en
Feedback
የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ

የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ

Open in Telegram

ይህ የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ ነው።ዓላማዬ የተለያዩ መፅሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶችን ማካፈልና ማድረስ ሲሆን ምክሮችን፥አባባሎችን፥ፀሎቶችንና ትዝብቶቼን የማካፍልም ይሆናል።የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ወደ ልቤ ያመጣውንና የተናገረኝንም እፅፋለሁ።ትውልዱን ወደ ኢየሱስ የሚያስጠጋውን የትኛውንም ነገር የምፅፍበት ገፄ ነው።በማንበብና ሼር በማድረግ ከአገልግሎቴ ጎን ይቁሙ።0984005562.

Show more
447
Subscribers
+224 hours
+87 days
+3030 days
Posts Archive
በአንድ ወቅት ቢሊ ግርሃም እንዲህ አሉ፦ 👉 #ሃብታችን_ሲበላሽ_ምንም_ነገር_እንዳልተበላሸ_ይቆጠራል 👉 #ጤንነታችን_ሲበላሽ_አንድ_ነገር_እንደተበላሸ_ይቆጠራል 👉 #ባህሪያችን_ሲበላሽ #ሁሉም_ነገር_እንደተበላሸ_ይቆጠራል። #ቢሊ_ግራሃም

#የጠበቁት_መሲሕና #ነቢያት_የተናገሩለት_መሲሕ 🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት 👉በጌታ ኢየሱስና በአይሁዳውያን መካከል ከፍተኛ አለመግባባት ነበር።መሲሕን እየጠበቁ ቢሆንም ቅሉ ከመጣው መሲሕ ጋር ተላለፉ።የጠበቁት መሲሕ የመጣውን መሲሕ ጋረደባቸው።በአእምሮአቸው ለተቀበሉትና ለሚጠብቁት መሲሕ ሲሉ አብ ለላከው መሲሕ የታወሩ ሆኑ። 👉ተአምራት ማድረጉ፤የሚያስተምረው ትምህርት፤የሚኖረው የቅድስና ሕይወት እያሳደደ የሚከሳቸው ቢሆንም የእነርሱ መሲሕ በፊታቸው እንደ አዚም ሆኖባቸው ነበር። 👉እነርሱ የሚጠብቁት መሲሕ ከድሃ ቤተሰብ ሊመጣ አይችልም…ኢየሱስ ግን ከድሃዋ ድንግል ማርያም ተወለደ።ሉቃ.2:22-24፤ማቴ.13:54-57 👉እነርሱ የሚጠብቁት መሲሕ ፈረሰኛና ጦረኛ እንዲሁም ከሮማውያን ነፃ የሚያወጣቸው ነው……ኢየሱስ ግን የሰላም አለቃ መሆኑን ለማሳየት በአህያ ውርንጫ የተቀመጠ ደግሞም ተዋጊ ያልሆነ ንጉሥ በመሆኑ አልተቀበሉትም።ማቴ.21:4-7 👉እነርሱ የሚጠብቁት መሲሕ ፈፅሞ የማይሞትና ለዘላለም የሚኖር ሲሆን ……የተገለጠው መሲሕ ግን የሚሞት ደግሞም የሚነሣ ሆነ።ዮሐ.12:34፤ዳን.9:26 👉እነርሱ የሚጠብቁት መሲሕ አይሁዶች የናቋቸውን ሴቶች፥ኃጢአተኞችንና ድሆችን የሚንቅ ሲሆን……የተገለጠው መሲህ ግን የሴት ደቀመዛሙርት ያሉት፥የኃጢአተኞች ወዳጅ፥የድሆች መጋቢ አባት ነበር።ማቴ.9:10-13፤ሉቃ.15:1-2፤ሉቃ.7:39፤ሉቃ.21:3 👉እነርሱ የሚጠብቁት መሲሕ ሕጋቸውን የሚያስጠብቅ፥ወጋቸውን የሚያስከብር ሲሆን…የተገለጠው መሲሕ ግን ሕግ ጠንቅቆ የፈፀመ ነገር ግን ፀጋን ያስተማረ፥ወጋቸውን የነቀፈና ድራማቸውን ያጋለጠ በመሆኑ አልተቀበሉትም።ማቴ.15:1-14፤ማቴ.23 🛑ዛሬም ብዙዎች አእምሮአቸው ላይ በፈጠሩት እግዚአብሔር ምክንያት በመፅሐፍ ቅዱስ ራሱን ለገለጠው እግዚአብሔር የታወሩ ናቸው። 🛑ዛሬም ብዙዎች አእምሮአቸው ላይ በፈጠሩት ኢየሱስ ምክንያት በመፅሐፍ ቅዱስ ራሱን ለገለጠው ኢየሱስ የታወሩ ናቸው። ዮሐንስ 10 ¯²⁴ አይሁድም ከበውት፣ “እስከ መቼ ልባችንን አንጠልጥለህ ታቈየናለህ? አንተ ክርስቶስ ከሆንህ በግልጽ ንገረን” አሉት።²⁵ ኢየሱስም እንዲህ ሲል መለሳላቸው፤ “እኔ ነግሬአችሁ ነበር፤ እናንተ ግን አታምኑም፤ በአባቴ ስም የማደርጋቸው ታምራትም ስለ እኔ ይናገራሉ፤ ²⁶ እናንተ ግን በጎቼ ስላልሆናችሁ አታምኑም፤²⁷ በጎቼ ድምፄን ይሰማሉ፤ እኔ ዐውቃቸዋለሁ፤ እነርሱም ይከተሉኛል፤²⁸ እኔ የዘላለም ሕይወት እሰጣቸዋለሁ፤ ከቶ አይጠፉም፤ ከእጄም ሊነጥቃቸው የሚችል ማንም የለም።²⁹ እነርሱን የሰጠኝ አባቴ ከሁሉ ይበልጣል፤ ከአባቴም እጅ ማንም ሊነጥቃቸው አይችልም።³⁰ እኔና አብ አንድ ነን።”³¹ አይሁድ ሊወግሩት እንደ ገና ድንጋይ አነሡ፤³² ኢየሱስ ግን፣ “ከአብ የሆኑ ብዙ ታላላቅ ታምራትን አሳየኋችሁ፤ ታዲያ ከእነዚህ ስለ የትኛው ትወግሩኛላችሁ?” አላቸው።³³ አይሁድም፣ “የምንወግርህ፣ ተራ ሰው ሆነህ ሳለህ፣ ራስህን አምላክ በማድረግ፣ የስድብ ቃል ስለተናገርህ ነው እንጂ ከእነዚህ ስለ የትኛውም አይደለም” ብለው መለሱለት።… ³⁶ ታዲያ፣ ‘የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ’ ስላልሁ፣ አብ ለራሱ ለይቶ የቀደሰውንና ወደ ዓለም የላከውን፣ ተሳድበሃል ብላችሁ ለምን ትወነጅሉኛላችሁ? ³⁷ አባቴ የሚያደርገውን ባላደርግ አትመኑኝ፤ ³⁸ የማደርገው ከሆነ ግን እኔን ባታምኑኝ እንኳ፣ አብ በእኔ እንዳለ እኔም በአብ እንዳለሁ ታውቁና ታስተውሉ ዘንድ ታምራቱን እመኑ።” ³⁹ እንደ ገናም ሊይዙት ሞከሩ፤ እርሱ ግን ከእጃቸው አመለጠ። 🙏 #በቃሉ_ለተገለጠው፥ #በነቢያት_ለተተነበየው፥#በሐዋርያት_ለተሰበከው፥#ለሞተው_ደግሞም_ለተነሣው፤ #ላረገው_ተመልሶም_ለሚመጣው #ለመሲሓችን_ለኢየሱስ_ክርስቶስ #ክብርና_ኃይል፤ #ባለጠግነትና_ሞገስ_ይሁን።አሜን። ዮሐንስ 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁴² እርሱ አስቀድሞ የራሱን ወንድም ስምዖንን አገኘውና፦ #መሢሕን_አግኝተናል አለው፤ ትርጓሜውም ክርስቶስ ማለት ነው።… ⁴⁶ ፊልጶስ ናትናኤልን አግኝቶ፦ #ሙሴ_በሕግ #ነቢያትም_ስለ_እርሱ #የጻፉትን የዮሴፍን ልጅ የናዝሬቱን #ኢየሱስን_አግኝተነዋል አለው። እባክዎን ለሌሎች ሼር ያድርጉት🙏 🗓17/08/2014 የምሕረት ዓመት✍

❤️የእለቱ መልእክት❤️ #ሰበብ_ያጣንለት_ኢየሱስ_ብቻ 🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት 👉ለእነርሱ ካለን ፍቅር የተነሳ ብንሞትላቸው ብለን የተመኘንላቸውን ሰዎች ዘግይቶም ቢሆንም ፍቅራችንም ሞታችንም አይገባቸውም ብለን አንቅረን ተፋናቸው።በተጠጋናቸው ቁጥር ሲርቁን፤በወደድናቸው ፋንታ ሲጠሉን፤ሁሌ ስናገኛቸው ሲሰለቹን አይተን "ሰበብ" አገኘንባቸው። 👉አዋቂዎች ናቸው ያልናቸው፥በእውቀትና ትጋታቸው ምክንያት ያከበርናቸው ሰዎች…አላዋቂነታችንን ሲነግሩን፤ከሰውነት ተራ አሳንሰው እነርሱን ለማግኘት ደጅ ሲያስጠኑን፥እውቀት እንጂ ፍቅር እንደሌላቸው ሲገባን ናቅናቸው።በልባችን እንዳይቆዩ "ሰበብ" አገኘንባቸው። 🗣ዝነኛ አገልጋይ ናቸው፤ጌታ ይጠቀምባቸዋል፤መንፈስ ቅዱስ የሞላባቸው ናቸው ብለን መድረኩንና ልባችንን፤መባችንንና ጊዜያችንን የሰጠናቸው ሰዎች……በትእቢት ተነፍተው ዝቅ አድርገው ሲያዩን፤ያለ እኛ ወደ ጌታ አትጠጉም ሲሉን፤አገልጋይ ናቸው ያልናቸው ነገሥታት ሆነው ሲገዙን፤እነርሱን ለማግኘትና ለማማከር ፈፅሞ የማይቻል ሆኖ ስናይ ለእነርሱ ባለን ፍቅርና ክብር ለመቀጠል አልቻልንም።"ሰበብ" አገኘንባቸው። 👉አንዱ ኢየሱስ ብቻ ግን ለሰበብ አይመችም።ከወደደ አይጠላንም።ለእኛ ክብር አለው።እውቀት አልባ መሆን ቀርቶ ቅድስና አልባ መሆናችን እንዲንቀን አላደረገውም።ኢየሱስ ትልቅ ነው ማንንም አይንቅም። 👉 #ኃይሉን_ለማዳን፤ #ቅድስናውን_ኃጢአተኛውን_ለመቀደስ_ይጠቀምበታል።ስንፈልገው እናገኘዋለን።ለማንኛውም ሰው ኢየሱስ ጊዜ አለው። 👉ኢየሱስ ላይ ብትፈልጉ እንኳን ሰበብ አታገኙበትም።ትሁትና ኃያል፤ሰው ወዳድና ታማኝ እረኛ ማን እንደ ኢየሱስ። 👉ፍቅሩ ይብዛላችሁ። #ተጠጉት። “ #እንግዲህ_ለእኛ_የሚያስፈልገን፣ #ቅዱስ፣ #ነቀፋ_የሌለበት፣ #ንጹሕ፣ #ከኀጢአተኞች_የተለየና #ከሰማያት_በላይ_የከበረ_እንደዚህ_ያለ_ሊቀ_ካህናት_ነው።” — ዕብራውያን 7፥26 🗓10/08/2014 የምሕረት ዓመት ✍

የፊታችን እሁድ መጋቢት 18 በሚኖረን የአምልኮና የቃል ጊዜ አብረውን እንዲሆኑ በጌታ ፍቅር ተጋብዘዋል። #እሁድ_ከሰአት #ከ9:00 #እስከ #11 #ሰአት። #ለተጨማሪ_መረጃ 0984005562/09311
የፊታችን እሁድ መጋቢት 18 በሚኖረን የአምልኮና የቃል ጊዜ አብረውን እንዲሆኑ በጌታ ፍቅር ተጋብዘዋል። #እሁድ_ከሰአት #ከ9:00 #እስከ #11 #ሰአት። #ለተጨማሪ_መረጃ 0984005562/0931153924

የመክፈቻ ጉባኤያችን
+5
የመክፈቻ ጉባኤያችን

መጋቢት 10 እና 11
መጋቢት 10 እና 11

#ወንጌል_ስንመሰክር_እነዚህን_ሰባት_መርሆዎች_እናስብ 🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት 1⃣፦ #ላልዳኑ_ሰዎች_ከማሰብና_እነርሱን_ከመውደድ_ስሜት_እንጂ_ቢያምኑ_ይመኑ_ከሚል_ስሜት_እንዳይሆን_መጠንቀቅ 2⃣፦ #ጥበብና_ቅንነት_በተሞላበት_መንፈስ_መመስከር 3⃣፦ #እንደቃሉ_ብቻ_ወንጌልን_መናገር_እንጂ_ብሽሽቅና_ክርክር_እንዳይሆን_መጠንቀቅ 4⃣፦ #በአንዴ_የመሰከርንላቸው_በአንዴ_ካላመኑ_አለማለት 5⃣፦ #የመሰከርንላቸው_ሁሉ_ባይድኑም_ተስፋ_ሳይቆርጡ_መመስከርን_መቀጠል 6⃣፦ #ከመመስከራችን_በፊት_መፀለይ 7⃣፦ #ለመሰከርንላቸውም_ሰዎች_መፀለይ እነዚህን ማሰብ ይጠቅማል። ሮሜ 1 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁶ በወንጌል አላፍርም፤ ምክንያቱም ለሚያምን ሁሉ ለድነት የሚሆን የእግዚአብሔር ኀይል ነው፤ ይህም በመጀመሪያ ለአይሁድ፣ ቀጥሎም ለአሕዛብ ነው። ¹⁷ በወንጌል የእግዚአብሔር ጽድቅ ተገልጦአልና፤ ጽድቁም ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ በእምነት የሆነ ነው፣ “ጻድቅ በእምነት ይኖራል” ተብሎ እንደ ተጻፈው። 🗓30/06/2014 የምሕረት ዓመት ✍

ጠቃሚ ምክር የምንሰብከውን ወንጌል መረዳት " ሐዋርያ ሊሆን የተጠራ የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ ጳውሎስ በነቢያቱ አፍ በቅዱሳን መጻሕፍት አስቀድሞ ተስፋ ለሰጠው ለእግዚአብሔር ወንጌል ተለየ።ይህም ወንጌል በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ ተወለደ እንደ ቅድስና መንፈስ ግን ከሙታን መነሣት የተነሣ በኃይል የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ ስለ ተገለጠ ስለ ልጁ ነው፤ እርሱም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። " ( ሮሜ 1: ¹ -⁴) ሐዋርያው ዻውሎስ ፣እግዚአብሔር አስቀድሞ በነቢያቱ አፍ በቅዱሳት መጽሐፍት በኩል ለመሰከረለት ለእግዚአብሔር ወንጌል እንደተለየ ይነግረናል። ወንጌል የእግዚአብሔር ነው እንጂ የሰው አይደለም። የሰው አይደለም ማለት ግን ለሰው አይደለም ማለት አይደለም። እውነተኛ አገልጋይ ለተለየለት የእግዚአብሔር ወንጌል በታማኝነት ይኖራል እንጂ አዲስ የሰው ወንጌል አይፈጥርም። አንዳንዶች ወንጌል ከሙታን ስለተነሳው መንፈስ ስለሆነው ስለ ክርስቶስ ነው ይላሉ። ሐዋርያው ግን ያለምንም መከፋፈል: -ወንጌል በሥጋ ስለተወለደው ፣እንደ ቅድስና መንፈስም ከሙታን ስለተነሳው ስለልጁ መሆኑን ያሰምርበታል። ይህ ማለት ደግሞ ኢየሱስ በሥጋ ከመወለዱ ጀምሮ ከሙታን እስከመነሳቱ ብሎም ማረጉንና ዳግመኛ መምጣቱ ድረስ ያለውን መልእክት መሰበኩን ያጠቃልላል። ክርስቶስ ስብእና ብቻ ሳይሆን ትምህርትም ነው። እርሱን ማዕከላዊ በማድረግ ውስጥ እግዚአብሔርን ወደ መምሰል እናድጋለን። ከዚያ ውጭ ግን :- " በመገለጥ " ስም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በግልጽ ከተቀመጠው መለኮታዊ አሳብ በተቃራኒ በሰው ወንጌል ( አሳብ) አጉል መራቀቅ ጥቅም የለውም። ሐዋርያው እነዚህ አይነት ሰዎች መለያቸው ትእቢት መሆኑን ይናገራል። " እነዚህን አስተምርና ምከር። ማንም ልዩ ትምህርት የሚያስተምር ከጌታችንም ከኢየሱስ ክርስቶስ በሆነው ጤናማ ቃልና እግዚአብሔርን ለመምሰል በሚስማማ ትምህርት የማይጠጋ ቢሆን፥በትዕቢት ተነፍቶአል አንዳችም አያውቅም " ( 1ኛ ጢሞ 6 ፥ 3 -5) አንድ ትምህርት እውነተኛ የመሆኑ መለኪያ እግዚአብሔርን ለመምሰል ይረዳል ወይስ አይረዳም? የሚለው ነው። ስለዚህ የምንገልጠው መልእክት እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚጠቅም መሆኑን በደንብ ማረጋገጥ አለብን። በተለይ አብዛኞቹ ካሪዝማዊ አገልግሎቶች የእግዚአብሔርን ቃል ክብር ወደ ጎን መጣላቸው ሳያንስ የሚያንጓጥጡ እየሆኑ በመምጣታቸው ለቤተክርስቲያን ፈተና እየሆኑ እንደሆኑ አስተውላለሁ። የእግዚአብሔር ቃልና መንፈስ ተለያይተው አያውቁም። መንፈሱ ያለቃሉ አይናገርም ፣ ቃሉም ያለመንፈሱ አይሠራም። እንደ አዽሎስ በመጸሐፍ እውቀት እየበረቱ በመንፈስ መቃጠል ይቻላል። " በወገኑም የእስክንድርያ ሰው የሆነ ነገር አዋቂ የነበረ አጵሎስ የሚሉት አንድ አይሁዳዊ ሰው ወደ ኤፌሶን ወረደ፤ እርሱም በመጻሕፍት እውቀት የበረታ ነበረ።እርሱ የጌታን መንገድ የተማረ ነበረ፥ የዮሐንስንም ጥምቀት ብቻ አውቆ በመንፈስ ሲቃጠል ስለ ኢየሱስ ይናገርና በትክክል ያስተምር ነበር።" ( ሐዋ 18 ፥ 24 - 25 ) በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን ወንጌል ለእኔና ለወንድሞቼ የምመኘው ነገር ለቃሉ እውነት ታማኝ በመሆን በመንፈስ ቅዱስ እንድናገለግል ነው። “ማንም ሰው የሚናገር ቢሆን፥ እንደ እግዚአብሔር ቃል ይናገር፤ የሚያገለግልም ቢሆን፥እግዚአብሔር በሚሰጠኝ ኃይል ነው ብሎ ያገልግል፤ ክብርና ሥልጣን እስከ ዘላለም ድረስ ለእርሱ በሚሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።”[ 1ኛ ጴጥ 4፥11 ] ጸጋ ከሁላችን ጋር ይሁን! አገልጋይ ቃለአብ ካሳዬ https://t.me/joinchat/AAAAAEU5RuzP9SnM2hcSYg

❤️የእለቱ መልእክት❤️ #ይሄን_ወንድ_እንዳታገቢው 🗣በአገልጋይ ብርሃኑ 👉ጋብቻ የከበረና በእግዚአብሔር የተመሠረተ ተቋም ነው።ጋብቻ ሠርግ አይደለም።ሠርግ ኪስሽን፤ጋብቻ ግን አቋምሽንን ይፈልጋል።ጋብቻ ንፁህ የክርስቶስና የቤተክርስቲያን ስእል ነው።ባል የሚወክለው ክርስቶስን፤ሚስት የምትወክለው ቤተክርስቲያንን ነው።ስለዚህ ክርስቲያን ሴቶች ይህን ንፁህ ስእል የሚያበላሽ ጋብቻን እንዳይመሰርቱ ከወዲሁ ሊያስቡበት ይገባል።ጋብቻ መግቢያ በር እንጂ መውጫ በር አልተሰራለትም።የፈቱ ሰዎች በር ሰብረው እንጂ ለመውጫ የሚሆን በር ተጠቅመው አልወጡም።ስለዚህ ከማግባቷ በፊት የፍቅር ጓደኛዋ ወይም እጮኛዋ ከዚህ በታች ከተዘረዘሩት አንዱን ችግር ካስተዋለችበት፥በቀላሉ ለመታረምም እድል እንደሌለው ካረጋገጠች ወዲያው ብትወስንና ብታቆም ይመከራሉ። 1⃣ #በእምነት_የማይመስልሽን፦ አንዳንድ ጊዜ በክርስቲያን ሴቶች የሚደመጠው አንድ ነገር፦ "ከአማኝ ወንዶች ያላመነ ይሻላል" የሚል ነው።አማኝ ወንድ ፈዘዘ…ዋሸ…ከኔ ውጭ ሄደ ወዘተ የሚል እንደሴቶቹ የተለያየ ምክንያት እንሰማለን።ግን መርሳት የሌለብሽ እውነት አማኝም ሰው መሆኑንና መንፈሳዊ ሕይወት እድገት መሆኑን ነው።በጭራሽ ግን ያላመነን ወንድ ካመነ ወንድ ይልቅ ልትመርጪው አይገባም።ለኔ ታማኝ ነው ብለሽ በአምልኮ ላይ የሚያመነዝር ሰው ካገባሽ ካንቺ በላይ ራስወዳድና ሰነፍ ከየት ይመጣል? እለወጣለሁ ብሎኛል ብለሽ ካመንሽው የእባብ ስብከት ካታለላት ሔዋን ልጅነት አልተላቀቅሽማ? ስለልጆችሽ፥ስለወደፊት መንፈሳዊ ሕይወትሽ ከምንም ስለ እግዚአብሔር ደስታና ፈቃድ ስትይ ካላመነ ሰው ጋር በማይመች አካሄድ አትጠመጂ። 2⃣ #የማያከብርሽን፦ ለሴትነትሽ ክብር የሌለው ወንድ ሁሌም ስላንቺ ሲያስብ የሚያስበው ትዳርን ሳይሆን አዳርን ነው።መሳደብ፥ማናናቅና ማጣጣል፥ላደረግሽለት ነገር ዋጋ አለመስጠት ወይም ይገባኛል ብሎ ማሰቡ በራሱ ላንቺ ክብር እንደሌለው የሚያሳይ ነው።ጆሮውንና ጊዜውን ካልሰጠሽ፥በተደጋጋሚ ቀጠሮ ከሰረዘ፤አብራችሁ ቁጭ ብላችሁ ሌሎች ሴቶችን የሚያይና የሚቀላውጥ ከሆነ ላንቺ ክብር የለውምና በጊዜ ወስኚ። 3⃣ #ለሴት_ጥሩ_አመለካከት_የሌለውን፦ ይሄን በወሬዎቹና በድርጊቶቹ ማወቅ ይቻላል።ሴቶች የቤት እመቤት ብቻ ነው መሆን ያለባቸው(በቤት ብቻ ይስሩ) የሚል አቋም ካለው፤ወንድ ሲያጠፋ ወይ ሲያመነዝር "ምን ያድርግ ወዶ አይደለም?" የሚልና "ውይ ሴቶች…ሴቶች እኮ" እያለ ሴትና ሴትነትን ሰይጣናዊነት ካስመሰለው…ምን ትጠቢቂያለሽ? ባልሽ አይሆንም። 4⃣ #ዓላማ_የሌለውን(ግዴለሽ)፦ አነሰም በዛ ያገኘውን ሥራ እየሰራ የማይደክም ከሆነ፥ለመሥራትና ለመለወጥ፥ለመማርና ለማደግ ማያስብ ከሆነ፥የቤተሰብ ውርስ ጠባቂ፥ከውጭ በሚላክለት ገንዘብ ተመፃዳቂ ከሆነ…በመዝናናትና ከቢጤ ጓደኞቹ ጋር ሆኖ ገንዘብ የሚያጠፋ ከሆነ…ነገ ላንቺም ለልጆቹም ኃላፊነት የሚሰማው ስላልሆነ በጊዜ ወስኚ። 5⃣ #የሴት_ዘመደ_ብዙውን፦ ስልኩ በሴቶች የተጨናነቀ…ሴቶችን የሚያደንቅ…ተፈቃሪና ተፈላጊ እንዲሁም ዘመደ ብዙ እንደሆነ የሚያስመስለውን ከፍቅር ሕይወትሽ blacklist ውስጥ አስገቢው።በጊዜ። 6⃣ #የሚያነፃፅርሽን፦ አንቺ አንቺ ነሽ።ሌላን ሴት መሆን አትችይም።ይሄን የሚቀበል ባልሽ ነው።አብራችሁ ሁናችሁ በወሬያችሁ መሃል ውበትሽንና አመለካከትሽን በማድነቅም ይሁን በማንኳሰስ "ከሴቶችና ከእገሊት" ጋር እያነፃፀረ የሚያወራ ከሆነ……Run. 7⃣ #ለውጫዊ_ውበትሽ_ብቻ_አድናቆት_ያለውን፦ አፍንጫሽ፥ዐይንሽ፥ፀጉርሽ፥ተክለ ቁመናሽ እያለ ውሎ ካደረ…ከውጫዊ ውበትሽ ይልቅ ለውስጣዊ ውበትሽ ምንም ኮሜንት ከሌለው…አለው እንኳን ብንል ትንሽ ብቻ ከሆነ መልእክቱ ሁለት ነው።አንደኛ፦አንቺም ለውጫዊ ውበትሽ እንጂ ለውስጣዊ ውበትሽ ግድ የሌለሽ ሴት ነሽ ማለት ነው።ሁለተኛም፦ ለሥጋዊ ፍላጎቱ ማርኪያ እቃ እንጂ ነገ ሚስቴ ትሆናለች ብሎ ለቁምነገር አያስብሽም።ጊዜውም ሲደርስ ጥሎሽ ይሄዳል ማለት ነው። 👉በየትኛውም የፍቅር ሕይወት የብስለት ድርሻውን አንቺ ልትወስጂ ይገባል።ለሚያፈቅርሽና ጌታን ለሚወድ ሰው ቅድሚያ ስጪ።ደግሞ አንድ ነገር አትርሺ፦ ለራስሽና ለሴትነትሽ ዋጋ፤ለፍቅራችሁ ጊዜ ስጪ።ተቻኩለሽ አትወስኚ።…… 🛑(ከላይ የገለፅኳቸው ጠባያት ማይናቁና ሊታዩ የሚገባቸው ጠባያት እንጂ አሻሚ ነገር የሌላቸው ፍፁም ምክር ስላልሆኑ የሚጠቅማችሁን ውሰዱ።.)🛑 🗓13/06/2014 የምሕረት ዓመት✍

❤️የእለቱ መልእክት❤️ #ይህችን_ሴት_እንዳታገባት 🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት (#ላላገቡ_ክርስቲያን_ወንዶች_ብቻ_የተፃፈ።… #ለሴቶችና_ላገቡ_ማንበብ_የተከለከለ_ነው) 👉ጋብቻ የከበረና በእግዚአብሔር የተመሠረተ ተቋም ነው።ጋብቻ ሠርግ አይደለም። #ሠርግ_ኪስህን፤ #ጋብቻ_ግን_አቋምህን_ይፈልጋል።ጋብቻ ንፁህ የክርስቶስና የቤተክርስቲያን ስእል ነው።ባል የሚወክለው ክርስቶስን፤ሚስት የምትወክለው ቤተክርስቲያንን ነው።ስለዚህ ክርስቲያን ወንዶች ይህን ንፁህ ስእል የሚያበላሽ ጋብቻን እንዳይመሰርቱ ከወዲሁ ሊያስቡበት ይገባል።ጋብቻ መግቢያ በር እንጂ መውጫ በር አልተሰራለትም።የፈቱ ሰዎች በር ሰብረው እንጂ ለመውጫ የሚሆን በር ተጠቅመው አልወጡም።ስለዚህ ከማግባቱ በፊት የፍቅር ጓደኛው ወይም እጮኛው ከዚህ በታች ከተዘረዘሩት አንዱን ችግር ካስተዋለባት፥ #በቀላሉ_ለመታረምም_እድል_እንደሌለው_ካረጋገጠ ወዲያው ቢወስንና ቢያቆሙ ይመከራሉ። 1⃣ #በእምነት_የማትመስልህን፦ አንተ በክርስቶስ የምታምን ሆነህ ሳለ፥በክርስቶስ የማታምን ሙስሊምና በእምነት የማትመስልህ ሴት ጋ ምን ትሠራለህ? ፍቅር ነው እንዳትለኝ እኔም የማወራው ስለፍቅር ስለ ክርስቶስ ነው።ለእርስዋ ብለህ ክርስቶስን ታሳዝናለህ? ወይስ ለሞተልህ ጌታ እኔነትህን ትገድለዋለህ? የቱ ይሻልሃል? ጳውሎስ እኮ "የማታምን ሚስት ያለችው አይፍታት" ብሎአል ምትለኝስ "ነገ ሚስት ስለምታደርጋት ሴት እንጂ ሚስትህ መች ሆነች?" ደግሞስ ጳውሎስ አንተ አሁን ስላለህበት ሁኔታ ሳይሆን ወንጌል ለባልና ለሚስት ስንሰብክ ባል ቀድሞ ቢያምን እርስዋ ደግሞ ባታምን "አይፋቱ" ለማለት እንደሆነ አልገባህምን? እለውጣታለሁ፥አሳምናታለሁ ብሎ ማግባትንስ ከወዴት አገኘኸው? በምን እርግጠኛ ሆንክ? ከጌታ ጋር መክረሃል? ጌታንስ መፈታተን አይሆንብህም? ባታምንስ ልትፈታት ነው? ልጅ ስትወልዱስ የማንን እምነት ሊከተል ነው? በጋራ ቃል አታጠኑ፥ቸርች አትሄዱ፥አብራችሁ አትፀልዩ…በቃ ላንተ ትዳር ማለት አብሮ መኖርና ግራ የገባው ቤተሰብ ውስጥ ለራሱ የተተወ ልጅ ወልዶ ማሳደግ ማለት ነው? በብሉይ ኪዳን እሥራኤላውያን ከአሕዛብ ጋር እንዳይጋቡ ይከለክላል።በአዲስ ኪዳንም ከማያምኑ ጋር በማይመች አካሄድ እንዳንጠላለፍ ያስተምራል።አሁኑኑ ወስን። 2⃣ #የቤት_እመቤት_ብቻ_ልሁን_የምትልህን፦ እግዚአብሔር ለአዳም ሔዋንን የፈጠረለት የምትመቸው ረዳት እንድትሆነው ነው።በሕይወትህ፥በሥራህ፥በዓላማህ፥በራእይህ፥በአገልግሎትህ በሀሳብ፥በፀሎት፥ጊዜ በመስጠት፥ሸክምን በመጋራት አብራህ እንደምትሆን ሳታረጋግጥ እንዳታገባት።ካልሆነ አንተ ብቻ የቤት አስቤዛ አሟላ እንጂ ሌላውን የራስህ ጉዳይ ካለች ወይም ከሁኔታዋ ይሄን ከተረዳህ እርስዋ ሚስትህ መሆን የለባትም።አግብተሃትም ብቻህን ትሆናለህና አስብበት።(የቤት እመቤት ሆና ከላይ እንደአጋር በሁሉ ነገርህ ትሳተፍ ለማለት እንጂ ወጥታ የግድ ትስራ ማለቴ አለመሆኑን አስተውል።) 3⃣ #የማታምንህን፦ በሁለት ጥንዶች መካከል መተማመን ከሌለ አብሮ ለመቀጠል ምንም ምክንያት የለም።መተማመን መሠረት ነው።ማታምንህ ሴት የዘወትር ጭቅጨቃዋ ይሄ ነው፦ "ከወደድከኝ የfbውንም የቴሌግራሙን፥የኢሞና የዋትስአፑን "ፓስወርድህን" ስጠኝ" ፎቶዬን ለምን አልፖሰትክም? እገሊት ማን ናት? ለምን ደወለችልህ?ከዛም እልፍ ሲል በfake አካውንት ገብታ ምትፈትንህና በሌላ ሴት ምታስፈትንህ ከሆነ 🤷 ገና ሳታገባህ እንዲ ካንገበገበችህ ስታገባህማ ወንድሜ RIP ⚰ 4⃣ #ወጪ_ላይ_ደፋር_የሆነችውን፦ ካፌ ስትቀመጡም ይሁን፥ገበያ ስትወጡ ውድ ውድ የሆነውን ለኔ ምትለውን ሴት፤ሁሉ ነገር ብራንድ ይሁን፥ዛሬ በልቼ ጠጥቼ ተደስቼ ልሙት ካለች ወንድሜ ምን ትጠብቃለህ።በጊዜ አሰናብት።ዓላማ የላትም።ኃላፊነትም አይሰማትም።ገንዘብም እንዴት እንደሚመጣ አታውቅም ወይም ማወቅም አትፈልግም።አንተ እርሷን ለማስደሰት ስትል የወር ደሞዝህን ወይም የወር ወጪህን አንድ እርስዋ ምትፈልገው ነገር ላይ ብቻ እንዴት ታጠፋለህ? በጊዜ ወስን። 5⃣ #የወንድ_ዘመደብዙ_የሆነችውን፦ ብዙ የወንድ ስልክ ጥሪዎችን እያስተናገደች ግራ ተጋብተህ "ማን ነው?" ስትል "አጎቴ፥አብሮአደጌ፥ወንድሜ፥የአክስቴ ልጅ፥ክላስሜቴ፥ባልደረባዬ ወዘተ ከበዛ…ልብህን በእርስዋ ላይ ባትጥል ጥሩ ነው።ወንድሜ አንተም ለሌላኛው ወንድ "አጎቴ ነው" ተብለህ ይሆናል።ብቻ እርግጠኛ ሁን።ጥርጣሬዎችህን አሳማኝ መልስ ስጣቸው።አስብበት። 🛑(ከላይ የገለፅኳቸው ጠባያት ማይናቁና ሊታዩ የሚገባቸው ጠባያት እንጂ አሻሚ ነገር የሌላቸው ፍፁም ምክር ስላልሆኑ የሚጠቅማችሁን ውሰዱ።.)🛑 🗓10/06/2014 የምሕረት ዓመት✍

❤️የእለቱ መልእክት❤️ #በእግዚአብሔር_ለእግዚአብሔር_የተፈጠረ!! 🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት 👉ትዳር ያልመሠረተ አብዛኛው ሰው "አሁን እንዲህች እንዲህች አይነት ሚስት ቢሰጠኝ፥እርፍ እላለሁ፤ከዛ ቀጥ ብዬ ጌታዬን ማምለክ ነው" ይላል።ግን ትዳር ሲይዝ ሌላ ሩጫ እንደሚጠበቅው አያውቅም።ሥራ የሌለው ሰው "ጌታ ሥራ ቢሰጠኝ፥እየሰራሁ አሥራቴን እያወጣሁ ወዘተ ደስ እያለኝ እኖራለሁ"ይላል።ሥራው ሲመጣ ደሞዙም እጁ ሲገባ፤በደሞዙ መጠን ወጪ ይጠብቀውና ሌላ የተሻለ ሥራ፤የተሻለ ገቢ ይፈልጋል።ሥራ እረፍት የሚሰጠውና የሰጠው ሰው የለም። 👉ለምን ይሆን ግን የጓጓንለት ነገር ሁሉ እጃችን ሲገባ የሚቀልብን? ሁሉንም ለምደን አዲስ ነገር ሁሌ የምንፈልገው ለምን ይሆን? 👉እርሱ ሠራን እኛም አይደለንም ተብሎ እንደተፃፈ ማንም ሰው ራሱን አልፈጠረም።እግዚአብሔር በልጁ በኢየሱስ የሚታየውንና የማይታየውን የፈጠረው ለእርሱ ለራሱ ነው።በእግዚአብሔር ለእግዚአብሔር ከተፈጠሩት ፍጥረት ዋነኛው ሰው ነው። 👉ሰው የተፈጠረው ለእግዚአብሔር ነው።ስለዚህ ለማንም መሆን አይችልም።ለእግዚአብሔር የተፈጠረ ሰው በምንም ነገር አይረካም። 👉ሰው ያለኝ ይበቃኛል የሚለው በጌታ ከሆነ ብቻ ነው።እረፍት ያለው በእረፍታችን በእግዚአብሔር ብቻ ነው።ቅዱስ አውግስጢኖስ በኑዛዜው፦ "እግዚአብሔር ሆይ እኛን ለአንተ ፈጥረኸናልና፥አንተን እስክናገኝ ድረስ እረፍት የለንም" እንዳለው።ለእርሱ ፈጥሮናልና ካላገኘነው በቀር አናርፍም። 👉ኢየሱስን ያገኘ እረፍትን ያገኛል።ክርስትና አርፈን የጀመርነው ሕይወት ነው።ኢየሱስን ያገኘ ደስታን፥ጥበብንና ፅድቅን አግኝቶአል።ኢየሱስን ያገኘ ሰላምን አግኝቶአል።በክርስቶስ የረካ ሰው ከእርሱ በቀር በምንም ነገር እንደማይረካ ያወቀ ሰው ነው። 📖“ዕረፉ፥ እኔም አምላክ እንደ ሆንሁ እወቁ፤ በአሕዛብ ዘንድ ከፍ ከፍ እላለሁ፥ በምድርም ላይ ከፍ ከፍ እላለሁ።” — መዝሙር 46፥10 📖“እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ።” — ማቴዎስ 11፥28 👉 #በእግዚአብሔር_ለእግዚአብሔር_የተፈጠረ_በእግዚአብሔር_ብቻ_ይረካል።እርካታ ከምንጩ ከእግዚአብሔር ዘንድ ይሆንለታል።ከእግዚአብሔር ውጭ በራሳችሁ መንገድና ጥረት ለመደሰትና ለመርካት ስትደክሙ "ሰማያትና ምድር ሳይቀር ይደነቁባችኋል" ኤርምያስ 2 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹² ሰማያት ሆይ፤ በዚህ ተገረሙ፤ በታላቅ ድንጋጤም ተንቀጥቀጡ፤” ይላል እግዚአብሔር። ¹³ “ሕዝቤ ሁለት ኀጢአት ፈጽመዋል፣ ሕያው የውሃ ምንጭ የሆንሁትን፣ እኔን ትተዋል፤ ውሃ መያዝ የማይችሉትን ቀዳዳ የውሃ ማጠራቀሚያ ጉድጓዶች፣ ለራሳቸው ቈፍረዋል። 🗓08/06/2014 የጌታ ዓመት✍

የፍቅር ትርጉም እንደተዛባና ፍቅር ዋጋ እንዳጣ ማሳያው Valantine's Day ነው።

#ፊሊፕ_ያንሲ 👉እኔ ከፊሊፕ ያንሲ መፅሐፍ ጋር የተዋወኩት ቁምላቸው ፋንታሁን ወደ አማርኛ በመለሰው "ያላወኩት ኢየሱስ" በሚለው መፅሐፋቸው ነው።ቀጥሎም "ቅይማት" የሚለውን መፅሐፋቸውን እየተደነኩ አንብቤያለሁ።ሦስተኛ መፅሐፋቸውን ማለትም "ፀሎት…እውን ለውጥ ያመጣልን?" የሚለውን እያጣጣምኩ እገኛለሁ። 👉እኔ የፊሊፕ ያንሲን መፅሐፍ ሳነብ የእውነተኛ ክርስቲያን መፅሐፍ እንደማነብ ይሰማኛል።ግብዝነትንና ሃይማኖተኝነትን በጭራሽ በእርሳቸው መፅሐፍ አታገኙም።ሁሌም የሚፅፉት ከደካማውና ከኃጢአተኛው ሰው ጎን ሆነው ነው።በማንም አይፈርዱም።ራሳቸውንና ስሜታቸውንም እንዲሁም ድካማቸውን ከማጋለጥ አያርፉም።ለምሳሌ "ያላወቅኹት ኢየሱስ" ለምን እንደፃፉት ሲናገሩ እንዲህ ብለዋል፦ 🗣"አንዳንዴ ኢየሱስ የሚያዝዘኝና የሚጠይቀኝን ሳላንገራግር እቀበላለሁ።ሌላ ጊዜ ግን፤ "ከሁለት ሺህ ዓመት በፊት ገሊላ በሚባል ምድር ኢየሱስ የሚባል ሰው ኖረና ለእኔ ምኔ ነው?" የሚል የጥርጥር ሽውታ በውስጤ ሲነፍስ ይሰማኛል።በተጠራጣሪውና በአፍቃሪው ማንነቴ መካከል ያለውን የውስጥ ውጥረት ማርገብ ይቻለኝ ይሆን? የምፅፈው የራሴን ጥርጣሬዎች ፊት ለፊት ለመጋፈጥ ስለምፈልግ ይመስለኛል።" ያላወቅኹት ኢየሱስ፡ ገፅ-13 😱ቅይማትና ፀሎት እንዲሁም ሌሎች መፃሕፍቶቻቸው የእርሳቸውና የሌሎች ክርስቲያኖች ጥርጣሬ፥ጥያቄና ውጥረት የወለዳቸው ናቸው። 1⃣ #ያላወቅኹት_ኢየሱስን አንብባችሁ ኢየሱስን በፊት በምታውቁት መንገድ ካወቃችሁት እኔ እቀጣለሁ።እባካችሁን አንብቡት። 2⃣ #ቅይማትን አንብቡና ሰውን ከነጥያቄው፤እግዚአብሔርን ከነመልሱ አግኙት።እባካችሁ አንብቡት። 3⃣ #ፀሎትን እያነበብኩት ነው ስጨርስ እንገናኝ።ግን እባካችሁ አንብቡት። 👉(ያላወቅኹት ኢየሱስ የሚለው መፅሐፍ ጀርባ ላይ ስለ ፊሊፕ ያንሲ እንዲህ ተፅፎአል።) 👉 #ፊሊፕ_ያንሲ የክርስቲያኒቲ ቱዴይ(ክርስትና በዛሬ ዘመን) መፅሔት ዋና አዘጋጅ ሆኖ ያገለግላል።ዐሥራ ሁለት የወርቅ ሜዳልያ ሽልማት አሸናፊ የሆኑ መፃሕፍት የፃፈ ሲሆን፦ The Jesus I Never Knew እና What Is So Amazing About Grace? ሁለት መፃሕፍቶቹ የECPA የዓመቱ ምርጥ መፃሕፍት ተብለው ተሸልመዋል።በቅርብ የፃፈው መፅሐፍ Prayer: Does it make any difference?(ፀሎት…እውን ለውጥ ያመጣልን?) የሚል ርእስ አለው።ያንሲ ባለትዳር ሲሆን አሁን በኮሎራዶ ይኖራል። 📖1ኛ ጢሞቴዎስ 4 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹³ እኔ እስክመጣ ድረስ #ለማንበብ፣ ለመምከርና ለማስተማር #ትጋ። … ¹⁵ ሰው ሁሉ ማደግህን ያይ ዘንድ በእነዚህ ነገሮች ላይ አትኵር፤ በትጋትም ፈጽማቸው፤ 🗓05/06/2014 የጌታ ዓመት✍