en
Feedback
የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ

የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ

Open in Telegram

ይህ የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ ነው።ዓላማዬ የተለያዩ መፅሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶችን ማካፈልና ማድረስ ሲሆን ምክሮችን፥አባባሎችን፥ፀሎቶችንና ትዝብቶቼን የማካፍልም ይሆናል።የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ወደ ልቤ ያመጣውንና የተናገረኝንም እፅፋለሁ።ትውልዱን ወደ ኢየሱስ የሚያስጠጋውን የትኛውንም ነገር የምፅፍበት ገፄ ነው።በማንበብና ሼር በማድረግ ከአገልግሎቴ ጎን ይቁሙ።0984005562.

Show more
447
Subscribers
+224 hours
+87 days
+3030 days
Posts Archive
#ፊሊፕ_ያንሲ 👉እኔ ከፊሊፕ ያንሲ መፅሐፍ ጋር የተዋወኩት ቁምላቸው ፋንታሁን ወደ አማርኛ በመለሰው "ያላወኩት ኢየሱስ" በሚለው መፅሐፋቸው ነው።ቀጥሎም "ቅይማት" የሚለውን መፅሐፋቸውን እየተደነኩ አንብቤያለሁ።ሦስተኛ መፅሐፋቸውን ማለትም "ፀሎት…እውን ለውጥ ያመጣልን?" የሚለውን እያጣጣምኩ እገኛለሁ። 👉እኔ የፊሊፕ ያንሲን መፅሐፍ ሳነብ የእውነተኛ ክርስቲያን መፅሐፍ እንደማነብ ይሰማኛል።ግብዝነትንና ሃይማኖተኝነትን በጭራሽ በእርሳቸው መፅሐፍ አታገኙም።ሁሌም የሚፅፉት ከደካማውና ከኃጢአተኛው ሰው ጎን ሆነው ነው።በማንም አይፈርዱም።ራሳቸውንና ስሜታቸውንም እንዲሁም ድካማቸውን ከማጋለጥ አያርፉም።ለምሳሌ "ያላወቅኹት ኢየሱስ" ለምን እንደፃፉት ሲናገሩ እንዲህ ብለዋል፦ 🗣"አንዳንዴ ኢየሱስ የሚያዝዘኝና የሚጠይቀኝን ሳላንገራግር እቀበላለሁ።ሌላ ጊዜ ግን፤ "ከሁለት ሺህ ዓመት በፊት ገሊላ በሚባል ምድር ኢየሱስ የሚባል ሰው ኖረና ለእኔ ምኔ ነው?" የሚል የጥርጥር ሽውታ በውስጤ ሲነፍስ ይሰማኛል።በተጠራጣሪውና በአፍቃሪው ማንነቴ መካከል ያለውን የውስጥ ውጥረት ማርገብ ይቻለኝ ይሆን? የምፅፈው የራሴን ጥርጣሬዎች ፊት ለፊት ለመጋፈጥ ስለምፈልግ ይመስለኛል።" ያላወቅኹት ኢየሱስ፡ ገፅ-13 😱ቅይማትና ፀሎት እንዲሁም ሌሎች መፃሕፍቶቻቸው የእርሳቸውና የሌሎች ክርስቲያኖች ጥርጣሬ፥ጥያቄና ውጥረት የወለዳቸው ናቸው። 1⃣ #ያላወቅኹት_ኢየሱስን አንብባችሁ ኢየሱስን በፊት በምታውቁት መንገድ ካወቃችሁት እኔ እቀጣለሁ።እባካችሁን አንብቡት። 2⃣ #ቅይማትን አንብቡና ሰውን ከነጥያቄው፤እግዚአብሔርን ከነመልሱ አግኙት።እባካችሁ አንብቡት። 3⃣ #ፀሎትን እያነበብኩት ነው ስጨርስ እንገናኝ።ግን እባካችሁ አንብቡት። 👉(ያላወቅኹት ኢየሱስ የሚለው መፅሐፍ ጀርባ ላይ ስለ ፊሊፕ ያንሲ እንዲህ ተፅፎአል።) 👉 #ፊሊፕ_ያንሲ የክርስቲያኒቲ ቱዴይ(ክርስትና በዛሬ ዘመን) መፅሔት ዋና አዘጋጅ ሆኖ ያገለግላል።ዐሥራ ሁለት የወርቅ ሜዳልያ ሽልማት አሸናፊ የሆኑ መፃሕፍት የፃፈ ሲሆን፦ The Jesus I Never Knew እና What Is So Amazing About Grace? ሁለት መፃሕፍቶቹ የECPA የዓመቱ ምርጥ መፃሕፍት ተብለው ተሸልመዋል።በቅርብ የፃፈው መፅሐፍ Prayer: Does it make any difference?(ፀሎት…እውን ለውጥ ያመጣልን?) የሚል ርእስ አለው።ያንሲ ባለትዳር ሲሆን አሁን በኮሎራዶ ይኖራል። 📖1ኛ ጢሞቴዎስ 4 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹³ እኔ እስክመጣ ድረስ #ለማንበብ፣ ለመምከርና ለማስተማር #ትጋ። … ¹⁵ ሰው ሁሉ ማደግህን ያይ ዘንድ በእነዚህ ነገሮች ላይ አትኵር፤ በትጋትም ፈጽማቸው፤ 🗓05/06/2014 የጌታ ዓመት✍

❤️የእለቱ መልእክት❤️ #በእግዚአብሔር_መታሰብ 🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት 👉 #በእግዚአብሔር_መታሰብ ማለት እግዚአብሔር ሲፈርድልህ፥ሲዋጋልህ፥ፀሎትህን ሲመልስልህ፥የድካምህን ዋጋ ሲከፍልህ ማለት ነው።በእግዚአብሔር እንደ መታሰብ ምንም ድልና ደስታ የለም። 👉 #እግዚአብሔር_ሲያስብ የደረቅ ማኅፀን ይለመልማል፥አለማፍራትና አለመከናወን ታሪክ ይሆናል።ዘፍጥ.21:1-2 👉 #እግዚአብሔር_ሲያስብ ድካማችሁ ዋጋ ያገኛል።ከጭንቀታችሁ ታርፋላችሁ።በጠላቶቻችሁ ፊት ትከብራላችሁ።አስጨናቂዎቻችሁ ግን ይዋረዳሉ።ሚልክያስ.3:13-18 👉 #እግዚአብሔር_ሲያስባችሁ ለስሙ ያሳያችሁትን ፍቅር፥ለወንጌል የከፈላችሁትን ዋጋ፥ለቃሉ እውነት ማድላታችሁ እንደ ተወደደ የመአዛ ሽታ በፊቱ ይቀርባል።ስለእናንተም እግዚአብሔር ለመፍረድ ይነሳል።ዕብ.6:10-12 👉 #እግዚአብሔር_ሲያስብ የፈሰሰ እንባ ከፈሰሰ ደም እኩል ዋጋ ያገኛል።ስለዚህም እግዚአብሔር ወደ አዘነው ሰው ይመጣል።የፈሰሰውንም ደም አይቶ ደም አፍሳሹን ይበቀላል።ዘፀ.3:7-8 #እንግዲያውስ_እንዲህ_ፀልዩ፦ 🙏😭“አምላኬ ሆይ፥ ስለዚህ #አስበኝ፤ ለአምላኬም ቤት ያደረግሁትን ወረታዬን አታጥፋ።” — ነሀምያ 13፥14 🙏😭“ አምላኬ ሆይ፥ ስለዚህ ደግሞ #አስበኝ፥ እንደ ምሕረትህም ብዛት ራራልኝ።” — ነሀምያ 13፥22 🙏😭“አምላኬ ሆይ፥ በመልካም #አስበኝ።” — ነሀምያ 13፥31 🙏😭“የልጅነቴን ኃጢአትና መተላለፍ አታስብብኝ፤ አቤቱ፥ ስለ ቸርነትህ ብዛት እንደ ምሕረትህ #አስበኝ።” — መዝሙር 25፥7 🙏😭“ እግዚአብሔር አምላክ ሆይ፥ እባክህ፥ #አስበኝ፤ አምላክ ሆይ፥ ይህን አንድ ጊዜ ብቻ፥ እባክህ፥ አበርታኝ” — መሳፍንት 16፥28 🙏እግዚአብሔር ያስባችሁ።።።።🙏 🗓የካቲት 3/2014 የምሕረት ዓመት✍

❤️ክርስቶስ ኢየሱስ ከገባህ…❤️ 🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት 👉ክርስቶስ ከገባህ ሁሉም እውነት ገብቶሃል።ክርስቶስ ሁሉ ነው ደግሞም በሁሉ ነውና።ቆላስ.3:11 👉 #የነቢያት_ትንቢታቸው፤ዮሐ.5:39 👉 #የሐዋርያት_ስብከታቸው፤1ቆሮ.1:23 👉 #የሰማእታት_ተጋድሎአቸው፤ሮሜ.8:36 👉 #የአባቶቻችን ያልተቀላቀለ ንፁህ #ሃይማኖታቸው…ዕብ.13:7-8፤ ክርስቶስ ኢየሱስ ብቻ ነው። ❤️ክርስቶስ የአብ ጥበብና ኃይል፤ የመንፈስ ቅዱስ መልእክትና እውነት ነው።1ቆሮ.1:24፤ዮሐ.15:26 ❤️አብርሃም የብሉዩ ኪዳን ሰው ሊያየው የተመኘው፤የአዲሱ ኪዳን ሐዋርያ ዮሐንስ ማራናታ ያለው አይጠገቤው ክርስቶስ ብቻ ነው።ዮሐ.8:56 ❤️ክርስቶስን የጠጣ አይጠማም።የበላው አይራብም።ኢየሱስ ያለው ሕይወት አለው።ክርስቶስ የሌለው የእግዚአብሔር ቁጣ በእርሱ ላይ ይኖራል እንጂ ሕይወት አያይም።ዮሐ.4:14፤6:35፤3:36 ❤️አብ ወደ እኛ የመጣው፥እኛም ወደ አብ የቀረብነው በክርስቶስ መካከለኛነት ነው።1ጢሞ.2:5 ❤️እኛን በሰማይ የወከለው ሰዋችን፤ እግዚአብሔርን ለእኛ ያብራራው መምህራችን ክርስቶስ ነው።ዕብ.7:26፤ዮሐ.14:9-10 ❤️አብን በምድር፤ሰውን በሰማይ የወከለ ብቁ ሊቀካህናት ኢየሱስ ብቻ ነው።ዕብ.7:26-28 ❤️በመሥዋእትነቱ በደልን ያስወገደ የእግዚአብሔር በግ፤ ለበጎቹ ነፍሱን ያኖረ መልካሙ እረኛ ክርስቶስ ነው።ዮሐ.1:29፤ዮሐ.10:11 በበሩ በክርስቶስ ግባ።ዮሐ.10:9 በእውነቱ በክርስቶስ እመን።ዮሐ.14:6 በብርሃኑ በክርስቶስ ተመላለስ።ዮሐ.8:12 በእረኛው በክርስቶስ ታምነህ ተሰማራ።ዮሐ.10:14-15 ❤️በትንሣኤው በክርስቶስ ከሙታን መንደር ውጣ።ዮሐ.11:25 ❤️በመንገዱ በክርስቶስ ወደ አብ ቅረብ።ዮሐ.14:6 ❤️በሊቀካህናት በክርስቶስ ከአብ ጋር ታረቅ።ዕብ.7:25-29 ❤️ከአቤል ደም በሚሻለው በአስታራቂው በክርስቶስ ደም ታጠብና ንፃ።ዕብ.12:24፤1ዮሐ.1:7 ❤️በክርስቶስ ድነህ።ለክርስቶስ ምሥክር ሁን።ማቴ.10:32-33 🙏ኢየሱስ ጌታ ነው።ያድናል ይታደግማል።በእርሱ የሚያምኑና ያመኑ ብፁአን ናቸው።🙏 🗓24/05/2014 የጌታ ዓመት✍

#የወንጌል_መልእክት_ሁለት_መዳረሻዎች 🗣አገልጋይ ብርሃኑ ታምራት 👉ወንጌል ኤዋንጌልዮን ከሚለው የግሪክ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም "መልካም ዜና/የምሥራች/" ማለት ነው።የምሥራችነቱ ግን ላመኑት ብቻ ሲሆን ለማያምኑት ግን መርዶ ነው። 👉የወንጌል ሁለት መዳረሻዎች የእግዚአብሔር ምሕረትና የእግዚአብሔር ፍርድ ናቸው።ምንም እንኳን እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ባለው ልክ የሌለው ፍቅር ምክንያት ከፍርዱ ይልቅ ምሕረቱ የበዛ ቢሆንም ፍርዱም የወንጌሉ ዋና መልእክት ነው። 👉በወንጌል ውስጥ ያለውን መልእክት ለመረዳት ኃጢአትንና የኃጢአትን ውጤት የመረዳትን ያህል ዋና ነገር የለም።የዘላለም ሞት ካልገባህ በፍፁም የዘላለም ሕይወት አይገባህም።አዳነኝ ብሎ ለመዘመር ምን ውስጥ እንደነበርክ ማወቅ አለብህ።ችግር ውስጥ እንደሆንክ ካላመንክ እግዚአብሔር የሚሰጥህን መፍትሄ ልትቀበል አትችልም። 👉ወደዋናውና ላይኛው ሀሳቤ ስመለስ የወንጌል ሁለቱ መዳረሻዎች ምሕረቱና ፍርዱ መገለጫዎች የሆኑትን ቦታዎች ላስታውስህ።መንግስተ ሰማያትና ገሃነመ እሳት የሚባሉትን። 👉አንዳንድ የዋህ አማኞች የወንጌልን ሀሳብ ካለመረዳት "ወንጌል የገሃነምና የመንግስተ ሰማያት ጉዳይ አይደለም ወንጌል ስለልጁ ብቻ ነው" ይላሉ።እርግጥ ነው ወንጌል ስለ ልጁ ብቻ ነው።ልጁ የመጣው ግን ለመንግስተሰማያትም በር ለገሀነምም መግባት ምክንያት ሆኖ ነው።ካመንከው ወደ መንግስተሰማያት የምትገባበት በር ነው።ካላመንከው ወደ ገሃነም ምትወርድበት ምክንያት እርሱ ይሆናል። 👉ቃሉ ምን ይላል፦ 👉“በልጁ #የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ በልጁ #የማያምን ግን የእግዚአብሔር ቍጣ በእርሱ ላይ ይኖራል እንጂ ሕይወትን አያይም።” — ዮሐንስ 3፥36 👉ሕይወት መንግስተሰማያትን ምትወርሰው በልጁ በማመን ነው።ቁጣውን ተሸክመህ ወደ ገሃነም ምትወርደው በልጁ ባለማመንህ ነው። 👉ደግሞም፦ 📖1ኛ ጴጥሮስ 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁶ በመጽሐፍ፦ እነሆ፥ የተመረጠና የከበረን #የማዕዘን_ራስ_ድንጋይ በጽዮን አኖራለሁ #በእርሱም_የሚያምን_አያፍርም ተብሎ ተጽፎአልና። ⁷ እንግዲህ #ክብሩ ለእናንተ #ለምታምኑት ነው፤ #ለማያምኑ_ግን አናጢዎች የጣሉት ድንጋይ እርሱ የማዕዘን ራስ #የዕንቅፋትም ድንጋይ #የማሰናከያም ዓለት ሆነ፤ ⁸ የማያምኑ ስለ ሆኑ በቃሉ ይሰናከሉበታልና፤ ለዚህ ደግሞ የተመደቡ ናቸው። 👉የማእዘኑ ራስ ድንጋይ ክርስቶስ ነው።በእርሱ የሚያምን ይድናል።የማያምን ግን በዛው ድንጋይ ይፈጭበታል። 👉ወንጌል መዳረሻው ምሕረቱና ፍርዱ ነው።መንግስተ ሰማያትና ገሃነመ እሳት ነው።ምሕረቱን የምንቀበለው በክርስቶስ ማመን ሲሆን ፍርዱን የሚጠጡትም ያላመኑት ናቸው። 👉ስለዚህ ቤተሰቦቼ የወንጌልን መልእክት አዛንፋችሁና የፍቅርና የምሕረት ብቻ በማድረግ ፍርዱን በማስረሳት አትስበኩት።እንደተፃፈው እንደዛው እመኑ ስበኩ። 👉የማሳረጊያ ቃልና የወንጌል መልእክት ሁለት መዳረሻዎችን እነሆ፦ 📖ራእይ 21 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁵ በዙፋንም የተቀመጠው፦ እነሆ፥ ሁሉን አዲስ አደርጋለሁ አለ። ለእኔም፦ እነዚህ ቃሎች የታመኑና እውነተኛዎች ናቸውና ጻፍ አለኝ። ⁶ አለኝም፦ #ተፈጽሞአል። አልፋና ዖሜጋ፥ መጀመሪያውና መጨረሻው እኔ ነኝ። ለተጠማ ከሕይወት ውኃ ምንጭ እንዲያው እኔ እሰጣለሁ። ⁷ ድል የሚነሣ ይህን ይወርሳል አምላክም እሆነዋለሁ እርሱም ልጅ ይሆነኛል። ⁸ ዳሩ ግን የሚፈሩና #የማያምኑ የርኵሳንም የነፍሰ ገዳዮችም የሴሰኛዎችም የአስማተኛዎችም ጣዖትንም የሚያመልኩ የሐሰተኛዎችም ሁሉ ዕድላቸው በዲንና በእሳት በሚቃጠል ባሕር ነው፤ ይኸውም ሁለተኛው ሞት ነው። 👉ወንጌል ላመኑትና ለሚያምኑት የምሥራች ነው።ላላመኑትና ለማያምኑት ደግሞ መርዶ ነው። 📖“እንግዲህ የእግዚአብሔርን ቸርነትና ጭከና ተመልከት፤ ጭከናው በወደቁት ላይ ነው፥ በቸርነቱ ግን ጸንተህ ብትኖር የእግዚአብሔር ቸርነት በአንተ ላይ ነው፤ ያለዚያ አንተ ደግሞ ትቆረጣለህ።” — ሮሜ 11፥22 🗓16/05/2014 የምሕረት ዓመት✍

#ነገረ_ድነት_እና_የሥላሴ_ሚና 🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት 👉አብ፥ወልድና መንፈስ ቅዱስ አንድ አምላክ ብለን እናምናለን።በአምላክነት አንድ የሆኑት አብ፥ወልድና መንፈስ ቅዱስ በአካል ሦስት ናቸው።በአካል ሦስት ናቸው ያልናቸው አብ፥ወልድና መንፈስ ቅዱስ በመለኮት አንድ ናቸው። 👉ሦስቱ አካላት አብ፥ወልድና መንፈስ ቅዱስ በነገረ ድነት ላይ የተለያየ ሚና ነው ያላቸው።የሚድነው አንድ ሰው፤መዳንም አንድ ቢሆንም በሦስቱ አካላት የተለያየ ሚና የተፈፀመ ነው።በእኔ መዳን የአብ ሚና ምን ነበር? የወልድ ሚናስ? የመንፈስ ቅዱስ ሚናስ ምን ነበር? የሚለውን እናያለን። #በነገረ_ድነት_የአብ_ሚና_ምንድን_ነው? 👉እንደሚታወቀው መዳን ከእግዚአብሔር የመነጨ፥በእግዚአብሔር የተሠራ፥ለእግዚአብሔር ክብር የሚሆን ነው።አብ ደግሞ ሁሌም የነገሮች ሁሉ ምንጭ ነው። 👉አብ የሚድኑ ሰዎችን ይመርጣል፥ይወስናል።ነገረ ድነትም በምን መልኩ መፈፀም እንዳለበት የወሰነው አብ ነው።ድነታችንን በሞት ይፈፅመው ዘንድ ወልድን(ኢየሱስን) ወደ ዓለም የላከልን አብ ነው።በዚህም ለእኛ ያለውን ፍቅር ገልፆልናል።ስለዚህ የአብ ሚና የሚድኑ ሰዎችን መምረጥ መወሰንና ሞቶ ያድነን ዘንድ አንድያ ልጁን ለሞት አሳልፎ መስጠት ነው።እነዚህ ጥቅሶች የሚያሳዩት የአብን ሚና ነው፦ 📖“በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር(አብ) አንድያ #ልጁን(ኢየሱስን) #እስኪሰጥ ድረስ #ዓለሙን_እንዲሁ_ወዶአልና።” — ዮሐንስ 3፥16 👉ክርስቶስ ኢየሱስ በሞቱ ያድነን ዘንድ የወሰነው አብ ነው። 📖“እርሱንም #በእግዚአብሔር(በአብ) #በተወሰነው #አሳቡና #በቀደመው #እውቀቱ #ተሰጥቶ በዓመፀኞች እጅ ሰቅላችሁ ገደላችሁት።” — ሐዋርያት 2፥23 👉እኛም የዳንነው በአብ ምርጫና ውሳኔ ነው። 📖ኤፌሶን 1¯⁴ #ዓለም_ሳይፈጠር፥ በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ #በክርስቶስ #መረጠን። ⁵ በበጎ ፈቃዱ እንደ ወደደ፥ #በኢየሱስ ክርስቶስ ሥራ ለእርሱ ልጆች ልንሆን አስቀድሞ #ወሰነን። #በነገረ_ድነት_ላይ_የወልድ_ሚና_ምንድነው? 👉በአብ የታቀደውና የታሰበው ነገር ሁሉ የሚሠራው በወልድ ነው።ሁሉ በኢየሱስ ሆነ ያለ ኢየሱስ የሆነ አንድም ነገር የለም።ዮሐ.1:1-3 👉ነገረ ድነትም በአብ ታቅዶ በወልድ የተሠራ ነው።ወልድ እኛን ለማዳን ሲል ራሱን ዝቅ አድርጎ ከድንግል ማርያም በመወለድ ፍፁም ሰው ሆነ።ሰው ካልሆነ በቀር እኛን በአብ ፊት ወክሎ መሞትና እዳችንን መክፈል አይችልምና።የወልድ ሚና ለእኛ ሲል ሰው መሆን፥መሞትና መነሳት ነው።እነዚህ ጥቅሶች የወልድን ሚና ይናገራሉ፦ 📖“ገና ደካሞች ሳለን #ክርስቶስ ዘመኑ ሲደርስ #ስለ_ኃጢአተኞች_ሞቶአልና።” — ሮሜ 5፥6 👉በወልድ(በኢየሱስ) በተከናወነ የመስቀል ሥራ ነው የኃጢአታችንን ሥርየት የተቀበልነው። 📖“ #በውድ_ልጁም፥ እንደ ጸጋው ባለ ጠግነት መጠን፥ #በደሙ_የተደረገ #ቤዛነታችንን_አገኘን እርሱም የበደላችን ስርየት።” — ኤፌሶን 1፥7 👉እኛን ለማዳን ሰው የሆነው ወልድ ብቻ እንጂ አብና መንፈስ ቅዱስ አይደሉም። 📖“እንግዲህ ልጆቹ በሥጋና በደም ስለሚካፈሉ፥ #እርሱ_ደግሞ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን በሞት እንዲሽር፥ ይኸውም ዲያብሎስ ነው፥ በሕይወታቸውም ሁሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ሁሉ ነጻ እንዲያወጣ፥ #በሥጋና_በደም_እንዲሁ_ተካፈለ።” — ዕብራውያን 2፥14-15 👉በእኛና በአብ መካከልም መካከለኛና አስታራቂ በመሆን አስታርቆናል። 📖“አንድ እግዚአብሔር አለና፥ #በእግዚአብሔርና_በሰውም መካከል ያለው #መካከለኛው ደግሞ #አንድ አለ፥ እርሱም #ሰው_የሆነ_ክርስቶስ_ኢየሱስ_ነው፤” — 1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥5 #በነገረ_ድነት_ላይ_የመንፈስ_ቅዱስ_ሚና_ምንድን_ነው? 👉በአብ ታቅዶ በወልድ የተሠራው ድነት ያለ መንፈስ ቅዱስ እውን አይሆንም።በአብ ታቅዶ በወልድ የተሠራውን ሥራ ካላመንን በቀር ልንድን አንችልም።እንድናምንና ዳግም እንድንወለድ መንፈስ ቅዱስ ያስፈልገናል።እነዚህ ጥቅሶች ስለመንፈስ ቅዱስ ሚና የሚናገሩ ናቸው፦ 📖ኤፌሶን 1¯¹³ እናንተም ደግሞ የእውነትን ቃል፥ ይኸውም የመዳናችሁን ወንጌል፥ ሰምታችሁ ደግሞም በክርስቶስ አምናችሁ፥ #በተስፋው_መንፈስ #በመንፈስ_ቅዱስ_ታተማችሁ፤ ¹⁴ #እርሱም_የርስታችን_መያዣ ነው፥ ለእግዚአብሔር ያለውን ሁሉ እስኪዋጅ ድረስ፥ ይህም ለክብሩ ምስጋና ይሆናል። 👉 #ስለ_ክርስቶስና_ስለ_መዳን_ያለውን_እውነት #መንፈስ_ቅዱስ_ካላበራልን በቀር ልናምን አንችልም።ካላመንን አንድንም። 📖“ #መንፈስም የእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር ስንኳ ሳይቀር #ሁሉን_ይመረምራልና ለእኛ እግዚአብሔር #በመንፈሱ_በኩል_ገለጠው።” — 1ኛ ቆሮንቶስ 2፥10 👉 #ከመንፈስ_ቅዱስ_ካልተወለዳችሁ_በቀር_የእግዚአብሔርን_መንግስት_አታዩም። 📖“ኢየሱስም መለሰ፥ እንዲህ ሲል፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ #ሰው_ከውኃና #ከመንፈስ_ካልተወለደ_በቀር #ወደ_እግዚአብሔር_መንግሥት #ሊገባ_አይችልም።” — ዮሐንስ 3፥5 #መንፈስ_ቅዱስ_በውስጣችሁ_ከሌለ #የክርስቶስ_ወገን_ልትሆኑ_አትችሉም። 📖“እናንተ ግን የእግዚአብሔር መንፈስ በእናንተ ዘንድ ቢኖር፥ በመንፈስ እንጂ በሥጋ አይደላችሁም። #የክርስቶስ_መንፈስ_የሌለው ከሆነ ግን ይኸው #የእርሱ_ወገን_አይደለም።” — ሮሜ 8፥9 #ማጠቃለያ፦ አብ፥ወልድና መንፈስ ቅዱስ በእኛ መዳን ላይ የተወጡት ሚና የተለያየ ቢሆንም መዳን አንድ ነው።የዳነውም አንድ ሰው ነው።በአካላት ሦስት እንደመሆናቸው የተለያየ ሚና ነበራቸው።በመለኮት(በአምላክነት) አንድ ናቸውና ሥራቸው አንድና ፍፁም(Perfect) ነበር። 🗓07/05/2014 የምሕረት ዓመት ✍

ብቸኛው መድኃኒት ተወለደ። ብቸኛው መልስ ተወለደ። የእግዚአብሔር ልጅ የሰው ልጅ ሆነ።ኢየሱስ💝

እግዚአብሔርን በሕይወታችን ሁሌም ቅድሚያ ልንሰጠው ይገባዋል። "በዚህ ጉዳይ ሀሳቡ ምንድነው? ያስደስተዋል ወይስ ያሳዝነዋል?" ብሎ እንደመጠየቅ ጥበብ የለም።

ስለ ኢየሱስ ያላችሁ የትኛውም እምነትና አስተምህሮ ሕይወታችሁ ላይ እንጂ የኢየሱስ ማንነት ላይ ለውጥ ስለማያመጣ #ለራሳችሁ እና #ለትምህርታችሁ_ተጠንቀቁ!!

ሶሻል ሚዲያንና የግል ሕይወታችሁን በተመለከተ ድንቅ ምክር ነው ተጠቀሙበት።
ሶሻል ሚዲያንና የግል ሕይወታችሁን በተመለከተ ድንቅ ምክር ነው ተጠቀሙበት።

ስለ ሌሎች ውድቀት በመጨነቅ፤የዘመኑን ምግባረ ብልሹነት አስሬ በማውጋት የሚመጣ ቅድስና የለም፤ #ቅድስና ልብን በመጠበቅ #ራስን_ማዳንና #በሕይወት_ሌሎችን_መኮነን ነው።ያኔ እውነተኛ ተሐድሶ ይሆናል።

#የክርስቶስን_ሞት_ከንቱ_ያደረገ_ኑፋቄ!!! 🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት 👉ስምሽን የጠራ፥መታሰቢያሽን ያደረገ እስከሰባት ትውልድ እምርልሻለሁ።በእሁድ ቀን እባብ የገደለ እምርልሃለሁ።እዚህ ቦታ ሄደህ ብትሳለም እንደ 40 ቀን ሕፃን ትሆናለህ(ይሄን ማመን በእርግጥም ሕፃንነት ቢሆንም)።በየዓመቱ ወደ ሲኦል እየወረደ በክንፎቹ ያመነ ያላመኑ ነፍሳትን ያወጣል።78ሰው በልቶ በምልጃ ዳነ።ፍትሃት ሲደረግለት ከሲኦል ወጣ………………ማለቂያ የለውም። 👉ይሄ ሁሉ ኑፋቄና ስህተት በመፅሐፍ ቅዱስ እውነት ሊታረም ይገባዋል። 👉አስቡት በድንግል ማርያም ምልጃ መዳን እየቻልን ክርስቶስ ያን ሁሉ መከራ በከንቱ ሲቀበል? 😳 👉ኢየሱስ ያን ሁሉ መከራ የተቀበለው ለአዳማዊ ኃጢአት ብቻ ሆኖ ሌሎች ተግባራዊ ኃጢአቶቻችንን ለቅዱሳን ምልጃ ሲተወው አስቡት? 🙈 👉ከዚህ በላይ ኑፋቄና ስህተት ከየት ይመጣል? 👉ቃሉ እንዲህ ይላል፦ 📖ዕብራውያን 10 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁸ የሙሴን ሕግ የናቀ ሰው ሁለት ወይም ሦስት ቢመሰክሩበት ያለ ርኅራኄ ይሞታል፤ ²⁹ #የእግዚአብሔርን_ልጅ_የረገጠ #ያንንም_የተቀደሰበትን_የኪዳኑን_ደም_እንደርኵስ_ነገር_የቆጠረ #የጸጋውንም_መንፈስ_ያክፋፋ፥ እንዴት ይልቅ #የሚብስ_ቅጣት የሚገባው ይመስላችኋል? ³⁰ በቀል የእኔ ነው፥ እኔ ብድራትን እመልሳለሁ ያለውን እናውቃለንና፤ ደግሞም፦ #ጌታ_በሕዝቡ_ይፈርዳል። ³¹ #በሕያው_እግዚአብሔር_እጅ_መውደቅ_የሚያስፈራ_ነው። 👉የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ።ከእግዚአብሔር ፍርድ አምልጡ።ኢየሱስና የኢየሱስ ደም በቂ ነው። 👉ጌታ በነገር ሁሉ ማስተዋልን ይስጣችሁ!!!! 🗓22/04/2014 የጌታ ዓመት

#የትውልዶች_ተስፋ 🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት 👉በብሉይ ኪዳን በብዙ ቦታዎች፤በአዲስ ኪዳን ግን በሁለት ቦታዎች ብቻ የዘር ሐረግ ቆጠራዎች ተዘግበዋል።በማቴዎስ ወንጌል(1:1-17) እና በሉቃስ ወንጌል(3:23-38)። 👉ከአዳም ጀምሮ ተስፋ የተደረገውን የሴቲቱን ዘር ፍለጋ ቆጠራው በጥንቃቄ እየተመዘገበ ተላለፈ።የዘር ቆጠራው ግብ ክርስቶስ ነበር።ክርስቶስ ሲገኝ ቆጠራው ይቆማል።ተገኘናም ቆመ። 👉አዳም ከወለዳቸው ብዙ ወንዶችና ሴቶች ልጆች መሀከል ሦስቱ ብቻ በስም ተጠቅሰዋል።አቤል ቃኤልና ሴት ናቸው።ክርስቶስ የሚመጣው በሴት በኩል ነውና ቆጠራው በሱ በኩል ሆነ።ዘፍጥ.5:1-8 👉በኖኅ ዘመን ከ8 ሰዎች በቀር የሰው ዘር በጠቅላላ በንፍር ውኃ ጠፋ።ኖኅም ሦስት ልጆች ነበሩት።ሴም፥ካምና ያፌት ናቸው።ኖኅም መሲሑ በሴም ድንኳን እንደሚያድር ትንቢት ተናገረ።ዘፍጥ.9:27 ቆጠራው እስከ አባቶች አባት አብርሃም ድረስ ቀጠለ። 👉እግዚአብሔር አዲስ ትውልድን ለራሱ ሕዝብ አድርጎ ማስነሳት ፈለገ።ለዚህም ተልእኮ አብርሃም ተመረጠ።አብርሃምም ከሦስት ሴቶች 8 ልጆችን ወለደ።ከ8ቱም አንዱን ይስሐቅን ለመሲሑ መምጫ መንገድ አድርጎ መረጠው። 👉በያእቆብም ዘመን ከ12ቱ ነገደ እሥራኤል ይሁዳን ለመሲሑ መምጫ መረጠው።ከዛም ጊዜ ጀምሮ የመሲሑ መምጫ ጊዜውና ነገዱ እየተቆጠረ በጥንቃቄ ተያዘ። 👉በመጨረሻም የትውልዶች ሁሉ ተስፋ ክርስቶስ በሥጋ ተገለጠ።በአባቱ በዳዊት ከተማም ተወለደ።ማቴ.2:1-6 👉ያኔ ተስፋችን የነበረው ዛሬም ተስፋችን እርሱ ነው።ያኔ እመጣለሁ ብሎ መጣ።ግን አልተቀበሉትም።አሁንም እመጣለሁ ብሏል ሳንተላለፍ የተባረከውን ተስፋ ክርስቶስን እንጠብቅ። 👉የትውልዶች ተስፋ ኢየሱስ ይመጣል። በብሉይ ትናፈቅ ነበረ ልደትህ እየተቆጠረ መጠህም ፍጥረት አልጠገበህ ይኖራል ማራናታ እያለህ🎼 22/04/2014 የጌታ ዓመት

የጌታ ሥራ በዝቶልኛል ደግሞም ይበዛልኛል።
የጌታ ሥራ በዝቶልኛል ደግሞም ይበዛልኛል።