es
Feedback
የጥበብ ማዕድ

የጥበብ ማዕድ

Ir al canal en Telegram

ዝም ብለህ ተቀላቀል!

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram የጥበብ ማዕድ

El canal የጥበብ ማዕድ (@yetbebmead_ab) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 880 suscriptores, ocupando la posición 5 407 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 116 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 880 suscriptores.

Según los últimos datos del 24 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 628, y en las últimas 24 horas de 31, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 2.61%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 2.09% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 415 visualizaciones. En el primer día suele acumular 332 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 9.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
ዝም ብለህ ተቀላቀል!

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 25 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 880
Suscriptores
+3124 horas
+1507 días
+62830 días
Archivo de publicaciones
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ያበሰራት ቅዱስ መላዕክ ማን ይባላል?

🏆 ለ ኦርቶዶክሳዊያን ብቻ የተከፈቱ በኢትዮጵያ የመጀመርያዎቹ ኦርቶዶክሳዊ ቻናሎች ❤️❤️❤️
🏆 ለ ኦርቶዶክሳዊያን ብቻ የተከፈቱ በኢትዮጵያ የመጀመርያዎቹ ኦርቶዶክሳዊ ቻናሎች ❤️❤️❤️

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በህ-ወጥ መንገድ ለገበያ ሊቀርብ የተዘጋጀ ስጋ ተያዘ ​ ​ በጥብቅ ፍተሻ ጤንነታቸው ያልተረጋገጡ 13 የታረዱ በጎች፣ 14 ፍየሎች እንዲሁም ፅዳቱ ያልተጠበቀ 312
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በህ-ወጥ መንገድ ለገበያ ሊቀርብ የተዘጋጀ ስጋ ተያዘ ​ በጥብቅ ፍተሻ ጤንነታቸው ያልተረጋገጡ 13 የታረዱ በጎች፣ 14 ፍየሎች እንዲሁም ፅዳቱ ያልተጠበቀ 312 ኪሎ ግራም ስጋ ተይዟል።   ​ ስጋውም እንዲወገድ ለአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የተረከበ ሲሆን ድርጊቱን የፈጸሙ ግለሰቦችም በህግ እንዲጠየቁ ተደርጓል።   ሲታይ ባያምርም ሳናይ ምንበላው እያለን መወገዱ ያሳዝናል።😒

እውቀት እውነት አይደለም

'ሚታደል ለማደል             ሳድን እድለኛ ከ'እድለኛው ዝርዝር              ተገኘው 'ባንደኛ እድሌ ሆነና       አልከሰርኩም ከቶ እጣው ለኔ ወጣ              እድለኛ ሸሽቶ!       Abu(Alazar Tewodros)

እባቡን ነው ወይስ መርዙን ነው የምትፈራው?

ሁሉማ ነገር አንፃራዊ ነው፤ አንድ ነጠላ ፀጉር ጭንቅላት ላይ ትንሽ ነው፤ ትኩስ ሾርባ ላይ ግን ብዙ ነው።

ከልብ ተጨንቀው ያወጧት አንዲት ቃል ፣ ብቻዋን መፅሐፍ ናት 👌

የሆነ ሰው ራሱ ላይ የማይሆን ውሳኔ እንዲወስን ከገፋፋችሁና suicide እንዲያደርግ፤እልፍ ቀናትን እስከ ወራት የደም እንባ እንዲያለቅስ ካደረጋችሁ በኋላ ቀብሩ ላይ ተገኝታችሁ ሰይጣን ገፋፍቶት ነው አትበሉ 😔🥺ማርያምን ከናንተ አንፃር እንደውም ሰይጣን ያ ሰው ራሱ ላይ እንዳይጨክን ሲገረግረው ነበር 🥺 ...... የምር ከናንተና ከሰይጣን ግን ማነው ሰይጣን¿??

ያስለመድከውን ለለት እንደከለከልከው ወዳጅህ ጠላትህ ራሱ ጠላት አይሆንህም።

አንዳንዴ ያንተ መኖር ለሌሎች በምትከፍለው መስዋትነት ውስጥ ይሆናል መገኛው።

መኖርን ሳታውቀው መኖር ጀምረህ ትገኛለህ።     መማር ሚገባን ቀለም ብቻ አልነበረም! ቀለም ከማወቅ በተጨማሪ ፍርሐትንም ነው የሚያስተምረን።      መኖርን መማር ነበረብን ብዙ ግራ የሚያጋቡ ሁነቶችን ስንደርስባቸው መቼ እንደተጠጋናቸውና እንዴት እንደምናልፋቸው አናውቅም!           እስቲ መኖርን አስተምሩን!

ደስታቸውን ማሳየት ብዙ ውለታቸውን እንደመክፈል ነው።

ሚረሳብህንና ሚረሳልህን አለዩልህም ለዛ ነው ዋጋህ ያልገባቸው።

ነገሩ እንደአደንዛዢ እፅ ነው...ልጆች ወይም ወጣቶች ተደብቀው የወደቀች ሲጋራ ጫት ወይም ቤት ውስጥ ጠላ መቀማመስ ይጀምራሉ...ተደብቀው "ይሳሳሙ "ይሆናል። መደበቅ የይሉኝታና የአክብሮት ስሜት አለው። የምሰራው ልክ አይደለም ሌሎች አይዮብኝ የሚል ፀፀት አለው። ከፍ ሲሉ ሲጋራው ተራ ይሆንባቸዋል ፣ ወደመጠጥ ቤት ወደሽሻ ቤት ይሄዳሉ፣  መደበቁን ይተውታል። ያም አያረካቸውም ወደከባድ መጠጦች፣ ወደአደንዛዢ እፅ ይሄዳሉ፣ ሴተኛ አዳሪወች ጋር ባለጌ ወንበር ላይ ይቀመጣሉ ፣  ወሲብ ፣ማርገዝ ፣ወልዶ መጣል፣ ማስወረድ  ወዘተ ተራ ነገር ይሆንባቸዋል። ጥርሳቸው መልካቸው ሰውነታቸው በቁማቸው መፈራረስ ይጀምራል ...እንኳን ምክርና ይሉኝታ ሞት ከሱሳቸው በላይ አያስፈራቸውም። ቤተሰብ ፣ ዕምነት ሕዝብ ተራ ይሆንባቸዋል። ከሞት አንድ ደረጃ ዝቅ ብለው ወደሞት ያዘግማሉ። እንደውም "ኖርማል ሰው" ሲመለከቱ ጤነኛ አይመስላቸውም። ለሱሳቸው ይዋሻሉ፣ ማንንም አሳልፈው ይሰጣሉ፣  ይሰርቃሉ፣ ይገድላሉ። አሁን ያለው ኢትዮጵያዊ የሶሻል ሚዲያ አጠቃቀም ሱስ በዚያ ደረጃ ላይ ነው።  ጥበብ፣ ውይይት አሽሙር፣  ቅኔ ፣ የሰከነ ሐሳብ ፣ ይሉኝታ ሞራል የሚባለውን ጉዳይ አልፏል። ተራ ስድድቦችንም ዘሏል። ወሲብ ነክ ጉዳዮች አደባባይ ላይ የማይታዮ ገመናወችን ዘሏል። ስለመገዳደል ካልተወራ ሬሳ ካላየ፣ ያዛጋዋል። የለየለት ፖርኖግራፊ እና የቆሸሸ የግል ገመና  ገበያ ሆኗል። በየሚሴንጀርና ቴሌግራም እንደቆሸሸ የከተማ ወንዝ ዝሙት ሲፈስ ውሎ ያድራል፣  ገምቷል ሸቷል።  በውስ የተራቆተው ከላይ ተከናንቦ ብቅ ይላል። ከፈጣሪ እስከነብያት ከአገር እስከህዝብ ከማንነት እስከተፈጥሮ ስብዕና የማይዘለፍ የማይንቋሸሽ የለም። ብዙ ሺወች ከየመንደሩ የከረፋ ባህሪያቸውን ተሸክመው  አደባባይ ወጥተዋል። የመላ ከተማው ቆሻሻ ተሰብስቦ እንደሚጣልበት ቆሸ ቆሻሻ መጣያ ሆኗል። ቤተሰብ እንኳን የሚፀየፋቸው ሰወች ሺህ ሚሊየን ሰው አስከትለው አደባባይ ውለዋል። የታዳሚው አእምሮ የቆሻሻ ሱስ ይዞት ቆሻሻ ያነፈንፋል። ቆሻሻው ላይ ሚሊየን ዝንቦች ያርፋሉ። "ማን ብዙ ዝንብ አለው " የሚለው ሐሳብ ኩራት ሆኗል። ድግሪ ያለው ዝንብ፣ ማስተርስ ያለው ዝንብ፣ ፒኤች ዲ የተሸከመ ዝንብ፣ ሐብት ያለው ዝንብ፣ ስልጣን ያለው ዝንብ፣ ሐይማኖተኛ ነኝ የሚል ዝንብ፣ ፖለቲከኛ ነኝ የሚል ዝንብ፣  ዲያስፖራ ነኝ የሚል ዝንብ፣ ቆንጆ ነኝ የምትል ዝንብ... ዝንባዊ ማንነት የሚኮራበት ሆኗል። "ለመኖር ስል ዝንብ ሆንኩ" ይልሃል። ንቦች ቆሻሻ ላይ ያበቀለ አበባ ፍለጋ አፍንጫቸውን ይዘው በቆሻሻ ክምር ላይ ክንፋቸው እስኪዝል ይበራሉ!  የጨነቀው አየሩ ያፈነው ጨዋ ትውልድ በዚህ ቆሻሻ ታፍኖ እየተጨነቀ ነው። አየሩ ቆሽሿል.... ንቦች የሚሰሩት ጥቂት ማርም ቢሆን ዝንብ ይሰፍርበታል። ዝንብ በቆሻሻና በማር መካከል ያለው ልዮነት አይገባውም። ሱሱ ግን አሁንም አልቆመም ነገ የከፋ ቆሻሻ ሊያዋልድ እያማጠ ነው።              ✍ Alex Abraham

.. ባለመግባባትና ጥል መሃከል የኔ ኣስተዋጾ ምንድነው ማለቱ የራስን ጉድለትና ተጠያቂነት ለማየት መሞከሩ ትልቅ ኣዋቂነትን ይጠይቃል። ሁሌ ራስን እንደተበዳይ ማባበል እውነቱን ይጋርዳል....

Happy mother's day መባል የሚገባን ያልወለድን እናቶች አለን መልካም የእናቶች ቀን ለኛ ለመጀመርያ ሴት ልጆች እንዲሁ ለሁሉም ታላላቅ እህቶች እንኳን አደረሳችሁ💞🥹
Happy mother's day መባል የሚገባን ያልወለድን እናቶች አለን መልካም የእናቶች ቀን ለኛ ለመጀመርያ ሴት ልጆች እንዲሁ ለሁሉም ታላላቅ እህቶች እንኳን አደረሳችሁ💞🥹

መቼ ነው ግን ሞልቶልኝ ለእናቴ የእናቶች ቀን የምቶደውን ልዩ ስጦታ የምሰጣት🥺 መች ነው ሚሞላልኝ
የምንል ሰዎች እግዚአብሔር መሻታችንን ሞልቶልን ጊዜ ሳይቀድመን እንድናሳካው ምኞቴ ነው 🥺 ፈጣሪ ያን ቀን ያቅርብልን😇🙏🏻 መልካም የእናቶች ቀን ሁሉንም እናቶች ፈጣሪ በእድሜ በፀጋ ይጠብቅልን ♥️💌

፡ ከአይኖቿ ህያው ቃል አለ ‎                  ይቀዳል ፍቅር ከደጇ ‎ችሮታ ፀጋ አድሏታል ‎መሰሰት ጭራሽ አታውቅም ‎                  ለጋስ ነው በረከት እጇ ‎ ‎ሸክሟ ቢበረታባት ‎ውስጧ በጭንቀት ቢላወስ ‎                  አዝና እንኳ ብታቀረቅር ‎ቅጥ አልባ ኑሮ ቢወዛ ‎                    እንደልብ ኑሮ ቢቸግር ‎ደክማ እንኳ ልታበረታ ‎                ቀን ተዳፍኖ ቢጨልማት ‎ሳይደላት ደልቶት ያደገ ‎               የልጇ ሳቅ ነው የሚያቀናት ‎ ‎ሲወድቅ እኔን ትላለች ‎ለልጇ ጥሩን ስትመኝ ‎ሲያመውም እኔን ይመመኝ ‎ሲርበው እኔን ትላለች ‎ሲጠማው እኔን ትላለች ‎የጌታ የአንድዬን እናት ‎ማርያምን ተመስላለች ‎ ‎አካሏ ጥቁርቁር ቢል ‎ጭንቀቷን በሳቅ ብትደብቅ ‎በእንክብክብ ልጇን ልትጠብቅ ‎የሕይወት ተስፋን ሰንቃ ‎ብትዝል ልትበቃ ለግብ ‎ነውና ልጇን ልትመግብ ‎ ‎ሸክሟ ቢበረታባት ‎ውስጧ በጭንቀት ቢላወስ ‎                  አዝና እንኳ ብታቀረቅር ‎ቅጥ አልባ ችግር ቢወዛ ‎                  እንደልብ ኑሮ ቢቸግር ‎ ‎በልጇ ደስታ 'ምትረካ ‎በሳቅ ውበቱ የምተፈካ ‎                  ትጉህ ብርታቷ ፅናት ‎ከሰው ልብ የማትጠፋ ‎ዘልአለም ተወዳ 'ምትኖር ‎                  እናት ምንጊዜም እናት ናት ‎ ✍ Mekdi @amen1995