en
Feedback
"ልጆቼ የቤተክርስቲያንን ነገር አደራ"

"ልጆቼ የቤተክርስቲያንን ነገር አደራ"

Open in Telegram

@Dan12bot ለአስተያየትዎ ይህን ይጠቀሙ እናመሠግናለን

Show more
1 134
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-2330 days
Posts Archive
''ስትጸልይ በማክበር ውስጥ መሆንን ተለማመድ፣ የልብና የሥጋ ማክበር ይኑርህ፣ የስሜቶች ሰላምም እንዲሁ። ቀስ በቀስ መዝሙራትን፣ ወንጌላትንና የዘወትር ጸሎቶችን አጥና። በሁሉም ጊዜ ውስጥ ጸሎት መጸለይን ተለማመድ፣ ስትሠራ፣ ስትራመድና ከሌሎች ሰዎች ጋር ስትቀመጥ እንኳ፣ ዘወትር ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ እኔ ኃጢአተኛውን ማረኝ እያልህ መጸለይን ተለማመድ። በማንኛውም ጊዜ ለሌሎች ሰዎች መጸለይን ተለማመድ፣ ለሁሉም ሰዎችም ፍቅር አሳይ፣ ለጠላቶችህና አንተን ለሚሰድቡህ ሰዎች እንድትጸልይ የሚያዝህን የእግዚአብሔር ትዕዛዝ ተለማመድና ተግባራዊ አድርግ።" #አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ

#ደብረ_ምጥማቅ  (ግንቦት_21) ግንቦት ሃያ አንድ በዚች ዕለት አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ በስሟ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ በብርሃን መርከብ ተቀምጣ ፊቷ በግልጥ ስለመታየቱ የክርስቲያን ወገኖች ሁሉም ታላቅ በዓልን ያደርጋሉ። እርሷም በልጅዋ የመለኮት ብርሃን የተጐናጸፈች ናት በዙሪያዋም የመላእክት ሠራዊት የመላእክት አለቆችም በየማዕረጋቸው ክንፋቸውን ዘርግተው ይቆሙ ነበር ይጋርዷታልም። ሱራፌልም ማዕጠንታቸውን ይዘው ለንግሥዋ ገናናነት ይሰግዳሉ በየስግደታቸውም እንዲህ እያሉ ያመሰግኗታል። አብ በሰማይ ሁኖ ተመለከተ እንደ አንቺ ያለ አላገኘም አንድ ልጁንም ልኮ ከአንቺ ሰው ሆነ። ሁለተኛ ሰማዕታትም በየማዕርጋቸው ረቂቃን በሆኑ ፈረሶቻቸው ተቀምጠው እየመጡ መጀመሪያ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከአምባላይ ፈረሱ ወርዶ ይሰግድላታል እንዲሁም ባልንጀሮቹ ሰማዕታት መጥተው ይሰግዱላታል ። ከእርሱ በኋላ የሚመጣው በዱሪ ፈረስ የሚቀመጥ ይህ መርቆሬዎስ ነው። ከዚህም በኋላ ሰማዕታት ሁሉ በመከታተል መጥተው ይሰግዱላታል ምስጋናም ያቀርቡላታል። ሁለተኛም ደግሞ የጻድቃን አንድነታቸው መጥተው በፊቷ ሰግደው ይመላለሳሉ። ሄሮድስ የገደላቸው ሕፃናትም መጥተው ይሰግዱላታል በፊቷም እየዘለሉ አንዱ በአንዱ ላይ እየዘለለ በመተቃቀፍም ይጫወታሉ የተሰበሰቡትም በአዩ ጊዜ ደስታ ይመላባቸዋል በሰማይም ያሉ ይመስላቸው ነበር። እናትና አባቱም የሞቱበት ቢኖር ወይም ከዘመዶቹ ወይም ባልንጀራዉ ቅድስት ድንግል እመቤቴ ሆይ ዕገሌን አሳዪኝ ብሎ በሚለምናት ጊዜ ቀድሞ በነበረበት መልኩ ያን ጊዜ ታመጣዋለች። ደግሞ መሀረባቸውን ወደላይ ይወረውሩላታል የወደደችውንም በእጇ ተቀብላ መልሳ ትጥልላቸዋለች ለበረከትም በየጥቂቱ ይካፈሉታል። እንዲህም አምስት ቀን ሁሉ ክርስቲያንም እስላሞችም አረማውያንም ያይዋታል። ወደ ቤታቸውም ለመሔድ ሲሹ በፊቷ ሰግደው ይሰናበቷታል እርሷም ትባርካቸውና ይመለሳሉ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም አምላክን በወለደች በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን:: (#ስንክሳር_ዘወርኀ_ግንቦት)

ጌታችን ሆይ በሰውነታችን ውስጥ በሚፈጠር አለመስማማት ምክንያት እንዳንስት፤ እኛን ለማገዝ ስትል መንፈሳዊ እርዳታህን አድርግልን፡፡ ከአንተ ጋር ኅብረት ከሌለን በቀር ከስሜቶቻችን እስረኝነት በቀላሉ ማምለጥ የማይታሰብ ነው፡፡ ፈቃዳችንን ገርተን እንድንኖር መንፈሳዊ በረከቶችን በምናገኝባቸው ተግባራት እንድንተጋ የአንተ ፍቅር በልቦናችን ውስጥ ይፍሰስ፡፡ መልካም የሆነው ጸጋህን እንቀበልና ጆሮአችን ወደ አንተ አዘንብሎ እንዲሰማ ፈቃዳችንን እንሰጥህ ዘንድ አድርገን፡፡               [ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ] መልካም ቀን ❤️

"ሰንበት ከሁሉ ዕለት ትበልጣለች ሰውም ከሁሉ ፍጥረት ይበልጣል ኖኀ በታቦት (በመርከቡ) ውስጥ ከፍ ከፍ አደረጋት አብርሃምም በመሠዊያው አከበራት ሙሴ ደግሞ ሕዝበ እስራኤል ሰንበትን በአንድነት ሆነው በእውነት እንዲያከብሩዋት አዘዛቸው፡፡"        ሊቁ ቅዱስ ያሬድ መልካም ዕለት ሰንበት!!!

"#እባክህን_ከእሳቱ_ላይ_አትውረድ"    አንድ ወንድም አባ ጴሜንን "ምከረኝ" ብሎ ጠየቀው። አባ ጴሜንም "ድስት በእሳት ላይ እያለ ምንም አይነት ተባይ ሊቀርበውና ሊያበላሸው አይችልም። ከእሳት ወጥቶ ሲቀዘቅዝ ግን ነፍሳት ሁሉ ለመግባትና ለማበላሸት ይቻላቸዋል። ክርስቲያንም ከመንፈሳዊ ተግባር ካልራቀ ጠላት የድቀት ምክንያት አያገኝበትም" አለው። ወዳጄ ሆይ ሕይወት ቀዝቅዛብሃለችን? ከእሳቱ ወደ መሬት ወርደህ በርደሃልን? የሕያውነትህ ሙቀት እሳት በማጣት ተንዘፍዝፏልን? ድስት የተባለ ሰውነትህ ክረምት የሚያህል ጉድን ተሸክሟልን? ዙሪያ ገባህ ፀሐይ እንደማትወጣበት ምእራብ ጨለማን የሚጠራ ሆኗልን? ማንነትህ እሳት እንዳጣ ምግብ ጥቃቅን ነፍሳት በተባሉ ኃጢአቶች (ቁጣ፣ ቸልተኛነት፣ ስስት፣ አልታዘዝ ባይነት፣ ጭንቀት፣ ሁሉን የመናቅ ስሜት፣ ተስፋ መቁረጥ፣ ...) ተወርሮ፣ መዓዛ ቅድስና ተለይቶት እጅ እጅ ብሏልን? ሞቅ የሚያደርገው አጥቶ በዓለማዊነት ሻግቷልን? የተባዮች መጫወቻ፣ የተውሳኮች መቀለጃ ሆኗልን? እንግዲያውስ በቶሎ ወደ እሳቱ ውጣ፡፡ ወዳጄ ሆይ ሃይማኖት በተባለችና ከሰማይ በወረደች ልዩ እሳት (ሉቃ.12፥49) ላይ ተቀምጠህ የድስትነትህን ሙቀት መልስ፡፡ እምነት፣ ተስፋና ፍቅር (1ቆሮ.13፥13) በተባሉ ሦስት ጉልቻዎች ላይ በምቾት ተጥደህ የሕይወትህን የኃጢአት ብርድ አስወግድ፡፡ ንስሐ በተባለች ነበልባል ውበትነት የክረምትህን ጽልመት በምስራቃዊ በጋነት ድል ንሳ፡፡ በሥጋ ወደሙ ፍምነት ድስት የተባለ ሰውነትህን በከዊነ እሳትነት ቀድስ፡፡ እባክህን በቶሎ ወደ እሳቱ ውጣ፡፡ ሃይማኖት የተባለ እሳትን ተባይ አይቀርበውም፡፡ እምነት ተስፋና ፍቅር የተሰኙ ጉልቻዎችን ተውሳኮች ሽቅብ አይወጡአቸውም፡፡ የነበልባለ ንስሐን ብርሃንና ሙቀት ነፍሳተ ጽልመት መቋቋም አይችሉም፡፡ ስለዚህ በእሳቱ ላይ እስካለህ ድረስ (በመንፈሳዊ ተግባራት እስከጠነከርክ ድረስ) አንተ ሁሌም ከተባይና ከነፍሳት ብልሽት (ከአጋንንት) የራቅክ ነህ፡፡ ወዳጄ እባክህን ከእሳቱ ላይ አትውረድ፡፡ እሳቱ በደንብ ይነድ ዘንድ ጾም፣ ጸሎት፣ ስግደት የተባሉ እንጨቶችንና ምጽዋት የተባለ ጋዝን መጨመርህን እንዳትዘነጋ፡፡ እንዲህ ከሆነ ዘንዳ ድስትነት ሁሌም የሞቀ ይሆናል፡፡ እጅ እጅ ከማለት፣ ከመሻገትና የተባይ መጫወቻ ከመሆን ትድናለህ፡፡ ወዳጄ ሆይ እባክህን ከእሳቱ ላይ አይትውረድ፡፡ በኃጢአት "እጅ እጅ '' ከማለትና በበደል ከመሻገት እግዚአብሔር ይሠውረን! አሜን! (ሕሊና በለጠ ዘኆኅተብርሃን)

#ዕርገተ_እግዚነ_ወመድኃኒነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ!! በዚህች ዕለት የክብር ባለቤት ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእኛ በነሣው ሥጋ ከአባቱና ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ ወደአለው የአንድነት አኗኗሩ ከ
#ዕርገተ_እግዚነ_ወመድኃኒነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ!! በዚህች ዕለት የክብር ባለቤት ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእኛ በነሣው ሥጋ ከአባቱና ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ ወደአለው የአንድነት አኗኗሩ ከሰማያት በላይ ያረገበት ሆነ። እርሱም በረቀቀ ጥበቡ በመከራው በሞቱና በመነሣቱ ሥራውን ከፈጸመ በኋላ አርባው ቀን ሲፈጸም በነፋሳት ክንፍ ላይ ሆኖ ዐረገ። ያን ጊዜ በኪሩቤል ላይ ተቀምጦ ወጣ በነፋሳትም ክንፎች ላይ ሁኖ ወጣ ያለው የዳዊት ትንቢት ተፈጸመ። በዚህም ዕርገቱ ለሚያምኑበት በልዕልና ወደሚኖሩበት የሚዐርጉ መሆናቸው ተረዳ ተረጋገጠ ራስ በአለበት ሕዋሳት ሊኖሩ ይገባልና ። አዳም አስቀድሞ በምድራዊ ርስቶች በሲኦልም እንደኖረ መኖርንም እንደ ቀደመ እንዲሁ ዳግማዊ አዳም ጌታ በመንግሥተ ሰማያት ርስት መኖርን ቀደመ። የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ዕርገቱን ከትንሣኤው አከታትሎ ወዲያውኑ አላደረገም መናፍቃን ዕርገቱ ምትሐት ናት ብለው እንዳያስቡ። ጌታችንም በረቀቀ ጥበቡ የደቀ መዛሙርቱን ተሸብሮ የነበረ ልቡናቸውን እያጽናና መነሣቱንም እያስረዳቸው ከትንሣኤው በኋላ አርባ ቀን ኖረ። በጌታችንም ዕርገት የዳንኤል ትንቢት ተፈጸመ እንዲህ የሚል ሌሊት በራእይ አየሁ እነሆ ታላቅ እንደ ሰው ልጅ የሆነ መጣ ዘመናትን ወደሚያስረጃቸው ደረሰ ከፊቱም አቀረቡት። የዘላለም አገዛዝ ጌትነት መንግሥት የዘላለም ሥልጣን ተሰጠው ሕዝቡና አሕዛቡ ሁሉ መንደር መንድረው የሚኖሩትና ነገዱም ነገሥታቱም ሁሉ ይገዙለታል አገዛዙም የዘላለም አገዛዝ ነው መንግሥቱም የማያልፍ የማይጠፋ ነዋሪ ነው። #ስንክሳር_ዘወርኀ_ግንቦት_8

ግንቦት 16 በዓሉ ለቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በዚህ ዕለት ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ በብዙ ምክንያቶች ዓመታዊ መታሰቢያ ክብረ በዓሉ እንደሆነ የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት ያስረዳሉ 1 በእስያ በኤፌሶን በዙሪያው ሁሉ ዞሮ ወንጌልን ማስተማሩ  መስበኩ ተዝካረ በዓል ለስብከቱ ነው (መጽሐፈ ስንክሳር የግንቦት 16 ንባብ) 2 በትምህርቱ በአምልኮተ ጣዖት የነበሩትን እስኪመልሳቸው ከሰይጣን ወጥመድ እስኪያድናቸው ድረስ በክፉዎች እጅ የተቀበለው መከራ ይታሰብበታል በመጽሐፈ ገድሉ እንደተጻፈው ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ወንጌልን ለመስበክ ወደ ኤፌሶን ሲሄድ ጀምሮ ከደቀ መዝሙሩ ከአብሮኮሮስ ጋር ብዙ መከራዎችን ተቀብለዋል በዚህ ዕለት ይህን እናስባለን 3 ሦስቱ ወንጌላውያን ያስቀሩትን በማካተት ወንጌልን መጻፉ ይታሰባል ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌሉን  ከሁሉ መጨረሻ የጻፈ በመሆኑ ሦስቱ ወንጌላውያን ያላካተቱትን የጌታን ትምህርቶች እና ተአምራቶች አካቶ ልዩ ወንጌል ጽፎልናል ከመጽሐፈ ስንክሳር ጋር አብሮ የሚገኘው የምስጋና መጽሐፍ መጽሐፈ አርኬ ላይ እንዲህ ተብሎ ተጽፏል ሰላም ለከ ሶበ ሰማዕከ ዐዋዴ፡ እምቃለ ወንጌል ዘወርቅ እንበለ ተምያን ወመፍዴ፡ ዮሐንስ ዘኮንከ በእንተ ጽድቅ ነጋዴ፡ መኒነከ እመ ወላዲተ ወአበ ወላዴ፡ ምስለ ነዳያን ነበርከ በዴዴ፡፡ (አዋጁን በሰማህ ጊዜ ያለ ግብዝነትና ያለ ክፍያ ወርቃማ ስለሆነው የወንጌል ቃል ብለህ የምትወልድ እናትና የሚወልድ አባትን ትተህ ስለጽድቅ ነጋዴ የሆንክና ከነዳያን ጋር በደጅ የኖርክ ዮሐንስ ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን) 4 ራእዩን ያየበት ዕለት መታሰቢያ ነው ሊቃውንት ቅዱስ ዮሐንስን ከሚጠሩባቸው ስያሜዎች መካከል አንዱ አቡቀለምሲስ ነው ባለራእይ ማለት ነው የሐዲስ ኪዳን የትንቢት መጽሐፍ የሚባለውን ራእይ ዮሐንስን የጻፈ ወደ ፊት የሚሆነውን አስቀድሞ በራእይ  የተመለከተ በመሆኑ የተሰጠ ስያሜ ነው 5 በእስክንድርያ ሀገር ውስጥ ቤተክርስቲያኑ የከበረችበት ቀን ነው የግንቦት 16 ስንክሳር የአርኬ ምስጋና ላይ ሰላም ለቅዳሴ ቤትከ በእለእስክንድርያ ሀገር፡ እለ ሐነፅዋ ኬነዉት ወጠበብተ ምክር፡ ወእንዘ ትበውእ ዮሐንስ ውስተ መቃብር፡ ተኀባዕከ ወተሠወርከ በሥልጣነ ኀይል መንክር ባሕቱ ልብስከ ዘተርፈ ለዝክር፡፡ ተጠባቢዎች በጠቢባኑ ምክር በእስክንድርያ ሀገር ላነፁት ቅዳሴ ቤትህ ሰላም እላለሁ፤ ዮሐንስ [ሆይ] ወደ መቃብር በገባህ ጊዜ ለመታሰቢያ እንዲሆን ልብስህ ብቻውን ቀርቶ በሚደንቅ ኃይል ባለው ስልጣን ተሰውረህ ታጣህ) ተብሎ እንደተጻፈ ቅዳሴ ቤቱ የከበረበትን ዕለት በዓል አድርገን እናከብራለን ♦ በአዲስ አበባ በሐዋርያው ስም በተሰየመው ብቸኛ ደብር በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን በዓሉ ታቦት ወጥቶ በንግስ ባይከበርም ለሊት በማሕሌት ጠዋት በቅዳሴ ማታ በልዩ የሠርክ ጉባኤ  ታስቦ ይውላል የሐዋርያው አባታችን ምልጃ እና ጸሎት አይለየን

“በቤት ውስጥ በሚስትህ ምክንያት አንድ ደስ የማያሰኝ ስሕተት ቢፈጠር ‘አይዞሽ’ ልትላት ይገባል እንጂ ኀዘኗን ልታባብሰው አይገባህም፡፡ ኹሉንም ነገር ብታጣም እንኳን ከጎኗ ኹን፡፡ እርግጥ ነው ለባልዋ ደንታ ከሌላት ሚስት በላይ ምንም አሳዛኝ ነገር የለም፡፡ በእናንተ መካከል ጸብ ክርክር ከሚፈጥር የሚስትህ ጥፋት በላይ አሳዛኝ ነገር የለም፡፡ ስለዚሁ ዋና ምክንያት ግን ለእርስዋ ያለህ ፍቅር እጅግ ጽኑዕ ሊኾን ይገባዋል፡፡ እኛ ክርስቲያኖች አንዳችን የሌላችንን ሸክም እንድንሸከም የታዘዝን ከኾነ፥ ከዚህ በላይ ደግሞ አንተ የሚስትህን ሸክም ልትሸከም ይገባሃል፡፡ በመኾኑም ድኻ ብትኾን ስለዚሁ ምክንያት በፍጹም አትናቃት፡፡ ሰነፍ ብትኾን ስለዚሁ ምክንያት አስተካክላት እንጂ አታዋርዳት፡፡ እርስዋ አካልህ ነችና፤ አንተም አካልዋ ነህና፤ አንድ አካል ናችሁና፡፡ ‘ክፉ ነች፤ ቁጡ ነች፤ ራስዋን መቈጣጠር የማትችል ግልፍተኛ ነች’ ልትለኝ ትችላለህ፡፡ ስለዚሁ ጠባይዋ እጅግ ልታዝን ይገባሃል፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር ይህን ጠባይ ያርቅላት ዘንድ ጸልይላት እንጂ አንተም መልሰህ አትቈጣት፡፡ ልታሳምናት ሞክር እንጂ ወደ ሙግት አትግባ፡፡ እነዚህን ክፍተቶችዋን ከእርስዋ ለማራቅ ኹሉንም ዓይነት በጎ ዘዴዎችን ተጠቀም፡፡” “ይህን እንደማድረግ ሚስትህን የምትመታትና የምታሠቃያት ከኾነ ግን እነዚህ ሕመሞችዋ እንዲድኑ አታደርጋቸውም፡፡ ኃይለኝነት የሚወገደው በጭካኔ ሥራ ሳይኾን በየውሃት ነውና፡፡ ከዚሁ በተጨማሪም ሚስትህ በየውሃት ስትይዛት ከእግዚአብሔር ዘንድ ሹመት ሽልማት እንደምታገኝ አስታውስ፡፡ ከአሕዛብ ፈላስፎች አንዱ ክፉ፣ መራራና ሥርዓት የለሽ ሚስት ነበረችው ይባላል፡፡ ከዕለታት በአንዱ ቀን ለምን ከእርስዋ ጋር እንደሚኖር (ለምን እንደማይፈታት) በተጠየቀ ጊዜ ጠቢቡ ሰው በገዛ ቤቱ ውስጥ የፍልስፍና ትምህርት ቤት እንዳለው ነበር የመለሰው፡፡ ‘ዕለት ዕለት በዚህ ትምህርት ቤት የምማር ከኾነ ከሌሎች ሰዎች ይልቅ ታጋሽ እኾናለሁ’ ነበር ያለው፡፡ በዚህ ተደነቅህን? እኔ ግን መላእክትን እንዲያውም ከእነርሱም በላይ የዋሃን ኾነን እግዚአብሔርን እንድንመስለው ከታዘዝነው ከእኛ ይልቅ አረማውያን ሰዎች ጠቢባን ኾነው ስመለከታቸው ፈጽሜ አለቅሳለሁ፡፡ ያ ፈላስፋ ሚስቱን እንዳይፈታት ምክንያት የኾነው የእርስዋ ክፉ ጠባይ ነው፡፡ እንዲያውም አንዳንድ ሰዎች ‘ይህ ፈላስፋ ይህቺን ሴት ሚስት ትኾነው ዘንድ ያገባት ይህን ለማግኘት ብሎ ነው’ ይላሉ፡፡ አንተም ዕጮኛ ስትመርጥ በምርጫህ ተሳስተህ ክፉ ሚስት አግብተህ ከኾነ (ብታገባ) ቢያንስ ቢያንስ ይህን አረማዊ ፈላስፋ አብነት አድርገው፡፡ ሚስትህን ለማስተካከል የተቻለህን አድርግ፡፡ ክፋትዋን በሌላ ክፋት አትመልስላት፡፡ ከእርስዋ ጋር ኾነህ የትዳርን ቀንበር የምትሸከም ከኾነ ሌሎች ብዙ ረብ ጥቅሞችንም ታገኛለህና፤ መንፈሳዊ ተግባራትን ለመተግበር ቀላል ይኾንልሃልና፡፡”  ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

🍂 አቡነ አረጋዊ አባታቸው ✥ ንጉስ ይስሐቅ እናታቸው ✥ እድና 🍂በቀደመ ስማቸው ዘሚካኤል ሲባሉ ከዘጠኙ ቅዱሳን መካከል አንዱ ናቸው። የንጉስ ልጅ ሆነው ሳለ የዓለምን ነገር ስለናቁ ወደ አባ ጳኩ
🍂  አቡነ አረጋዊ    አባታቸው  ✥ ንጉስ ይስሐቅ እናታቸው  ✥  እድና 🍂በቀደመ ስማቸው ዘሚካኤል ሲባሉ ከዘጠኙ ቅዱሳን መካከል አንዱ ናቸው። የንጉስ ልጅ ሆነው ሳለ የዓለምን ነገር ስለናቁ ወደ አባ ጳኩሚስ ዘንድ በመሄድ በአስራ አራቱ ዓመታቸው ስርዓት ምንኩስናን ተቀብለዋል። 🍂እናታቸውም ንግስት እድና የምናኔው ሕይወት ስለሳባት ወደ ገዳሙ በመምጣት እንደ ልጇ መንኩሳለች። 🍂ስለ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ በመጻሕፍት ስላነበቡ እንዲሁም ለእመቤታችን ድንግል ማርያም የአስራት ሀገር ሆና መሰጠቷን ከተረዱ በኋላ ይህችን ቅድስት ሀገር ለመጎብኘ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ጎብኝተው ወደ ሮም ተመለሰዋል። 🍂ከዚያም ተመለሰው ለስምንት ባልንጀሮቻቸው ሃገርስ ባሳየኋችሁ ሐዋርያ ሳያስተምራት በህጉ በስርዓቱ ጸንታ የምትኖር ብለው ከስምንቱ ጋር ከኬልቄዶን ጉባኤ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ መጥተዋል ። 🍂አባታችን አቡነ አረጋዊ በዓት ፍለጋ ለብዙ ጊዜ ደክመዋል ኋላም በእግዚአብሔር ፍቃድ ደብረ ዳሞ በሚባለው ቦታ ደርሰዋል፤ በተራራውም ጫፍ ብርሃን ቢታያቸውም ተራራማ ስለነበር መውጫው ቢቸግራቸው የታዘዘላቸው ዘንዶ ተራራው ጫፍ አውጥቷቸዋል። 🍂ዘጠና ዘጠኝ አመት ሲሞላቸው ጌታችን በመንፈቀ ሌሊት ተገልጾላቸው ምድራዊ መንግስትን ትተህ ስላገለገልኝ ህልፈት ሽረት የሌለባትን ሰማያዊ መንግስቴን አወርስሀለው ብሎ ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል። 🍂በስምህ የተማጸነውን እስከ አስራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሀለው አንተም ከሞት ኃይል ትሰወረላህ ብሏቸዋል። እነደ ተነገራቸውም አንደ ሄኖክና ኤልያስ ሞትን ሳያዩ ተሰውረዋል። 🙏 የጻድቁ አባታን አቡነ አረጋዊ ረድኤት በረከት አይለየን 🙏

🍂 አቡነ አረጋዊ አባታቸው ✥ ንጉስ ይስሐቅ እናታቸው ✥ እድና 🍂በቀደመ ስማቸው ዘሚካኤል ሲባሉ ከዘጠኙ ቅዱሳን መካከል አንዱ ናቸው። የንጉስ ልጅ ሆነው ሳለ የዓለምን ነገር ስለናቁ ወደ አባ ጳኩ
🍂  አቡነ አረጋዊ    አባታቸው  ✥ ንጉስ ይስሐቅ እናታቸው  ✥  እድና 🍂በቀደመ ስማቸው ዘሚካኤል ሲባሉ ከዘጠኙ ቅዱሳን መካከል አንዱ ናቸው። የንጉስ ልጅ ሆነው ሳለ የዓለምን ነገር ስለናቁ ወደ አባ ጳኩሚስ ዘንድ በመሄድ በአስራ አራቱ ዓመታቸው ስርዓት ምንኩስናን ተቀብለዋል። 🍂እናታቸውም ንግስት እድና የምናኔው ሕይወት ስለሳባት ወደ ገዳሙ በመምጣት እንደ ልጇ መንኩሳለች። 🍂ስለ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ በመጻሕፍት ስላነበቡ እንዲሁም ለእመቤታችን ድንግል ማርያም የአስራት ሀገር ሆና መሰጠቷን ከተረዱ በኋላ ይህችን ቅድስት ሀገር ለመጎብኘ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ጎብኝተው ወደ ሮም ተመለሰዋል። 🍂ከዚያም ተመለሰው ለስምንት ባልንጀሮቻቸው ሃገርስ ባሳየኋችሁ ሐዋርያ ሳያስተምራት በህጉ በስርዓቱ ጸንታ የምትኖር ብለው ከስምንቱ ጋር ከኬልቄዶን ጉባኤ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ መጥተዋል ። 🍂አባታችን አቡነ አረጋዊ በዓት ፍለጋ ለብዙ ጊዜ ደክመዋል ኋላም በእግዚአብሔር ፍቃድ ደብረ ዳሞ በሚባለው ቦታ ደርሰዋል፤ በተራራውም ጫፍ ብርሃን ቢታያቸውም ተራራማ ስለነበር መውጫው ቢቸግራቸው የታዘዘላቸው ዘንዶ ተራራው ጫፍ አውጥቷቸዋል። 🍂ዘጠና ዘጠኝ አመት ሲሞላቸው ጌታችን በመንፈቀ ሌሊት ተገልጾላቸው ምድራዊ መንግስትን ትተህ ስላገለገልኝ ህልፈት ሽረት የሌለባትን ሰማያዊ መንግስቴን አወርስሀለው ብሎ ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል። 🍂በስምህ የተማጸነውን እስከ አስራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሀለው አንተም ከሞት ኃይል ትሰወረላህ ብሏቸዋል። እነደ ተነገራቸውም አንደ ሄኖክና ኤልያስ ሞትን ሳያዩ ተሰውረዋል። 🙏 የጻድቁ አባታን አቡነ አረጋዊ ረድኤት በረከት አይለየን 🙏

🍂 አቡነ አረጋዊ አባታቸው ✥ ንጉስ ይስሐቅ እናታቸው ✥ እድና 🍂በቀደመ ስማቸው ዘሚካኤል ሲባሉ ከዘጠኙ ቅዱሳን መካከል አንዱ ናቸው። የንጉስ ልጅ ሆነው ሳለ የዓለምን ነገር ስለናቁ ወደ አባ ጳኩ
🍂  አቡነ አረጋዊ    አባታቸው  ✥ ንጉስ ይስሐቅ እናታቸው  ✥  እድና 🍂በቀደመ ስማቸው ዘሚካኤል ሲባሉ ከዘጠኙ ቅዱሳን መካከል አንዱ ናቸው። የንጉስ ልጅ ሆነው ሳለ የዓለምን ነገር ስለናቁ ወደ አባ ጳኩሚስ ዘንድ በመሄድ በአስራ አራቱ ዓመታቸው ስርዓት ምንኩስናን ተቀብለዋል። 🍂እናታቸውም ንግስት እድና የምናኔው ሕይወት ስለሳባት ወደ ገዳሙ በመምጣት እንደ ልጇ መንኩሳለች። 🍂ስለ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ በመጻሕፍት ስላነበቡ እንዲሁም ለእመቤታችን ድንግል ማርያም የአስራት ሀገር ሆና መሰጠቷን ከተረዱ በኋላ ይህችን ቅድስት ሀገር ለመጎብኘ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ጎብኝተው ወደ ሮም ተመለሰዋል። 🍂ከዚያም ተመለሰው ለስምንት ባልንጀሮቻቸው ሃገርስ ባሳየኋችሁ ሐዋርያ ሳያስተምራት በህጉ በስርዓቱ ጸንታ የምትኖር ብለው ከስምንቱ ጋር ከኬልቄዶን ጉባኤ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ መጥተዋል ። 🍂አባታችን አቡነ አረጋዊ በዓት ፍለጋ ለብዙ ጊዜ ደክመዋል ኋላም በእግዚአብሔር ፍቃድ ደብረ ዳሞ በሚባለው ቦታ ደርሰዋል፤ በተራራውም ጫፍ ብርሃን ቢታያቸውም ተራራማ ስለነበር መውጫው ቢቸግራቸው የታዘዘላቸው ዘንዶ ተራራው ጫፍ አውጥቷቸዋል። 🍂ዘጠና ዘጠኝ አመት ሲሞላቸው ጌታችን በመንፈቀ ሌሊት ተገልጾላቸው ምድራዊ መንግስትን ትተህ ስላገለገልኝ ህልፈት ሽረት የሌለባትን ሰማያዊ መንግስቴን አወርስሀለው ብሎ ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል። 🍂በስምህ የተማጸነውን እስከ አስራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሀለው አንተም ከሞት ኃይል ትሰወረላህ ብሏቸዋል። እነደ ተነገራቸውም አንደ ሄኖክና ኤልያስ ሞትን ሳያዩ ተሰውረዋል። 🙏 የጻድቁ አባታን አቡነ አረጋዊ ረድኤት በረከት አይለየን 🙏

ፍልሰተ ሥጋሁ ለአቡነተክለሃይማኖት ግንቦት12 እንኳን አረሳችሁ አደረሰን !! ግንቦት ፲፪ ቀን የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት ፍልሰተ ሥጋ የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት የዕረፍት ጊዜያቸው ሲደርስ ጌታ እመቤታችንን መላእክትን ነቢያትን ሐዋርያትን ጻድቃን ሰማዕታትን አስከትሎ መጥቶ ወዳጄ ሆይ ልመናህን ሰምቻለው ከድካምህ ላሳርፍህ መጣሁ መንፈሳዊ ደስታ ካለበት ትኖራለህ በተስፋህ ያመነውን በቃል ኪዳንህ የተማጸነውን ሥጋህን ቆረስክበትን ደምህን ያፈሰስክበትንም ቦታ እጅ የነሳውን ሁሉ ከሞተ ነፍስ አድንልሀለሁ ከዚህ ቦታ በተስፋ ጸንተው በኪዳንህ ተማጽነው የሚኖሩ ልጆችህን እንደ ሰማይ ከዋክብት አበዛልሀለሁ በ፶፯ ዘመን በኋላ ደቀ መዛሙርትህ ቤተ ክርስቲያን አንጸው ሥጋህን ወደዚያ ያፈልሱታል ብሎ ቃል ኪዳን ገብቶላቸው ነበር፡፡ ጊዜው ሲደርስ ለአበ ምኔቱ ለአባ ሕዝቅያስ ተገልጾ ጌታዬ የነገረኝን ተስፋ ሊፈጸም ጊዜው ደርሷልና በሩቅም በቅርብም ያሉ ደቀ መዛሙርቴን ሰብስበህ በ፲፪ (አስራ ሁለቱ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ደቀመዛሙር በተለያየ ቦታ ቃለ ወንጌልን የሰበኩ ያስተማሩ በነገሥታቱ ፊት በጽናት የመሰከሩ ቅዱሳን ናቸው) ሥጋዬን አፍልሱ እኔም ከቅዱስ ሚካኤል ጋር እመጣለሁ ምልክት ይሆንህ ዘንድ ስትገባ መብራቶቹን አጥፋ እኛ ስንመጣ ይበራል አሉት፡፡ እንዳሉትም ደቀ መዛሙርቶቻቸውን ከሩቅም ከቅርብም ሰብስቦ በዚህ ዕለት ሥጋቸው ካረፈበት ከመካነ አስቦ /ጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ቢገቡ እንደ ሽቶ መዓዛው አምሮ አግኝተው ተሸክመው ወደ ቤተ መቅደስ አመጡት፡፡ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖትም ከቅዱስ ሚካኤል ጋር መጥተው ከመንበሩ ተቀመጡ ሲመጡም የጠፉት መብራቶች በርተው ተገኝተዋል :: እኒያም በእልልታ በደስታ አጽማቸው ከእግረ መንበሩ ሥር አኑረውታል፡፡ ጸሎታቸውና በረከታቸው ረድኤታቸውና ምልጃቸው በመላው ሕዝበ ክርስቲያን ላይ አድሮ ይኑር ለዘለዓለሙ አሜን።

የይቅርታ  እናት  ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ   ! ✍️-የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ የተጋድሎ ታሪክ እንደ ባሕር አሸዋ፣እንደ ሰማይ ክዋከበት ተቆጥሮ ተሰፍሮ ከማያልቀው ነገረ ቅዱሳን  መካከል አንዱ ነው።       -ነገረ ቅዱሳንን መረዳት፣ማስረዳት ፣ማወቅና ማሳወቅም የወንጌልን አዝመራ መሰብሰብ ነው።      - ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ በዚህ ዓለም ከከበሩ እግዚአብሔርን ከሚፈሩ ደጋግ ባልና ሚስት የተገኘችና የተመረጠች እናት ናት። ✍️የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ የአባቷ ስም ደራሳኒ፣የእናቷም ስም እሌኒ ይባላሉ። በሸዋ ክፍለ ሀገር በቡልጋ አውራጃ ጌየ በተባለች አካባቢ እንደ ተወለደች ታሪኳ ያስረዳል።(#ገድለ ክርስቶስ ሠምራ ዘወርኃ መስከረም -ቊጥር-፪ )     ደረሳኒ እና ዕሌኒ ልጃቸውን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራን በሃይማኖታዊና ሥነ-ምግባራዊ ሥርዓት አሳደጓት(ገድለ ክርስቶስ ሠምራ ዘመስከረም -ቊጥር፬ ) መጽሐፈ ገድሏ" ልጅቱ ክርስቶስ ሰምራ ባደገችና ዐቅመ ሔዋን በደረሰች ጊዜ የንጉሥ ባለሟል የሆነ••••የኢየሱስ ሞዓ ልጅ ለሠምራ ጊዮርጊስ በሕግ አጋቧት"ይላል።( ገድለ ክርስቶስ ሠምራ ዘመስከረም -ቊጥር፮ )እግዚአብሔር በረድኤት ከሚገለጥባቸው የቅድስና መንገዶች አንዱ ቅዱስ ጋብቻ ነው። ✍️- ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ለሠምረ ጊዮርጊስ ፲፩ ልጆች ወለደችለት ከነዚህም መካከል ፱ ወንዶች፣ ፪ቱሴቶች ነበሩ።(ገድለ ክርስቶስ ሠምራ ዘመስከረም -ቊጥር- ፲፬) ልጆቿንም ሕገ እግዚአብሔርን እያስተማረች በክብርና በሥርዓት አሳደገቻቸው። ✍️- ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ የትዳሯ ሰላማዊነት፣የባሏ አክብሮትና ፍቅር፣የልጆቿ መብዛት ፣የሀብትና ንብረቷ መድለብ እየሠመረ ቢሄድም የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ልብ ግን የሚያስበው ግን ምናኔ ነበር።ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ፣ከዚያም በኋላ ልብሰ ምንኲስናዋን፣ ማለትም ቆቧን፣ ቀሚሷን፣ አጽፏን፣መታጠቂያዋን፣ አዘጋጀች። ✍️ ያልተለመደ ነገር ሲደረግ የተመለከቱት ቤተሰቦቿ ለምን እንደ ምታዘጋጀው ፣ለጠየቋት ጥያቄ " #ሃይማኖት ያስተማሩኝ አባቴ ልብስ አልቆባቸዋል፣ሲሉ ሰምቼ ለእርሳቸውም ነው የማዘጋጀው ፣"አለቻቸው።       ከዚህ ላይ ሃይማኖታዊ ጥበብ ያልተከሰተላቸው አስመሳዮች ለምን የሌላ ነው አለች" ሊሉ ይችላሉ።ይህ ሥርዓት ግን ለ፪ ነገር ይጠቅማል። ፩•የምናኔ ጉዞ ገና ሳይጀመር በውዳሴ ከንቱ ላለመጠለፍ፣ ፪•ይህን ርምጃዋን ዲያብሎስ በተለያዩ ሰዎች አድሮ ሊያደናቅፈው ስለሚችል ከዓላማዋ ሊገታት ስለሚችል መልካም ጥበብ ነው።በሌላ በኩል ልማደ መጻሕፍትም ነው። -✍️ ከዕለታት አንድ ቀን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ አገልጋዮችን " ወደ ቤተ ክርስቲያን እንሂድ" ብላ ይዛቸው ወደ ቤተ ክርስቲያን ሄደች ።የምናኔው መጀመሪያ ነበር። ✍️- ከዚያም ቤተ ክርስቲያን ጥቂት እንደምትቆይ ለቤተሰቦቿ አንዲት ፣ሠራተኛና አንድ ሕፃን ብቻ አስቀርታ ሌሎችን አሰናብታ ምናኔው ተጀመረ፣የወላድ መናኝ የሚያልፈውን በማያልፈው ዓለም ለመለወጥ ልጇን አዝላ እግሬ አውጭኝ ብላ ገሠገሠች።እግሮቿ በደም ታጠቡ፣የራስ ፀጒሯ ተላጭቶ ወደቀ።የገዳማውያን አለባበሷን ለብሳ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ገባች።ማቴ 10÷37 በተግባር ላይ ሲተረጎም ተመለከትን። ✍️የተጋድሎ ሕይወቷ እየቀጠለ ኼዶ ከመከራዋ ብዛት ከገድሏ ጽናት ሰውነቷ ተበሳስቶ የዓሣ መመላለሻ እስኪሆን ድረስ ከባሕሩ ገብታ ወደ ግራና ቀኝ ሳትል ፲፪ ዓመት ሙሉ በጣና ባሕር ውስጥ ቆማ ትጸልይ ዘንድ ኃይለ እግዚአብሔር ተሰጣት።፲፪ ዓመት ሙሉ በባሕር ውስጥ መቆየት የሚቻለው ማነው? የሚል ጎደሎ እምነት ያለው ወገን ካለ: ባሕረ ኤርትራ እንደ ግድግዳ ቆሞላቸው እስራኤላውያን ማሻገር ይችላሉ ወይ?" ለሚያምን ሁሉ ይቻላል"(ማር 9÷22) ✍️መሴ በሲና ተራራ 40መዓልትና 40 ሌሊት ያለምግብ መቆየት ይችላል ወይ?ሠለስቱ ደቂቅ እሳት ውስጥ ገብተው ሳይቃጠሉ መውጣት ይችላሉ ወይ? ብሎ መጽሐፍ ቅዱስን መጠየቁ የተሻለ ይሆናል። ✍️" ከአቤል ጀምሮ እስከ ዛሬ የሞቱት ከዛሬም በኋላ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ የሚሞቱትን አቤቱ ማራቸው ይቅርም በላቸው "አለችው ( ገድለ ክርስቶስ ሠምራ ዘግንቦት -ቊጥር፲፯ ) √ የአማላጅነት ጸጋዋ: የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ሕይወት የቅድስና ሕይወት በመሆኑ ለአማላጅነት የተመቸ ነው። ✍️ጌታ ምን አደርግልሽ ዘንድ ትሻለሽ? አላት ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ " አቤቱ ፈጣሪየ ሆይ ! ፈቃድህስ ቢሆን የአዳም ልጆችን ከሥቃይ ከኵነኔ ይድኑ ዘንድ ዲያብሎስን ይቅር ትለው ወይም ትምረው ዘንድ እለምንሃለሁ:የኃጥእን መመለሱን እንጂ የጥፋቱን አትወድምና አለችው ፣ የምለምንህ ወይም ማረው የምልህ ዲያብሎስን ወድጄው አይደለም ነገር ግን እሱ ከተማረ በአዳም ልጆች ላይ ሥቃይና ኵነኔ ሊኖር አይችልም ብየ በመገመት ነው እንጂ " ( ገድለ ክርስቶስ ሠምራ ዘግንቦት -ቊጥር36 -38 )ይህን ልመና ጌታችን የሚያስደንቅ ልመና ብሎታል።ይህ መልካም ሐሳብ የሚመነጨው የእምነት ፍቅር ካላቸው ሰዎች ልብ ውስጥ ብቻ ነው። - የዲያብሎስን ተንኮል የሚያውቅ መድኃኔዓለም የቅድስት ክርስቶስ ሠምራን የአማላጅነት ነጻነት አልገደበውም። √ የተሰጣት ቃል ኪዳን ✍"ሥጋሽን እንደ እናቴ እንደ ድንግል ማርያም ሥጋ እቀድሰዋለሁ" ማለት የእመቤታችን ሥጋ በኅሊና አምላክ የተቀደሰ ሲሆን የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ሥጋ ደግሞ በገድል ፣በትሩፋት ተቀጥቅጦ ማኅደረ መንፈስ ቅዱስ መሆኑን ያመልክታል።ነሐሴ 24 የዕረፍት መታሰቢያዋ ይከበራል።    በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ወርቃማዋ ፎገራ(The Golden lans scape of Fogera)  በደሴተ ጓንጉት ደብረ ምሕረት ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ክብረ በዓል ዓመታዊ በዓሏ በየዓመቱ ግንቦት ፲፪ ቀን በድምቀት ይከበራል፡፡ከወረታ ከተማ በስተ ምዕራብ በኩል  25 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ጣና ዳር ዋገጠራ ቀበሌ ትገኛለች ፡ - የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ  በረከቷ ፣ረድኤቷ ፣አማላጅነቷ አይለየን! #ምንጭ - ሐመር መጽሔት ግንቦት /ሰኔ 1997ዓ/ም - ነገረ ቅዱሳን -፪ ( ገጽ-68) - ገድለ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ(በትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት- 1992ዓ/ም ) - ልሳነ ተዋሕዶ ዘኦርቶዶክስ ሚያዝያ 7ቀን 1993 ቁ 53                መ/ር ተመስገን ዘገዬ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የገነተ ኢዩሱስ ገነተ ማርያም  ቤተ ክርሰቲያን ሰባኬ ወንጌል !

የይቅርታ እናት ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ! ✍️-የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ የተጋድሎ ታሪክ እንደ ባሕር አሸዋ፣እንደ ሰማይ ክዋከበት ተቆጥሮ ተሰፍሮ ከማያልቀው ነገረ ቅዱሳን መካከል አንዱ ነው። -ነገረ ቅዱሳንን መረዳት፣ማስረዳት ፣ማወቅና ማሳወቅም የወንጌልን አዝመራ መሰብሰብ ነው። - ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ በዚህ ዓለም ከከበሩ እግዚአብሔርን ከሚፈሩ ደጋግ ባልና ሚስት የተገኘችና የተመረጠች እናት ናት። ✍️የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ የአባቷ ስም ደራሳኒ፣የእናቷም ስም እሌኒ ይባላሉ። በሸዋ ክፍለ ሀገር በቡልጋ አውራጃ ጌየ በተባለች አካባቢ እንደ ተወለደች ታሪኳ ያስረዳል።(#ገድለ ክርስቶስ ሠምራ ዘወርኃ መስከረም -ቊጥር-፪ ) ደረሳኒ እና ዕሌኒ ልጃቸውን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራን በሃይማኖታዊና ሥነ-ምግባራዊ ሥርዓት አሳደጓት(ገድለ ክርስቶስ ሠምራ ዘመስከረም -ቊጥር፬ ) መጽሐፈ ገድሏ" ልጅቱ ክርስቶስ ሰምራ ባደገችና ዐቅመ ሔዋን በደረሰች ጊዜ የንጉሥ ባለሟል የሆነ••••የኢየሱስ ሞዓ ልጅ ለሠምራ ጊዮርጊስ በሕግ አጋቧት"ይላል።( ገድለ ክርስቶስ ሠምራ ዘመስከረም -ቊጥር፮ )እግዚአብሔር በረድኤት ከሚገለጥባቸው የቅድስና መንገዶች አንዱ ቅዱስ ጋብቻ ነው። ✍️- ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ለሠምረ ጊዮርጊስ ፲፩ ልጆች ወለደችለት ከነዚህም መካከል ፱ ወንዶች፣ ፪ቱሴቶች ነበሩ።(ገድለ ክርስቶስ ሠምራ ዘመስከረም -ቊጥር- ፲፬) ልጆቿንም ሕገ እግዚአብሔርን እያስተማረች በክብርና በሥርዓት አሳደገቻቸው። ✍️- ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ የትዳሯ ሰላማዊነት፣የባሏ አክብሮትና ፍቅር፣የልጆቿ መብዛት ፣የሀብትና ንብረቷ መድለብ እየሠመረ ቢሄድም የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ልብ ግን የሚያስበው ግን ምናኔ ነበር።ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ፣ከዚያም በኋላ ልብሰ ምንኲስናዋን፣ ማለትም ቆቧን፣ ቀሚሷን፣ አጽፏን፣መታጠቂያዋን፣ አዘጋጀች። ✍️ ያልተለመደ ነገር ሲደረግ የተመለከቱት ቤተሰቦቿ ለምን እንደ ምታዘጋጀው ፣ለጠየቋት ጥያቄ " #ሃይማኖት ያስተማሩኝ አባቴ ልብስ አልቆባቸዋል፣ሲሉ ሰምቼ ለእርሳቸውም ነው የማዘጋጀው ፣"አለቻቸው። ከዚህ ላይ ሃይማኖታዊ ጥበብ ያልተከሰተላቸው አስመሳዮች ለምን የሌላ ነው አለች" ሊሉ ይችላሉ።ይህ ሥርዓት ግን ለ፪ ነገር ይጠቅማል። ፩•የምናኔ ጉዞ ገና ሳይጀመር በውዳሴ ከንቱ ላለመጠለፍ፣ ፪•ይህን ርምጃዋን ዲያብሎስ በተለያዩ ሰዎች አድሮ ሊያደናቅፈው ስለሚችል ከዓላማዋ ሊገታት ስለሚችል መልካም ጥበብ ነው።በሌላ በኩል ልማደ መጻሕፍትም ነው። -✍️ ከዕለታት አንድ ቀን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ አገልጋዮችን " ወደ ቤተ ክርስቲያን እንሂድ" ብላ ይዛቸው ወደ ቤተ ክርስቲያን ሄደች ።የምናኔው መጀመሪያ ነበር። ✍️- ከዚያም ቤተ ክርስቲያን ጥቂት እንደምትቆይ ለቤተሰቦቿ አንዲት ፣ሠራተኛና አንድ ሕፃን ብቻ አስቀርታ ሌሎችን አሰናብታ ምናኔው ተጀመረ፣የወላድ መናኝ የሚያልፈውን በማያልፈው ዓለም ለመለወጥ ልጇን አዝላ እግሬ አውጭኝ ብላ ገሠገሠች።እግሮቿ በደም ታጠቡ፣የራስ ፀጒሯ ተላጭቶ ወደቀ።የገዳማውያን አለባበሷን ለብሳ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ገባች።ማቴ 10÷37 በተግባር ላይ ሲተረጎም ተመለከትን። ✍️የተጋድሎ ሕይወቷ እየቀጠለ ኼዶ ከመከራዋ ብዛት ከገድሏ ጽናት ሰውነቷ ተበሳስቶ የዓሣ መመላለሻ እስኪሆን ድረስ ከባሕሩ ገብታ ወደ ግራና ቀኝ ሳትል ፲፪ ዓመት ሙሉ በጣና ባሕር ውስጥ ቆማ ትጸልይ ዘንድ ኃይለ እግዚአብሔር ተሰጣት።፲፪ ዓመት ሙሉ በባሕር ውስጥ መቆየት የሚቻለው ማነው? የሚል ጎደሎ እምነት ያለው ወገን ካለ: ባሕረ ኤርትራ እንደ ግድግዳ ቆሞላቸው እስራኤላውያን ማሻገር ይችላሉ ወይ?" ለሚያምን ሁሉ ይቻላል"(ማር 9÷22) ✍️መሴ በሲና ተራራ 40መዓልትና 40 ሌሊት ያለምግብ መቆየት ይችላል ወይ?ሠለስቱ ደቂቅ እሳት ውስጥ ገብተው ሳይቃጠሉ መውጣት ይችላሉ ወይ? ብሎ መጽሐፍ ቅዱስን መጠየቁ የተሻለ ይሆናል። ✍️" ከአቤል ጀምሮ እስከ ዛሬ የሞቱት ከዛሬም በኋላ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ የሚሞቱትን አቤቱ ማራቸው ይቅርም በላቸው "አለችው ( ገድለ ክርስቶስ ሠምራ ዘግንቦት -ቊጥር፲፯ ) √ የአማላጅነት ጸጋዋ: የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ሕይወት የቅድስና ሕይወት በመሆኑ ለአማላጅነት የተመቸ ነው። ✍️ጌታ ምን አደርግልሽ ዘንድ ትሻለሽ? አላት ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ " አቤቱ ፈጣሪየ ሆይ ! ፈቃድህስ ቢሆን የአዳም ልጆችን ከሥቃይ ከኵነኔ ይድኑ ዘንድ ዲያብሎስን ይቅር ትለው ወይም ትምረው ዘንድ እለምንሃለሁ:የኃጥእን መመለሱን እንጂ የጥፋቱን አትወድምና አለችው ፣ የምለምንህ ወይም ማረው የምልህ ዲያብሎስን ወድጄው አይደለም ነገር ግን እሱ ከተማረ በአዳም ልጆች ላይ ሥቃይና ኵነኔ ሊኖር አይችልም ብየ በመገመት ነው እንጂ " ( ገድለ ክርስቶስ ሠምራ ዘግንቦት -ቊጥር36 -38 )ይህን ልመና ጌታችን የሚያስደንቅ ልመና ብሎታል።ይህ መልካም ሐሳብ የሚመነጨው የእምነት ፍቅር ካላቸው ሰዎች ልብ ውስጥ ብቻ ነው። - የዲያብሎስን ተንኮል የሚያውቅ መድኃኔዓለም የቅድስት ክርስቶስ ሠምራን የአማላጅነት ነጻነት አልገደበውም። √ የተሰጣት ቃል ኪዳን ✍"ሥጋሽን እንደ እናቴ እንደ ድንግል ማርያም ሥጋ እቀድሰዋለሁ" ማለት የእመቤታችን ሥጋ በኅሊና አምላክ የተቀደሰ ሲሆን የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ሥጋ ደግሞ በገድል ፣በትሩፋት ተቀጥቅጦ ማኅደረ መንፈስ ቅዱስ መሆኑን ያመልክታል።ነሐሴ 24 የዕረፍት መታሰቢያዋ ይከበራል። በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ወርቃማዋ ፎገራ(The Golden lans scape of Fogera) በደሴተ ጓንጉት ደብረ ምሕረት ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ክብረ በዓል ዓመታዊ በዓሏ በየዓመቱ ግንቦት ፲፪ ቀን በድምቀት ይከበራል፡፡ከወረታ ከተማ በስተ ምዕራብ በኩል 25 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ጣና ዳር ዋገጠራ ቀበሌ ትገኛለች ፡ - የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ በረከቷ ፣ረድኤቷ ፣አማላጅነቷ አይለየን! #ምንጭ - ሐመር መጽሔት ግንቦት /ሰኔ 1997ዓ/ም - ነገረ ቅዱሳን -፪ ( ገጽ-68) - ገድለ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ(በትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት- 1992ዓ/ም ) - ልሳነ ተዋሕዶ ዘኦርቶዶክስ ሚያዝያ 7ቀን 1993 ቁ 53 መ/ር ተመስገን ዘገዬ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የገነተ ኢዩሱስ ገነተ ማርያም ቤተ ክርሰቲያን ሰባኬ ወንጌል !

#ግንቦት_11 #ቅዱስ_ያሬድ_ካህን_ወማኅሌታይ ግንቦት ዐሥራ አንድ በዚህች ዕለት የሱራፌል አምሳላቸው የሆነ ኢትዮጵያዊው ማኅሌታይ ያሬድ የተሰወረበት ነው። ይህም ቅድስ ከአባ ጌዴዎን ዘመዶች ወገን ነው እርሱም በኢትዮጵያ አገር ከታነፁ አብያተ ክርስቲያን ለምትቀድም ከአክሱም ካህናት ውስጥ ነው እርሷም አስቀድሞ የክብር ባለቤት የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሃይማኖት በውስጥዋ የተሰበከና አምላክን በወለደች በእመቤታችን በከበረች ድንግል ማርያም ስም የከበረች ናት። ይህም አባ ጌዴዎን ትምህርትን ሊአስተምረው በጀመረ ጊዜ መቀበልም ማጥናትም እስከ ብዙ ዘመን ተሳነው። በአንዲት ዕለትም መምህሩ በእርሱ ላይ ተበሳጭቶ መትቶ አሳመመው። ያሬድም ሸሽቶ ከዱር ውስጥ ገባ ከኀዘኑም ብዛት የተነሣ ከዛፍ ሥር ተጠለለ። ወደ ዛፉ ላይም ትል ሲወጣ አየ ትሉም ከዛፉ እኩሌታ ደርሶ ይወድቅ ነበረ እንዲሁም ብዙ ጊዜ ከአደረገ በኋላ በጭንቅ ከዛፉ ላይ ወጣ። ቅዱስ ያሬድም የትሉን ትጋት በአየ ጊዜ ወደ መንፈሳዊ መምህሩ ተመልሶ አባቴ ሆይ ይቅርታ አድርግልኝና እንደ ወደድክ አድርገኝ አለው መምህሩም ተቀበለው። ከዚህ በኋላ በብዙ ልቅሶ ወደ እግዚአብሔር በለመነ ጊዜ ልቡናው ብሩህ ሆኖለት በአጭር ጊዜ የብሉይና የሐዲስ መጻሕፍትን ተምሮ ፈጸመ ዲቁናም ተሾመ። በዚያም ወራት እንደ ዛሬ በከፍተኛ ቃል የመዝሙር ማኅሌት የለም ነበር በትሑት እንጂ። እግዚአብሔርም መታሰቢያ ሊአቆምለት በወደደ ጊዜ ከኤዶም ገነት ሦስት አዕዋፍን ላከለት እነርሱም በሰው አንደበት ተናግረውት ወደ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ከእሳቸው ጋራ አወጡት በዚያም ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ የሚያመሰግኑበትን ማኅሌታቸውን ተማረ። ወደ አነዋወሩ ወደ ምድርም በተመለሰ ጊዜ በአክሱም ዳር ወደ ከበረች ቤተ ክርስቲያን በሦስት ሰዓት ገባ በታላቅም ቃል ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ የጽዮንም ደገኛዋ ሰማይን ፈጠረ። ዳግመኛም እንዴት እንደሚሠራት የድንኳንን አሠራር ለሙሴ አሳየው አስተማረው አለ። ይቺንም ምስጋና አርያም ብሎ ጠራት። የቃሉንም ድምፅ በሰሙ ጊዜ ንጉሡም ንግሥቲቱም ጳጳሱም ከካህናቱ ሁሉ ጋራ የመንግሥት ታላቆችና ሕዝቡ ሁሉ ወደርሱ ሮጡ ሲሰሙትም ዋሉ። ከዚያም በኋላ ከዓመት እስከ ዓመት በየክፈለ ዘመኑ በክረምትና በበጋ በመጸውና በጸደይ በአጽዋማትና በበዓላት በሰንበታትም እንዲሁም በመላእክት በዓል በነቢያትና በሐዋርያት በጻድቃንና በሰማዕታት በደናግልም በዓል የሚሆን አድርጎ በሦስቱ ዜማው ሠራ ይኸውም ግዕዝ ዕዝል አራራይ ነው። የሰው ንግግር የአዕዋፍ የእንስሳትና የአራዊት ጩኸት ከዚህ ከሦስቱ ዜማው አይወጣም። በአንዲት ዕለትም ቅዱስ ያሬድ ከንጉሥ ገብረ መስቀል እግር በታች ቁሞ ሲዘምር ንጉሡም የያሬድን ድምፅ እያዳመጠ ልቡ ተመሥጦ የብረት ዘንጉን በያሬድ እግር ላይ ተከለው ከእርሱም ደምና ውኃ ፈሰሰ። ያሬድም ማኅሌቱን እስከ ሚፈጽም አልተሰማውም። ንጉሡም አይቶ ደነገጠ በትሩንም ከእግሩ ላይ ነቀለ ስለ ፈሰሰው የደምህ ዋጋ የፈለግኸውን ለምነኝ ብሎ ለያሬድ ተናገረው ያሬድም ላትከለክለኝ ማልልኝ አለው። ንጉሥም በማለለት ጊዜ ወደገዳም ሔጄ እመነኲስ ዘንድ አሰናብተኝ አለው ንጉሡም ሰምቶ ከመኳንንቱ ጋራ እጅግ አዘነ ተከዘም እንዳይከለክለውም መሐላውን ፈራ እያዘነም አሰናበተው። ከዚህ በኋላም ቅዱስ ያሬድ ወደ ቤተክርስቲያን ገብቶ በታቦተ ጽዮን ፊት ቆሞ ፈጽሞ የከበረሽና የተመሰገንሽ ከፍ ከፍም ያልሽ የብርሃን መውጫ የሕይወት ማዕረግ የሆንሽ የሚለውን ምስጋና እስከ መጨረሻው በተናገረ ጊዜ ክንድ ያህል ከምድር ከፍ ከፍ አለ። ከዚህ በኋላ ወደ ሰሜን አገር ሒዶ በጾም በጸሎት ተወስኖ ሥጋውን እጅግ እያደከመ ኖሮ ገድሉን በዚያ ፈጸመ። እግዚአብሔር ስሙን ለሚጠራ መታሰቢያውን ለሚያደርግ ቃል ኪዳን ሰጥቶታል። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባታችን ያሬድ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። (#ስንክሳር_ዘወርኀ_ግንቦት)

"ባልና ሚስት እንደ እጅና እንደ ዓይን ሊሆኑ ይገባል፡፡ እጅ ሲጎዳ ዓይን ሊያለቅስ፥ ዓይን ሲያለቅስም እጅ እንባን ሊያብስ ይገባል፡፡" ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ