Abdu & Hasu
Open in Telegram
Abdulhak & Hasenet <የኢቅራእ ቢስሚ ረቢከ /አንብብ በጌታህ ስም/ ትውልዶች እንጂ ፣ የኢቅራእ /የአንብብ / ትውልዶች አይደለንም።> አላህ ያወቅነውን የምናሳውቅ ፣ ባወቅነው ደግሞ የምንጠቀም ያድርገን። አሚን!! For any comment ⇄ @ABDU_EMRE
Show more4 275
Subscribers
-224 hours
-337 days
-12130 days
Data loading in progress...
Similar Channels
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+1
in 0 channels
August '26
+21
in 0 channels
Get PRO
July '26
+29
in 0 channels
Get PRO
June '26
+25
in 1 channels
Get PRO
May '26
+56
in 2 channels
Get PRO
April '26
+81
in 0 channels
Get PRO
March '26
+18
in 0 channels
Get PRO
February '26
+17
in 0 channels
Get PRO
January '26
+22
in 0 channels
Get PRO
December '25
+10
in 0 channels
Get PRO
November '25
+29
in 0 channels
Get PRO
October '25
+23
in 0 channels
Get PRO
September '25
+37
in 1 channels
Get PRO
August '25
+95
in 0 channels
Get PRO
July '25
+170
in 0 channels
Get PRO
June '25
+44
in 0 channels
Get PRO
May '25
+83
in 0 channels
Get PRO
April '25
+42
in 0 channels
Get PRO
March '25
+322
in 0 channels
Get PRO
February '25
+137
in 0 channels
Get PRO
January '25
+325
in 0 channels
Get PRO
December '24
+344
in 0 channels
Get PRO
November '24
+495
in 1 channels
Get PRO
October '24
+621
in 0 channels
Get PRO
September '24
+657
in 0 channels
Get PRO
August '24
+1 431
in 0 channels
Get PRO
July '24
+989
in 1 channels
Get PRO
June '24
+1 097
in 0 channels
Get PRO
May '24
+1 162
in 3 channels
Get PRO
April '240
in 1 channels
Get PRO
March '24
+8
in 0 channels
Get PRO
February '24
+18
in 1 channels
Get PRO
January '24
+18
in 0 channels
Get PRO
December '23
+83
in 2 channels
Get PRO
November '23
+78
in 0 channels
Get PRO
October '23
+58
in 1 channels
Get PRO
September '23
+70
in 0 channels
Get PRO
August '23
+83
in 0 channels
Get PRO
July '23
+102
in 0 channels
Get PRO
June '23
+64
in 0 channels
Get PRO
May '23
+91
in 0 channels
Get PRO
April '23
+93
in 0 channels
Get PRO
March '23
+70
in 0 channels
Get PRO
February '23
+25
in 0 channels
Get PRO
January '23
+34
in 0 channels
Get PRO
December '22
+17
in 0 channels
Get PRO
November '22
+23
in 0 channels
Get PRO
October '22
+26
in 0 channels
Get PRO
September '22
+42
in 0 channels
Get PRO
August '22
+33
in 0 channels
Get PRO
July '22
+109
in 0 channels
Get PRO
June '22
+91
in 0 channels
Get PRO
May '22
+103
in 0 channels
Get PRO
April '22
+131
in 0 channels
Get PRO
March '22
+626
in 0 channels
Get PRO
February '22
+398
in 0 channels
Get PRO
January '22
+103
in 0 channels
Get PRO
December '21
+45
in 0 channels
Get PRO
November '21
+49
in 0 channels
Get PRO
October '21
+147
in 0 channels
Get PRO
September '21
+558
in 0 channels
Get PRO
August '21
+318
in 0 channels
Get PRO
July '21
+191
in 0 channels
Get PRO
June '21
+541
in 0 channels
Get PRO
May '21
+953
in 0 channels
Get PRO
April '21
+71
in 0 channels
Get PRO
March '21
+37
in 0 channels
Get PRO
February '21
+8
in 0 channels
Get PRO
January '21
+90
in 0 channels
Get PRO
December '20
+1 618
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 07 September | 0 | |||
| 06 September | 0 | |||
| 05 September | 0 | |||
| 04 September | 0 | |||
| 03 September | +1 | |||
| 02 September | 0 | |||
| 01 September | 0 |
Channel Posts
#የሰይዲና_ኸድር_ቅዳሜ
<ሹዐቡል ኢማን> በተሰኘው መፀሀፋቸው ኢማም አል-በይሀቂ፡ ሰይድና ኸድር እና ነብዩ ሙሳ ሲለያዩ ሰይዲ ኸድር ለሙሳ የመከሯቸውን ምክር ይገልፃሉ፦
«ሁልጊዜ ፈገግታን አሳይ፤ ያለ ምክንያት አትሳቅ።»
«ያለ ጥቅም አትቆጣ፤ ቁጣህ የአላህ ፍላጎት ብቻ ይሁን።»
«አስፈላጊ ካልሆነ በቀር አትጓዝ፤ አላህን ሳታስታውስ እና ሳትጠቅም አትቀመጥ።»
«ሰዎችን በጥቅማቸው እንጂ በስህተታቸው አትመዝናቸው። ሰዎችን ከምትወቅስ ይልቅ የራስህን ስህተት ለማረም ተጋል።»
«ዱንያን እንደ ድልድይ ቁጠራት፤ በእርሷ ላይ እለፍባት እንጂ አትገንባት። ልብህን ከቁሳቁስ ጋር አትሰር፤ ልቡ ከዱንያ ጋር የታሰረ ሰው አላህን የመፍራት ጥበብ ይሸሸዋል።»
«እውቀትን ለሰዎች ለማውራት ብቻ አትማር፤ ተግባር ላይ ለማዋል ተማረው። እውቀት ያለ ስራ እንደ ደረቅ ዛፍ ነው—ፍሬ አይሰጥም፣ ጥላም አይሆንም።»
«ምላስህን ካልጠበቅከው ልብህን ያበላሸዋል። ልቡ የተበላሸ ሰው ደግሞ የመንፈሳዊነትን ጣዕም ማወቅ አይችልም።»
*አላሁመ ሷሊ አላ ሩሂል ውጁድ፤ ወአላ ሰይዲና ኸድር!
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier
| 2 | #ለይለተል_ጁሙኣ
መካና መዲና በ19ኛው ክፍለ ዘመን (በ1800ዎቹ) በኦቶማን ኢምፓየር አስተዳደር ስር በነበሩበት ወቅት፣ በመካ የመውሊድ በዓል ዝግጅት የሚጀመረው ረቢዕ አል-አወል ወር እንደገባ ሲሆን፤ በ12ኛው ሌሊት የመካው አሚር (ሸሪፍ)፣ የኦቶማን አካባቢ አስተዳዳሪዎች፣ የሐረም ኢማሞች፣ ቃዲዎች (ዳኞች) እና ህዝቡ በሙሉ በመስጂደል ሐራም ይሰበሰባሉ። ከዒሻ ሶላት በኋላ ሁሉም በአንድ ላይ ሻማዎችን እና ፋኖሶችን በማብራት በቡድን ወደ ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) የልደት ቦታ ያመራሉ፤ ይህም ስነ-ስርዓት "መርከብ" በመባል ይታወቃል።
በወቅቱ በነቢዩ ልደት ቦታ ላይ በተገነባው ሕንፃ ውስጥ ታላላቅ ዑለሞች (ሊቃውንት) እና ቁርዓን ቀሪዎች ይቀመጣሉ። የነቢዩን አወላለድ፣ አስተዳደግ እና መልካም ጸባያት የሚያወሱ ድርሳናት (በተለይም የኢማም አል-በርዘንጂ የመውሊድ ኪታብ) በዜማ ይነበባሉ።
በበዓሉ ሌሊት እና በሚቀጥለው ቀን ለድሆች፣ ለሀጅ እና ዑምራ ተሳላሚዎች ከፍተኛ መጠን ያለው ምግብ፣ ስጋ እና ጣፋጮች ይ ታደሉ ነበር። ሀብታሞችና ነጋዴዎች ቤቶቻቸውን በማስጌጥ እንግዶችን ይጋብዙ ነበር።
በመዲና ደግሞ የአከባበሩ ማዕከል ቀጥታ መስጂድ አል-ነበዊ (የነቢዩ መስጊድ) ነበር።
በ12ኛው ሌሊት ከመግሪብ ሶላት በኋላ በነቢዩ መስጊድ ውስጥ የሚገኙት መብራቶችና ሻማዎች በሙሉ ይበራሉ። የመስጊዱ ወለል በጥሩ ምንጣፎች ይሸፈናል፤ የዑለሞች እና የሙሪዶች ክበብ (ሐልቃ) ይዘጋጃል።
በታዋቂ ቁርዓን ቀሪዎች ጣፋጭ ድምፅ ቁርዓን ከተቀራ በኋላ፣ የነቢዩን ውዳሴ የሚያነሱ መንዙማዎችና ሰለዋቶች በጋራ ይወርዳሉ። በተለይም የበርዘንጂ መውሊድ ሲነበብ የነቢዩን የልደት ወቅት የሚያታውሰው ክፍል ("መሃል አል-ቂያም") ሲደርስ ህዝቡ በሙሉ ለክብራቸው በመቆም ሰለዋት ያወርድ ነበር።
በኦቶማን ዘመን የነበሩት የሐረም ጠባቂዎች (አጋዎች) በበዓሉ ቀን ልዩ ባህላዊ አልባሳታቸውን ለብሰው ሰልፍ በመውጣት ለህዝቡ አጥርተው የተዘጋጁ እጣኖችን እና የኦሮንጅ አበባ ውኃ (ማእ ወርድ) ይረጩ ነበር።
የሁለቱም ከተሞች ጎዳናዎች፣ ሱቆች እና የመኖሪያ ቤቶች ደጃፍ በመብራቶችና በባንዲራዎች ይሸለሙ ነበር።
ህፃናት አዳዲስ ልብሶችን ይለብሳሉ፤ በየመንገዱ ጣፋጭ ምግቦችና መጠጦች በነፃ ይሰራጩ ነበር።
የበዓሉ ዕለት ከተማዋ ሙሉ በሙሉ በደስታ፣ በዚክር እና በሰለዋት ድምፅ ትሞላ ነበር።
የአባባ የጁሙኣ ሰለዋት ስጦታ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ وَعَلَى كُلِّ نَبِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا أَبِي بَكْرٍ وَعَلَى كُلِّ وَلِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا عُمَرَ وَعَلَى كُلِّ تَقِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا عُثْمَانَ وَعَلَى كُلِّ سَخِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا عَلِيٍّ وَعَلَى كُلِّ رَضِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا جِبْرِيلَ وَعَلَى كُلِّ مَلَكٍ (عَشْرَ مَرَّاتٍ).
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 129 |
| 3 | አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ መርከዙል ኢትቃን ኦላይን መድረሳ የ ቃኢደቱል ኑራንያ ደረስ የጨረሱ ውድ እና እንቁ ተማሪዎቹን በቀን 22 ማለትም ዛሬ ማታ እለተ ጁምዓ ከምሽቱ 2:30 ጀምሮ ተማሪዎቹን ስለሚያስመርቅ በ እለቱ እንዲገኙ እና የፕሮግራሙ ታዳሚ እንዲሆኑ በክብር ጠርተኖታል ።
የክብር ኡስታዞች
✅ኡስታዝ ሙዓዝ
✅ኡስታዝ አብዱል ፈታህ
✅ኡስታዝ አንዋር
✅ኡስታዝ አብዱ ረህማን
✅ኡስታዝ አቡ ሙጃሂድ
✅ኡስታዝ አቡ አብደሏህ
ይገኙበታል
ቦታ በኢሞ ቤታችን
ቀን ጁምዓ
ቀን ነሃሴ 22
ስአት ከምሽቱ 2:30
መርከዙል ኢትቃን ኦላይን የቂርአት ማዕከል
ከታች ባለው ሊንክ ወደ ኢሞ ቤታችን ጎራ በማለት ይህን ልዩ ፕሮግራም ትታደሙ ዘንድ በክብር ጠርተነዎታል
👇👇👇👇👇👇
We're talking about እነሆ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የቃኢዳቱ ኣልኑራኒያ ደርስ የእህቶቻቸን ምርቃን ዛሬ ማታ 2:30ሲል ይጀምራል🐪🐐🐐🐓🐓🔪. Click the link to join us! https://imo.onelink.me/RAdY?af_dp=imo%3A%2F%2Fbig_group%2F%3Fshare_id%3D_3p5fJJF2jLCppsH5O%26actionType%3Daction_type_voice_room%26shareFrom%3Dshare&af_web_dp=https%3A%2F%2Fimo.im&from=other
https://t.me/alif_jema | 4 |
| 4 | #የሰይዲና_ኸድር_ቅዳሜ
ከእለታት አንድ ቀን ሠይዲ አባራሙዝ ከተወሰኑ ሙሪዶች ጋር በተቀማመጡበት አንድ ገሪብ የሆነ ሰው ወደ ኸልዋ መጥቶ ገባ... ጌቶችን አውራድ እንዲሰጡት ጠየቀ.. እሳቸውም አሁን የምትለው ዚክር (አውራድ) የለህምን? ሲሉ ጠየቁት ... አለኝ አላቸው:: ምን ትላለህ? አሉት
<እኔ አንድ እላለው... አንተ አንድ ትላለህ... እኔ ያልኩት ይቀራል ...አንተ ያልከው ይሆናል::> ይህንን ነው የምለው አላቸው፤ በቃ እሱ ይበቃሀል አሉት::
ሰውዬው ተነስቶ ወጣ... ከአፍታ ቆይታ በኋላ ለሙሪዶቻቸው ያሁኑን ሰውዬ አውቃችሁታል? በማለት ሸኾች ጠየቁ ... አረ በፍፁም አላወቅነውም አሉ ፤ ሰይድና ኸድር ነው ሲሏቸው ለመዘየር ይሁን ለማየት እንጃ እየተራወጡ ፍለጋ ወጡ... ከመሀል አንዱ ፍለጋ የወጡ ሰዎችን ሁኔታ አይቶ "ሊዘይሩት የመጡለት እዚሁ አጠገባቸው እያለ ለመዘየር የመጣውን ፍለጋ ይወጣሉ?" ሲል ግርምታውን ተናገረ:: ፍለጋ የወጡ ሰዎችም በአራቱም አቅጣጫ ፈልገው አጥተውት ተመለሱ::
*አላሁመ ሷሊ አላ ሩሂል ውጁድ፤ ወአላ ሰይዲና ኸድር!
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 305 |
| 5 | #ለይለተል_ጁሙኣ
በታላቁ ነብይ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ውልደትና ታላቅነት ዙሪያ የተለያዩ ሊቃውንት የተናገሯቸው ንግግሮች፦
ኢማም አል-ቡሲሪ፦ "የነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ውልደት የላቀ መሆኑን ተፈጥሮአቸው ይመሰክራል፤ መጀመሪያቸውም ሆነ መጨረሻቸው በብርሃን የተዋበ ነው። ውልደታቸው ለዓለም ሁሉ የምስራች፣ የደስታና የእፎይታ ምንጭ ሆኖ መጣ።"
ሸይኽ አብዱልቃድር አል-ጂላኒ፦ "አላህ በመጀመሪያ የፈጠረው የነቢዩን (ሰ.ዐ.ወ) ብርሃን ነው። ያ ብርሃን የእውቀት፣ የእዝነትና የፍጥረታት ሁሉ መነሻ ነው። የሳቸው ወደዚች ምድር በሰው ልጅ ቅርጽ መምጣት ደግሞ አላህ ለፍጥረታቱ የለገሰው ትልቁ እዝነት ነው።"
ኢብኑ አጣኢላህ አል-እስከንደሪ፦ አላህ ለፍጥረታቱ ብዙ ጸጋዎችን ሰጥቷል፤ ነገር ግን በትልቁ ያነሳውና የመነዳበት ጸጋ የነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) መላክ ነው። ውልደታቸው የታሪክ አጋጣሚ ሳይሆን የፍጥረተ ዓለም የመንፈስ ህይወት የተበሰረበት ታላቅ ቀን ነው።"
መውላና ጃላሉዲን ሩሚ፦ "ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የፍቅርና የእዝነት ባህር ናቸው። የሳቸው ውልደት የዓለምን ጨለማ የበተነ፣ የልቦችን ዝገት ያጠራና ሰዎችን ወደ አላህ መንገድ የመራ ታላቅ የብርሃን ወጋገን ነው።"
ኢማም አሊይ አል-ሀበሺ፦ "የነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ውልደት በሰማይም በምድርም ታላቅ ደስታ የተበሰረበት ነው። ያ ቀን የረህመት በሮች የተከፈቱበት፣ የጨለማ መጋረጃዎች የተገፈፉበትና የፍቅር ብርሃን በዓለም ላይ የፈሰሰበት ልዩ ዕለት ነው።"
የአባባ የጁሙኣ ሰለዋት ስጦታ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ وَعَلَى كُلِّ نَبِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا أَبِي بَكْرٍ وَعَلَى كُلِّ وَلِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا عُمَرَ وَعَلَى كُلِّ تَقِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا عُثْمَانَ وَعَلَى كُلِّ سَخِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا عَلِيٍّ وَعَلَى كُلِّ رَضِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا جِبْرِيلَ وَعَلَى كُلِّ مَلَكٍ (عَشْرَ مَرَّاتٍ).
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 322 |
| 6 | ሼር የማድረግ ጥሪ/ቻሌንጅ
በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው አዲሱ የኢስላሚክ የስነልቦና አገልግሎት የሚሰጥ የቴሌግራም ቻናል ተከፈተ
- እውነተኛ የህይወት ታሪኮች
- የስነልቦና ምክሮች ፣ ጥያቄዎች እና አገልግሎቶችን ያገኛሉ።
- ስለ ኢስላማዊ ሳይኮሎጂ ይማራሉ።
ለሁሉም በማጋራት የሙስሊሙ ኡማ ጤና የሚጠበቅበትን ይህን ቻናል እናሳድግ
ለወዳጅ ዘመድ ማጋራት አይርሱ
join ለማለት 👇👇
https://t.me/usmanic_psychology | 54 |
| 7 | #መውላዬ
የዛሬዋ ቀን (ረቢዑል-አወል 6) በዓለማችን ታሪክ ውስጥ ትልቅ መንፈሳዊና ሥነ-ጽሑፋዊ አሻራ ያሳረፉት የመውላና ጀላሉዲን ሩሚ የልደት ቀን ናት። ሩሚ የተወለዱት በ604 ዓ.ሂ. በበልኽ ከተማ ሲሆን፣ ሩሚ መጀመሪያ ላይ የታወቁ የሸሪዐና የፊቅህ ሊቅ ነበሩ። ከሸምሰ-ተብሪዚ ጋር ያደረጉት ጉዞ ከደረቅ እውቀት ወደ ጥልቅ የመንፈስ ፍቅር ያሸጋገራቸው ትልቅ መታጠፊያ ሆነ። እውቀትን በልብ ፍቅር አምቀው ማቅረባቸው እስከ ዛሬ ድረስ ሕያው ያደርጋቸዋል።
° ሰዎችን በሃይማኖት፣ በቋንቋ ወይም በዘር አይለያዩም ነበር። በሥጋ የመጣን ማንኛውንም ሰው በፈጣሪ ፍቅርና እኩልነት ይመለከቱ ነበር፤ "ኑ! መንገድ የሳታችሁም ብትሆኑ ኑ!" የሚለው ጥሪያቸው የዚሁ ማረጋገጫ ነው።
° ታላቁ ሥራቸው "መስነቪ"፣ የሰውን ልጅ ውስጣዊ ስቃይ፣ ፍለጋና ተስፋ በጥበብ የሚተነትኑ ናቸው። ሕመምንና ስቃይን ሳይቀር ወደ ፈጣሪ መቃረቢያ መንገድ አድርገው ያሳያሉ።
«ከመጥፎና ከክፉ ነገሮች ባሻገር አንድ ትልቅ ሜዳ አለ... እዚያ እንገናኝ! ነፍስ እዚያ ሳር ላይ ስትጋደም፣ ዓለም ስለምታወራው ነገር ማሰብን ትተዋለች፤ ‘እኛ’ እና ‘እነሱ’ የሚሉት ቃላት እንኳ ትርጉም ያጣሉ።»
«ቁስልህ እኮ የመብራት ብርሃን ወደ አንተ የሚገባበት ቦታ ነው... አትዘን፤ የምታጣው ማንኛውም ነገር በሌላ መልክ ተመልሶ ይመጣልሃል፤ የምትፈልገው ነገር እኮ አንተንም እየፈለገህ ነው...>>
<ባሕር አይደለህም በአንድ ጠብታ ውስጥ ያለህ፣ አንተ ሙሉ ባሕር ነህ—በአንዲት ጠብታ ውስጥ የተሰወርክ! ትላንት ብልህ ነበርኩ — ዓለምን ለመለወጥ ሞከርኩ፤ ዛሬ ግን ጥበበኛ ነኝ—ራሴን መለወጥ ጀመርኩ።>
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 278 |
| 8 | #የዘመኑ_ንጉስ
አልሀምዱሊላህ ለዚህ ለተከበረው ወር ደርሰናል፤ በዚህ ወር የሰጠንን ስጦታ ቆጥረን አንጨርሰውም የስጦታው ሁሉ ስጦታ ካኢናቱን ሁሉ ለእርሳቸው ሲል ያስገኘላቸው ታላቁ ነብይ مُحَمَّد ﷺ የተወለዱበት ወር ነው
❤️የዛሬዋ ቀን ረቢዕ 3ደግሞ እጅግ ትልቅ ቀን ነው የብዙሀኑ የጉራጌ ህብረተሰብ ከመብረቅ አምልኮ ወጥቶ ወደ ዲነል ኢስላም ለመምጣት ሰበብ የሆኑት, ከጉራጌም አልፈው ለመላው ሀበሻ ብርሃን የሆኑት, ሲራቸውን ከኸለቃቸው ኻሊቃቸው ውጪ ማንም ያላወቀው የቃድሪያን ጦሪቃ ፍንትው አድርገው ያዛኸሩ ተከትብው የተያዙ 286 ኪታቦችን ለዑማው ያበረከቱ ቸር ለጋሹ ታላቁ የአብሬት ሸይህ ሸምሰዲነል አብሬትይ (አበል ራሙዝ ) ቀደሰሏሁ ሲረሁ የተወለዱበት ቀን ነው::
#አልሀምዱሊላህ
#ሸፈኣ_ያረሱለሏህ
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 271 |
| 9 | #ለይለተል_ጁሙኣ
ታላቁ መሪና የልብ ዐሪፍ አቡ ዐብዱል-ራህማን አል-ሱለሚ (ረሒመሁላህ) ከቀደሙት ዓሪፎች የዘገቡት አስደናቂ መንፈሳዊ ታሪክ፡
በአንድ ወቅት በበስራ ከተማ የሚኖሩ አንድ አቡበክር አል-ዋሲቲ የተባሉ ታላቅ አሪፍ ስለ ረቢዑል አወል ወር እና ስለ ጁሙኣ ምሽት ታላቅነት ሲያስተምሩ፣ አንድ ሙሪዳቸው እንዲህ ሲል ጠየቃቸው፡
"ሸይኼ ሆይ! የረቢዕ ወር የመንፈስ ጸደይ ነው፤ ለይለቱል ጁሙኣ ደግሞ የሳምንቱ ንግሥት ናት። እነዚህ ሁለቱ የተባረኩ ጊዜያት በአንድ ላይ ሲገናኙ መንፈሳዊ ሚስጥሩ ምንድን ነው?"
ሸይኹም ፈገግ ብለው እንዲህ ሲሉ መለሱለት፡
"በአንድ ወቅት ታላቁ አሪፍ ማዕሩፍ አል-ኸርኺ (ረሒመሁላህ) በሕልማቸው የነቢያት አለቃ የሆኑትን ነቢዩን (ሰ.ዐ.ወ) አዮቸው።ነቢዩም (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሏቸው፡ ‘ማዕሩፍ ሆይ! በአመቱ ውስጥ በፀደይ ወራት በምድር ላይ አበቦችና ለምለም ተክሎችን እንደሚፈኩ ሁሉ፣ በረቢዕ ወር የምትመጣው ለይለቱል ጁሙኣ ደግሞ በተኙት የአማኞች ልብ ውስጥ ያለውን የእዝነት እና የፍቅር ዘር ታነቃቃለች። በዚህች ምሽት አንድ ሰው እጁን ወደ ሰማይ ዘርግቶ በኔ ላይ ሶለዋት አውርዶ፣ «አላህ ሆይ! በሐቢብህ (በወዳጅህ) መወለድ ወር እና በዚች በለይለቱል ጁሙኣ እዝነትህ ልቤን አዲስ አድርግልኝ» ብሎ የጠየቀ እንደሆነ፤ አላህ ያንን ልብ በጭራሽ አይመልሰውም፤ የደረቀችውንም መንፈሱን እንደ እንደ ጸደይ ያለመልማታል’ አሉት።"
የአባባ የጁሙኣ ሰለዋት ስጦታ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ وَعَلَى كُلِّ نَبِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا أَبِي بَكْرٍ وَعَلَى كُلِّ وَلِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا عُمَرَ وَعَلَى كُلِّ تَقِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا عُثْمَانَ وَعَلَى كُلِّ سَخِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا عَلِيٍّ وَعَلَى كُلِّ رَضِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا جِبْرِيلَ وَعَلَى كُلِّ مَلَكٍ (عَشْرَ مَرَّاتٍ).
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 407 |
| 10 | #የሽግግር_ዘመን!
ታላቁ ሱልጣን ሰላሃዲን አዩቢ ቁድስን ከመስቀላውያን እጅ ነፃ ለማውጣት በሚዘጋጅበት ወቅት፣ በዙሪያው ያሉ በርካታ ተፎካካሪ መንግስታት፣ የውስጥ ክፍፍሎች እና የመስቀላውያን ጠንካራ ምሽጎች ትልቅ ስነ-ልቦናዊና ፖለቲካዊ ጫና ፈጥረውበት ነበር። በወቅቱ ሰላሃዲን ሌሊቱን ሙሉ በሶላት፣ በዱዓ እና በዕቅድ ያሳልፍ ነበር። በአንድ የሰኞ መዳረሻ ሌሊት እንቅልፍ ሲወስደው የሚከተለውን ታላቅ መናም አየ፡ በሕልሙ በታላቁ የአል-አቅሷ መስጂድ ግቢ ነቢዩ ሙሐመድ ሰ.ዐ.ወ) ከሶሃቦቻቸው ከሚወዳቸው ሰይዲ ጀይላኒ ጋር ተቀማምጠው ያያል፤ ሰላሃዲን ወደ ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ቀርቦ ሰላምታ ሲያቀርብ፣ ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) በፈገግታ ተቀብለው የአል-አቅሷን መስጂድ ቁልፍ በእጁ ያኖሩበታል። “ያ ሳላሃዲን! አላህ ይህንን የተቀደሰ ቦታ በእጅህ ነፃ ያወጣዋል፤ የፅናትና የፍትህ ሰው ሁን” የሚል መልእክትና ማበሰሪያ (ቡሽራ) ሰጡት።
*እነሆ በዛሬዋ ቀን በሰፈር 27 589 ሂጅራ የዛሬ 860 አመት ነበር እኚህ ታላቅ መሪ የተሻገሩት። አል-ፋቲሃ
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 402 |
| 11 | ወልቂጤ፣ ከአዲስ-አበባ 150 ኪ.ሜ ያህል ትርቃለች። ለተከታታይ ትውልድ ምንጭ ሆኖ ያገለገለውን፣ የቃጥባሬ ማዕከልን አቅፋ ይዛለች። ቃጥባሬ፣ የሼህ ዒሳ ሁላዊ ግምዳይ፣ የልህቀታቸው አደባባይ። እርሳቸው ታላቅ ተምሳሌት፣ ዕውቅ ሙቀረብ፣ ደሚቅ ሊቅ፣ የጀግንነት ምልክት፣ የአያሌ ተዓምራት ቁንጮ፣ የደግነት አምባ፣ የመልካምነት ጉልላት፣ ሊቀ-ሊቃውንት - የቃጥባሬ ታዛ፣ ደማሙ ሼህ ዒሳ ሀምዛ። የትውልዶች መሪ፣ የሊቃውንት አስተማሪ፣ የምዕመናን አስከባሪ፣ የማህበረሳባን አቅኝ፣ በተለይም በዘመናቸው በጉራጌ የገነኑ በርካታውን ጠርበው እያስተካከሉ፣ ከፈሰሱበት እያቃኑ የመሩ፣ ሰበ-አዊ ብርሀን ናቸው። የድንቅ ታሪክ ባለቤት፣ የሀገር አባት፣ የማንነት ቁጥራት፣ የዕውቀትና የስልጣኔ መነሻና ድራሾት ነበሩ።
ሼኽ ዒሳ-ቃጥባሬ ከሼኽ አህመደ-ዳንይ ምሩቃኖች መካከል ተጠቃሹ ናቸው።
በመሀል አዲስ አበባ የመጀመሪያውን መስጂድ፣ ኑር መስጂድ (አሁን በኒን) ታግለውና ህዝቡን አስተባብረው ያሠሩ ሼኽ ዒሳ ነበሩ።
የቃጥባሬ ሸይኽ የሆኑት ሸይኽ ኢሳ ሀምዛ ማህበረሰቡ ወደ አላህ (ሱብሐነሁ ወተዐላ) እንዲቀርብ የነብያችን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ፍቅር እንዲኖረው በዲን ጉዳይ እንዲመካከር ካበጁዋቸው መገናኛ መንገዶች አንዱ ሳምንታዊው የኢስነይን ፕሮግራም ነው።
በመቃመ ኸድር ደረጃ ላይ ያለ ሰው የሚያገኘው እውቀት በድካም ወይም በንባብ የሚገኝ ሳይሆን፣ «ወዐለምናሁ ሚን ለዱና ዒልማ» (ከእኛ ዘንድ የሆነን እውቀት አስተማርነው) በሚለው የቁርኣን አንቀጽ መሠረት የሚሰጥ ነው። ኢማም ጋዛሊ እንደሚሉት፣ ይህ እውቀት እንደ ምንጭ ውሃ ከልብ ውስጥ የሚፈልቅ እንጂ እንደ ኩሬ ከውጭ የሚቀዳ አይደለም።
በዚህ ማዕረግ የተጎናጸፉ አውሊያኦች ከሰይድና ኸድር የሚወርሱት ሌላው ባህሪ «ጠይዩል አርድ» (ርቀትና ቦታ የመታጠፍ/የመቀነስ ምስጢር) ነው። በአንድ ጊዜ በበርካታ ቦታዎች መገኘት ወይም ረጅም መንገድን በቅጽበት ማቋረጥ የመቃመ ኸድር ቁሳዊ እና መንፈሳዊ መገለጫ ተደርጎ ይወሰዳል።
በመቃመ ኸድር ያለ መንፈሳዊ ሰው በአላህ ፈቃድ በሰው ልጅ ሕይወት፣ በችግሮች እና በክስተቶች ውስጥ ምስጢራዊ ማስተካከያ የማድረግ (ተስሪፍ) አቅም ይሰጠዋል። ለምሳሌ የኸድር መርከቧን መብሳት ወይም የወጣቱን ህይወት ማለፍ በወቅቱ አስከፊ ቢመስልም፣ ወደፊት የሚመጣን ትልቅ መከራ ለመታደግ የተደረገ መንፈሳዊ ጣልቃ ገብነት ነበር።
ያ መውላ ሰሊ ወሰለም አላ ሙሐመድ፤ ወከዛ አላ ሰይድና ኸድር!
#ዱስቱር_ያ_ቃጥባሪዩ
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 400 |
| 12 | #ለይለተል_ጁሙኣ
በሐዲስ እንደተገለጸው፦ "ፀሐይ ከወጣችባቸው ቀናት ሁሉ በላጯ ቀን የጁሙዓ ቀን ናት፤ አደም የተፈጠረው፣ ወደ ጀነት የገበውና ከጀነት የወጣው በዚህች ቀን ነው"። ሊቃውንት የእነዚህን ሁነቶች ምስጢር እንዲህ ይፈታሉ፦
የፍጥረት መፈጸሚያ (አክመሉል-ወጁድ)፦ አላህ ፍጥረታትን በሙሉ አዘጋጅቶ ካጠናቀቀ በኋላ፣ የፍጥረት ሁሉ ዘውድና መገለጫ የሆኑትን አባታችን አደምን በጁሙዓ ቀን ፈጠራቸው። ስለዚህ ጁሙዓ የሰው ልጅ ክብር የተገለጸበት ቀን ናት።
የ"ሩሕ" (የመንፈስ) መነፋት ምስጢር፦ አላህ ከአፈር ለበጀበጀው የአደም አካል መለኮታዊውን መንፈስ (ሩሕ) የነፋበት ቀን በመሆኑ፣ የጁሙዓ ምሽትና ቀን የሰው ልጅ የመንፈስ ሕይወት ያገኘበት ታላቅ ጊዜ ነው።
የጀነትና የምድር ተልዕኮ (ኺላፋ)፦ አላህ አደምን በጀነት እንዲሁም ከዚያ ቡኃላ በምድር ላይ "ኸሊፋ" (አስተዳዳሪ) አድርጎ የመደበበትና የሰው ልጅ ምድራዊ ተልዕኮ የጀመረበት ታላቅ ምስጢር ነው።
የብርሃን አደራ (አል-አማና)፦ አላህ አደምን ሲፈጥረው በግንባሩ ላይ የነቢዩን ሙሐመድ (ሶ.ዐ.ወ) ብርሃን (ኑረ-ሙሐመዲ) አስቀምጦ ነበር። መላእክት ለአደም ሱጁድ ያደረጉት ይህንኑ መለኮታዊ ብርሃን በግንባሩ ላይ በመመልከታቸው ነው። ይህ ታላቅ ክስተት የተፈጸመው በጁሙዓ ቀን ነው።
የአደም ተውበት (ንሰሐ) ተቀባይነት ማግኘት፦ አባታችን አደም ተውበት አድርጎ ወደ ፈጣሪው ሲመለስ፣ አላህ ንሰሐውን ተቀብሎ የምህረት መጋረጃውን ያነሳለት በዚሁ በጁሙዓ ቀን ነበር። ስለዚህ ለይለተል ጁሙዓ የንሰሐና የዕርቅ ምሽት ናት።
የዓለማት ስብሰባ (ጁሙዐ - መሰብሰብ)፦ "ጁሙዐ" የሚለው ቃል "ጀመዐ" (ሰበሰበ) ከሚለው ግስ የተወሰደ ሲሆን፣ ቁሳዊውና መንፈሳዊው ዓለም፣ አካልና መንፈስ፣ እንዲሁም አደም እና ሐዋእ የተገናኙበትና የተሰበሰቡበትን ምስጢር ይዟል።
የቂያማ ቀን መቆም፦ የፍጥረት መጀመርያ በጁሙዓ እንደሆነ ሁሉ፣ የዚህ ዓለም ፍጻሜና የሰዎች በሙሉ ለፍርድ የመሰብሰቢያ ቀን (ቂያማ) የሚቆመው በጁሙዓ ቀን ነው።
ለይለተል ጁሙዓ እና ቀን የአባታችን አደም የመፈጠሪያ፣ የመንፈስ ማገኛ፣ የንሰሐ መቀበያ እና የሰው ልጅ የምድር ንጉሥ (ኸሊፋ) ሆኖ የተሾመበት ታላቅ መለኮታዊ የምስጢራት ማዕከል ናት።
የአባባ የጁሙኣ ሰለዋት ስጦታ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ، صَلَاةً تَرْزُقُنَا بِهَا الْخُلُقَ النَّفِيسَ، يَا رَحْمَانُ يَا قُدُّوسُ!
አላሁመ ሷሊ ወሰሊም አላ ሰይዲና ሙሀመድ፤ ወአላ አሊ ሰይዲና ሙሀመድ ሷላተን ተርዙቁና ቢሃል ኹሉቀ ነፊስ ያረህማኑ ያቁዱስ!
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 354 |
| 13 | #የሰይዲና_ኸድር_ቅዳሜ
ታላቁ የሐዲስ ሊቅ ኢማም ኢብኑ ሐጀር አል-ዐስቀላኒ (የ"ፈትሑል ባሪ" ደራሲ) ገና በወጣትነታቸው በዒልም እና በመንፈሳዊ ናፍቆት ውስጥ እያሉ፣ ሰይድና ኸድርን ለማየት እና ከእሳቸው በረከት ለመቀበል ጥልቅ ፍላጎትና ናፍቆት ነበራቸው።
አንድ ቀን በካይሮ መስጂድ ውስጥ ሁልጊዜ የሚቀመጡበት ቦታ ላይ በናፍቆት ተከዝ ብለው ሳሉ፣ አንድ የማያውቁት በእድሜ የገፉ አዛውንት መጥተው ከጎናቸው ተቀመጡ።
አዛውንቱ የኢማም ኢብኑ ሐጀርን የልብ ናፍቆት በማወቅ፦ "እኔን ማየት ትናፍቅ አልነበረም?" ብለው ጠየቋቸው።
ኢማም ኢብኑ ሐጀርም ደንግጠው አዩአቸው። ሰይድና ኸድርም የመንፈሳዊ ዒልምና የበረከት ዱዓ ካደረጉላቸው በኋላ፣ "ፍላጎትህ እና ናፍቆትህ እውነተኛ ስለነበር አላህ ወደ አንተ ላከኝ።" ከዚያች ቀን በኋላ የኢማም ኢብኑ ሐጀር የሐዲስና የመረዳት አቅም እጅግ እንደጨመረ ይነገራል።
ሰይድ አቡል ሐሰን ሻዚሊ በመንፈሳዊ ጉዞአቸው መጀመሪያ ላይ ለረጅም ጊዜ በብቸኝነት ተራራ ላይ በመሆን አላህን በመገዛትና ሰይድና ኸድርን ለመገናኘት በጥልቅ ናፍቆት ያሳልፉ ነበር።
አንድ ቀን በተራራው ላይ ሳሉ ሰይድና ኸድር በድንገት ተገለጡላቸውና እንዲህ አሏቸው፦ "አቡል ሐሰን ሆይ! እኔን ፍለጋ እና ናፍቆት ለምን በተራራ ላይ ትቸገራለህ? ወደ ከተማ ተመለስና ከሰዎች ጋር እየኖርክ ሰዎችን ወደ አላህ ምራ። እውነተኛ ናፍቆት አላህን እና ነቢዩን (ﷺ) ማፍቀር ነው፤ እኔ ደግሞ ያን ጊዜ ሁልጊዜ ከጎንህ እሆናለሁ" በማለት የልባቸውን ናፍቆት ወደ አላህ ፍቅር በመቀየር ትልቅ የመንፈሳዊ መሪነት መንገድ አሳይተዋቸዋል።
*አላሁመ ሷሊ ወሰሊም አላ መርከዚል አንቢያዕ ወል አውሊያዕ!
*አላሁመ ሷሊ አላ ሰይዲና ኸድር!
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 375 |
| 14 | #ለይለተል_ጁሙኣ
ኢማም ቡሰይሪ በሕይወት ዘመናቸው ሙሉ ልባቸው የሚመታው ለመዲናና ለነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) ረውዳ ነበር።
«አሚን ተዘኩሪ ጂራኒን ቢዚ-ሰለሚ...»
"(በዚ-ሰለም/በመዲና ያሉትን ጎረቤቶች [ነቢዩን] በማስታወስ ነውን እምባህ ከደም ጋር ተቀላቅሎ የሚፈሰው?)"
የሚለው ስንኛቸው የተጻፈው መዲናንና ረሱልን (ሶ.ዐ.ወ) እጅግ ከመናፈቃቸው የተነሳ እንቅልፍ አጥተውና ከስተው በነበረበት ወቅት እንደነበር ይነገራል። በመጨረሻም አላህ መንገዱን አገራላቸውና ወደ መካ ለሐጅ፣ ከዚያም ወደ መዲና አል-ሙነወራ ለዚያራ ተጓዙ።
መዲና ከተማ አቅራቢያ ሲደርሱና የነቢዩን (ሶ.ዐ.ወ) መስጂድ ጉልላት (ቁበተል ኸድራእ) ከሩቅ ሲመለከቱ፣ ከፈረሳቸው ላይ ወርደው «የነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) እግር በረገጠበት አፈር ላይ እኔ በጫማ አልሄድም» በማለት በባዶ እግራቸው፣ እምባቸው እየፈሰሰ ወደ መስጂዱ ገቡ።
ወደ ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) መቃብር (ረውዳ) ተጠግተው በፍጹም ትህትናና ግርማ ቆሙ። በዚያም ሰላምታ ካቀረቡ በኋላ፣ ለነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) ያዘጋጇቸውን የመድሕ ስንኞች በቅንነት ማቅረብ ጀመሩ። በወቅቱ አብረዋቸው የነበሩ ተጓዦች እንደሚተርኩት፦
*ኢማም አል-ቡሲሪ ግጥማቸውን እያነበቡ ሳለ፣ በረውዳው አካባቢ እጅግ ውብና ታላቅ የሆነ መልካም ሽታ አካባቢውን ሞላው።
ከዛም አንድ የመዲና አሊም የሚያወድሰው በምን ዓይነት ቃላትና ስንኝ ነው?» ብሎ ሊፈትናቸውና ሊያያቸው ወደ መስጂዱ ይመጣል። ያ አሊም ወደ ቡሰይሪ ተጠግቶ፡
«ቡሰይሪ ሆይ! የነቢዩን (ሶ.ዐ.ወ) ማዕረግና ደረጃ በግጥምህ ለመግለጽ ትሞክራለህ፤ የሰው ልጅ ብዕርና ቃላት የሳቸውን ታላቅነት ሙሉ በሙሉ ሊገልጹ ይችላሉ ብለህ ታምናለህ?»* ሲል ጠየቃቸው።
ሰይዲ-ቡሰይሪ ዓይኖቻቸው በእምባ ተሞልተው ወደ ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) ረውዳ እያዩ እንዲህ ሲሉ መለሱለት፦
«በአላህ ይሁንብኝ! እኔ ያቀናኋቸው ግጥሞችና የተናገርኳቸው ቃላት የነቢዩን (ሶ.ዐ.ወ) ደረጃ የገለጹ ሳይሆን፣ እኔንና ብዕሬን የከበሩ ያደረጉ ናቸው! የሰው ልጅ ቃላት የረሱልን (ሶ.ዐ.ወ) ታላቅነት ሊጨርሱ አይችሉም!»
ከዚያም በረውዳው ፊት ሆነው ታዋቂውን ስንኛቸውን አሰሙ፦
«ወከይፈ ቱድሪኩ ፊድ-ዱንያ ሐቂቀተሁ... ቀውሙን ኒያሙን ተሰሉ ዐንሁ ቢል-ሐሉሚ...»
*(በዚህች ዓለም ያሉ ሰዎች በሕልምና በምናብ እንጂ የነቢዩን (ሶ.ዐ.ወ) ጥልቅ እውነታና ደረጃ እንዴት ሙሉ በሙሉ ሊረዱ ይችላሉ?!)
በመዲና በቆዩበት ወቅት በጁሙኣ ሌሊት፣ ኢማሙ በነቢዩ መስጂድ አቅራቢያ ተኝተው ሳለ በሕልማቸው ነቢዩን (ሰ.ዐ.ወ) አዩአቸው፤ እንዲህ አሏቸው፦
«ቡሰይሪ ሆይ! ወደ እኔ በመምጣትህና በፍቅርህ አጋጣሚ ደስ ብሎኛል። የጻፍካቸው ግጥሞችና ያቀረብከው መድሕ በአላህ ዘንድ የተወደደ ነው፤ እኔም ለአንተ ያለኝን ወዳጅነት አረጋግጥልሃለሁ!»
*አንድ ሰው በፍጹም ልቡና በፍቅር ሲጓዝ፣ አላህ መንገዱን በረካና እረፍት ያደርግለታል።
የአበባ የጁሙኣ ሰለዋት ስጦታ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ وَعَلَى كُلِّ نَبِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا أَبِي بَكْرٍ وَعَلَى كُلِّ وَلِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا عُمَرَ وَعَلَى كُلِّ تَقِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا عُثْمَانَ وَعَلَى كُلِّ سَخِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا عَلِيٍّ وَعَلَى كُلِّ رَضِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا جِبْرِيلَ وَعَلَى كُلِّ مَلَكٍ (عَشْرَ مَرَّاتٍ).
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 402 |
| 15 | #የሰይዲና_ኸድር_ቅዳሜ
አንድ ታላቅ ዓሊም በባህር ዳርቻ ላይ እየተንሸራሸረ ሳለ፣ በልቡ ውስጥ፦ "እኔ ያልተማርኩትና የማላውቀው የእስልምና ዕውቀት ይኖር ይሆን?" የሚል የኩራት ሀሳብ መጣበት።
በዚያ ቅጽበት፣ አሳ አጥማጅ መስለው በባህሩ ዳርቻ ላይ የተቀመጡት ሰይድና ኸድር ዓሊሙን ሰው ጠርተው፦ "ሸይኻችን ሆይ! እስኪ ወደዚህ ባህር ተመልከት፤ ምን ታያለህ?" አለው።
ዓሊሙም በታበየ ድምፅ፦ "እጅግ በጣም ሰፊና ጥልቅ የሆነ ባህር አያለሁ" ሲል መለሰ። በዚያው ቅጽበት፣ አንዲት ትንሽ ወፍ በርራ መጥታ በባህሩ ዳርቻ ላይ አረፈች። ወፏም አፉን ወደ ባህሩ ውኃ አቅርባ *አንድ ጠብታ ውኃ* በአፏ ቆንጥራ በመያዝ ወደ ሰማይ በረረች።
ሰይድና ኸድርም (ዐ.ሰ) ወደ ዓሊሙ ዘወር ብለው እንዲህ አሉት፦
"ይህች ወፍ ከአስደናቂውና ከሰፊው ባህር የወሰደቻትን ያችን አንዲት ትንሽ ጠብታ ውኃ አየሃት?"
ዓሊሙም፦ "አዎ አየኋት" አለ።
ሰይድና ኸድርም ቀጥለው እንዲህ አሉት፦ "አንተ የተማርከው ዕውቀት፣ የዓለም ዑለማኦችና የሰው ልጆች በሙሉ የሚያውቁት ዕውቀት ተደምሮ፣ እንዲሁም የነብያት ዕውቀት ተደባልቆ ሲወሰድ... ከዚህ ታላቅ የባህር ውኃ አንጻር ሲነጻጸር ያች ወፍ በአፏ የያዘቻትን *አንዲት ጠብታ ውኃ* እንኳን አይሞላም! የመለኮት (የአላህ) ዕውቀት ደግሞ እንደዚህ ወሰን የሌለው ባህር ነው! ታዲያ ሰው በያዛት ትንሽ ጠብታ ዕውቀት እንዴት ይኮራል?"
*አላሁመ ሷሊ ወሰሊም አላ መርከዚል አንቢያዕ ወል አውሊያዕ!
*አላሁመ ሷሊ አላ ሰይዲና ኸድር!
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 434 |
| 16 | #ለይለተል_ጁሙኣ
ሱልጣኑል አሪፊን አቡ ያዚድ አል-ቡስጣሚ፣ በጁሙኣ ለይል ዚክር ላይ እያሉ ያዩትን ሰፊ የከሽፍ ገለጣ በሰፊው ይተርካሉ።
"በአንድ ሌሊት ልቤ ከዱንያ ግድግዳ ተላቆ ወደ ሰማያውያኑ ዓለም ወጣ። በመጀመሪያው ሰማይ ውስጥ የሚዘክሩ የመላእክት ሀድራ ተገለጠልኝ። መላእክቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰፍ ሠርተው በታላቅ ድምፅ አላህን ያወድሱ ነበር። የዚያን ሀድራ ብርሃን ስመለከት ነፍሴ በመንፈሳዊ ፍቅር (እሽቅ) ተሞላች። መላእክቱ ወደ እኔ ዘወር ብለው 'ያ አቡ ያዚድ! ወደ እኛ ሀድራ ተቀላቀል' አሉኝ። እኔ ግን ወደ አላህ ፍጹም ቅርበት እንጂ ሌላ አልሻምና ወደ ላይኛው ሰማይ ቀጠልኩ። በእያንዳንዱ ሰማይ ውስጥ የተለያዩ የመላእክት ሀድራዎች ነበሩ—አንዳንዶቹ ከተፈጠሩ ጀምሮ በሱጁድ ላይ ያሉ፣ አንዳንዶቹ በሩኩዕ ላይ ያሉ፣ አንዳንዶቹ ደግሞ 'ሱብሐነል-መሊኪል-ቁዱስ' እያሉ በብርሃን ክንፎቻቸው ሰማዩን የሞሉ ነበሩ። በዚያች ሌሊት የመላእክት ሀድራና የአላህ ጥበብ ሰፊነት በልቤ ላይ እንደ ባሕር ፈሰሰ።"
ታላቁ የግብፅ አሪፍ ኢማም ዐብደልወሐብ ሸዕራኒ፣ ስለ መምህራቸው ስለ ሸይኽ ዐሊይ አል-ኻዋስ በሌሊት ሀድራ ያዩትን ታሪክ ያወሳሉ፦
በአንድ የጁሙኣ ለይል፣ ሸይኽ ዐሊይ አል-ኻዋስ በታላቅ የዚክር ስብስብ ላይ እያሉ ድንገት ሳቅ አሉ። ሀድራው ሲያልቅ ኢማም ሸዕራኒ «የተከበሩ! በዚክሩ መካከል ያስቀዎት ወይም የተገለጠልዎት ነገር ምንድን ነው?» ብለው ጠየቋቸው።
ሸይኽ ዐሊይ አል-ኻዋስ እንዲህ አሏቸው፦
"በዚክሩ መካከል የከሽፍ መጋረጃ ተነሳልኝ። በዚያን ጊዜ በሰማይ ያሉ መላእክት የእኛን የዚክር ሀድራ ከበው ሲወርዱ አየሁ። ከመካከላቸው አንዱ ታላቅ መልአክ ወደ ሀድራችን ሲወርድ፣ በምድር ላይ ያለ አንድ ትንሽ ትንኝ በሰዎቹ መካከል ስትሄድ አየ። መልአኩ ያችን ትንሽ ፍጡር ላለመጨፍለቅ ሲል ክንፉን ሰብስቦ በአደብና ጥንቃቄ በሀድራችን ዙሪያ ሲቀመጥ አየሁት። የመላእክቱ ትህትናና ለአላህ ዚክርና ፍጡራን ያላቸው ማክበር አስደንቆኝና አስደስቶኝ ነው የሳቅሁት።"
ሩሚ እንዲህ ይላሉ፦ "በሌሊት ጸጥታ ውስጥ ትልቅ ድምፅ አለ፤ የሥጋ ዓይንህን ጨፍነህ የልብህን ዓይነ-መንፈስ ብትከፍት፣ ሰማያት በሙሉ በመላእክት መዝሙርና ዚክር ሲንቀጠቀጡ ታያለህ።"
የአባባ የጁሙኣ ሰለዋት ስጦታ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ، صَلَاةً تَرْزُقُنَا بِهَا الْخُلُقَ النَّفِيسَ، يَا رَحْمَانُ يَا قُدُّوسُ!
አላሁመ ሷሊ ወሰሊም አላ ሰይዲና ሙሀመድ፤ ወአላ አሊ ሰይዲና ሙሀመድ ሷላተን ተርዙቁና ቢሃል ኹሉቀ ነፊስ ያረህማኑ ያቁዱስ!
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 425 |
| 17 | #የሰይዲና_ኸድር_ቅዳሜ
ታላቁ የፋርስ ገጣሚ ሃፊዝ ሺራዚ ገና ወጣት ሳለ በሺራዝ ከተማ ውስጥ በአንድ ዳቦ ቤት ውስጥ ሊጥ አብኪ እና ጋጋሪ ሆኖ ይሰራ ነበር። ከእለታት በአንዱ ቀን በአቅራቢያው ለሚገኝ አንድ ባለጸጋ መኖሪያ ቤት ዳቦ ለማድረስ በሄደበት ወቅት፣ "ሻካ-ነባት" የምትባል እጅግ ውብ የሆነች የባለጸጋውን ልጅ በአጋጣሚ ያያታል። ሃፊዝ በመጀመሪያ እይታ በእሷ ፍቅር እብድ ሆነ። ነገር ግን እሷ የሀብታም ልጅ፣ እሱ ደግሞ ደሃ በመሆኑ እሷን ማግኘት ፍጹም የማይታሰብ ህልም ነበር።
በሺራዝ ከተማ ውስጥ አንድ የታወቀ እምነት ነበር፤ እሱም፡- "አንድ ሰው 'ባባ ኩሂ' በተባለው ተራራ ላይ ለ40 ተከታታይ ቀናትና ሌሊቶች ጸልዮ ካደረ፣ ሰይድና ኸድር ይገለጥለታል። ሃፊዝ ፍቅሩን ለማግኘት ሲል ይህንን ከባድ ተጋድሎ ለመጀመር ወሰነ። በየቀኑ በዳቦ ቤት ውስጥ ስራውን ይሰራና፣ ሌሊት ሌሊት ወደ ባባ ኩሂ ተራራ እየወጣ እስከ ንጋት ድረስ በጸሎትና በለቅሶ ያሳልፍ ነበር። ይህንን ለ39 ቀናት በትጋት ቀጠለ። በ40ኛው ምሽት ላይ ሃፊዝ በከፍተኛ ድካም እና ተስፋ መቁረጥ ውስጥ ሆኖ ሳለ፣ በድንገት ተራራው በብርሃን ተሞላ። በአይን ሊታይ የማይችል ውበት ያለው፣ አረንጓዴ የለበሰና ረጅም ነጭ ፂም ያለው ሽማግሌ ከፊቱ ቆመ። ኸድርም ወደ ሃፊዝ ቀረብ ብለው በደግነት፡ "የልብህን መሻት አውቃለሁ፤ ለአርባ ቀናት ያሳየኸው ታማኝነትና ጽናት ተቀባይነት አግኝቷል። በዚህ ጊዜ ኸድር ለሃፊዝ መለኮታዊ የሆነ የብርሃን ጽዋ (አንዳንዶች የጀነት ወይን ይሉታል) አቀረበለት። ሃፊዝ ከጽዋው በተጎነጨ ጊዜ በአእምሮውና በልቡ ውስጥ የነበረው ምድራዊ መጋረጃ ተቀደደ።
የኸድርን መለኮታዊ መጠጥ እንደቀመሰ፣ የሃፊዝ ልብ በአንድ ጊዜ ተቀየረ። የ"ሻካ-ነባት" ምድራዊ ውበት፣ ከመለኮታዊውና ከፈጣሪ ፍቅር ውበት ጋር ሲነጻጸር በጣም ኢምንት ሆና ታየችው። "እኔ የምፈልገው ይህንን የፈጣሪን ፍቅር፣ የዓለማትን ምስጢርና ጥበብን ነው" አሉ ሺራዚ። ኸድርም በሃፊዝ ምርጫ እጅግ ተደስተው፡ "የማይጠፋ የጥበብና የቅኔ ምንጭ ተሰጥቶሃል፤ ከአሁን በኋላ አንተ 'ሊሳን አል-ገይብ' (የስውሩ ዓለም አንደበት) ተብለህ ትጠራለህ" ብለው ዱኣ አደረጉለት።
*ሃፊዝ ከተራራው ወርዶ ወደ ሺራዝ ከተማ ሲመለስ፣ እስከዚያ ቀን ድረስ አንድም መስመር ግጥም መጻፍ የማይችለው ወጣት፣ በአንደበቱ እጅግ ጥልቅና ረቂቅ የሆኑ መለኮታዊ ግጥሞችን ማዝነብ ጀመረ። የሺራዝ ሊቃውንት ሳይቀሩ በእሱ ግጥሞች ጥልቀት ተደነቁ።
*ሻካ-ነባት ራሷ በኋላ ላይ በሃፊዝ መንፈሳዊ ታላቅነትና ውበት ተማርካ ወደ እሱ መጣች አገባት።
ሀፊዝ በዲቫኑ (የግጥም ስብስቡ) ላይ ስለ ኸድር እና ስለ "ህይወት ውሃ" እየጠቀሰ፣ ያንን የለውጥ ምሽት በምስጢራዊ ቃላት ያወሳል።
ታላቁ የፋርስ ገጣሚ ፈሪዱዲን አጣር የከተማዋ ትልቅ ፋርማሲስት
የመድኃኒትና የሽቶ ቀማሚ ሀብታም ነጋዴ ነበር። አጣር በሱቁ ውስጥ ተቀምጦ ሳለ አንድ ድሃ ደረሳ (መንፈሳዊ መንገደኛ) ወደ ሱቁ ይመጣል። ድሃው ሰው የአጣርን ሀብትና በምድራዊ ስራ መጠመድ አይቶ በጥልቅ ትንፋሽ ተከዘ። አጣርም ተናዶ "ለምን አትሄድም?" አለው።
ድሃው ሰውም፡ "እኔማ እጄ ላይ ካለችው ከዚች የምግብ ሳህን በስተቀር ምንም የለኝም፤ ከዚህ ዓለም መውጣት (መሞት) ለእኔ በጣም ቀላል ነው። አንተ ግን በዚህ ሁሉ ሀብትና ንብረት ተከበህ እንዴት ልትሞት እንደምትችል ሳስበው አዝንልሃል" አለው።
አጣርም ፡ "ለመሆኑ አንተ ከዚህ ዓለም እንዴት ነው የምትወጣው?" አለው። ድሃው ደረሳም ወዲያውኑ የያዛትን ሳህን ተንተርሶ መሬት ላይ ተኛ፣ "አላህ!" አለና በዚያው ቅጽበት ነፍሱ ወጣች።
አጣር ምድራዊ ህይወቱን ትቶ ወደ መንፈሳዊው ዓለም ከገባ በኋላ፣ ለዓመታት በጥልቅ ጸሎትና ተጋድሎ ውስጥ አሳለፈ። በሰይዲና ኸድር መሪነትም ከመለኮታዊው ደጃፍ ደረሰ።
አጣር በግጥሞቹ ውስጥ ስለ ሰይዲ ኸድር ሲያነሳ እንዲህ ይላል፡- "የኸድርን መንገድ የተከተለ ሰው፣ መጀመሪያ ራሱን ማጥፋት (ከምድራዊ ፍላጎት መራቅ) አለበት። ያኔ የህይወት ውሃን ከምንጩ ይጠጣል።"
*አላሁመ ሷሊ አላ ሰይድና ወሀቢቢና ሙሐመድ ፤ ወአላ ሰይዲና ኸድር!
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 448 |
| 18 | #ለይለተል_ጁሙኣ
ከመውላና ጀላሉዲን ሩሚ ድንቅ ድንቅ የመስነቪ ታሪኮች መካከል፣
አንድ ጁሙኣ ለይል ነቢዩ ሙሳ (ዐ.ሰ) በበረሃ ውስጥ ሲጓዙ፣ አንድ ምስኪን እረኛ ብቻውን ቆሞ ወደ አላህ ሲጸልይ ተመለከቱት። እረኛው ልቡ በፈጣሪ ፍቅር ተነክቶ፣ እጆቹን ወደ ሰማይ ዘርግቶ ይማጸን ነበር፦
"አምላኬ ሆይ! የት ነህ? ልምጣና ልብስህን ልስፋልህ? ፀጉርህን ላበጥርልህ? ጫማህን ልጠገንልህ?... ጌታዬ ሆይ! ብትታመም እያስታመምኩህ እግርህን ባሸሁልህ... ማታ ማታ የሚጠጣ ወተት አቅርቤልህ ብርድ እንዳይመታህ ብርድ ልብስ ባለበስኩህ... አንተ የኔ ማር፣ የኔ ውድ ጌታ!"
ነቢዩ ሙሳ (ዐ.ሰ) የእረኛውን ንግግር ሲሰሙ በጣም ደነገጡ። ወደ እረኛው ጠጋ አሉና በቁጣ እንዲህ አሉት፦ "አንተ ሰው! ይህ የምትናገረው ነገር ምንድነው? አላህ እኮ ልብስ፣ ጫማ፣ ወተትም ሆነ እንክብካቤ አያስፈልገውም! እርሱ ከምንም ነገር የተፈጠረ አይደለም፣ አይታመምም፣ አይራብም። ይህ የምትናገረው ንግግር ክህደት (ኩፍር) ነው! አሁኑኑ ዝም በል!"
ምስኪኑ እረኛ የነቢዩ ሙሳን ንግግር ሲሰማ ልቡ በድንጋጤና በሀዘን ተሰበረ። ራሱን ዝቅ አድርጎ፣ እያለቀሰና እየተቆጨ ዋሽንቱንና በጎቹን ትቶ ወደ በረሃው እያለቀሰ ሮጦ ጠፋ።
እረኛው እንደሄደ፣ አላህ (ሱ.ወ) ለነቢዩ ሙሳ በወህይ (ራዕይ) እንዲህ አላቸው፦
"ሙሴ ሆይ! እረኛውን ባሪያዬን ከእኔ ለምን አራቅኸው? አንተን ወደ ምድር የላኩህ ሰዎችን ወደ እኔ እንድታቀርብልኝ ነው ወይስ ባሮቼን ከእኔ እንድታርቅብኝ? እኔ ወደ ውጫዊው ንግግርና ቃላት አልመለከትም። እኔ የምመለከተው ወደ ልብና ወደ ውስጣዊው ቅንነት ነው። ያ እረኛ ቃላቶቹ ስህተት ቢኖርባቸውም፣ ልቡ ግን በንጹህ ፍቅር ተሞልቶ ነበር። አንተ ውጫዊውን ስርዓት ተመልክተህ የልቡን ፍም አጠፋኸው!"
ነቢዩ ሙሳ (ዐ.ሰ) ይህንን መለኮታዊ ወቀሳ ሲሰሙ እጅግ ተጸጸቱ። ወዲያውኑ እረኛውን ፍለጋ ወደ በረሃው ሮጡ። በረሃውን አቋርጠው፣ አቧራ ለብሰው ሲፈልጉት ቆይተው በመጨረሻም እረኛውን በረሃ ውስጥ በለቅሶ ተደፍቶ አገኙት።
ሙሳም ወደ እረኛው ቀረቡና፦ "የምስራች! አላህ ወቀሰኝ። ምንም ሳትጨነቅ ልብህ በፈቀደው፣ በፍቅርህ በለመደው ቋንቋና ቃላት ፈጣሪህን መማጸን ትችላለህ። ያንተ ንጹህ ልብ በአላህ ዘንድ ተቀባይነት አለው" አሉት።
እረኛውም ግንባሩን ቀና አድርጎ ፈገግ አለና እንዲህ አለ፦ "ሙሳ ሆይ! ያንተ ወቀሳ መጀመሪያ ልቤን ሰብሮት ነበር፤ ነገር ግን ያ ስብራት ወደ ጥልቅ መንፈሳዊ ደረጃ አሻገረኝ። አሁን ከቃላት ባለፈ የፈጣሪዬን ብርሃን በልቤ ማየት ጀምሬያለሁ" አላቸው።
መውላና ሩሚ በመቀጠል እንዲህ ይላሉ፦ "አላህ ዘንድ ዋጋ ያለው የተሽቆጠቆጡ ቃላት መደርደር ሳይሆን፣ የተሰበረና በቅንነት የተሞላ ልብ ነው።"
በጁሙኣ የአባባ ሰለዋት ስጦታ
<اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى مَركَز الأَنْبِيَاءُ وَالأَوْلِيَاءُ ، وَآلِهِ وَصَحْبِهِ أُولِي الْفَضْلِ وَالأَتْقِيَاءِ.>
*"አላሁመ ሷሊ ወሰሊም አላ መርከዚል አንቢያዕ ወል አውሊያዕ፤ ወአሊሂ ወሷህቢሂ ኡሊል ፈድሊ ወል አትቂያዕ።"
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 396 |
| 19 | #የአእዋፋት_ጉባኤ
ፈሪዱዲን አታር በ12ኛው ክፍለ ዘመን የኖረ ታላቅ የፋርስ (ኢራን) ሱፊ ገጣሚ እና ፈላስፋ ነው። የእሱ ድንቅ ስራ የሆነው "የአእዋፋት ጉባኤ" (መናጢቀ ጠያር) በዓለም ስነ-ጽሁፍ ውስጥ እጅግ በጣም ጥልቅ እና ውብ ከሆኑ መንፈሳዊ ምሳሌያዊ ታሪኮች ነው።
"አንድ ቀን በዓለም ላይ ያሉ ወፎች ሁሉ በአንድ ላይ ተሰበሰቡ። ንጉስ የሌለው ህዝብ ሰላምና ስርዓት አይኖረውም በሚል መሪ የሚሆን ንጉስ መፈለግ እንዳለባቸው ተስማሙ። በዚህ ጊዜ ሁድድ ወደ መድረክ ወጣች፤ በጥበቧ የምትታወቅ፣ የንጉስ ሱለይማን መልእክተኛ የነበረች እና የዓለማትን ምስጢር የተረዳች ወፍ ናት። እንዲህ አለች፦
"እኔ ንጉሳችሁን አውቀዋለሁ፤ ስሙም ሲሙርግ ይባላል። የሚኖረውም ከዓለም ዳርቻ ባለ፣ እሳታማና አስፈሪ በሆነው በቃፍ ተራራ ላይ ነው። እሱ ለእኛ በጣም ቅርብ ነው፣ እኛ ግን ከእሱ በጣም የራቅን ነን። እሱን ለማግኘት ግን የሞትና የህይወትን መንገድ ማለፍ አለብን!"
ሁድሁድ የጉዞውን አስቸጋሪነት ስትገልጽላቸው፣ እያንዳንዱ ወፍ የራሱን ምድራዊ ምቾትና ድክመት እያነሳ ማምለጫ ሰበብ መደርደር ጀመረ።
*የለሊት ወፍ፦ "እኔ የሮዝ (የጽጌረዳ) አበባ ፍቅረኛ ነኝ። ያለ እሷ ውበት መኖር አልችልም። ጽጌረዳን ጥዬ ወደዚያ አስፈሪ ጉዞ አልሄድም" አለች።
*በቀቀን፦ "እኔ ለዘላለም የሚያኖርኝን የህይወት ውሃ (የእድሜ ማራዘሚያ) ነው የምፈልገው። ይህ ውብ ቤቴ ይበቃኛል፤ ረጅሙን መንገድ አልፈልግም" አለች።
* ፒኮክ፦ "እኔ ቀድሞ የጀነት ወፍ ነበርኩ። በሰይጣን መታለሌ ምክንያት ነው ወደ ምድር የተጣልኩት። እኔ የምፈልገው ወደ ጀነት መመለስ ብቻ ነው፤ የሲሙርግ ንጉስነት አያሳስበኝም" አለች።
* ዳክዬ፦ "እኔ ያለ ውሃ መኖር አልችልም። ውሃ ህይወቴ፣ መስገጃዬና መታጠቢያዬ ነው። በየብስ ላይ ረጅም መንገድ መጓዝ አልችልም" አለች።
*ጉጉት፦ "እኔ ሰዎች የሚኖሩበትን ቦታ አልወድም። የምኖረው በፈራረሱ ቤቶች ውስጥ ውድ ሀብት ፍለጋ ነው። ይህንን ፍለጋዬን ትቼ አልመጣም" አለች።
በመጨረሻም በሁድሁድ ንግግር የተነሳሱት በሺዎች የሚቆጠሩ ወፎች ክንፋቸውን ዘርግተው ወደ ቃፍ ተራራ በረሩ። ነገር ግን መንገዱ እጅግ አስፈሪ ነበር። በየመንገዱ ረሃብ፣ ጥም፣ ሙቀትና ቅዝቃዜ አደቀቃቸው። ከሰባቱ ሸለቆዎች ሲያልፉ፦
1)የፍለጋ ሸለቆ: ምኞትንና ቁሳዊ ፍላጎትን ትቶ እውነትን በጽናት መፈለግ መጀመር።
2)የፍቅር ሸለቆ: አእምሮንና አመክንዮን ወደ ጎን አድርጎ በፍቅር መቃጠል።
3)የእውቀት ሸለቆ: ዓለምን በውጫዊ መልክዋ ሳይሆን በውስጣዊ ምስጢሯ መረዳት።
4)የነጻነት/የመላቀቅ ሸለቆ: ከምድራዊ ትስስር እና ከዓለማዊ ስጋቶች ሙሉ በሙሉ መላቀቅ።
5)የአንድነት ሸለቆ: በፍጥረት ሁሉ ውስጥ ያለውን መለኮታዊ አንድነት ማየት፤ "እኔ" እና "አንተ" የሚለው መለያየት መጥፋቱ።
6)በ"የድንቅ ሸለቆ"፦በመለኮታዊው ውበት ተደንቆ ግራ መጋባትና ራስን መርሳት። በዚ ሸለቆ ላይ አእምሯቸውን ስተው መንገድ የሳቱ ብዙ ነበሩ።
በየሸለቆው ፍርሃት ሲጠናባቸው፣ አንዳንዶቹ ወደ ኋላ ተመለሱ፤ ሌሎቹ በድካም ሞቱ፤ የተወሰኑት ደግሞ በበረሃው አውሬዎች ተበሉ።
7)የሞትና የህይወት ሸለቆ: "እኔነትን" ሙሉ በሙሉ አጥፍቶ በመለኮታዊው ውቅያኖስ ውስጥ መሞት።
በመጨረሻም፣ ከአዝማሪዎቹ፣ ከጀግኖቹና ከቆንጆዎቹ ወፎች መካከል በህይወት ተርፈው የሲሙርግ ቤተመንግስት ደጃፍ ላይ የደረሱት 30 ወፎች ብቻ ነበሩ። ላባቸው ረግፏል፣ ክንፋቸው ቆስሏል፣ በረሃብና በስቃይ ሰውነታቸው አልቋል። የቤተመንግስቱ በር ጠባቂ መጀመሪያ ላይ አናገራቸው፦ "እናንተ እነማን ናችሁ? እዚህ ምን ትፈልጋላችሁ? ሲሙርግ የእናንተን መሰል ደካማ ፍጥረታት አይፈልግም፤ ሂዱ ተመለሱ!" አላቸው።
ወፎቹ ግን ማልቀስ ጀመሩ። "እኛ እዚህ የምንሞት ቢሆንም እንኳ ከደጃፉ አንንቀሳቀስም" አሉ። ይህንን ፍጹም እጅ መስጠትና ጽናት ሲያይ፣ በር ጠባቂው በሩን ከፈተላቸው። ወደ ውስጥ ሲገቡ ታላቅ ብርሃን ፈነጠቀባቸው። አንድ መጽሐፍ ተሰጣቸው፤ መጽሐፉን ሲያነቡት በጉዞው ላይ ያሳለፉትን ስቃይ፣ የሰሩትን ስህተትና ህይወታቸውን በሙሉ የያዘ መስተዋት ሆነባቸው።
በመጨረሻም ወደ ዙፋኑ ሲመለከቱ ምንም አይነት አካላዊ ወፍ አላዩም። ያዩት ነገር ቢኖር የራሳቸውን ነጸብራቅ ብቻ ነበር።
*በዚያ የነበረውን መለኮታዊ ብርሃን ሲመለከቱ እነሱ ራሳቸው ሲሙርግ መሆናቸውን ተረዱ። ወደ ዙፋኑ ሲመለከቱ ግን ዙፋኑ ላይ ያለውና እነሱ አንድ ሆኑ።
በዚህ ጊዜ አንድ ድምፅ እንዲህ አላቸው፦
"እናንተ የመጣችሁት 30 ወፎች ሆናችሁ ነው፤ በመስተዋቱም ላይ የታየው 30 (ሲ-ሙርግ = 30 ወፍ ማለት ነው) ነው። ብዙ ሆናችሁ ብትመጡ ኖሮ እዚህ የምታዩትም ብዙ ነበር። ይህ የእናንተ እውነተኛ ማንነት መስተዋት ነው።"
ይህ ምሳሌ፦ በምድራዊ ፍቅርና ስሜት፤ በሀይማኖታዊ ስነስርአት ብቻ ተወስነው ውስጣዊ ጥልቀትን የማይፈልጉ፤ ፈጣሪን ለፀጋው (ለጀነት ምቾት) ብቻ እንጂ ፍቅሩን የማይረዱ፤ ለውጥን የሚፈሩ፤ በቁሳዊ ሀብት ፍለጋ የታወሩ፤ እንዲሁም ለጌታቸው ፍቅር ሁሉን የሚተዉትን ሰዎች ይወክላል።
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 349 |
| 20 | #የሰይዲና_ኸድር_ቅዳሜ
በአንድ ወቅት ታላቁ ዐሪፍ ቢሽር አል-ሀፊ በባግዳድ ጎዳናዎች ላይ ባዶ እግራቸውን እየተጓዙ ሳለ፣ አንድ የማያውቁትና ፊቱ በኑር (በብርሃን) የተሞላ እንግዳ ሽማግሌ መንገድ ላይ ያገኛሉ። ሽማግሌው ወደ ቢሽር በመምጣት ስማቸውን ጠርቶ ሰላምታ አቀረበ።
ሽማግሌው ሰው ለቢሽር እንዲህ አለ፦ "አንተ ቢሽር ሆይ! አንተ በምድር ላይ ብቻ ሳይሆን በሰማይ መላእክት ዘንድም የምትታወቅ የላቅክ የአላህ ወዳጅ ነህ" አላቸው።
ቢሽርም በንግግሩ ተገርሞ "የአላህ ወዳጅ ሆይ! እባክህ ማንነትህን ንገረኝ?" ሲል ጠየቀ። ሽማግሌውም ፈገግ ብሎ፦ "እኔ ወንድምህ ኸድር ነኝ" አሉ።
ቢሽር ሰይዲና ኸድር መሆናቸውን ሲያውቅ እጅግ ደነገጠ፤ በደስታም ተሞሉ። ከዚያም "ሰይዲና ኸድር ሆይ! እባካችሁ ለአላህ ስም ስትሉ ዱዓ አድርግልኝ" አላቸው። ሰይዲና ኸድርም እጃቸውን ወደ ሰማይ አንስተው፦ "አላህ ሆይ! ለአንተ ያለውን መታዘዝ አግኝቶታልና የአንተን መውደድ (ሪዷን) ጨምርለት፣ ለአንተ መስራቱንም አግኝቶታልና በደረጃው ላይ ማዕረግን ጨምርለት" ብለው ዱዓ አደረጉለት። ከዚህ ክስተት በኋላ ቢሽር በመንፈሳዊ ደረጃቸው ላይ ከፍተኛ እድገት አገኙ።
*አላሁመ ሷሊ አላ መርከዚል አንቢያዕ ወል አውሊያዕ!
*አላሁመ ሷሊ አላ ሰይዲና ኸድር
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 365 |
