cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

የአኺራ ስንቅ زاد الآخرة

قالَ اللهُ تباركَ وتعالى: ﴿وَتَزَوَّدُوا فإنَّ خَيْرَ الزَّاد التَّقْوَى﴾ [ سورة البقرة،ءاية 197]

Show more
Advertising posts
189
Subscribers
No data24 hours
-47 days
-830 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ነሲሓ ኮንፈረንስ የሚታደሙበትን የመግቢያ ትኬት online በመመዝገብ በነፃ ይውሰዱ ታላላቅ ኡለማዎች የሚሳተፉበት ልዩ የነሲሓ ኮንፈረንስ በአላህ ፈቃድ በሚሊኒየም አዳራሽ መጋቢት 1/2016 ይካሄዳል። በተከታዩ ሊንክ ከዌብሳይታቸን በስምዎ ነፃ የመግቢያ ቲኬት ማግኘት ይችላሉ። https://conference.nesiha.tv ለፕሮግራሙ ድጎማ በማድረግ አጋራችን ለመሆን Cbe 444 የሂሳብ ቁጥራችንን ይጠቀሙ። እናመሰግናለን ____ 🕌 ibnu Masoud islamic Center @merkezuna
Show all...
Adaban yaado bisô maxcòoy magaaliyyo Takkalem macaay? *** Kaxxam naba hoteelil daffeyaanaah Limo mangoh tan maaqo amrisaanaah yakmeenim magaaliyyo. Sukkar sinni qeerole bunaytu yaaqubeeniih Aaqabinnaanih caagid selê kah gudel cabaanam magaaliyyo edde celta mari yan.ceelalloh Shaahita selê kah gudel cabaanam, Juus yooqobeenik gudel cabanam kaxxa magaaliyyo yakkalen, Elle yooqobe afeena foyyah caba num yubleenik baduwtuuy Barrí numu ken garil. -IPhone kee Galaxy Altra gabat haanam magaaliyyo -Qusba Modeelih tan makiinah Maftaac gabat hayyaay, kataysiis elle daffeyta aracih foocal daffessa haanam magaaliyyo! -Telphonuh inkih yan hangí ucuyyaay, lih daffeyak sugem marak Kaxxa Saqoltí kah haytem ceelisak Telphone haa Saqal sissigiih daruurih yan caagidih kaa faxam ceelisak keenik baxsimuh idni esseram magaaliyyo -Qusbih tewqe kabellaay, BHS kee Gersí sartan xaamitaanaah Fashion katayaanam magaaliyyo -Yaabat inkí inkí English qangorut yantifiqeenim, Ceelloh #Already, #Actually innah tan qangoor magaaliyyo. - Migaaqitte yargiggiqeenim magaaliyyo Ceelalloh Macammadak Malle , Mame, Halima H, Zaynabaay Zahrak, Z iyyan. -Kulli mari Aaxige Weelem yakkalem maaqooqah migaaqittet Xeflih yaabaanaah, mangò udduur Maaqô qarwaa(Hoteelittee) kee Makaayintit Walalaanamih caaloota tan. - Mango weeloh tan limo mango Qatritteh Xaamiyyat waktii kee lakqo isinnik baysaamam magaaliyyoh tan. - Baadal kaxxam yamixxige marih migaaq Aliilih yaaxigeenim magaaliyyo, Ceelalloh Koqsoh celeemittey baadak tamixxige buttat digirtah migaaq inkih Aliilih (Cifzih) yaaxigeenim magaaliyyo! - Dariifal aytî gexxo le marittê luk abeenih yanin walal kee keenil yeceenih yanin tû mabul Tannah tanim magaaliyyoo kee bisô maxco hinna finqâ kal! ✍✍✍✍✍✍✍✍✍ Mucammad Awwal Samara
Show all...
🎞ከንቱ ምኞት!Ⅰ ኡስታዝ ተውፊቅ ራህመቶ @HanifMultimedia
Show all...
የዕለተ ሰኞ 27/05/2016 ስርጭት https://hanifradio.mixlr.com/events/3142661
Show all...
Hanif Radio | Hanif Radio's live audio

ሐኒፍ ሬዲዮ፤ ኢስላማዊ የድምጽ ትምህርቶች ዳዕዋዎች እና ፈትዋዎች የሚተላለፉበት የኦንላይን ሬድዮ ነው።

☝🏻☝🏻☝🏻 📚 የረጀብ ወር ቢድዓዎች 🎯 በእስልምና ቀን አቆጣጠር መሰረት 7ኛ ወር የሆነው ረጀብ ከሌሎች ወራቶች ተለይቶ የሚፈጸሙ ኢባዳዎች አሉት? 🎯 ኢስራዕ እና ሚዕራጅ 🎙 በሸይኽ ኢልያስ አሕመድ ____ 🏳️ የኡስታዝ ኢልያስ አህመድ የትምህርት መድረክ https://www.facebook.com/ustathilyas @ustazilyas
Show all...
ሸይኻችንን እናሳክም ዘንድ የቀረበ ጥሪ! 🛑🛑🛑🛑🛑🛑🛑🛑🛑🛑🛑 በዓፋር ክልል በአዉሲረሱ ዞን በዱብቲ ወረዳ ሰላም ጃሚዕ መስጅድ መስራች፣ ኢማም፣ ኻጢብና ሙዓሊም(መምሕር) የሆኑት ሸይኽ ሷሊሕ ሙስጠፋ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በልብ ሕመም ምክንያት ከሚወዱት ማሕበረሰብ ተነጥለዉ የቆዩ ሲሆን በአሁን ሰዓት ሕመሙ ጠንቶባቸዉ ወደከፍተኛ የልብ ሕመም ስትሮክ ደረጃ ተሻግሮ ከባቲ ወደ ደሴ ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሪፈር ተብለዉ በኢትዮጠቢብ ሆስፒታል ሕክምናቸዉን እየተከታተሉ ይገኛሉ። ይሁን እንጂ ከኢትዮ ጠቢብ ሆስፒታል ዶክተሮች በኩል ሸይኹን ለማዳን የበኩላቸዉን ጥረት እንደሚያደርጉና ነገር ግን ሕመሙ ከበድ ያለ በመሆኑ ለከፍተኛ ሕክምና ራሳቸዉን እንዲያዘጋጁ የሸይኹን ቤተሰብ አሳስቧል። በአሁን ሰአት ሸይኹን ከጎናቸዉ ሆኖ እያስታመመ የሚገኘዉ ብቸኛ ወንድ ልጃቸዉም ቢሆን ለዚህ ሕክምና የሚሆን አቅም የለለዉ በመሆኑ በከፍተኛ ጭንቀትና ሀሳብ ዉስጥ ይገኛል። እስከ አሁን ድረስ ባለፈዉ አንድ ወር ሙሉ ለሸይኹ ሕክምና ወጪ የ400,000ብር የብድር ዕዳ ያለባቸዉ ሲሆን ከዚህ በኋላ ለሚደረገዉ ሕክምና ተገማች 2ሚሊዮን በድምሩ 2.4(ሁለት ሚሊዮን አራመቶ ሺህ ብር) የሚያስፈልግ በመሆኑ ሁሉም ሙስሊም ማሕበረሰብ እንዲሁም ማንኛዉም ሀገርና ወገን ወዳድ የሆነ ሁሉ የሸይኹን ሕይወት ለመታደግ እንረባረብ ዘንድ አደራ ለማለት እንወዳለን። ከስር የተጠቀሱት የሸይኹ ልጃቸዉ የባንክ አካዉንት ቁጥሮች ናቸዉ። ሙሉ ስም: Abdusomed Sualih Mustefa 🛑 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ: 1000214014355 📌አቢሲኒያ ባንክ: 80152628 🛑አዋሽ ባንክ: 01304266942800 📌ዘምዘም ባንክ: 0000320820101
Show all...
ዝምድና! ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿الرَّحِمُ مُعَلَّقَةٌ بالعَرْشِ تَقُولُ مَن وصَلَنِي وصَلَهُ اللَّهُ، ومَن قَطَعَنِي قَطَعَهُ اللَّهُ.﴾ “ዝምድና በአርሽ ላይ ተንጠልጥላለች። እኔን የቀጠለ አላህ ይቀጥለው እኔን የቆረጠኝን አላህ ይቁረጠው ትላለች።” 📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 2555 በነዚህ አድራሻዎች ይከታተሉን፦ Telegeram፦ https://bit.ly/4ayf0xJ Whatsup፦ https://bit.ly/486xnrS Facebook፦ https://bit.ly/41zEZkk Instagram፦ https://bit.ly/4arMbTx X፦ https://bit.ly/41tIUPv Youtube፦ https://bit.ly/41yPkNg
Show all...
የቪዲዮ ምስልን ለደዕዋ መጠቀም ~ ምስልን ለአስገዳጅ ጉዳይ መጠቀምን በተመለከት ምስል መጠቀምን የሚከለክሉ ዓሊሞች ጭምር የሚፈቅዱት እንደሆነ የሚታወቅ ነው። በዚህ ላይ የተለየ መኖሩን አላውቅም። እናም ወንጀለኞችን ለማደን፣ ለመታወቂያ፣ ለመንጃ ፈቃድ፣ ለፓስፖርት፣ ወዘተ ፈቃጁም ከልካዩም ወገን ይፈቅዱታል። ምስልን ለደዕዋ መጠቀምን በተመለከተ ግን ከልካዮቹ ሃሳባቸው ለሁለት ይከፈላል። ከፊሎቹ ለማስተማሪያም ቢሆን ድምፅ በቂ ነው በሚል በወጥነት የከለከሉ አሉ። ለምሳሌ ሸይኹል አልባኒን መውሰድ ይቻላል። በሌላ በኩል ምስል መጠቀምን የሚከለክሉ ከመሆናቸው ጋር ለደዕዋ አገልግሎት መጠቀምን የፈቀዱ አሉ። ለምሳሌ ኢብኑ ባዝን መውሰድ ይቻላል። የሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚንን አቋም ከልካዩም ፈቃጁም ስለሚጓተተው ትቼዋለሁ። እንደ ሸይኽ ፈውዛን ያሉት ደግሞ ክልከላቸው ቢታወቅም በቪዲዮ የተቀዱ ትምህርቶቻቸው ግን በሰፊው ይሰራጫሉ። እስካሁን ያወራሁት ከልካዮቹን በተመለከተ ነው። ምክንያታቸው ቢለያይም በደፈናው የሚፈቅዱም በተጨባጭ እንዳሉ ለማህበራዊ መገናኛዎች ቅርበት ያለሁ አካል የሚያረጋግጠው ነው። ለደዕዋና መሰል ሐጃዎች ቀርቶ “ከእከሌ ጋር ተገናኘን” እያሉ የሚለጥፉ ብዙ መሻይኾች አሉ። እነዚህን በዑለማኦቹ በኩል የሚታዩትን የተለያዩ ሁኔታዎች ስንመለከት ከታች ያለው ማህበረሰበ በጉዳዩ ላይ እንደሚለያይ የሚጠበቅ ነው። ከፊሉ በወጥነት ይከለክላል። ከፊሉ ለዶሩራ እና ወይም ለሐጃ ይፈቅዳል። ከፊሉ በደፈናው ይፈቅዳል። ከኛ የሚጠበቀው አንደኛ ጉዳዩን ከስሜት ነፃ ሆኖ መመርመርና አቋም መያዝ ነው። ሁለተኛ ጉዳዩን ዑለማኦቹ በያዙት መጠን መያዝ ነው። በዒልም መተራረሙ እንዳለ ሆኖ ፈቃጅ ዑለማኦች ከልካዮቹን በፅንፈኝነት አልፈረጁም። ማሾፍና መሳለቅ ውስጥም አልገቡም። ከልካዮቹም የፈቃጆቹን መንሃጅ ጥያቄ ውስጥ አልከተቱም። ለማጉደፍና የጥላቻ ዘመቻ ለመክፈትም አልተጠቀሙትም። እኛስ ዘንድ ያለው? እኛ ጋር በፈቃጅም ይሁን በከልካይ በኩል የሚታየው ፅንፍ ነው። ፈቃጁ፦ እነ እከሌ ትናንት ይከለክሉ እንዳልነበር ይሄው ዛሬ ራሳቸው በቪዲዮ መቅረብ ያዙ እያለ ለሹፈት ለመሳለቅ የሚያነሳ አለ። በጉዳዩ ላይ ግለሰቦች የአቋም ለውጥ ካሳዩም ምንም ለሹፈት የሚያበቃ ነገር የለም። መስለሐን በማስላት ወይም የፈቃጆቹ ትንታኔ አሳምኗቸው አቋም ቢቀይሩ ይሄ ፈፅሞ የሚያስወግዝ ነገር አይደለም። መረጃ አሳምኗቸው ሳይሆን ስሜታዊነት አሸንፏቸው ከሆነ ሂሳባቸው ከጌታቸው ዘንድ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ከልካዩ ክፍል ጉዳዩን ለቡድናዊ ፍረጃ ሲጠቀመው ማየት የተለመደ ሆኗል። ይሄ ክፍል ጉዳዩን ለማውገዝ የሚያስጮኸው ሰው እየመረጠ ነው። ከዑለማኦች ውስጥ የሚፈቅዱ እንዳሉ ያውቃል። እዚያ ላይ ትንፍሽ አይልም። ሌላው ቀርቶ እዚያው ከጎኑ የተሰለፉ ምስል የሚጠቀሙ እንዳሉ እያወቀ የውግዘት ዘመቻ ውስጥ አይገባም። ጉዳዩን የሚያነሳው የሆኑ ቂም የተጋባቸውን አካላት ለማጠልሸት በማለም ነው። በሱ ቤት ለዲን፣ ለሱና መታገሉ ነው። የለየለት ቡድንተኝነት እያራመደ ሰዎችን በቡድን ይፈርጃል። ወንድሜ ሰዎችን ብትሸውድ አላህን አትሸውድም። ለማንኛውም ሃሳቤን በሸይኽ ሱለይማን አሩሐይሊይ ትንታኔ ልዝጋ። ሃሳባቸውን ጨመቅ አድርጌ ነው የማቀርበው። እንደሳቸው ህይወት ያላቸውን ነገሮች መሳል አራት አይነት ነው። 1. እንደ ሃውልትና ቅርፃቅርፅ ያሉ ጥላ ያላቸው ምስሎችን መሳል በክልክልነቱ ላይ ዑለማኦች ተስማምተዋል። ከትልልቅ ወንጀሎች ውስጥ ነው። 2. ጥላ የሌለው ወረቀት፣ ጨርቅና መሰል ነገሮች ላይ በእጅ ተነድፎ የሚሳል ምስል አብዛኞቹ ዓሊሞች ከልክለውታል። ከፊል ታቢዒዮችና ጥቂት ዑለማኦች ወደ መፍቀዱ ሄደዋል። ሚዛን የሚደፋው - አዋቂው አላህ ነው - ሐራም ነው የሚለው ነው። (ምክንያታቸውን ቦታው ላይ ዘለግ አድርገው ስላሰፈሩ የፈለገ ይመልከተው።) 3. እንደ ካሜራና ሞባይል ስልክ ባሉ መሳሪያዎች ተንቀሳቃሽ ያልሆኑ ቋሚ ምስሎችን መሳልን በተመለከተ የዘመናችን ዑለማኦች ተለያይተውበታል። ከፊሎቹ ስእል መሳልን የሚከለክሉ መረጃዎች ጠቅላይ ስለሆኑ እንዲሁም በነዚህ መሳሪያዎች የሚፈፀመውም ሁሉም እንደሚስማሙት ምስል መሳል (ተስዊር) ስለሆነ ሐራም እንደሆነ ገልፀዋል። ከፊሎቹ ደግሞ የተለያዩ መነሻዎችን በመጥቀስ የተፈቀደ ነው ብለዋል። ሸይኹ መጨረሻ ላይ ይሄኛውም ሐራም እንደሆነ ገልፀዋል። (የሚቀርቡትን ትንታኔዎችና የሸይኹን ምላሾች የፈለገ ከቦታው ይመልከት።) ባይሆን እንድ የህክምና ጉዳይ ላሉ አስገዳጅ ጉዳዮች እና እንደ ለበጎ አድራጎት ተግባራት ያሉ ማሳያዎች ያሉ ለአንገብጋቢ ሐጃዎች ይፈቀዳል ብለዋል። 4. ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ማስገኘትን በተመለከተ ለሁለት ከፍለውታል። የቀጥታ ስርጭትን በተመለከተ ይፍቀዳል ይላሉ። ልክ በመስታዎት እያንፀባረቁ የሰዎችን ምስል እንደመመልከት እንደሆነም ይገልፃሉ። ቀጥታ ያልሆነውን (የቪዲዮ) ቅጂ በተመለከተ ከፊል ዓሊሞች ለደዕዋ መጠቀምን ጨምሮ ሐራም ነው ይላሉ። ከፊሎቹ ሐራም እንደሆነ ከመግለፃቸው ጋር ለደዕዋ ማስተላለፊያ መጠቀምን ይፈቅዳሉ። የኢብኑ ባዝ አቋም እዚህ ላይ ነው የረጋው። ቀድመው ይከለክሉ ነበር። ኋላ ግን ለፓስፖርትና ለዶክመንቶች ከመጠቀም ይልቅ ይሄኛው የበለጠ አንገብጋቢ እንደሆነ በማመን በቴሌቪዥን እየቀረቡ የሚያስተምሩትንም ፈቅደዋል። የራሳቸውም የተወሰኑ ትምህርቶች በቪዲዮ ተቀርፀው ወጥተዋል። ከፊል ዓሊሞች ደግሞ ይሄ ልክ እንደ መስታዎት ነፀብራቅ እንጂ ከነ ጭራሹ ምስል መሳል አይደለም በማለት ፈቅደውታል። እኔ ዘንድ ግን - “እኔ ዘንድ” ማለት የሚግገባኝ ከሆንኩኝ - ከዑለማኦቹ አቋሞች ውስጥ ሚዛን የሚደፋው - አዋቂው አላህ ነው - በቪዲዮ መቀረፅ ከአሻሚ ጉዳዮች ውስጥ ነው። ግልፅ ከሆነ ሐላልም አይደለም። ግልፅ ከሆነ ሐራምም አይደለም። ወደ ክልከላው የሚጠራ ነገር አለ። እሱም ምስል ነውና። ይህን የሚገፋ ደግሞ አለበት። አማኝ ሊርቀው የተገባ ነው። ለእምነቱም፣ ለክብሩም የተሻለ ነው ይሄ። እንደ ሙሓዶራትና የኪታብ ትምህርቶች ያሉ ፋይዳዎች (መስለሐዎች) ካልታየበት በስተቀር። በመጨረሻም እኔ በታየኝ ድምዳሜ ላይ ልትስማማም፣ ልትቃረንም ትችላለህ ይላሉ። [ሸርሑ ኪታቢ ተውሒድ፡ 1627 - 1635] (ኪታቡ በጣም ምርጥ ሸርሕ ነው። የምትፈልጉ ካላችሁ የpdf ፋይሉን ቴሌግራም ቻናሌ ላይ ላያይዝላችሁ እችላለሁ።) ረጅሙ ፅሑፌ በአንድ አረፍተ ነገር ሲጠቃለል ጉዳዩን ዑለማኦቹ በያዙት መጠን በልኩ እንያዘው የሚል ነው። አደብ የጎደለው ሃሳብ ይሰረዛል። Ibnu Munewor = * የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor * የዋትሳፕ ቻናል፦ https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M * ፌስቡክ https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL
Show all...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

ሰላትን የሚጠባበቅ፣ ወቅቷን ጠብቆ የሚሰግድ በሁለት ሶላቶች መካከል ይሞታል። የሰገደው ሰላትና ገና ሊሰግደው በልቡ ነይቶት ሲጠባበቅ የነበረው። ሶላትን አጥብቀን እንያዝ በጀመአ መስጊድ ሳይመጣብን ሞት አስገድዶ ሚወስድ።
Show all...
አልኢማም አዩብ አሲኽቲያኒ. እንዲህ ብለው ነበር:"የሱና ባለቤት የሆነ ሰው የሞት መርዶ ሲደርሰኝ፣ አንድ አካሌን አንዳጣሁ ይሰማኛል።" ሱብሃነ ረቢ እውነታቸውን ነው። አይ ሰው አለ ሲባል እርግፍ!!!! አላህ ህይወት እንዲህ ናት!!!! አላህ ይማራቸው! የጀነት ያድርጋቸው! ለልጆቻቸው አላህ ወልይ ይሁንላቸው! ሰብሩን ቻይነቱን ይለግሳቸው! ሸይኽ ዐብዱ ጥሩ የአላህ ሰው ነበሩ! هكذا نحسبه ولا نزكي على الله أحدا Ustaz Mohammed Hassen Mamme
Show all...