የአገልጋይ ቃለአብ ካሳዬ ገጽ
Closed channel
በጸጋው ቃል እና በመንፈስ ቅዱስ ኀይል የእግዚአብሔርን መንግሥት ትውልድ ማዘጋጀት።
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
309
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Data loading in progress...
Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
November '22
November '22
+1
in 0 channels
October '220
in 0 channels
Get PRO
September '22
+9
in 0 channels
Get PRO
August '22
+7
in 0 channels
Get PRO
July '22
+5
in 0 channels
Get PRO
June '22
+5
in 0 channels
Get PRO
May '22
+7
in 0 channels
Get PRO
April '22
+9
in 0 channels
Get PRO
March '22
+9
in 0 channels
Get PRO
February '22
+3
in 0 channels
Get PRO
January '22
+2
in 0 channels
Get PRO
December '21
+4
in 0 channels
Get PRO
November '21
+5
in 0 channels
Get PRO
October '21
+27
in 0 channels
Get PRO
September '21
+2
in 0 channels
Get PRO
August '21
+4
in 0 channels
Get PRO
July '21
+4
in 0 channels
Get PRO
June '21
+2
in 0 channels
Get PRO
May '210
in 0 channels
Get PRO
April '21
+4
in 0 channels
Get PRO
March '21
+19
in 0 channels
Get PRO
February '21
+3
in 0 channels
Get PRO
January '21
+22
in 0 channels
Get PRO
December '20
+339
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 10 November | 0 | |||
| 09 November | 0 | |||
| 08 November | 0 | |||
| 07 November | 0 | |||
| 06 November | 0 | |||
| 05 November | 0 | |||
| 04 November | +1 | |||
| 03 November | 0 | |||
| 02 November | 0 | |||
| 01 November | 0 |
Channel Posts
| 2 | https://youtu.be/6b9jSwBowMA | 66 |
| 3 | #መዳን እና #መሥራት
አብዛኞቹ የሃይማኖት ቤቶች "መዳን በሥራ" እንደሆነ ያስተምራሉ። አማኞችም ጭምር የራስ ጽድቅ አስተሳሰብ አዳብረዋል። የእግዚአብሔር ቃል ግን "መዳን በጸጋ" "ጽድቅ በእምነት" እንደሆነ አስረግጦ ይናገራል።
"አሁን ግን በሕግና በነቢያት የተመሰከረለት የእግዚአብሔር ጽድቅ ያለ ሕግ ተገልጦአል፥ እርሱም፥ ለሚያምኑ ሁሉ የሆነ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ ነው፤ ልዩነት የለምና፤" ሮሜ 3፥21_22።
“ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤“ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም።” — ኤፌሶን 2፥8_9።
ወገኖቼ እኛ እስራኤላውያን አልነበርንም። በዚህም ምክንያት በሕግ ስለሆነው ጽድቅ አናውቅም። የእነርሱም የሥራ ሕግ ቢሆን ቀርቷል።
<<ትምክህት እንግዲህ ወዴት ነው? እርሱ ቀርቶአል። በየትኛው ሕግ ነው? በሥራ ሕግ ነውን? አይደለም፥ በእምነት ሕግ ነው እንጂ።>> ሮሜ 3 ÷27።
አሁን ከእግዚአብሔር በመሥራት የሚገኝ ጽድቅ የለም። ስለአይሁዳውያንም ስለእኛም ስለ አሕዛብም <<ጻድቅ የለም>> ብሎ መጽሐፉ ዘግቶታል። ሮሜ 3÷11።
<<ማንም በእግዚአብሔር ፊት በሕግ እንዳይጸድቅ ግልጥ ነው።>> ገላ 3÷11።
ስለዚህ "መዳን በእምነት" እንደሆነ ማመን ይኖርብናል። ይህ የክርስትና ጅማሬ ነው። በወንድማችን በጳውሎስ በኩል የተብራራው እውነት የእግዚአብሔር ጽድቅ በእምነት በኩል እኛ ጋር እንደደረሰ የሚያወሳ ነው።
«ሰው ያለ ሕግ ሥራ በእምነት እንዲጸድቅ እንቈጥራለንና» ሮሜ 3፥28።
ስለዚህ በመጀመሪያ #አምኖ #መዳን፤ ከዚያ #ድኖ #መልካም #መሥራት አስፈላጊ ነው።
ሰው በሕግ ሥራ የማይድን ከሆነ ታዲያ ለምን እንሰራለን?
ሰው በክርስቶስ አዲስ ፍጥረት ከሆነ በኋላ ወይም በእምነት ከዳነ በኋላ የሚሰራው መልካም ሥራ አለ። ይህንን በተመለከተ የአሕዛብ ሐዋርያ የሆነው ጳውሎስ «እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን» በማለት ገልጾታል። ኤፌ 2÷10፡፡
መልካም ሥራችን ደግሞ ወደ ፊት ብድራት እንዳለው አስተምሯል።
«መልካምም ቢሆን ክፉ እንዳደረገ በሥጋው የተሠራውን በብድራት ይቀበል ዘንድ ሁላችን በክርስቶስ በፍርድ ወንበር ፊት ልንገለጥ ይገባናልና» ተብሎ ተገልጿል 2ቆሮ 5÷10፡፡
«ሁላችን በክርስቶስ የፍርድ ወንበር ፊት እንቆማለንና» ይላል ሮሜ 14÷10፡፡
በዚህ ቃል ውስጥ «ሁላችን» የሚለው ቃል ጸሐፊው ጳውሎስ ራሱን ጨምሮ መናገሩን ያሳያል፤ ጳውሎስ የዳነ መሆኑን ግልጽ ነው። ስለዚህ ጳውሎስን ጨምሮ ሁላችን የምንቀርብበት ይህ የክርስቶስ የፍርድ ወንበር የመዳን ወይም ያለ መዳን ጉዳይ ገና የሚረጋገጥበት ዙፋን ሳይሆን የዳኑ ሰዎች በሥጋ ዘመናቸው ለሠሩት ሥራ ተገቢው የጽድቅ ብድራት የሚከፈልበት የፍርድ ወንበር ነው፡፡ ስለዚህ በመልካም ሥራችን የምናገኘው መዳንን ሳይሆን እንደየሥራችን የሆነ ብድራት ወይም ዋጋ ነው፡፡ ይህም «የማይጠፋ አክሊል» መሆኑ የተገለጸ ሲሆን 1ቆሮ9÷15 ፣ በ2ጢሞ 4÷8 ላይ «የጽድቅ አክሊል»፣ ተብሎ ተጠርቷል።
አገልጋይ ቅዱስ ቃሉ
የከሳቴ #ብርሃን #ተሐድሶ #ቤተክርስቲያን #ጭሮ #አጥቢያ መጋቢ
ለሌሎች አጋሩ!
ከስር ያለውን ሊንክ ለ10 ሰዎች ላኩ!
የጸጋው ቃል ለብዙዎች እንዲደርስ አብረውን ይስሩ!
👇
#Grace #Commission
https://t.me/gracecom | 50 |
| 4 | https://vm.tiktok.com/ZMFe7eWj4 | 112 |
| 5 | https://vm.tiktok.com/ZMFe7rqGr | 102 |
| 6 | https://vm.tiktok.com/ZMFe7jdDg | 86 |
| 7 | https://vm.tiktok.com/ZMNKUPFvD | 81 |
| 8 | https://vm.tiktok.com/ZMNKUqEES | 0 |
| 9 | https://vm.tiktok.com/ZMNKS1GKG/ | 0 |
| 10 | #አእምሮን #ማደስ (2)
ማክሰኞ ጳጉሜን 1 2014 ዓ.ም
"የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ።" ( ሮሜ 12፥2) ።
“And be not conformed to this world: but be ye transformed by the renewing of your mind, that ye may prove what is that good, and acceptable, and perfect, will of God.” ( Rom 12፥2 (KJV)
ከላይ "በልባችሁ መታደስ ተለወጡ" የሚለውን ቃል የንጉሥ ጀምስ ትርጉም "transformed by the renewing of your mind" ብሎታል። ያ ማለት "ልብ" የሚለውን "አእምሮ" ብሎ ጠርቶታል። ስለዚህ በልብ መታደስ መለወጥ ማለት አእምሮን ማደስ ማለት ነው።
አእምሮን ማደስ ማለት ደግሞ አዲሱ ሰው ያለውን አመለካከት ወይም አቋም መያዝ ማለት ነው። አእምሮን ማደስ ማለት በክርስቶስ ካገኘነው ሕይወት አንፃር ኑሯችንን መቅረፅ የምንችልበትን እውቀት ማግኘት ማለት ነው። ስለዚህ አእምሯችን ታደሰ የሚባለው ነገሮችን በእግዚአብሔር ቃል መንገድ ማሰብ ስንጀምር ነው።
ዻውሎስ "አእምሮን ማደስን" የተግባራዊ ክርስትና መሠረት አድርጎ ያቀርበዋል። አንድ አማኝ አእምሮው ካልታደሰ የአዲሱን ማንነቱን መልክና ሕይወት መግለጥ አይችልም። የአማኝ ትልቁ አገልግሎት ለእግዚአብሔር "ሰውነቱን ማቅረብ" ነው። (ሮሜ 12፥1)። ይህን ለማድረግ ግን አስቀድሞ አእምሮው መታደስ ይኖርበታል። ሮሜ 12፥1 ለመፈጸም ሮሜ 12፥2 እጅግ በጣም አስፈላጊ ነው። "ለአእምሮ የሚመች አገልግሎትን" ወይም በግሪኩ ገለጻ መሠረት "መንፈሳዊ አምልኮን" ለማቅረብ በእእምሮ መታደስ ቁልፍ ነገር ነው።
ኑሯችንም የሚገልጠው በአእምሮአችን ውስጥ ያለውን ነው። መጽሐፍ ሰው “በልቡ እንዳሰበ እንዲሁ ነውና፤” እንደሚል (ምሳሌ 23፥7) አሳባችን እኛን ይገልጸናል። ስለዚህ በእግዚአብሔር ቃል ብርሃን እና በመንፈስ ቅዱስ አመራር አእምሯችንን እናድሰው። አስታውሱ! አእምሮን ማደስ የሕይወት ዘመን ሥራ ነው።
አገልጋይ ቃለአብ ካሳዬ
#የጸጋውን #ቃል #በየቀኑ #ይማሩ!.
ለሌሎች #Share በማድረግ አብረውን ያገልግሉ!.
👇
#GRACE #COMMISSION
https://t.me/gracecom | 46 |
| 11 | በሕይወት ውስጥ የምትኖሩለትን ነገር መቀማትም ሆነ ፣ ለምትኖሩለት ነገር እንደሚገባ አለመኖር የሚፈጥሩትን ሕመም ያህል ሌላ ሕመም ምድር ላይ ያለ አይመስለኝም። | 73 |
| 12 | egziabher%20hayle%207.mp3 | 102 |
| 13 | ጥቂት ምክር ለአገልጋይ ስለአገልግሎቱ
" ለአገልግሎቱ ሾሞኝ ታማኝ አድርጎ ስለ ቈጠረኝ፥ ኃይል የሰጠኝን ክርስቶስ ኢየሱስን ጌታችንን አመሰግናለሁ፤"(1ኛ ጢሞ1 ፥ 12)።
እግዚአብሔር በክርስቶስ በማመናችን የተቀበልነውን ሕይወት የምንኖረው በልጅነት ሲሆን ይህን ሕይወት ለሌሎች እንዲደርስ ደግሞ የአዲስ ኪዳን አገልግሎት ተሰጥቶናል ።ለዚህም ለአገልግሎቱ የሾመን ታማኝ አድርጎም የቆጠረን ፣ ለአገልግሎቱም መፈጸም ኃይልን የሰጠን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብሩክ ነው።
ከዚህ በመቀጠል ከጌታ የተቀበልነውን አገልግሎት እንዴት ብናገለግል መልካም እንደሆነ በልቤ የሞላውን ላካፍላችሁ እወዳለሁ።
አገልጋይ: -
① ለጸሎትና ለቃሉ ቅድሚያ ይሰጣል
“የእግዚአብሔርን ቃል ትተን ማዕድን እናገለግል ዘንድ የሚገባ ነገር አይደለም…. እኛ ግን ለጸሎትና ቃሉን ለማገልገል እንተጋለን” (ሐዋ 6÷2 እና 4)
አገልጋይ የቃሉ ተሸካሚ ነው። ቃሉን የተቀበለው በእምነት፣ የሚወጣው በጸሎት የሚያዳርሰው በስብከት፣ የሚሰጠው በፍቅር ነው። አገልጋይ ቢታማ እንኳ ለክብሩ እንዲሆን በእውነተኛ አገልግሎቱ እንጂ በሆዱ መሆን የለበትም። ለአገልጋይ የወንጌል ደመወዝ ተገቢ ደግሞም በመጽሐፍ ቅዱስ የተደነገገ ቢሆንም አገልግሎ የሚበላ መልካም ነው እንጂ ለመብላት የሚያገለግል አገልጋይ የአገልግሎትን ዋጋ ያረክሣል (1ኛ ቆሮ 9÷3-12)።
② በትህትና ያገለግላል
ጌታ “ከእኔ ተማሩ፣ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፣ ለነፍሣችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ” ይለናል (ማቴ 11÷29)።
አገልግሎት አያደክምም። እግዚአብሔር ዕረፍታችንን ያስቀመጠው በአገልግሎት ድካማችን ውሰጥ ነው። የሚያደክመው ትዕቢታችን ነው። ስለዚህ ጌታ ከእኔ ተምራችሁ ትሁት ስትሆኑ “ለነፍሳችሁ ዕረፍት ታገኛላችሁ” አለ።
ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ልካችንን ሰፍሮት ሔዷል። የእኛ ልክ ማድረግ የሚገባንን ሳናደርግ ይቅርና ልናደርገው የሚገባንን አድርገን እንኳ :- “የማንጠቅም ባሪያዎች ነን በሉ” የሚል ነው። አገልጋዮች ሆይ:- በአገልግሎት ባርነት እንጂ ጌትነት ባያምረን ጥሩ ነው (ሉቃ 17÷10)።
③.በፍቅር ይማርካል
“ሥራው ታላቅና ሠፊ ነው። እኛም በቅጥሩ ላይ ተበታትነናል። አንደኛውም ከሁለተኛው ርቋል (ነህ 4÷19)”
በአገልግሎት ከሚገኘው ደስታ በላይ ፍቅርን በማጣት የሚሆነው ክፍፍል የብዙዎችን ልብ አሳዝኗል። የፍቅራችን ትርጓሜ ወርቅ ያለበትን ጭቃ መጸየፍ ሳይሆን በጭቃ ውስጥ ያለውን ወርቅ መውደድ መሆን አለበት። ያለፍቅር ሁሉም ከንቱ ነው(1ኛ ቆሮ13-1) አገልግሎታችን ከከንቱ በታች እንዳይውል በፍቅር እናክብረው።
④ በጸሎት ይተጋል
“ያለጸሎት ከሚደረግ አገልግሎት ያለአገልግሎት የሚደረግ ጸሎት ይሻላል”
አገልጋይና ጸሎት ከተለያዩ የሚቀጥለው ድክመት ነው። አለመጸለይ የፈተናን በር እስከመጨረሻው መክፈት ነው። ያለጸሎት አገልግሎት የሞኝ ጦርነት ነው። ወደፈተና ላለመግባት ተግቶ መጸለይ ተገቢ ሲሆን እንዳለመጸለይ ግን ከባድ ፈተና የለም!
☞ እግዚአብሔርን የምናደምጠው (ሐዋ10÷9)፣
☞ ኃይለኛውን /ሰይጣንን/ የምናስረው (ማቴ 12÷29)፣
☞ ክፋ መናፍስትን የምናርቀው (ሐዋ 18÷16)፣
☞ በመንፈስ ቅዱስ ደስታ የምንሞላው (ሐዋ 1÷19 እና 2÷1)፣
☞ መንጋውን ከእግዚአብሔር ጋር የምናገናኘው (ፈሊ 1÷11)፣
☞ የአገልግሎት ስንቅ የማይጎድልብን (ሐዋ13÷3)፣
☞ የፈተናን ወጀብ የምንሻገረው (ማቴ 26÷4) በጸሎት ነውና አገልጋዩች ሆይ እንጸልይ!
⑤ እየኖረ የሚያኖር ነው
እናት የምትመገበው ለእርሷ ምግብ ለልጇ ደግሞ የጡት ወተት ሆኖ ይጠቅማል። የጡጦ ወተት ግን በቀጥታ ልጇን ብቻ የሚጠቅም ነው። የአገልጋዩ አገልግሎት እንደ እናት ምግብ ራሱንም የሚያገለግላቸውንም የሚጠቅምና የሚያንጽ መሆን አለበት። እንደጡጦ ወተት ለራሱ ሳይጠቀም ሌላውን የሚጠቅም አገልጋይ ትርፉ ምንድነው? ሐዋርያው ጳውሎስ “እኔ ያለ አሳብ እንደሚሮጥ ሁሉ እንዲሁ እልሮጥም፣ ነፋስን እንደሚጎስም ሁሉ እንዲሁ አልጋደልም። ነገር ግን ለሌሎች ከሰበክሁ በኃላ ራሴ የተጣልሁ እንዳልሆን ሥጋየን እየጎሰምሁ አስገዛዋለሁ።” በማለት የሕይወት ተሞክሮውን አካፍሎናል (1ኛ ቆሮ 9÷26-27) ።
⑥ በትጋት ያገለግላል
“ አገልግሎትም ቢሆን በአገልጋሎት እንትጋ “ (ሮሜ 12÷7-8)
አገልጋይ በመልካም ነገር ሁሉ እየተጋ ማገልገል ይጠበቅበታል። ሐኬት የሰነፎች መዝናኛ ክበብ ሲሆን እግዚአብሔር ግን ትጋትን ይወዳል። አገልግሎትም ኀይሉን የሚያገኘው በሰው አድናቆት ሳይሆን በትጋት ነውና ትጋት የከበረ ሀብት ነው። “ ለሰው የከበረ ሀብት ትጋት ነው። “(ምሳ 12÷27)።
የአገልግሎት እንቅፋቶች
ከዚህ ቀጥሎ ያሉት የአገልጋይም የአገልግሎትም እንቅፋት ናቸውና ልንጠነቀቅባቸውና ልንርቃቸው ይገባል።
እነርሱም፡- የአገልግሎትን ጥሪ አለማወቅ፣ የአገልግሎትን ከፍታ እንደብቃት መቁጠር፣ ከሌላ ለመማር ፈቃደኛ አለመሆን፣ ትዕቢት፣ ምክር አለመቀበል፣ አድርባይነት፣ ዝሙት፣ አለማንበብና አለማሰላሰል፣ አለመጾም፣ አለመጸለይ፣ አለመብሰል ( አርቆ አለማየት)፣ ራስን ከሌሎች ጋር ማወዳደር፣ የሌሎችን ጸጋ መናቅ፣ ማሳደድ፣ በቅሬታ /በቂም መኖር/፣ የአገልግሎትን ውለታ መቁጠር፣ ሁልጊዜ እንደትናንት ለማገልገል መሞከርና የመሳሰሉት ናቸው።
"ዕንቅፋትን አውጡ !" ……….. “(ት.ኢሳ 57÷14)
አገልጋይ ቃለአብ ካሳዬ | 0 |
| 14 | ለደከሙ ፣ ለተጨነቁ ፣ ብዙ ነገር ለከበዳቸው ፣ ግራ ለተጋቡ ፣ ላዘኑ ሰዎች የሚሆን የእረፍት ቦታ ተገኝቷል። እርሱም ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው !
" እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ። ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤ ቀንበሬ ልዝብ ሸክሜም ቀሊል ነውና። " ( ማቴ 28 ፥ 28 -30)
ሕይወታችሁን በቀላሉ ከኢየሱስ ጋር ስታገናኙ ጌታ ምን ያህል አሳራፊ፣ ታማኝ ፣ እና ደስ የሚያሰኝ መሆኑን ትረዳላችሁ።
Simply join your life with jesus ! You will discover easy to please ! | 75 |
| 15 | (((ካነበብኩት ነገር እስኪ እናንተም ተማሩበት)))
አንዲት ወጣት ሴት በአንድ ወቅት አንድ ከባድ ወንጀል ፈጸመች፡፡ ይህም ወንጀል በፍርድ ፊት አቆማት፡፡ ወንጀሉ ሙሉ በሙሉ የእድሜ ልክ እስራት የሚያስፈርድ ነበር፡፡ የፍርድ ሂደቱ በሚከናወንበት ወቅት ፊቷ በእንባ እየታጠበ ለይቅርታ ብትማጸንም ሰሚ ግን አላገኘችም፡፡
ቤተሰቦቿ እና ወዳጅ ጓደኞቿ በእንባ ከመራስ ውጭ ምንም አማራጭ አልነበራቸውም፡፡ ነገር ግን በዚህ አስጨናቂ ወቅት እንድ ሰው ምስክሮች በሚቆሙበት ሳጥን ውስጥ ገብቶ ፍርድ ቤቱን በመማጸን ፍርዱ ከመወሰኑ በፊት ስለዚች ወጣት ሴት ዳኞቹን ይለምንና ይማልድ ጀመር፡፡
ጉዳዩ ከባድ ቢሆንም እርሱ ግን ያለ የሌለ ኃይሉን ተጠቅሞ በዚህች ሴት ምትክ ይሟገት ጀመር፡፡ ከብዙ ውጣውረድ እና ልፋት በኋላ ድካሙ ፍሬ አፍርቶ ልጅቱ በነጻ ተለቀቀች፡፡ ልጅቱም ሰውየው ባደረገላት ነገር ተደንቃ በፊቱ ወደቀች፡፡ ከልቧም አመሰገነችው፡፡
ብዙም ሳይቆይ ይቺው ወጣት በሌላ ተመሳሳይ ወንጀል ውስጥ ተገኘች፡፡ ልክ የፍርድ ቤቱን በር አልፋ አይኖቿን ወደ ዳኞቹ ስታቀና ባለፈው እርሷን ከፍርድ ለማዳን ሲማጸን እና ሲማልድ የነበረው ሰው ዳኛ ሆኖ አገኘችው፡፡ ለካስ ያኔ ጠበቃ ሆኖ ሲሟገትላት የነበረው ሰው አሁን ዳኛ ሆኗል፡፡ ወጣቷ ይህ ሰው ዳኛ ሆኖ ስላገኘችው ደስ አላት፡፡ እንደገና መጣሁ በሚል መንፈስ ይመስላል፡፡
ሰውየው እጆቹን ወደላይ አነሳና ይህውልሽ ትናንት ጠበቃ ነበርኩ ለዚህ ነው አንቺን ለማዳን የተከራከርኩልሽ አሁን ግን ዳኛ ነኝ፡፡ እንደ ዳኛ ደግሞ ትክክለኛውን ፍርድ መፈጸም አለብኝ አላት፡፡ ልጅቱም አይኗ በእንባ እየራሰ ለመሆኑ አንተ ማን ነህ አለችው፡፡
እርሱም፡ የትናንቱ ጠበቃ የአሁኑ ዳኛ ነኝ አላት፡፡
ወዳጄ ዛሬ ኢየሱስ ጠበቃ ነው፡፡ ለጥፋትህ ሁሉ እየማለደ ወደ ሕይወት መንገድ ትገባ ዘንድ ስለአንተ ይማልዳል፡፡ ነገር ግን ኢየሱስ ጠበቃ እንደሆነ አይቀጥልም ዳኛ ሆኖ የሚገለጥበት ወቅት ይመጣል፡፡ ቀኑም ቀርቧል፡፡
አምናለሁ አንተም ተዘጋጅተሃል፡፡👍👍👍 | 83 |
| 16 | "ዕውነትን ማወቅ ትልቅ ጥረት ይጠይቃል። ዕውነትን መናገር ደግሞ ትልቅ ድፍረት፣ ዕውነትን ለመኖር ከሁሉ የሚበልጥ መስዕዋትነት ያስከፍላል። ምክንያቱም ዕውነትን ለመረዳት ብሩህ ልቦና፣ ለመናገር ንፁህ ህሊና፣ ለመኖር ደግሞ የሰውን ሁለንተና ይጠይቃል።"
ዶ/ር ምህረት ደበበ | 111 |
| 17 | No text... | 48 |
| 18 | https://youtu.be/vrinH2oMyH4 | 212 |
| 19 | ☞ ጠንካራ እንድትሆን ፀለይክ ፣ እግዚአብሄር ጥንካራ ሰው ሊያደርግህ በመከራ እንድታልፍ ፈቀደ።
☞ ጥበብ እንዲሰጥህ ፀለይክ ፣ እግዚአብሄር መልሱን እንድታውቀው ጥበብን ሊሰጥህ በብዙ ፈተና እንድታልፍ ፈቀደ።
☞ ጽናት እንዲኖርህ ፀለይክ ፣ እግዚአብሄር ጽናትን ሊያስተምርህ በብዙ ትግል እንድታልፍ ፈቀደ።
☞ ፍቅር እንዲኖርህ ፀለይክ ፣ እግዚአብሄር ልብህን ሊሰራው ብዙ የተቸገሩ ሰዎችን ሰጠህ።
መልሱ ያለው አንተ በጠየከው እና እርሱ በሰጠህ መካከል ነው።
☞ መከራው ሲመጣ ምን አደረክ?
☞ ፈተና ሲገጥምህ ምን አደረክ?
☞ ትግል ሲገጥምህ ምን አደረክ?
☞ የተቸገረ ሰው ወዳንተ ሲመጣስ ምን አደረክ?
በጸጋ ምስባክ መረን ያረገን ጠማማው ወንጌል ሳይሆን አሰራሩ እንደዚ ነው የኛ ጌታ! በምንም ሁኔታ ውስጡ ይሁን ያለነው ☞ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን!
“ልጆች ሆይ፤ እናንተ ከእግዚአብሔር ናችሁ፤ እነርሱንም አሸንፋችኋቸዋል፤ ምክንያቱም በእናንተ ውስጥ ያለው በዓለም ካለው ይበልጣል።” (1ኛ ዮሐንስ 4፥4)
Have a blessed bright day! 🌅 | 183 |
| 20 | https://youtu.be/dExHgsL_EtM | 63 |
