የጥበብ ማዕድ
📈 Analytical overview of Telegram channel የጥበብ ማዕድ
Channel የጥበብ ማዕድ (@yetbebmead_ab) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 880 subscribers, ranking 5 407 in the Religion & Spirituality category and 2 116 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 880 subscribers.
According to the latest data from 24 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 628 over the last 30 days and by 31 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 2.61%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 2.09% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 415 views. Within the first day, a publication typically gains 332 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 9.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“ዝም ብለህ ተቀላቀል!”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 25 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.
ነገሩ እንደአደንዛዢ እፅ ነው...ልጆች ወይም ወጣቶች ተደብቀው የወደቀች ሲጋራ ጫት ወይም ቤት ውስጥ ጠላ መቀማመስ ይጀምራሉ...ተደብቀው "ይሳሳሙ "ይሆናል። መደበቅ የይሉኝታና የአክብሮት ስሜት አለው። የምሰራው ልክ አይደለም ሌሎች አይዮብኝ የሚል ፀፀት አለው። ከፍ ሲሉ ሲጋራው ተራ ይሆንባቸዋል ፣ ወደመጠጥ ቤት ወደሽሻ ቤት ይሄዳሉ፣ መደበቁን ይተውታል። ያም አያረካቸውም ወደከባድ መጠጦች፣ ወደአደንዛዢ እፅ ይሄዳሉ፣ ሴተኛ አዳሪወች ጋር ባለጌ ወንበር ላይ ይቀመጣሉ ፣ ወሲብ ፣ማርገዝ ፣ወልዶ መጣል፣ ማስወረድ ወዘተ ተራ ነገር ይሆንባቸዋል። ጥርሳቸው መልካቸው ሰውነታቸው በቁማቸው መፈራረስ ይጀምራል ...እንኳን ምክርና ይሉኝታ ሞት ከሱሳቸው በላይ አያስፈራቸውም። ቤተሰብ ፣ ዕምነት ሕዝብ ተራ ይሆንባቸዋል። ከሞት አንድ ደረጃ ዝቅ ብለው ወደሞት ያዘግማሉ። እንደውም "ኖርማል ሰው" ሲመለከቱ ጤነኛ አይመስላቸውም። ለሱሳቸው ይዋሻሉ፣ ማንንም አሳልፈው ይሰጣሉ፣ ይሰርቃሉ፣ ይገድላሉ።
አሁን ያለው ኢትዮጵያዊ የሶሻል ሚዲያ አጠቃቀም ሱስ በዚያ ደረጃ ላይ ነው። ጥበብ፣ ውይይት አሽሙር፣ ቅኔ ፣ የሰከነ ሐሳብ ፣ ይሉኝታ ሞራል የሚባለውን ጉዳይ አልፏል። ተራ ስድድቦችንም ዘሏል። ወሲብ ነክ ጉዳዮች አደባባይ ላይ የማይታዮ ገመናወችን ዘሏል። ስለመገዳደል ካልተወራ ሬሳ ካላየ፣ ያዛጋዋል። የለየለት ፖርኖግራፊ እና የቆሸሸ የግል ገመና ገበያ ሆኗል። በየሚሴንጀርና ቴሌግራም እንደቆሸሸ የከተማ ወንዝ ዝሙት ሲፈስ ውሎ ያድራል፣ ገምቷል ሸቷል። በውስ የተራቆተው ከላይ ተከናንቦ ብቅ ይላል። ከፈጣሪ እስከነብያት ከአገር እስከህዝብ ከማንነት እስከተፈጥሮ ስብዕና የማይዘለፍ የማይንቋሸሽ የለም።
ብዙ ሺወች ከየመንደሩ የከረፋ ባህሪያቸውን ተሸክመው አደባባይ ወጥተዋል። የመላ ከተማው ቆሻሻ ተሰብስቦ እንደሚጣልበት ቆሸ ቆሻሻ መጣያ ሆኗል። ቤተሰብ እንኳን የሚፀየፋቸው ሰወች ሺህ ሚሊየን ሰው አስከትለው አደባባይ ውለዋል። የታዳሚው አእምሮ የቆሻሻ ሱስ ይዞት ቆሻሻ ያነፈንፋል። ቆሻሻው ላይ ሚሊየን ዝንቦች ያርፋሉ። "ማን ብዙ ዝንብ አለው " የሚለው ሐሳብ ኩራት ሆኗል። ድግሪ ያለው ዝንብ፣ ማስተርስ ያለው ዝንብ፣ ፒኤች ዲ የተሸከመ ዝንብ፣ ሐብት ያለው ዝንብ፣ ስልጣን ያለው ዝንብ፣ ሐይማኖተኛ ነኝ የሚል ዝንብ፣ ፖለቲከኛ ነኝ የሚል ዝንብ፣ ዲያስፖራ ነኝ የሚል ዝንብ፣ ቆንጆ ነኝ የምትል ዝንብ... ዝንባዊ ማንነት የሚኮራበት ሆኗል። "ለመኖር ስል ዝንብ ሆንኩ" ይልሃል።
ንቦች ቆሻሻ ላይ ያበቀለ አበባ ፍለጋ አፍንጫቸውን ይዘው በቆሻሻ ክምር ላይ ክንፋቸው እስኪዝል ይበራሉ! የጨነቀው አየሩ ያፈነው ጨዋ ትውልድ በዚህ ቆሻሻ ታፍኖ እየተጨነቀ ነው። አየሩ ቆሽሿል.... ንቦች የሚሰሩት ጥቂት ማርም ቢሆን ዝንብ ይሰፍርበታል። ዝንብ በቆሻሻና በማር መካከል ያለው ልዮነት አይገባውም። ሱሱ ግን አሁንም አልቆመም ነገ የከፋ ቆሻሻ ሊያዋልድ እያማጠ ነው።
✍ Alex Abraham
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
