዩንና መከራውን በመቻላቸው፤ ቁስላቸው ተልቶ ትሎቹን የገዳሙ አእዋፋት እስኪመገቡት ድረስ በመታገሣቸው፡፡ *** በርካታ ቃል ኪዳን አምላካችን ሰጥቷቸው በተወለዱ በ470 ዓመታቸው ዐርፈዋል፡፡ #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#ታኅሣሥ_29_ልደታቸው_ከጌታችን_ልደት_ጋር_የተባበረላቸው_ቅዱሳን፤ #አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ፤ #ቅዱስ ላሊበላ፤ #ቅዱስ ነዓኵቶ ለአብ፤ #አቡነ አብሳዲ ዘደብረ መጕናና የቆብ ልጃቸው #አቡነ መዝራዕ
+5
#ታኅሣሥ_29_ልደታቸው_ከጌታችን_ልደት_ጋር_የተባበረላቸው_ቅዱሳን፤ #አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ፤ #ቅዱስ ላሊበላ፤ #ቅዱስ ነዓኵቶ ለአብ፤ #አቡነ አብሳዲ ዘደብረ መጕናና የቆብ ልጃቸው #አቡነ መዝራዕተ ክርስቶስ፤ #ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ፤ #ቅዱሳን ነገሥታት አብርሃ ወአጽብሃ፤ #አቡነ አካለ ክርስቶስ፤ #መስፍኑ ኢያሱ፤ #አቡነ ዳንኤል ዘገርዓልታ፤ #ዳግማዊ ቂርቆስ ዘቡልጋና ሌሎችም ቅዱሳን አሉ፤ ነገር ግን ከቅዱሳን በዓል በላይ የጌታ በዓል መከበር ስለሚገባው የቅዱሳኑ ዋና በዓላቸው በሌላ ቀናት /በዕረፍታቸው…../ ቀን ይታሳባል፡፡ #የቅዱስ_ላላበላ_ክብረ_በዓል_የሚከበርባቸው_ቦታዎች_፤ ፠ በደብረ ሮሐ ላስታ ቅዱስ ላሊበላ ፠ በመዲናችን በአዲስ አበባ አንቀጸ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ፤ በድርብነት ይከብራል፡፡ ፠ በአሸዋ ሜዳ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ላሊበላ ወቅዱስ መርቆሬዎስ ወኪዳነ ምሕረት ወቅድስት ሥላሴ፡፡ ..(ሌሎችም ካሉ ከነፎቷቸው ጨምሩበት) #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#የሕይወት_ፈተና_ምንጮች_ክፍል_፮፡፡ #ዐርብ_ታኅሣሥ_30፤ #ከ፲፪-፪ ሰዓት Shareee, Like … እንዳያመልጥዎ በጕባኤው ላይ ይገኙ፡፡ ለምን እንፈተናለን፤ ፈተናዎች ለምንና እንዴት ይመጣሉ፤ ፈ
+1
#የሕይወት_ፈተና_ምንጮች_ክፍል_፮፡፡ #ዐርብ_ታኅሣሥ_30፤ #ከ፲፪-፪ ሰዓት Shareee, Like … እንዳያመልጥዎ በጕባኤው ላይ ይገኙ፡፡ ለምን እንፈተናለን፤ ፈተናዎች ለምንና እንዴት ይመጣሉ፤ ፈተናዎችን እንዴት አድርገን ድል እናድርጋቸው፤ …. ……እንዳያመልጣችሁ፤ በሌሎችም ርዕሶች ዙሪያ በብዙ ጕባኤያት ላይ ያልተዳሰሱ ርዕሶች የሚዳሰሱበት ጕባኤ ስለሆነ እንዳያመልጣችሁ፤ #ደግመን_እንላለን_ይህ_ትምህርት_በፍጹም_እንዳያመልጣችሁ!!!!! ለተከታታይ ሳምንታት፤ ትምህርቱ ተከታታይነት ስላለው መቅረትና ማርፈድ አይመከርም!!፡፡ (፻፶፮ኛ ሳምንት የዐርብ ጕባኤ) #ዐርብ_ታኅሣሥ_፴፤ #ከ፲፪-፪ ሰዓት አሁንም በድጋሚ እንላለን ለሕይወታችን ወሳኝና በብዙ የትምህርት ጕባኤያት ላይ የማይዳሰሱ ትምህርቶች ስለሆኑ እንዳያመልጣችሁ!!!! የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት፡፡ #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

በልደት በዓል ከምዕመናን ጋር በመተባበር ነዳያንን ማስፈሰክ ከጀመርን እነሆ 3ኛ ዓመታችን ይህን ይመስላል፡፡ ሰ/ትቤታችን ዛሬ በሁሉም አጥቢያ የሚደረገው በትንሣኤ ነዳያንን የማስፈሰክ ተግባር በግንባ
+1
በልደት በዓል ከምዕመናን ጋር በመተባበር ነዳያንን ማስፈሰክ ከጀመርን እነሆ 3ኛ ዓመታችን ይህን ይመስላል፡፡ ሰ/ትቤታችን ዛሬ በሁሉም አጥቢያ የሚደረገው በትንሣኤ ነዳያንን የማስፈሰክ ተግባር በግንባር ቀደምትነት ከ50 ዓመታት በፊት መጀመሩ ይታወቃል፡፡ ለነዳይን የሚያስብ እርሱ ምስጉን ነው፡፡ #በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ #በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

ለነዳያን የሚያስብ እርሱ ምስጉን ነው፤ እነሆ ለ3ኛ ጊዜ የልደት ነዳያንን የማስፈክ መልካም ሥራ ከምዕመናን ጋር በመተባበር ዘንድሮም ይቀጥላል፡፡
+2
ለነዳያን የሚያስብ እርሱ ምስጉን ነው፤ እነሆ ለ3ኛ ጊዜ የልደት ነዳያንን የማስፈክ መልካም ሥራ ከምዕመናን ጋር በመተባበር ዘንድሮም ይቀጥላል፡፡

የጌታችን ልደት በዋናነት የሚከበርባቸው ዐበይት ገዳማትና አድባራት፤ (ሌሎችም ካሉ ከተቻለ ከነፍቷቸው ላኩልን፡፡) ፠ በኢየሩሳሌም ቤተ ልሔም፤ ጌታችን በተወለደባት ፠ በማኅበረ ሥላሴ ገዳም፤ ለመጀመሪ
+8
የጌታችን ልደት በዋናነት የሚከበርባቸው ዐበይት ገዳማትና አድባራት፤ (ሌሎችም ካሉ ከተቻለ ከነፍቷቸው ላኩልን፡፡) ፠ በኢየሩሳሌም ቤተ ልሔም፤ ጌታችን በተወለደባት ፠ በማኅበረ ሥላሴ ገዳም፤ ለመጀመሪያ ጊዜ ጌታ በተወለደባት ዕለት የጌታችን መወለድ የተበሠረባት /ቋራና መተማ/ ፠ ሰረባር በዓለ እግዚአብሔር፤ ቅዱስ ላሊበላ ከሕንፃዎቹ ሁሉ መጀመሪያ ያነጸው ውቀር ቤ.ክ. /ስሜን፤ ደረስጌ አጠገብ/ ፠ ደብረ ሮሐ ላስታ ላሊበላ ፠ ርዕሰ አድባራት አደባባይ ኢየሱስ ቤ.ክ. /እጅግ ጥንታዊ ታሪክ ያለው ጽላቱ ከደበቡ ኢትዮጵያ የሄደና ኋላ ቊጥሩ ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ የሆነ፤ ጎንደር ከተማ/ ፠ ደብረ ስብሐት ቀሃ ኢየሱስ /ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ፤ ጎንደር ከተማ/ ፠ ቂልጠፋት በዓለ ወልድ፤ (ጉራጌ ፥ እንደጋይ ወረዳ) ፠ ጉንችሬ በዓለ ወልድ፤ (ጉራጌ ፥ እነሞር ወረዳ) ፠ አሸዋ ሜዳ ቤሮ ደብረ ምህረት ቅዱስ ላሊበላ ቤተክርስቲያን፤ (በምዕራብ ሸዋ ፥ ወልመራ ወረዳ) በአዲስ አበባ ደረጃ የሚገኙ፤ ፠ አዲስ አበባ መካነ ሥላሴ ቅዱስ በዓለ ወልድ /በ1883ዓ.ም. የተመሠረተ፤ 4ኪሎ፤ አዲስ አበባ/ ፠ ፊሊዶሮ መድኀኔዓለም ቅዱስ ላሊበላ፡፡ # ፠በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ # ፠በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት - Statistics & analytics of Telegram channel @finotehiwott