Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览
频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 383 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 582,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 194 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 383 名订阅者。
根据 09 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 38,过去 24 小时变化为 -1,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 21.91%。内容发布后 24 小时内通常能获得 9.42% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 370 次浏览,首日通常累积 1 449 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 25。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 10 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
15 383
订阅者
-124 小时
-67 天
+3830 天
帖子存档
#አቡነ_አብሳዲ_ዘደብረ_መጒና_፤ #ታኅሣሥ 29 ልደታቸው ከጌታችን ልደት ጋር ከተባበረላቸው ቅዱሳን መካከል አንዱ ናቸው፡፡
፠ #የበረሃው_ዕንቊ_ገዳም_መንበረ_ልዑል_ጽርሐ_አርያም_ደብረ_መጕናን_የመሠረቱ፡፡
፠ አብርሃም ቅድስት ሥላሴን እንዳስተናገደ፤ #አቡነ_አብሳዲ_ደግሞ_ጌታችንን_ተቀብለው_እግሩን_ያጠቡ_ናቸው፡፡ (ፎቶውን ይመልከቱ)
፠ #ደቀ_መዛሙርቶቻቸው_በተሰየፉበት_አንገረብ_ወንዝ_ላይ_ #44ት #የፍል_ውኃ_ፈዋሽ_ጠበል_አንገረብ_የሚባል_ያላቸው፤ በሃገራችን ብዙሃን ሕዝብ ከሚጠመቅባቸው ጠበሎች ዋነኛው ከተጠማቂው ሕዝብ ብዛት የተነሣ #ቀንና_ሌሊት_ጥምቀት_የሚካሄድበት፡፡ (ፎቶውን ይመልከቱ)
፠ ከብቃታቸው የተነሣ ወደ ላይ ጽርሐ አርያምን ወደ ታች በርባሮስ ድረስ የሚደረገውን የሚመለከቱ፤
፠ #ወላዴ_አእላፍ ፥ #ወላዴ_ቅዱሳን_ሊቃውንት፥ #አበ_ብዙኃን፥ #ወላዴ_ሰማዕታት የሆኑ፤
፠ በፀሐይ ሰረገላ፥ በብርሃን መንኰራኵር እየተጫኑ እንደ ሐዋርያት የሚያስተምሩት፤
፠ 470 ዓመታትን የኖሩት፡፡
፠ ታኅሣሥ 29 የጌታችንና,ን የጻድቁን የልደት በዓል፤ ሙሉ አርማጭሆ እንዲሁም የትክል ድንጋይ፣ የዳንሻና አካባቢው ምዕመናን በ10ሺዎች የሚቈጠር ሕዝብ የሚያከብርላቸው፡፡
* ምንኵስናን የተቀበሉት ከአቡነ ዮሐንስ ከማ ነው፡፡
* በማንዳባ ገዳም ከ7ቱ ከዋክብትና ከ7ቱ ከዋክብተ ጣና አንዱ ከኾኑትና ደንጊያን እንደ ጀልባ ከሚጠቀሙት ከአቡነ ያሳይ ጋር ብዙ የጽድቅ ሥራና የትሩፋት ተጋድሎን ፈጽመዋል፡፡
* ቀድሞ በኤርታ ደብረ ማርያም ነበር የሚኖሩት፤ ኋላ ታቦተ ማኅበረ በኵርንና ታቦተ ኪዳነ ምሕረትን ይዘው ብዙ ቅዱሳንን ወዳፈለቁበት መሥዋዕተ ኦሪት ይሠዋበት ወደነበረው ገዳመ መጕና መጡ፤ ገዳሙ የሚገኘውም በጎንደር ታች አርማጭሆ ነው፡፡
‹‹በሬ ሜዳ›› የሚባለው ቦታ ላይ የጌታችን ልደትና የጻድቁ ልደት ዝክር የሚዘከርበት ምርፋቅ ነው፡፡
ጻድቁ የተጓዙባቸው ምዕራፋት ከቁርባኔ ወንዝ እስከ መታጠቂያ በር 13ት ሲሆኑ የ13ቱ ሕማማት ምሳሌ ሲሆኑ፤ የመታጠቂያ በር ደግሞ የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው፡፡
በ1407 ዓ.ም. በአፄ ይስሐቅ ዘመን ‹‹ዳሩ እሳት ፥ መሐሉ ገነት፡፡›› ተብሎ ተገድሟል፡፡
ወላዴ አእላፍ አበ ብዙኃን ዐምዳ ወብርሃና ለደብረ መጒና በቆብ የወለዷቸው በርካታ ቅዱሳን ቢኖርም፤
#ገዳማትን_የመሠረቱ_ለአብነት_ዋናዎቹ_፤
፠ #አቡነ_ስነ_ኢየሱስ_ (ቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ ገዳምን የመሠረቱ)
፠ አቡነ ሥልጣነ ክርስቶስ (አመራ ቊስቋም ገዳምን የመሠረቱ)
፠ #አቡነ_ልብሰ_ክርስቶስ_ (ዳውጨና አማኑኤል ገዳምን የመሠረቱ)
፠ አቡነ ማቴዎስ (ያይራ ተክለ ሃይማኖት ገዳምን የመሠቱ)
፠ #አቡነ_ዮሐንስ_ዘመረባ (ጊዮርጊስ ገዳምን የመሠረቱ)
፠ ሰማዕቱ አቡነ ጽጌ ድንግል (እንኮ ድብ ገዳምን የመሠረቱ)
፠ #አቡነ_ዘወልደ_ዳዊት (ጐረፍ ተክለ ሃይማኖትን የመሠረቱ)
፠ አቡነ መቅደሰ ክርስቶስ (ሳይኮ ኪዳነ ምሕረትን የመሠረቱ)
፠ #አቡነ_ህላዌ_ክርስቶስ (አምስትያ ገዳምን የመሠረቱ)
፠ አቡነ ተላዌ ክርስቶስ ( ገዳምን የመሠረቱ)
፠ #አቡነ_ከናፍረ_ክርስቶስ (ገዳምን የመሠረቱ)
፠ አቡነ የማነ ክርስቶስ (ገው ጊዮርጊስን የመሠረቱ)
፠ #አቡነ_ዕደ_ክርሰቶስ (የኢትዮጵያና የግብፅ ሐዋርያ ፥ የደብረ መጕና 3ኛ መምህር /አበምኔት/)
፠ አቡነ መዝራዕተ ክርስቶስ (በትግራይ ገዳምን የመሠረቱ፤ ልደታቸው ከአባታቸው ጋር በታኅሣሥ 29 የተባበረላቸው)
፠ #ሰማዕቱና_በአባታቸው_ወንበር_የተተኩት_አቡነ_አምኀ_ጊዮርጊስ፡፡ (የደብረ መጕና 2ኛው መምህረ /አበምኔት/) ሲሆኑ፤
#ቅዱሳን_ደራስያን_ሊቃውንት_ከሆኑት_መካከል_ለአብነት_፤
፠ #አባ_ገብረ_ኢየሱስ_ (የሰቈቃወ ድንግል ደራሲ)
፠ #እጨጌ_በትረ_ጊዮርጊስ_ (በአፄ ፋሲል ዘመን የኢትዮጵያ ሊቃውንት አፈ ጕባኤ የነበሩና የቅባት ሃይማኖት መሪዎች እነ አልፎንሱ ሜንዴዝን የረቱ …. በዚህም ሊቃነታቸው በዐይኑ ያየ ባለቅኔ፤
‹‹ወረከብናሁ ለበትር ዘያደክማ ለሮሜ፤
ቅሩጸ በንባብ ወጽሩበ በትርጓሜ፡፡›› ብሎ የተቀኘላቸው የሊቃውንት ዋልታ፡፡
፠ #አባ_ስብሐት_ለአብ_ (የመልክ ሥላሴ፣ ሰይፈ ሥላሴ፣ ዘይነግሥን የደረሱና 14ቱን ቅዳሴ ያመሠጠሩና በአንድምታ የተረጐሙ፣ በጎንደር ደብረ ብርሃን ሥላሴ ከብዙ ሊቃወንት ጋር በመሆን የቅኔና የመጻሕፍትን ምሥጢር ከነሙሉ አገባቡና እርባ ቅምሩን እንዲሁም የአቡሻኽርን ሁሉ የቀመሩ፤ የንጉሡ የአድያም ሰገድ ኢያሱ መምህረ ንስሐ የነበሩ)
፠ #አባ_ዳንኤል_፤ (ብዙ መጻሕፍትን ያሰባሰቡና የጻፉ፤ ንዋያተ ቅድሳትን የሚሠርቅ ‹‹ቢዘራ ለበረድ ፥ ቢወልድ ልጁን ለጕጓድ፡፡›› ብለው ከ8000 በላይ ሊቃውንትን በማሰባሰብ እንዲወሰን ያደረጉ፡፡
#ከላይ_ያሉትን_ለአብነት_የጠቀስናቸውን_ቅሳንና_ሊቃውንት_አስተምረውና_ወልደው_፤
ለ90 ዓመታት ፍሬና ቅጠላ ቅጠል ተመግበው፤
ራቁታቸውን በጋ ከክረምት በበረሃው መንነው፤
ሳማ (አበርባራን) ለትሩፋትና ለተጋድሎ ለብሰው፤
በፀሐይ ሰረገላ፥ በብርሃን መንኰራኵር እየተጫኑ እንደ ሐዋርያት በማስተማራቸው፤ የጸጋና የቅብዐት ተካተዮችን እያስተማሩ ወደ እናት ቤ/ክ በመመለሳቸው፤
** የሚያምረውን ሥጋዊ ደም ግባታቸውንና ሰውነታቸው እንደ ጻድቁ ቅዱስ ኢዮብና እንደ ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ወደ ቁስል በመቀየራቸውና ሥስቃዩንና መከራውን በመቻላቸው፤ ቁስላቸው ተልቶ ትሎቹን የገዳሙ አእዋፋት እስኪመገቡት ድረስ በመታገሣቸው፡፡
*** በርካታ ቃል ኪዳን አምላካችን ሰጥቷቸው በተወለዱ በ470 ዓመታቸው ዐርፈዋል፡፡
#በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
#በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
#ታኅሣሥ_29_ልደታቸው_ከጌታችን_ልደት_ጋር_የተባበረላቸው_ቅዱሳን፤
#አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ፤
#ቅዱስ ላሊበላ፤
#ቅዱስ ነዓኵቶ ለአብ፤
#አቡነ አብሳዲ ዘደብረ መጕናና የቆብ ልጃቸው #አቡነ መዝራዕተ ክርስቶስ፤
#ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ፤
#ቅዱሳን ነገሥታት አብርሃ ወአጽብሃ፤
#አቡነ አካለ ክርስቶስ፤
#መስፍኑ ኢያሱ፤
#አቡነ ዳንኤል ዘገርዓልታ፤
#ዳግማዊ ቂርቆስ ዘቡልጋና ሌሎችም ቅዱሳን አሉ፤ ነገር ግን ከቅዱሳን በዓል በላይ የጌታ በዓል መከበር ስለሚገባው የቅዱሳኑ ዋና በዓላቸው በሌላ ቀናት /በዕረፍታቸው…../ ቀን ይታሳባል፡፡
#የቅዱስ_ላላበላ_ክብረ_በዓል_የሚከበርባቸው_ቦታዎች_፤
፠ በደብረ ሮሐ ላስታ ቅዱስ ላሊበላ
፠ በመዲናችን በአዲስ አበባ አንቀጸ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ፤ በድርብነት ይከብራል፡፡
፠ በአሸዋ ሜዳ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ላሊበላ ወቅዱስ መርቆሬዎስ ወኪዳነ ምሕረት ወቅድስት ሥላሴ፡፡
..(ሌሎችም ካሉ ከነፎቷቸው ጨምሩበት)
#በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
#በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
#የሕይወት_ፈተና_ምንጮች_ክፍል_፮፡፡ #ዐርብ_ታኅሣሥ_30፤ #ከ፲፪-፪ ሰዓት
Shareee, Like … እንዳያመልጥዎ በጕባኤው ላይ ይገኙ፡፡
ለምን እንፈተናለን፤
ፈተናዎች ለምንና እንዴት ይመጣሉ፤
ፈተናዎችን እንዴት አድርገን ድል እናድርጋቸው፤ ….
……እንዳያመልጣችሁ፤ በሌሎችም ርዕሶች ዙሪያ በብዙ ጕባኤያት ላይ ያልተዳሰሱ ርዕሶች የሚዳሰሱበት ጕባኤ ስለሆነ እንዳያመልጣችሁ፤ #ደግመን_እንላለን_ይህ_ትምህርት_በፍጹም_እንዳያመልጣችሁ!!!!!
ለተከታታይ ሳምንታት፤ ትምህርቱ ተከታታይነት ስላለው መቅረትና ማርፈድ አይመከርም!!፡፡
(፻፶፮ኛ ሳምንት የዐርብ ጕባኤ)
#ዐርብ_ታኅሣሥ_፴፤ #ከ፲፪-፪ ሰዓት
አሁንም በድጋሚ እንላለን ለሕይወታችን ወሳኝና በብዙ የትምህርት ጕባኤያት ላይ የማይዳሰሱ ትምህርቶች
ስለሆኑ እንዳያመልጣችሁ!!!!
የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል
ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት፡፡
#በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
#በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
በልደት በዓል ከምዕመናን ጋር በመተባበር ነዳያንን ማስፈሰክ ከጀመርን እነሆ 3ኛ ዓመታችን ይህን ይመስላል፡፡ ሰ/ትቤታችን ዛሬ በሁሉም አጥቢያ የሚደረገው በትንሣኤ ነዳያንን የማስፈሰክ ተግባር በግንባር ቀደምትነት ከ50 ዓመታት በፊት መጀመሩ ይታወቃል፡፡
ለነዳይን የሚያስብ እርሱ ምስጉን ነው፡፡
#በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
#በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
ለነዳያን የሚያስብ እርሱ ምስጉን ነው፤ እነሆ ለ3ኛ ጊዜ የልደት ነዳያንን የማስፈክ መልካም ሥራ ከምዕመናን ጋር በመተባበር ዘንድሮም ይቀጥላል፡፡
የጌታችን ልደት በዋናነት የሚከበርባቸው ዐበይት ገዳማትና አድባራት፤
(ሌሎችም ካሉ ከተቻለ ከነፍቷቸው ላኩልን፡፡)
፠ በኢየሩሳሌም ቤተ ልሔም፤ ጌታችን በተወለደባት
፠ በማኅበረ ሥላሴ ገዳም፤ ለመጀመሪያ ጊዜ ጌታ በተወለደባት ዕለት የጌታችን መወለድ የተበሠረባት /ቋራና መተማ/
፠ ሰረባር በዓለ እግዚአብሔር፤ ቅዱስ ላሊበላ ከሕንፃዎቹ ሁሉ መጀመሪያ ያነጸው ውቀር ቤ.ክ. /ስሜን፤ ደረስጌ አጠገብ/
፠ ደብረ ሮሐ ላስታ ላሊበላ
፠ ርዕሰ አድባራት አደባባይ ኢየሱስ ቤ.ክ. /እጅግ ጥንታዊ ታሪክ ያለው ጽላቱ ከደበቡ ኢትዮጵያ የሄደና ኋላ ቊጥሩ ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ የሆነ፤ ጎንደር ከተማ/
፠ ደብረ ስብሐት ቀሃ ኢየሱስ /ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ፤ ጎንደር ከተማ/
፠ ቂልጠፋት በዓለ ወልድ፤ (ጉራጌ ፥ እንደጋይ ወረዳ)
፠ ጉንችሬ በዓለ ወልድ፤ (ጉራጌ ፥ እነሞር ወረዳ)
፠ አሸዋ ሜዳ ቤሮ ደብረ ምህረት ቅዱስ ላሊበላ ቤተክርስቲያን፤ (በምዕራብ ሸዋ ፥ ወልመራ ወረዳ)
በአዲስ አበባ ደረጃ የሚገኙ፤
፠ አዲስ አበባ መካነ ሥላሴ ቅዱስ በዓለ ወልድ /በ1883ዓ.ም. የተመሠረተ፤ 4ኪሎ፤ አዲስ አበባ/
፠ ፊሊዶሮ መድኀኔዓለም ቅዱስ ላሊበላ፡፡
# ፠በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/
# ፠በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem
17. ተወልደ ኢየሱስ tewele eyesus.mp35.25 KB
16. እምድንግል ቃል ሥጋ ኮነ emdingel.mp34.18 KB
15. አንፈርዓፁ ሰብአ ሰገል anferatsu.mp34.28 KB
14. ለመግሥትከ ሰፋኒት lemenegesteke.mp36.79 KB
13. ወልድ ተወልደ welde tewelde.mp36.59 KB
12. በማኅፀነ ድንግል bemahetsene dingel.mp37.61 KB
11. መሠረታቲሃ meseretateha.mp31.13 MB
10. ርእይዎ ኖሎት reeyewo.mp34.51 KB
9 . በኮከብ መጽኡ bekokebe metsu.mp34.84 KB
8 . ተወልደ ኢየሱስ tewelede eyesus.mp36.17 KB
7 . ዮም ፍሥሓ yom fiseha.mp34.31 KB
6 . ትምክህተ ዘመድነ timkehete kuline.mp35.00 KB
