Abdu & Hasu
前往频道在 Telegram
Abdulhak & Hasenet <የኢቅራእ ቢስሚ ረቢከ /አንብብ በጌታህ ስም/ ትውልዶች እንጂ ፣ የኢቅራእ /የአንብብ / ትውልዶች አይደለንም።> አላህ ያወቅነውን የምናሳውቅ ፣ ባወቅነው ደግሞ የምንጠቀም ያድርገን። አሚን!! For any comment ⇄ @ABDU_EMRE
显示更多4 539
订阅者
+124 小时
-207 天
-10730 天
数据加载中...
吸引订阅者
七月 '26
七月 '26
+2
在0个频道中
六月 '26
+25
在0个频道中
Get PRO
五月 '26
+56
在0个频道中
Get PRO
四月 '26
+81
在0个频道中
Get PRO
三月 '26
+18
在0个频道中
Get PRO
二月 '26
+17
在0个频道中
Get PRO
一月 '26
+22
在0个频道中
Get PRO
十二月 '25
+10
在0个频道中
Get PRO
十一月 '25
+29
在0个频道中
Get PRO
十月 '25
+23
在0个频道中
Get PRO
九月 '25
+37
在1个频道中
Get PRO
八月 '25
+95
在0个频道中
Get PRO
七月 '25
+170
在0个频道中
Get PRO
六月 '25
+44
在0个频道中
Get PRO
五月 '25
+83
在0个频道中
Get PRO
四月 '25
+42
在0个频道中
Get PRO
三月 '25
+322
在0个频道中
Get PRO
二月 '25
+137
在0个频道中
Get PRO
一月 '25
+325
在0个频道中
Get PRO
十二月 '24
+344
在0个频道中
Get PRO
十一月 '24
+495
在1个频道中
Get PRO
十月 '24
+621
在0个频道中
Get PRO
九月 '24
+657
在0个频道中
Get PRO
八月 '24
+1 431
在0个频道中
Get PRO
七月 '24
+989
在1个频道中
Get PRO
六月 '24
+1 097
在0个频道中
Get PRO
五月 '24
+1 162
在3个频道中
Get PRO
四月 '240
在1个频道中
Get PRO
三月 '24
+8
在0个频道中
Get PRO
二月 '24
+18
在1个频道中
Get PRO
一月 '24
+18
在0个频道中
Get PRO
十二月 '23
+83
在2个频道中
Get PRO
十一月 '23
+78
在0个频道中
Get PRO
十月 '23
+58
在1个频道中
Get PRO
九月 '23
+70
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+83
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+102
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+64
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+91
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+93
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+70
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+25
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+34
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+17
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+23
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+26
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+42
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+33
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+109
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+91
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+103
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+131
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+626
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+398
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+103
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+45
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+49
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+147
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+558
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+318
在0个频道中
Get PRO
七月 '21
+191
在0个频道中
Get PRO
六月 '21
+541
在0个频道中
Get PRO
五月 '21
+953
在0个频道中
Get PRO
四月 '21
+71
在0个频道中
Get PRO
三月 '21
+37
在0个频道中
Get PRO
二月 '21
+8
在0个频道中
Get PRO
一月 '21
+90
在0个频道中
Get PRO
十二月 '20
+1 618
在0个频道中
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 07 七月 | 0 | |||
| 06 七月 | +1 | |||
| 05 七月 | 0 | |||
| 04 七月 | 0 | |||
| 03 七月 | 0 | |||
| 02 七月 | 0 | |||
| 01 七月 | +1 |
频道帖子
በቴህራን በተካሄደው የአያቶላ አሊ ኻሜኒ (ረ) የስንብት ሥነ-ሥርዓት ላይ የኢራን መንግሥት የአገራት የዲፕሎማቲክ ልዑካን ቡድኖች ወደ አስከሬኑ ሲጠጉ የተነበበው ቁርኣን አንቀጽ (አያህ)
ቻይና፦ አል-ዒምራን (3:126) — “አላህም (ይህንን እርዳታ) ለእናንተ ብስራት እንድትሆንና ልቦቻችሁም በእርሱ እንዲረኩ እንጂ ለሌላ አላደረገውም። ድልም ከአሸናፊው ጥበበኛው አላህ ዘንድ እንጂ ከሌላ አይደለም።”
ሩሲያ፦ አል-ቀሰስ (28:83) — “ይህች የመጨረሻይቱ ዓለም (ገነት) በምድር ላይ ትዕቢትንና ጥፋትን ለማይፈልጉ ሰዎች እናደርጋታለን፤ መልካም ፍጻሜም ለጠባቂዎቹ (ለጻድቃኑ) ነው።”
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ (UAE)፦ አል-ማኢዳህ (5:51) -- “እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አይሁዶችንና ክርስቲያኖችን ረዳቶች (ወዳጆች) አድርጋችሁ አትያዙ፤ ከፊላቸው ለከፊሉ ረዳቶች ናቸውና። ከእናንተም ውስጥ ወዳጅ የሚያደርጋቸው ሰው እርሱ ከእነሱ ነው። አላህ አመጸኞችን ሕዝቦች አይመራም።”
የአውሮፓ አገራት ተወካዮች፦ ሱራህ ኢብራሂም (14:42) -- “አላህንም እነዚያ በደለኞች ከሚሰሩት ነገር ዘንጊ አድርገህ አታስበው፤ የሚያቆያቸው (የሚቀጣቸው) ዓይኖች በድንጋጤ ለሚፈጡበት ቀን ብቻ ነው።”
ሳውዲ አረቢያ፦ አል-ኢምራን (3:13) -- “በእርግጥ በነዚያ በተገናኙት ሁለት ጭፍሮች ውስጥ ለእናንተ አስደናቂ ምልክት አለ። አንደኛይቱ ጭፍራ በአላህ መንገድ ላይ የምትጋደል ስትሆን ሌላኛይቱ ደግሞ ከሃዲዎች ነበሩ... አላህም በራሱ እርዳታ የሚሻውን ሰው ይደግፋል።”
ሊባኖስ፦ አን-ኒሳእ (4:66) — “እኛም በእነርሱ ላይ ‘ነፍሶቻችሁን ግደሉ ወይም ከአገሮቻችሁ ውጡ’ ማለትን በጻፍንባቸው (በደነገግንባቸው) ኖሮ ከእነርሱ ጥቂቶቹ እንጂ አይሰሩትም ነበር...”
ሃማስ፦ አል-አሕዛብ (33:23) — “ከምእመናን ውስጥ በአላህ ላይ በእርሱ የገቡትን ቃል የፈጸሙ ወንዶች አሉ። ከእነርሱም ስለቱን (ሰማዕትነትን) የጨረሰ አለ፤ ከእነርሱም ገና የሚጠባበቅ አለ። (ቃል ኪዳናቸውን) ምንም መለወጥን አለወጡም።”
ሒዝቦላህ፦ ሱራህ አል-ማኢዳህ (5:56) -- “አላህንና መልክተኛውን እነዚያ ያመኑትንም ወዳጅ የሚያደርግ ሰው (የአላህ ጭፍራ ነው)፤ የአላህም ጭፍራዎች እነሱ በእርግጥ አሸናፊዎች ናቸው።”
የመን ሐውቲዎች፦ አል-ፈትሕ (48:29) — “ሙሐመድ የአላህ መልዕክተኛ ነው፤ እነዚያም ከእርሱ ጋር ያሉት (ምእመናን) በከሃዲዎች ላይ የበረቱ፣ በመካከላቸው አዛኞች ናቸው...”
ቱርክ፦ አን-ኒሳእ (4:95) —“ምእመናን ከሆኑት ሰሪዎች (ተዋጊዎች) ውስጥ ያለ ጉዳት (ቤት) ተቀማጮቹና እነዚያ በአላህ መንገድ ላይ በገንዘቦቻቸውና በነፍሶቻቸው የሚጋደሉት አይስተካከሉም። አላህ በገንዘቦቻቸውና በነፍሶቻቸው የሚጋደሉትን ከተቀማጮቹ በደረጃ አበለጠ...።”
የኢራቅ ታጣቂዎች፦ አል-ዒምራን (3:169–170) -- “እነዚያንም በአላህ መንገድ የተገደሉትን ሙታን አድርገህ አታስብ፤ ይልቁንም እነሱ በጌታቸው ዘንድ ሕያዋን ናቸው፤ ሲሳይንም ያገኛሉ። አላህ ከችሮታው በሰጣቸው ነገር ተደሳቾች ሲሆኑ...”
ሶሪያ፦ አል-ኢስራእ (17:5) -- “ከሁለቱ መጀመሪያይቱ (የማጥፋት) ጊዜ በመጣ ጊዜ በናንተ ላይ ኃያላን የሆኑ ባሮቻችንን እንሰድባችኋለን፤ በቤቶችም መካከል ይመላለሳሉ (ይበረብራሉ)፤ ፍጻሜውም የሚፈጸም ቃል ኪዳን ነበረ።”
ፓኪስታን እና አፍጋኒስታን፦ አል-ሁጁራት (49:10) -- “ምእመናን ወንድማማቾች ናቸው፤ በመካከላቸውም አስታርቁ፤ አላህንም ፍሩ፣ ይታዘንላችሁ ዘንድ።”
*አላህ ለዘመኑ ግፍኞችና በደለኞች መድሀኒት የሆኑትን ሰይድ መህዲ አ.ሰ ያምጣልን! አሚን!
@abduftsemier
@abduftsemier
| 2 | #ለይለተል_ጁሙኣ
ታላቁ ወሊይ ዘኑን አል-ሚስሪ ቀ.ሲ በጁሙዓ ለይል ከካይሮ ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኝ አንድ ጭር ባለ በረሃማ መንገድ ላይ ብቻቸውን ይጓዙ ነበር። ሌሊቱ እጅግ ቀዝቃዛና ጨለማ ነበር። ሸይኹ ልባቸውን በዝክርና በሶለዋት ሞልተው እየተጓዙ ሳለ፣ ድንገት በዚያ ጭለማ ውስጥ አንድ የሚያስፈራ ትልቅ ድምፅ ሰሙ። ድምፁን ተከትለው ጠጋ ሲሉ፣ አንድ ትልቅ አንበሳ መሬት ላይ ወድቆ በከፍተኛ ህመም ሲጮኽና ሲያቃስት ተመለከቱ። ተራ ሰው ቢሆን በፍርሃት ይሸሻል፤ ዘኑን ግን ፍጥረታትን በሙሉ በራህመት ስለሚያዩ ወደ አንበሳው በጥንቃቄ ቀረቡ። ሲመለከቱት፣ የአንበሳው እግር ውስጥ ትልቅና ስለታም እሾህ ገብቶ ቆስሎና አብጦ አገኙት።
ዘኑን አል-ሚስሪ "ይህ በዚህች በተባረከች የጁሙዓ ለይል አላህ የላከብኝ የፈተና ማዕድ ነው" አሉ። ወዲያውኑ ቢላዋቸውን አውጥተው፣ በአላህ ስም እሾሁን ከአንበሳው እግር ላይ በጥንቃቄ ነቀሉለት። ቁስሉንም ከልብሳቸው ላይ ቀደው ጨርቅ አሰሩለት። አንበሳው ወዲያውኑ ከህመሙ ሲገላገል፣ በሚያስገርም ሁኔታ ሰይዲን ሊጎዳቸው አልሞከረም። ይልቁኑ ራሱን መሬት ላይ አድርጎ፣ በትልቅና በሚያስተጋባ ድምፅ መጮኽ ጀመረ።
በዚያ ሰዓት፣ አላህ ለዘኑን አል-ሚስሪ የመንፈሳዊ ከሽፍ (መገለጥ) ከፈተላቸው። የአንበሳው ጩኸት በልባቸው ውስጥ እንዲህ ሲል ተሰማቸው፦
"ያ አላህ! ይህ የአንተ ወዳጅ በዚህች የጁሙዓ ለይል ለእኔ አዘነልኝ፣ ከህመሜም ፈወሰኝ። አንተም በዚህች ምሽት የልቡን ጭንቀት በሙሉ አስወግድለት፣ ወደ አንተ የሚወስደውንም የመጨረሻውን የመክፈቻ በር ክፈትለት።"
አንበሳው ዱዓውን አድርጎ በጨለማው በረሃ ውስጥ ተሰወረ። ዘኑን አል-ሚስሪ ግን በዚያው ቦታ ላይ ሆነው ወደ ሰማይ ሲመለከቱ፣ የሰማይ በሮች በሙሉ ተከፍተው የራህመትና የኑር መጋረጃ ሲወርድ ተመለከቱ። ልባቸው ከዚህ በፊት ደርሳበት የማታውቀው ጥልቅ የሆነ መለኮታዊ እውቀትና ፍቅር (ማዕሪፋ) ውስጥ ሰጠመች።
እሳቸው ራሳቸው ስለዚያች ሌሊት ሲናገሩ እንዲህ ብለዋል፦
"በእውቀቴና በኢባዳዬ ብዛት ያላገኘሁትን ትልቅ መንፈሳዊ ከፍታና ከሽፍ፣ አላህ በዛች ጁሙዓ ለይል በአንድ ምስኪንና በታመመ ፍጡር ላይ እንዳዝን በማድረጉ ሰበብ ብቻ ሰጠኝ።"
*"በምድር ላሉት እዘኑ፣ በሰማይ ያለው ያዝንላችኋል" የሚለው የነቢዩ (ﷺ) ቃል ማሳያ ነው።
የአባባ የጁሙኣ ሰለዋት ስጦታ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ، صَلَاةً تَرْزُقُنَا بِهَا الْخُلُقَ النَّفِيسَ، يَا رَحْمَانُ يَا قُدُّوسُ!
አላሁመ ሷሊ ወሰሊም አላ ሰይዲና ሙሀመድ፤ ወአላ አሊ ሰይዲና ሙሀመድ ሷላተን ተርዙቁና ቢሃል ኹሉቀ ነፊስ ያረህማኑ ያቁዱስ!
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 180 |
| 3 | #ለይለተል_ጁሙኣ
ታላቁ ወሊይ ዘኑን አል-ሚስሪ ቀ.ሲ በጁሙዓ ለይል ከካይሮ ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኝ አንድ ጭር ባለ በረሃማ መንገድ ላይ ብቻቸውን ይጓዙ ነበር። ሌሊቱ እጅግ ቀዝቃዛና ጨለማ ነበር። ሸይኹ ልባቸውን በዝክርና በሶለዋት ሞልተው እየተጓዙ ሳለ፣ ድንገት በዚያ ጭለማ ውስጥ አንድ የሚያስፈራ ትልቅ ድምፅ ሰሙ። ድምፁን ተከትለው ጠጋ ሲሉ፣ አንድ ትልቅ አንበሳ መሬት ላይ ወድቆ በከፍተኛ ህመም ሲጮኽና ሲያቃስት ተመለከቱ። ተራ ሰው ቢሆን በፍርሃት ይሸሻል፤ ዘኑን ግን ፍጥረታትን በሙሉ በራህመት ስለሚያዩ ወደ አንበሳው በጥንቃቄ ቀረቡ። ሲመለከቱት፣ የአንበሳው እግር ውስጥ ትልቅና ስለታም እሾህ ገብቶ ቆስሎና አብጦ አገኙት።
ዘኑን አል-ሚስሪ "ይህ በዚህች በተባረከች የጁሙዓ ለይል አላህ የላከብኝ የፈተና ማዕድ ነው" አሉ። ወዲያውኑ ቢላዋቸውን አውጥተው፣ በአላህ ስም እሾሁን ከአንበሳው እግር ላይ በጥንቃቄ ነቀሉለት። ቁስሉንም ከልብሳቸው ላይ ቀደው ጨርቅ አሰሩለት። አንበሳው ወዲያውኑ ከህመሙ ሲገላገል፣ በሚያስገርም ሁኔታ ሰይዲን ሊጎዳቸው አልሞከረም። ይልቁኑ ራሱን መሬት ላይ አድርጎ፣ በትልቅና በሚያስተጋባ ድምፅ መጮኽ ጀመረ።
በዚያ ሰዓት፣ አላህ ለዘኑን አል-ሚስሪ የመንፈሳዊ ከሽፍ (መገለጥ) ከፈተላቸው። የአንበሳው ጩኸት በልባቸው ውስጥ እንዲህ ሲል ተሰማቸው፦
"ያ አላህ! ይህ የአንተ ወዳጅ በዚህች የጁሙዓ ለይል ለእኔ አዘነልኝ፣ ከህመሜም ፈወሰኝ። አንተም በዚህች ምሽት የልቡን ጭንቀት በሙሉ አስወግድለት፣ ወደ አንተ የሚወስደውንም የመጨረሻውን የመክፈቻ በር ክፈትለት።"
አንበሳው ዱዓውን አድርጎ በጨለማው በረሃ ውስጥ ተሰወረ። ዘኑን አል-ሚስሪ ግን በዚያው ቦታ ላይ ሆነው ወደ ሰማይ ሲመለከቱ፣ የሰማይ በሮች በሙሉ ተከፍተው የራህመትና የኑር መጋረጃ ሲወርድ ተመለከቱ። ልባቸው ከዚህ በፊት ደርሳበት የማታውቀው ጥልቅ የሆነ መለኮታዊ እውቀትና ፍቅር (ማዕሪፋ) ውስጥ ሰጠመች።
እሳቸው ራሳቸው ስለዚያች ሌሊት ሲናገሩ እንዲህ ብለዋል፦
"በእውቀቴና በኢባዳዬ ብዛት ያላገኘሁትን ትልቅ መንፈሳዊ ከፍታና ከሽፍ፣ አላህ በዛች ጁሙዓ ለይል በአንድ ምስኪንና በታመመ ፍጡር ላይ እንዳዝን በማድረጉ ሰበብ ብቻ ሰጠኝ።"
*"በምድር ላሉት እዘኑ፣ በሰማይ ያለው ያዝንላችኋል" የሚለው የነቢዩ (ﷺ) ቃል ማሳያ ነው።
የአባባ የጁሙኣ ሰለዋት ስጦታ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ، صَلَاةً تَرْزُقُنَا بِهَا الْخُلُقَ النَّفِيسَ، يَا رَحْمَانُ يَا قُدُّوسُ!
አላሁመ ሷሊ ወሰሊም አላ ሰይዲና ሙሀመድ፤ ወአላ አሊ ሰይዲና ሙሀመድ ሷላተን ተርዙቁና ቢሃል ኹሉቀ ነፊስ ያረህማኑ ያቁዱስ!
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 1 |
| 4 | #ለይለተል_ጁሙኣ
ታላቁ ወሊይ ዘኑን አል-ሚስሪ ቀ.ሲ በጁሙዓ ለይል ከካይሮ ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኝ አንድ ጭር ባለ በረሃማ መንገድ ላይ ብቻቸውን ይጓዙ ነበር። ሌሊቱ እጅግ ቀዝቃዛና ጨለማ ነበር። ሸይኹ ልባቸውን በዝክርና በሶለዋት ሞልተው እየተጓዙ ሳለ፣ ድንገት በዚያ ጭለማ ውስጥ አንድ የሚያስፈራ ትልቅ ድምፅ ሰሙ። ድምፁን ተከትለው ጠጋ ሲሉ፣ አንድ ትልቅ አንበሳ መሬት ላይ ወድቆ በከፍተኛ ህመም ሲጮኽና ሲያቃስት ተመለከቱ። ተራ ሰው ቢሆን በፍርሃት ይሸሻል፤ ዘኑን ግን ፍጥረታትን በሙሉ በራህመት ስለሚያዩ ወደ አንበሳው በጥንቃቄ ቀረቡ። ሲመለከቱት፣ የአንበሳው እግር ውስጥ ትልቅና ስለታም እሾህ ገብቶ ቆስሎና አብጦ አገኙት።
ዘኑን አል-ሚስሪ "ይህ በዚህች በተባረከች የጁሙዓ ለይል አላህ የላከብኝ የፈተና ማዕድ ነው" አሉ። ወዲያውኑ ቢላዋቸውን አውጥተው፣ በአላህ ስም እሾሁን ከአንበሳው እግር ላይ በጥንቃቄ ነቀሉለት። ቁስሉንም ከልብሳቸው ላይ ቀደው ጨርቅ አሰሩለት። አንበሳው ወዲያውኑ ከህመሙ ሲገላገል፣ በሚያስገርም ሁኔታ ሰይዲን ሊጎዳቸው አልሞከረም። ይልቁኑ ራሱን መሬት ላይ አድርጎ፣ በትልቅና በሚያስተጋባ ድምፅ መጮኽ ጀመረ።
በዚያ ሰዓት፣ አላህ ለዘኑን አል-ሚስሪ የመንፈሳዊ ከሽፍ (መገለጥ) ከፈተላቸው። የአንበሳው ጩኸት በልባቸው ውስጥ እንዲህ ሲል ተሰማቸው፦
"ያ አላህ! ይህ የአንተ ወዳጅ በዚህች የጁሙዓ ለይል ለእኔ አዘነልኝ፣ ከህመሜም ፈወሰኝ። አንተም በዚህች ምሽት የልቡን ጭንቀት በሙሉ አስወግድለት፣ ወደ አንተ የሚወስደውንም የመጨረሻውን የመክፈቻ በር ክፈትለት።"
አንበሳው ዱዓውን አድርጎ በጨለማው በረሃ ውስጥ ተሰወረ። ዘኑን አል-ሚስሪ ግን በዚያው ቦታ ላይ ሆነው ወደ ሰማይ ሲመለከቱ፣ የሰማይ በሮች በሙሉ ተከፍተው የራህመትና የኑር መጋረጃ ሲወርድ ተመለከቱ። ልባቸው ከዚህ በፊት ደርሳበት የማታውቀው ጥልቅ የሆነ መለኮታዊ እውቀትና ፍቅር (ማዕሪፋ) ውስጥ ሰጠመች።
እሳቸው ራሳቸው ስለዚያች ሌሊት ሲናገሩ እንዲህ ብለዋል፦
"በእውቀቴና በኢባዳዬ ብዛት ያላገኘሁትን ትልቅ መንፈሳዊ ከፍታና ከሽፍ፣ አላህ በዛች ጁሙዓ ለይል በአንድ ምስኪንና በታመመ ፍጡር ላይ እንዳዝን በማድረጉ ሰበብ ብቻ ሰጠኝ።"
*"በምድር ላሉት እዘኑ፣ በሰማይ ያለው ያዝንላችኋል" የሚለው የነቢዩ (ﷺ) ቃል ማሳያ ነው።
የአባባ የጁሙኣ ሰለዋት ስጦታ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ، صَلَاةً تَرْزُقُنَا بِهَا الْخُلُقَ النَّفِيسَ، يَا رَحْمَانُ يَا قُدُّوسُ!
አላሁመ ሷሊ ወሰሊም አላ ሰይዲና ሙሀመድ፤ ወአላ አሊ ሰይዲና ሙሀመድ ሷላተን ተርዙቁና ቢሃል ኹሉቀ ነፊስ ያረህማኑ ያቁዱስ!
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 4 |
| 5 | #የሰይዲና_ኸድር_ቅዳሜ
ሼህ አብዱልኻሊቅ አል-ጉጅዱዋኒ ገና በወጣትነት ዕድሜያቸው ቁርአንን እና የሸሪዓ እውቀቶችን እያጠኑ። አንድ ቀን በቁርአን ውስጥ ያለውንና ስለ ውስጣዊ/ሚስጥራዊ ዚክር (የልብ ዚክር) የሚናገረውን የጌታችንን ቃል ያነባሉ፡-
“ጌታህን በነፍስህ ውስጥ በጭምትነትና በፍርሃት... ጥዋትና ማታ አውሳው፤ ከዘንጊዎችም አትሁን።” (ሱረቱል አዕራፍ፡ 205)
ወጣቱ አብዱልኻሊቅ በዚህ አንቀጽ ላይ በጥብቅ አሰላሰሉና መምህራቸውን እንዲህ ሲሉ ጠየቁ፡-
“ይህ ዚክር እንዴት ነው የሚደረገው? በድምፅ (በምላስ) ካደረግኩት ሰዎች ይሰሙኛል፣ ይህ ደግሞ ለይዩልኝ ሊዳርገኝ ይችላል። በልቤ ብቻ ካደረግኩት ደግሞ ሰይጣን የሰውን ልጅ የደም ስር ተከትሎ ስለሚዘዋወር በልቤ የማስበውን ያውቅብኛል። ታዲያ ፍጹም ሚስጥራዊ እና ሰይጣንም ሆነ ሰው የማያውቅበትን ዚክር እንዴት ማድረግ እችላለሁ?”
መምህራቸውም “ልጄ ሆይ፣ ይህ የላቀ መለኮታዊ እውቀት ነው፤ አላህ ከፈለገ ከቅዱሳን ባሮቹ በአንዱ በኩል ይገልጥልሃል” አሏቸው።
ብዙም ሳይቆይ፣ ወጣቱ አብዱልኻሊቅ በሶላት ላይ እያሉ ፍጹም መንፈሳዊ ድባብ ተፈጠረ። በወቅቱ የነበሩት ታላቁ መሪ ሰይድና ኸድር (ዐ.ሰ) በአካል ተገለጡላቸው። ሰይድና ኸድርም ለአብዱልኻሊቅ መንፈሳዊ አባትና መሪ እንደሚሆኑ በመግለጽ፣ ያንን የፈለጉትን ሚስጥራዊ ዚክር ሊያስተምሯቸው መጡ። ሰይድና ኸድር ወጣቱን አብዱልኻሊቅን ይዘው ወደ አንድ የውሃ ኩሬ ሄዱ። ከዚያም በውሃው ውስጥ እንዲጠልቁና እዚያ ውስጥ ሆነው ትንፋሻቸውን አፍነው፣ ምላሳቸውን ከላንቃቸው ጋር አጣብቀው በልባቸው “ላ ኢላሀ ኢልለላህ፣ ሙሐመዱ ረሱሉላህ” እያሉ እንዲያወሱ አዘዟቸው።
ይህ ዚክር “ኸፊ” (ፍጹም ሚስጥራዊ) ይባላል። በውሃ ውስጥ ትንፋሽን አፍኖ የሚደረግ በመሆኑ፡- ምላስ አይንቀሳቀስም (ሰዎች አይሰሙትም)፣ ትንፋሽ አይወጣም (የሰውነት እንቅስቃሴ ስለማይታይ ሰይጣንም የተደበቀውን መንፈሳዊ ብርሃን በቀላሉ ሊሰርቅ አይችልም)።
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 270 |
| 6 | #ለይለተል_ጁሙኣ
ሰይዱ ጧኢፋ ኢማም ጁነይድ በአንድ የጁሙዓ ሌሊት በባግዳድ መስጂድ ውስጥ ዒባዳ እያደረጉ ሳለ፣ አንድ ዓይነ ስውር ምስኪን ሰው ወደ መስጂዱ ይገባል። ይህ ሰው በጣም ፍጹም በሆነ ፍቅር (ሸውቅ) ሆኖ በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ላይ ሰለዋት ያወርዳል።
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ، طِبِّ الْقُلُوبِ وَدَوَائِهَا، وَعَافِيَةِ الأَبْدَانِ وَشِفَائِهَا، وَنُورِ الأَبْصَارِ وَضِيَائِهَا، وَعَلَى آلِهِ وَصَحْبِهِ وَسَلِّمْ.
"አላሁመ ሷሊ ወሰሊም ዓላ ሰይዲና ሙሐመዲን፣ ጢቢል ቁሉቢ ወደዋኢሃ፣ ወዓፊየቲል አብዳኒ ወሺፋኢሃ፣ ወኑሪል አብሷሪ ወዲያኢሃ፣ ወዓላ አሊሂ ወሷሕቢሂ ወሰሊም"
ይህ ሰለዋት እጅግ ልብ የሚነካና ጥልቅ የሆነ የፍቅር መግለጫ ያለው ነው። ኢማም ጁነይድ የሰውየውን ሰለዋት ሲሰሙ፣ በልባቸው ውስጥ ለየት ያለ መንፈሳዊ ስሜት ይሰማቸዋል፤ በሰውየው ላይ ያለው የአላህ እዝነትና ብርሃንም ይታያቸዋል።
በዚህ ጊዜ ኢማም ጁነይድ ወደ ሰውየው ጠጋ አሉና፡-
"አንተ የአላህ ባሪያ ሆይ! ይህ የምታወርደው ሰለዋት እጅግ አስደናቂ ነው፤ ይህንን ሰለዋት ማን ነው ያስተማረህ?"ሲሉ ይጠይቁታል።
ሰውዬም ፈገግ አለና እንዲህ አላቸው፡-
"አቡል ቃሲም ሆይ! እኔማ ዕውርና ደካማ ሰው ነኝ። ነገር ግን በአንድ የጁሙዓ ሌሊት በህልሜ ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) አየኋቸው። ወደ እሳቸው ጠጋ ብዬ 'የአላህ መልእክተኛ ሆይ! እኔ ዓይኔ የማያይ ምስኪን ነኝ፤ አላህ ዘንድ ትልቅ ደረጃ የሚያሰጠኝን ሰለዋት ያስተምሩኝ' አልኳቸው። እሳቸውም ይህንን ሰለዋተ ኑራኒያ አስተማሩኝ። ከዚያን ቀን ጀምሮ በየጁሙዓው ሌሊት ይህንን ሰለዋት ሳወርድ፣ የነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መንፈሳዊ ቅርበትና ብርሃን አይለየኝም" አላቸው።
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 264 |
| 7 | #የድል_ቀን
አሹራ ቀን (ሙሀረም 10) ላይ የተከሰቱትን ታላላቅ መለኮታዊ ድሎች፦
* የነቢዩላህ ኣደም (ዐ.ሰ)፦ አላህ ንስሐቸውን የተቀበለውና ይቅርታ ያደረገላቸው በዚህ ቀን ነው።
* የነቢዩላህ ኑህ (ዐ.ሰ)፦ ታላቁ የጥፋት ውሃ ጎርፍ አብቅቶ፣ እርሳቸውና አማኞች የነበሩበት መርከብ በ“ጁዲ” ተራራ ላይ በሰላም ያረፈችው በዚህ ዕለት ነው።
* የነቢዩላህ ኢብራሂም (ዐ.ሰ)፦ ነቢዩላህ ኢብራሂም የተወለዱትም በዚህ ቀን ሲሆን፥ ከናምሩድ እሳት ውስጥ በተጣሉ ጊዜ አላህ እሳቱን ቀዝቃዛና ሰላም (በርደን ወሰላማ) አድርጎ ያዳናቸው በዚህ ዕለት ነው።
* የነቢዩላህ ሙሳ (ዐ.ሰ)፦ ፈርዖንና ግፈኛው ሰራዊቱ በባህር ውስጥ የሰጠሙበት፣ ሙሳና የኢሥራኢል ልጆች ግን ባህሩ ተከፍሎላቸው በሰላም የተሻገሩበትና ከባርነት ነፃ የወጡበት ታላቁ የድል ቀን ነው።
* የነቢዩላህ ዩሱፍ (ዐ.ሰ)፦ በወንድሞቻቸው ምቀኝነት ጥልቅ ጉድጓድ ውስጥ ከተጣሉ በኋላ፣ ከአላህ በረከት ጋር ከጉድጓዱ የወጡበት እንዲሁም ከዓመታት በኋላ ከግብፅ እስር ቤት የተፈቱበት ቀን ነው።
*የነቢዩላህ ያዕቆብ (ዐ.ሰ)፦ ከልጃቸው ከነቢዩ ዩሱፍ መለየት የተነሳ አልቅሰው ጠፍቶ የነበረው ዓይናቸው (ዕይታቸው) በአላህ ፈቃድ የተመለሰላቸውና ብርሃን ያገኙበት በዚህ ቀን ነው።
* የነቢዩላህ አዩብ (ዐ.ሰ)፦ አላህ ሙሉ ጤንነታቸውንና ያጡትን ሀብት የመለሰላቸው በአሹራ ቀን ነው።
* የነቢዩላህ ዩኑስ (ዐ.ሰ)፦ በአሳ ነባሪ ሆድ ውስጥ ሆነው ካደረጉት ጥልቅ ዚክርና መማጸን በኋላ፣ አላህ ከአሳው ሆድ በሰላም ያወጣቸውና ወደ ምድር የመለሳቸው በዚህ ዕለት ነው።
* የነቢዩላህ ሱለይማን (ዐ.ሰ)፦ አላህ ለነቢዩ ሱለይማን ታላቅ የሆነውንና ማንኛውንም ፍጡር (ሰውን፣ ጂንንና ንፋስን) የሚገዛበትን ንግሥናና ስልጣን የለገሳቸው በዚህ ቀን ነው።
*የነቢዩላህ ዳውድ (ዐ.ሰ)፦ አላህ ለነቢዩ ዳውድ ያደረገላቸውን ትልቅ ይቅርታና ወንጀላቸውን የማራቸው ዕለት።
* የነቢዩላህ ዒሳ (ዐ.ሰ)፦ ጠላቶቻቸው ሊገድሏቸውና ሊሰቅሏቸው ባሴሩ ጊዜ፣ አላህ ከእነሱ ተንኮል ጠብቆ ወደ ሰማይ ያነሳቸው በዚህ ቀን ነው።
* የነቢዩላህ እድሪስ (ዐ.ሰ)፦ አላህ በቁርኣን ውስጥ “ከፍተኛም ስፍራ አነሳነው” (መርየም፡ 57) በማለት የገለጸውና ነቢዩላህ እድሪስን ወደ አራተኛው ሰማይ ከፍ ያደረገበት ዕለት።
* የነቢዩላህ ሹዐይብ (ዐ.ሰ)፦ ነቢዩላህ ሹዐይብ ለህዝቦቻቸው ጥመትና መከራ ካላቸው ከባድ ሀዘን የተነሳ አልቅሰው ዓይናቸው ጠፍቶ የነበረ ሲሆን፣ አላህ ሙሉ ዕይታቸውን የመለሰላቸው በዚህ ቀን ነው።
* የነቢዩላህ ሁድ (ዐ.ሰ)፦ አላህ አመጸኞቹን የ“ዓድ” ህዝቦች በብርቱና አውዳሚ ንፋስ ባጠፋበት ወቅት፣ ነቢዩ ሁድንና አብረዋቸው የነበሩትን አማኞች ከጥፋት ያዳነበት ዕለት አሹራ ነው።
* የነቢዩላህ ሷሊህ (ዐ.ሰ)፦ ታላቋ ግመል (የአላህ ተአምር) በድንጋይ ውስጥ የወጣችበት እንዲሁም ሰሙዶች ግመሏን ካረዱ በኋላ የመጣባቸውን የመብረቅና የጩኸት ቅጣት ተከትሎ ነቢዩ ሷሊህና ሙስሊሞች የዳኑት በዚህ ቀን ነው።
* የነቢዩላህ ሎጥ (ዐ.ሰ)፦ የሰዶም (የሎጥ ህዝቦች) ከተማ ከመገልበጧና የድንጋይ ዝናብ ከመዝነቡ በፊት፣ አላህ ነቢዩ ሎጥንና ቤተሰቦቻቸውን ሌሊቱን በሰላም ያስወጣበትና ያዳነበት ዕለት እንደሆነ ይገለጻል።
* የነቢዩ ሙሐመድ ﷺ፦ አላህ በቅዱስ ቁርዐን ሱራ ፈትህ (48:2) "አላህ ከወንጀልህ ያለፈውንና የሚመጣውንም ለአንተ ሊምርልህ፣ ጸጋውንም በአንተ ላይ ሊሞላልህ፣ ቀጥተኛውንም መንገድ ሊመራህ (ይህን ታላቅ ድል አጎናጸፈህ)።"
በማለት የተናገረለትን ታላቅ የምህረትና የክብር አክሊል ለነቢያችን ﷺ ያረጋገጠበት ዕለት ነው።
የተሰውፍ ሊቃውንት (መሻኢኾች) እንደገለጹት፣ አላህ ይህንን ዓለም በውጫዊ ነገሥታት ብቻ ሳይሆን በውስጣዊ አውሊያኦቹ (በመንፈሳዊ መዋቅር ወይም ዲዋን) ያስተዳድራታል። ይህ መዋቅር ደግሞ በየዓመቱ በአሹራ ሌሊትና ቀን ትልቅ ሽግግር ያደርጋል።
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 257 |
| 8 | #ሹማምንት
በተሰውፍ ውስጥ የመንፈሳዊ መሪዎች እና የወሊዮች (አውሊያኦች) መንፈሳዊ የሹመት ደረጃ በዝርዝር እንደሚከተለው ነው፦
1. ቁጥብ፦ በአንድ ዘመን በአለም ላይ አንድ ቁጥብ ብቻ ሲኖር የበላይ መሪ ነው። የአለም መንፈሳዊ ምሰሶ ነው፤ መለኮታዊ እዝነት፣ ኑር (ብርሃን) እና ሲሳይ ወደ አለም የሚፈስሰው በእሱ ልብ አማካኝነት ነው።
2. ኢማመይን፦ ሁለት ሲሆኑ ከቁጥቡ ቀጥሎ ያሉ የግራና የቀኝ ረዳቶች ናቸው።
*የቀኙ ኢማም፦ የማይታየውንና የመንፈሳዊውን አለም (ዓለመል መለኩት) ይቆጣጠራል።
*የግራው ኢማም፦ የሚታየውንና ቁሳዊውን አለም (ዓለመል ሙልክ) ይከታተላል። ቁጥቡ ሲያልፍ በቦታው የሚተካው ይህ የግራው ኢማም ነው።
3. አውታድ፦ ቁጥራቸው አራት ሲሆኑ የአለም አራቱ ማዕዘናት ምሰሶዎች ናቸው። እያንዳንዱ አውታድ በአራቱ የአለም አቅጣጫዎች (ምስራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ) ተመድበው በየአቅጣጫው ያለውን ሰላምና ሚዛን የመጠበቅ አደራ አለባቸው።
4. አብዳል፦ ብዛታቸው አርባ ሲሆን፤ በአለም ላይ በረከትና እዝነት እንዲወርድ፣ ጦርነትና መቅሰፍት እንዲከላከል ሌሊትና ቀን የሚጸልዩ ናቸው። አንዱ ሲሞት ሌላው ወዲያው ስለሚተካ "አብዳል" (ተለዋዋጮች) ተባሉ። መሪያቸው ሰይዲ ኸድር አሰ ናቸው።
5. ኑቀባእ፦ ብዛታቸው ሰላሳ ሲሆን የሰዎችን ውስጣዊ ማንነት፣ የልብ ሚስጥር እና የተንኮል ሀሳቦችን የመለየት ልዩ መንፈሳዊ እውቀት ተሰጥቷቸዋል።
6. ኑጀባእ፦ ሰባ የሚደርሱ ሲሆን፤ የሰዎችን ከባድ ሸክምና ችግር በመሸከም፣ ሰዎችን በማስታረቅ እና ሰብአዊ እርዳታዎችን በመንፈሳዊው መንገድ በማቅለል ላይ የተሰማሩ ናቸው።
7. አኽያር፦ እስከ 500 ይደርሳሉ ሁልጊዜ በመልካም ስራ ላይ የተሰማሩ፣ ከክፉ ነገር የራቁ እና ዱአቸው ፈጣን ምላሽ የሚያገኝ ታላላቅ ወሊዮች ናቸው።
8. አብራር፦ ቁጥራቸው በውል አይታወቅም። መላ ህይወታቸውን ለዒባዳ እና ሰዎችን ለመርዳት የሰጡ፣ ልባቸው ከቂምና ከምቀኝነት የጠራች ወሊዮች ናቸው። በአለም ላይ የሚከሰቱ አብዛኞቹን በጎ ነገሮች በዱዓቸው ይደግፋሉ።
9. አምድ ወይም ዐሙድ፦ ብዛታቸው 360 ነው። በእያንዳንዱ የአለም ክፍል ተበትነው የሚኖሩ፣ የሰዎችን እምነትና መንፈሳዊ ጥንካሬ ልክ እንደ አምድ ደግፈው የሚይዙ ታላላቅ ባሮች ናቸው።
10. ኡመላእ ፦ በቁጥር አይገደቡም፤ እነዚህ በአላህና በፈጣሪ መካከል። ያሉትን ሚስጥራት ጠባቂዎች ናቸው። ሸሪዓን በትክክል በመተግበር እና ለሰዎች በማስተማር ይታወቃሉ።
11. አምሳል፦ በጣም ብዙ ናቸው። "ምሳሌዎቹ" ማለት ነው፤ በህዝብ መካከል እየኖሩ በመልካም ስነ-ምግባራቸው፣ በትህትናቸውና በቁጥብነታቸው ለሌላው ሰው አርአያና ምሳሌ የሚሆኑ አማኞች ናቸው።
12. ሷሊሒን፦ እነዚህ ግዴታ የሆኑትን የእምነት ስራዎች በትክክል የሚተገብሩ፣ ከተከለከሉ (ሀራም) ነገሮች ሙሉ በሙሉ የሚርቁ እና በሰዎች መካከል በደግነታቸው የሚታወቁ አማኞች ናቸው። ለሌላው ደረጃ መሸጋገሪያ የመጀመሪያው መሰላል ተደርገው ይወሰዳሉ።
13. ቃኒቲን፦ ለፈጣሪ ትዕዛዝ ፍጹም ተገዢ የሆኑ፣ በኢባዳ ላይ ረጅም ጊዜ የሚያሳልፉ እና ውስጣዊ ትህትና ያላቸው (ኹሹዕ ያላቸው) ባሮች ናቸው።
14. ሻኪሪን፦ በደስታም ሆነ በመከራ ጊዜ አምላካቸውን ከማመስገን የማይቦዝኑ፣ ፈጣሪ በሰጣቸው ጥቂት ነገር የሚረኩ (ቃኒዕ የሆኑ) ናቸው።
15. ሳቢሪን፦ በመከራ፣ በበሽታ ወይም በችግር ጊዜ ፍጹም ትዕግስትን የሚያሳዩ፣ በፈጣሪ ውሳኔ (ቀዷ ወቀድር) ላይ የማይማረሩ እና በትዕግስታቸው ምክንያት መንፈሳዊ ጥንካሬን የሚያገኙ ናቸው።
16. ሙእሚኒን፦ በልባቸው ውስጥ እውነተኛ እምነት (ኢማን) ያላቸው፣ ነገር ግን አሁንም ድረስ ከራሳቸው ነፍስና ስሜት ጋር የሚታገሉ፣ ጥፋት ሲያጠፉ ወዲያውኑ ተውበት (ንስሀ) የሚያደርጉ አጠቃላይ ሙስሊሞች ናቸው።
#አፍራድ፦ ከጠቅላላው የሪጃሉል ጋይብ (የማይታየው አለም ሰዎች) መዋቅር እና ህግጋት ውጪ የሆኑ፣ ቀጥታ ከአላህ ብቻ ትዕዛዝ የሚቀበሉ በጣም ጥቂትና ነጻ የሆኑ ታላላቅ ነቢያትና ወሊዮች የሚገኙበት ደረጃ ነው። ከነዚህ ውስጥ ኸድር (ዐ.ሰ) እና ነቢዩ ኢልያስ (ዐ.ሰ) ይገኙበታል።
ማሳሰቢያ፦ እነዚህ ሁሉ መንፈሳዊ መሪዎች እራሳቸውን ደብቀው፣ ዝናን ሳይፈልጉ፣ በተራ ህዝብ መካከል ተደባልቀው የሚኖሩ በመሆናቸው በተራ አይን በቀላሉ አይታወቁም። መዋቅሩ የአለምን መንፈሳዊ ሰላምና ስነ-ስርዓት ለመጠበቅ በአላህ ፍቃድ የሚሰራም ነው።
#መገርገቢያ
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 225 |
| 9 | #የሰይዱና_ኸድር_ቅዳሜ
"ቢስሚላሂ ማሻአላህ፣ ላ የሱቁል ኸይረ ኢለላህ። ቢስሚላሂ ማሻአላህ፣ ላ የሥሪፉ ሱአ ኢለላህ። ቢስሚላሂ ማሻአላህ፣ ማ ካነ ሚን ኒዕመቲን ፈሚነላህ። ቢስሚላሂ ማሻአላህ፣ ላ ሐውላ ወላ ቁወተ ኢላ ቢላህ።"
(በአላህ ስም አላህ የሻው ይሆናል፤ መልካም ነገርን ከአላህ በስተቀር ማንም አይሰጥም። በአላህ ስም አላህ የሻው ይሆናል፤ መጥፎ ነገርን ከአላህ በስተቀር ማንም አይመልሰውም። በአላህ ስም አላህ የሻው ይሆናል፤ ማንኛውም ጸጋ ከአላህ ዘንድ ነው። በአላህ ስም አላህ የሻው ይሆናል፤ ከአላህ በስተቀር ምንም ብልሃትና ኃይል የለም።)
ይህንን ዚክር ጠዋትና ማታ 3 ወይም 7 ጊዜ ማለት ሰይድና ኸድርን ለመገናኘት ይረዳል።
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 278 |
| 10 | #ለይለተል_ጁሙኣ
ታላቁ ታቢዒይ ጣዉስ ኢብኑ ከይሳን (ረሒመሁላህ) እንዲህ ይላሉ፦
አንድ የጁሙዓ ምሽት በመካ በካዕባ አጠገብ ሳለሁ፣ በአለባበሱ በጣም ደሃና ምስኪን የሆነ፣ የጉዞ ድካም ያለበት ሰውዬ አየሁ። ሰውየው ወደ መቃሙ ኢብራሂም ተጠጋና የሌሊት ሶላት መስገድ ጀመረ።
ሶላቱን ጨርሶ ሱጁድ ወረደ። ጣዉስ እንዲህ ይላሉ፡ "ለመሆኑ በዚህ በተባረከ ሌሊት ምን እያለ ዱዓ እንደሚያደርግ ለመስማት ጆሮዬን ጠጋ አደረግኩ።"
ሰውየው በሱጁድ ላይ ሆኖ በዕንባ እየታጠበ አራት አጫጭር ቃላትን ብቻ በተደጋጋሚ ይል ነበር፡
"إِلَهِي عُبَيْدُكَ بِبَابِكَ.. سَائِلُكَ بِبَابِكَ.. فَقِيرُكَ بِبَابِكَ.. مِسْكِينُكَ بِبَابِكَ"
"ጌታዬ ሆይ! ይኸው ትንሽ ባሪያህ በደጅህ ቆሟል.. ጠያቂህ በደጅህ ቆሟል.. ድሃህ በደጅህ ቆሟል.. ምስኪንህ በደጅህ ቆሟል (ማረኝ፣ ስጠኝ)።"
ጣዉስ ይላሉ፦ "እነዚህን ቃላት ደጋግሞ ሲል ልቤ ተነካ። ከዚያን ቀን ጀምሮ እኔም በሕይወቴ ማንኛውም ከባድ ጭንቀት ሲገጥመኝ፣ በለይለተል ጁሙዓ ሌሊት ሱጁድ ወርጄ ይህችን ዱዓ ማድረግ አልተውኩም። ያደረግኳት ጊዜም አላህ ጭንቀቴን ሳይፈታው ቀርቶ አያውቅም!"
የአበባ የጁሙኣ ሰለዋት ስጦታ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ وَعَلَى كُلِّ نَبِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا أَبِي بَكْرٍ وَعَلَى كُلِّ وَلِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا عُمَرَ وَعَلَى كُلِّ تَقِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا عُثْمَانَ وَعَلَى كُلِّ سَخِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا عَلِيٍّ وَعَلَى كُلِّ رَضِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا جِبْرِيلَ وَعَلَى كُلِّ مَلَكٍ (عَشْرَ مَرَّاتٍ).
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 326 |
| 11 | #ጊዜው_ደርሷል
1448ኛው አ.ሂ እነሆ ገብቷል! ዓመቱ የዓለም የኃይል ሚዛን (የፖለቲካና የጂኦፖለቲካ መዋቅር) የሚቀየርበት፣ የድሮዎቹ ኃያላን የሚዳከሙበትና አዳዲስ ኃይሎች የሚወጡበት የሽግግር ወቅት ይሆናል። ይህ ውጥረትና መናወጥ ምድርን በፍትህ ለመሙላት ለሚመጣው መለኮታዊ ለውጥ መንገድ ጠራጊ ነው ተብሎ ይታመናል።
ሼሆቹ እነዚህን ክስተቶች የሚናገሩት ሰውን ለማስፈራራት ሳይሆን፣ መንፈሳዊ ዝግጅት እንዲያደርግ ነው። ለዚህ ዓመት የሚከተሉትን ሶስት ነገሮች አጥብቁ ይላሉ፦
1. ኢስቲግፋር (ምህረት መለመን)
2. ኡዝላህ (ራስን ከጩኸት ማራቅ)
3. ሱህባህ (ከመልካሞች ጋር መሆን)፦ በዚህ የፈተና ዘመን ብቻውን የሚጓዝ ሰው ይበላል፤ ስለዚህ ልባቸው ከፈጣሪ ጋር ከተገናኘ መልካም ሰዎችና መሻኢኮች ጋር መጣበቅ።
ባጭሩ ሼሆቹ የዚህን ዓመት ፍሰት ሲያጠቃልሉት፦ "ውጫዊው ዓለም በከፍተኛ ፍጥነት ይናወጣል፣ ይለወጣልም፤ ነገር ግን በልቡ ውስጥ የአላህን ፍቅርና ሰላም የገነባ ሰው ማዕበሉ አይነካውም" ይላሉ።
በዚህ ዓመት ልቡን አጥብቆ፣ በእውነተኛ ስሜትና እምነት ዱዓእ ለሚያደርግ ሰው ምላሹ በጣም በፍጥነት እንደሚመጣ ይናገራሉ። በተለይ የተበደሉ ሰዎች፣ ምስኪኖችና የልብ ስብራት ያላቸው ሰዎች ጸሎት ምድርን የመለወጥ ኃይሉ ከፍተኛ የሚሆንበት ዓመት ነው።
*ደግ ምንሰማበትና ምናይበት አመት ያድርግልን!
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 589 |
| 12 | #የሰይዲና_ኸድር_ቅዳሜ
የዑስማኒያ ታሪክ ጸሐፊና ተጓዥ ኤቭሊያ ቸለቢ በጉዞ ማስታወሻቸው ላይ እንዲህ ይላሉ፦ ሱልጣን ሙራድ 4ኛ ልክ እንደሌሎቹ የኦቶማን ሱልጣኖች፣ የተራ ሰው ልብስ ለብሰው፣ በሌሊት የሕዝቡን ሁኔታ መፈተሽ ያዘወትሩ ነበር። አንድ ቀን ሌሊት ሱልጣኑ ከታማኝ አገልጋዩ ጋር ሆኖ በኢስታንቡል ታዋቂው የንግድ ማዕከል አቅራቢያ ሲያልፍ፣ በአንድ ትንሽ ሱቅ ውስጥ መብራት በርቶ ይመለከታል። ወደ ሱቁ ጠጋ ሲሉ፣ አንድ በጣም ረጋ ያለ፣ ሽበት የበዛበትና ፊቱ በብርሃን የተሞላ ጫማ ሰፊ ብቻውን ተቀምጦ ጫማ ሲሰፋ ያገኙታል።
ሱልጣኑና አገልጋዩ ተራ መንገደኛ መስለው ወደ ሱቁ ገቡና «ሰላም ላንተ ይሁን አባት ሆይ፣ በዚህ ሌሊት ምን እየሰሩ ነው?» አሉ። ሽማግሌው ቀና ብለው ተመለከቱ፤ የሚገርመው፣ ሱልጣኑ ልብሱን ቀይሮ የመጣ ቢሆንም፣ ገና ሲያዩት ማንነቱን አውቀው ነበር። ሽማግሌውም ፈገግ አሉና «ሰላም ላንተም ይሁን ሱልጣኔ! እንኳን ደህና መጣህ። እኔ የአላህን ሲሳይ ፍለጋ ጫማ እየሰፋሁ ነው» አሉ። ሱልጣን ሙራድ በማንነቱ መታወቅ እጅግ ደነገጠ። ወዲያውም ይህ ሰው ተራ ጫማ ሰፊ እንዳልሆነ ተረዳ። ሱልጣኑ በክብር ተቀምጦ ከሽማግሌው ጋር ማውራት ጀመረ። በጨዋታቸው መሃል፣ ሽማግሌው ጫማውን በሰፉ ቁጥር፣ «ያ ኸድር... ያ ኸድር...» እያሉ ይተነፍሱ ነበር።
ሱልጣኑ ይህንን ሲሰማ በጥንቃቄ ተመለከታቸውና እንዲህ አለ፦ «አባት ሆይ! "ያ ኸድር" እያልክ ትጠራለህ። ለመሆኑ ኸድርን (ዐ.ሰ) አይታችሁ ታውቃላችሁ? ወይስ ዝም ብላችሁ ነው ስሙን የምታነሱ?» ጫማ ሰፊው ሽማግሌ መርፌቸውን አስቀመጡና ወደ ሱልጣን ሙራድ 4ኛ ቀረብ ብለው ፈገግ አሉ፦ «ሱልጣን ሆይ! አንዳንድ ሰዎች ኸድርን ለማግኘት እድሜያቸውን ሙሉ በተራራና በባህር ዳርቻ ይፈልጉታል። ነገር ግን ኸድር አንዳንድ ጊዜ በየቀኑ ወደ ሱቃቸው እየመጣ አጠገባቸው እንደሚቀመጥ አያውቁም። ለምሳሌ አሁን እኔ "ያ ኸድር" ባልኩ ቁጥር፣ እርሱ እዚህ አጠገቤ ተቀምጦ መርፌውን ሲያቀብለኝ ይታየኛል» አሉ።
ሱልጣኑ ይህንን ሲሰማ በሰውነቱ ላይ የደስታና የፍርሃት ስሜት ፈሰሰ። ወዲያውኑ ሽማግሌውን በጥብቅ ተመልክቶ «እባክህ ያ ሰይዲና! አንተ እራስህ ኸድር ነህ አይደል?» ብሎ እጁን ሊስም ተጠጋ። ሽማግሌው ግን እጃቸውን ሳቡና፦ «አይደለሁም ሱልጣኔ፣ እኔማ የኸድር ምስኪን ወዳጁ ነኝ። እርሱ ግን አሁን ከዚህ ሱቅ ወጥቶ ወደ ባህር ዳርቻው ሄዷል» አሉት። ሱልጣን ሙራድ 4ኛ ከዚያ ሱቅ የወጣው የዱንያ ንግሥና ከተራው ጫማ ሰፊ መንፈሳዊ ደረጃ ጋር ሲነጻጸር ምን ያህል ኢምንት እንደሆነ ተረድቶ ነበር።
አላሁመ ሷሊ ወሰሊም አላ ሰይዲና ሙሐመድ!
አላሁመ ሷሊ አላ ሰይዲና ኸድር!
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 367 |
| 13 | #ለይለተል_ጁሙኣ
ታዋቂው የኦቶማን ተጓዥ እና የታሪክ ጸሐፊ እቭሊያ ቸለቢ ገና የ20 ዓመት ወጣት እያለ፣ ልቡ በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ፍቅር የተቃጠለ እና ሁልጊዜም እርሳቸውን በህልሙ ለማየት የሚናፍቅ ስስ ልብ የነበረው ወጣት ነበር። በኢስታንቡል ከተማ ይኖር በነበረበት ወቅት፣ በአንድ የተባረከ የጁምዓ ምሽት (ለይለተል ጁምዓ) ሌሊቱን ሙሉ ቁርዓን ሲቀራ፣ ሰለዋት ሲያወርድና እያለቀሰ ዱዓ ሲያደርግ አደረ። በለሊቱ መጨረሻ ላይ እዚያው ቁርዓኑ ላይ እንዳለ እንቅልፍ ወሰደው። እቭሊያ ቸለቢ በህልሙ እራሱን በኢስታንቡል ከተማ በሚገኘው በታዋቂው "አሂ ቸለቢ መስጂድ" ውስጥ አገኘው። መስጂዱ በሰው የተሞላ ቢሆንም፣ በውስጡ ያሉት ሰዎች በሙሉ መላእክት፣ ታላላቅ ሶሃቦችና ሰማዕታት ነበሩ። መላው መስጂድ በብርሃን (ኑር) ተሞልቷል።
በድንገት ከመስጂዱ ሚህራብ (የሶላት መሪው ቦታ) አጠገብ ፍጹም ብርሃን የሆኑት ነብዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) በግርማ ሞገስ ተቀምጠው ተመለከተ። ሰሃባው ሰዕድ እብኑ አቢ ወቃስ (ረ.ዐ) እቭሊያ ቸለቢን እጁን ይዞ ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ፊት አቀረበው።
ወጣቱ እቭሊያ ቸለቢ በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ግርማ ሞገስና ውበት ፍጹም ተደንቆ፣ ልቡ በደስታና በፍርሃት እየመታች እግራቸው ስር ወደቀ። ከመምጣቱ በፊት በለይለተል ጁምዓ ሲያለቅስ የነበረው ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) "የእርስዎን አማላጅነት (ሸፋዐት) እፈልጋለሁ" ለማለት ነበር።
ነገር ግን በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ፊት በቆመ ጊዜ፣ በደስታና በድንጋጤ ብዛት አንደበቱ ተሳሰረ። "ሸፋዐት ያ ረሱለላህ" ማለት ሲገባው፣ በአፉ የመጣውና የተናገረው እንዲህ ነበር፡ "ሰያሀት ያ ረሱለላህ!" (የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ጉዞ/ጉብኝትን እሻለሁ!)
ታላቁ ነብዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የወጣቱን መሳሳትና የልቡን ንፅህና ተመልክተው በደማቅ ሁኔታ ፈገግ አሉ። ከዚያም የተሳሳተውንም ያልተሳሳተውንም አጣምረው እንዲህ አሉት፦ "አላህ ሁለቱንም ይስጥህ! ሸፋዐቴም (አማላጅነቴም)፣ ሰያሀትህም (ጉዞህም) ይስጥህ፤ የአለምን ድንቆች የምታይበትና የምትመሰክርበት ረጅም እድሜ ይስጥህ!" አሉት።
በመቀጠልም በቦታው የነበሩት ሶሃቦች በሙሉ ለእቭሊያ ቸለቢ ዱዓ አደረጉለት። ከህልሙ በደስታና በዕንባ ተውጦ ሲነቃ፣ ያ የተባረከ የአርብ ምሽት ህልም የሕይወቱ መመሪያ እንደሆነ ተረዳ።
ከዚህ የለይለተል ጁምዓ መናም በኋላ፣ እቭሊያ ቸለቢ ከኢስታንቡል በመነሳት በመላው የኦቶማን ግዛት፣ በአውሮፓ፣ በሰሜን አፍሪካ እና በመካከለኛው ምስራቅ (መካ እና መዲናን ጨምሮ) ለ50 ዓመታት ያህል ተጓዘ። ያየውንና የታዘበውን ሁሉ "ሰያሀት ናሜ" (የጉዞ ማስታወሻ) በሚባለው ታዋቂ የ10 ጥራዝ መጽሐፉ ውስጥ አሰፈረው።
በጁሙኣ የአባባ ሰለዋት ስጦታ
<اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى مَركَز الأَنْبِيَاءُ وَالأَوْلِيَاءُ ، وَآلِهِ وَصَحْبِهِ أُولِي الْفَضْلِ وَالأَتْقِيَاءِ.>
#መደድ_ያአላህ!
#ሸፈኣት_ያረሱሉሏህ!
#ሂመት_ያአባራሙዝ!
@abduftsemier
@abduftsemier | 385 |
| 14 | أهل المودة في فناء جالو
إلى أن وصلوا في الجهات سارو
اللهم صلى على محمد (٢)
مدينة النور وأرباب الصفا | 1 |
| 15 | #የሰይዲና_ኸድር_ቅዳሜ
ሱልጣን አብዱልሀሚድ በጣም አስቸጋሪና የሀገር ህልውና የሚወሰንበት ዲፕሎማሲያዊ ቀውስ በገጠማቸው ቁጥር፣ ወደ ግል መስገጃ ክፍላቸው (ኸልዋ) ይገቡና ረጅም ሰዓት ይቆያሉ። በአንድ ወቅት፣ አንድ የቅርብ አገልጋያቸው በሩ ላይ ቆሞ ሳለ፣ ሱልጣኑ በክፍሉ ውስጥ ከሌላ ሰው ጋር በዝቅተኛ ድምፅ ሲነጋገሩ ይሰማል። ነገር ግን ወደ ክፍሉ የገባ ምንም ሰው አልነበረም። በኋላ ላይ ሱልጣኑ ከክፍሉ ሲወጡ ፊታቸው በደስታ በርቶ ነበር። አገልጋዩ ደፍሮ «ሱልጣኔ ሆይ! ብቻዎን ሆነው ማንኑን እያማከሩ ነበር?» ብሎ ጠየቃቸው። ሱልጣኑም ፈገግ ብለው፦ «በዚህ የጭንቅ ሰዓት ዑስማኒያን ብቻዋን የማይተዋትና በአላህ ፍቃድ መመሪያ ይዞልኝ የሚመጣው ሰይዲና ኸድር ነበረ። እርሱ አሁን የመጣው የፈረንሳይንና የእንግሊዝን ተንኮል እንዴት እንደምሰብር ሊነግረኝ ነው» በማለት ምስጢሩን ገልጠውለታል።
በሌላ ጊዜ የጁምዓ ሶላት ከተሰገደ በኋላ፣ ሱልጣን አብዱልሀሚድ ከሕዝቡ ጋር ሰላምታ እየተለዋወጡ ሳለ፣ አንድ በጣም ያረጀ ልብስ የለበሰ፣ አይኑ ገርመም የሚያደርግ ሽማግሌ ወደ ሱልጣኑ ቀረበ። ሽማግሌው የሱልጣኑን እጅ በጥብቅ ይዞ ሰላም ካላቸው በኋላ፣ በጆሯቸው ጠጋ ብሎ «የአላህ አደራ በአንተ ላይ ይሁን፣ በፅናት ቁም!» አላቸው። ሱልጣኑ የሰውየውን እጅ በያዙበት ቅጽበት፣ በሰውነታቸው ላይ ልዩ የመንፈስ እርካታና ሙቀት ተሰማቸው። ሰውየው ሰይዲና ኸድር መሆናቸውን ወዲያውኑ የተረዱት ሱልጣኑ፣ እጃቸውን ሳይለቁ «ዱዓእ አድርጉልኝ ያ ሰይዲና» አሏቸው። ሽማግሌውም ፈገግ ብለው «አላህ ካንተ ጋር ነው» ካሉ በኋላ፣ ወደ ህዝቡ መሃል ገብተው በአንድ ቅጽበት ተሰውሩ።
ሱልጣን አብዱልሀሚድ በ1909 ዓ.ም (በምዕራባውያንና በሀገር ውስጥ ተንኮለኞች ሰበብ) መፈንቅለ መንግስት ሲደረገባቸውና ዑስማኒያ ወደ መፍረስ በተቃረበችበት ወቅት፣ በኢስታንቡል የነበሩ ታላላቅ አውሊያዎች (ለምሳሌ እንደ ሸይኽ ዛፊር ያሉ) በህልማቸውና በከሽፋቸው ያዩትን ታሪክ እንዲህ ሲሉ ዘግበውታል፦ «ሱልጣኑ ከስልጣን በወረዱበት ሌሊት፣ ሰይዲና ኸድር በኢስታንቡል ባህር ዳርቻ ላይ ቆመው በከፍተኛ ሃዘን ሲያለቅሱ ታዩ። "ዛሬ የዑስማኒያ መንፈሳዊ ጋሻ ተሰበረ፣ ለኢስላም ኡማ የሚያለቅሰው የአላህ ወዳጅ ወደቀ" እያሉ አዝነዋል።»
"O yüce Osmanlılara selam olsun!"
"ሰላም ለታላቆቹ ዑስማኖች!"✋
*አላሁመ ሷሊ ወሰሊም አላ መርከዚል አንቢያዕ ወል አውሊያዕ!
*አላሁመ ሷሊ አላ ሰይዲና ኸድር!
#አባ_ደዋም
#እነሆ_አዲሱ_ዘመን!
@abduftsemier
@abduftsemier | 388 |
| 16 | #101_አመታት_ያለ_ኸሊፋ💔
ታላቁ ኸሊፋ የፍልስጤም ጠበቃ የኡስማኖች ሱልጣን አብዱልሀሚድ ሁልጊዜ የኸሚስ ምሽት (የጁሙዓ ለሊት) ሲመጣ የመንግስትን ስራዎች በሙሉ ያቆሙና ለሊቱን በሰለዋት፣ በዚክርና በሰላት ያሳልፉ ነበር። "ይህ ለሊት የአላህና የመልእክተኛው (ሰ.ዐ.ወ) ብቻ ነው" በማለት።
አንድ የጁሙዓ ለሊት ግን በሚቀጥለው ቀን ጠዋት መውጣት ያለበት እጅግ አስቸኳይና የኡማውን ደህንነት የሚመለከት ውሳኔ ነበረ። ሱልጣኑ ለሊቱን በዒባዳ አሳልፈው በሰለዋት ተመስጦ ላይ ሳሉ እንቅልፍ ይወስዳቸዋል። በህልማቸውም ነቢዩ ሙሐመድን (ሰ.ዐ.ወ) ያያሉ። የአላህ መልእክተኛም (ሰ.ዐ.ወ) ፈገግ ብለው እንዲህ አሏቸው፦
<"ልጄ አብዱልሀሚድ ሆይ! ዛሬ በጁሙዓ ለሊት በእኔ ላይ የምታወርደው ሰላዋት ደርሶኛል። የኡማው ጉዳይ አያስጨንቅህ፣ ወደ ስራህ ተመለስ፤ እኛ ከጎንህ ነን።">
ሱልጣን አብዱልሀሚድ በከፍተኛ ድንጋጤና ደስታ ከህልማቸው ባነኑ፤ ወዲያውኑ በእኩለ ሌሊት ፓሻውን አስጠሩት። ፓሻው በለሊት መጠራታቸው አስደንግጦቸው ሲመጡ፣ ሱልጣኑ ሰነዱን አውጥተው ፈረሙበት። ሱልጣኑ እያለቀሱ ለፓሻው እንዲህ አሉት፦ "ይህንን ሰነድ የፈረምኩት በራሴ ፍላጎት አይደለም፤ የጁሙዓ ለሊት ባለቤት የሆኑት ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ፈርመው ስላሉኝ ነው!" ይህንን ሲሰሙ በጋራ እያለቀሱ ለሊቱን በሰለዋት አደሩ።
*ሱልጣኑ የጁሙዓ ለሊት ሲገባ ቀኑን ሙሉ በውዱእ ለመቆየት ይጥሩ ነበር። ሌላው ቀርቶ ከእንቅልፋቸው ሲነቁ ውዱእ ለማድረግ እስከሚሄዱ ድረስ መሬቱን በባዶ እግራቸው እንዳይረግጡ ከአልጋቸው አጠገብ ያለውን አፈር ታያሙም ያደርጉበት ነበር።
*በጁሙዓ ለሊት ከመካና መዲና የሚመጡ ደብዳቤዎች ካሉ፣ ሌላውን የመንግስት ስራ አቁመው እነዚያን ቅዱሳን ቦታዎች ለማክበር ሲሉ ደብዳቤዎቹን በቆሙበት ሆነው ያነቡ ነበር።
"O yüce Osmanlılara selam olsun!"
"ሰላም ለታላቆቹ ዑስማኖች!"✋
በጁሙኣ የአባባ ሰለዋት ስጦታ
<اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى مَركَز الأَنْبِيَاءُ وَالأَوْلِيَاءُ ، وَآلِهِ وَصَحْبِهِ أُولِي الْفَضْلِ وَالأَتْقِيَاءِ.>
በእነዚህ 101 አመታት ሙስሊሙ አለም ጭንቅላት እንደሌለው ሰው ሆኖል። በቃቹ ይበለን!
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 830 |
| 17 | #ሂ_ባባ
በቻይና የእስልምና ታሪክ ውስጥ የቃዲሪያ ጠሪቃን እና ማህበረሰቡን በመንፈሳዊ እውቀት ያነፁ ታላቅ መሪ ናቸው። በቻይና ሙስሊሞች ዘንድ «ሂላል አል-ዲን» ወይም በሰፊው «ሂ ባባ» እየተባሉ በታላቅ አክብሮት ይጠራሉ።
ሂ ባባ ስማቸው ጪ ጂንግዪ (祁静)
ሲሆን፤ የተወለዱት በ1656 እ.ኤ.አ. በኪንግ ስርወ-መንግስት ዘመን በጋንሱ ግዛት በሊንዢያ ከተማ ነው። ከተማዋ በታሪኳ በርካታ ሙስሊሞች የሚኖሩባት እና «የቻይናዋ መካ» እየተባለች የምትጠራ ስፍራ ናት። ሂ ባባ ገና በወጣትነታቸው በዒባዳ የጠነከሩ እና ጥልቅ የሆነ መንፈሳዊ ጥማት የነበራቸው ሰው ነበሩ። በወቅቱ በመካከለኛው እስያ እና በቻይና መካከል የነበረውን የሐር ንግድ ተከትለው የሚመጡ ታላላቅ መሻይኾችን በማግኘት እውቀት ለመቅሰም ከፍተኛ ጥረት ያደርጉ ነበር።
የሂ ባባ ህይወት ሙሉ በሙሉ የተቀየረው በ1672 እ.ኤ.አ. ታላቁን መምህር ኸውጃ አፋቅ በተገናኙ ጊዜ ነበር። ኸውጃ አፋቅ ከመካከለኛው እስያ (ከካሽጋር) ተነስተው እስልምናን ለማስተማር ወደ ዢኒንግ መጥተው ነበር። ሂ ባባ ወደ መምህሩ ዘንድ በመቅረብ የሱፊያ መንገድን በጥልቀት ተማሩ። ኸውጃ አፋቅ የሂ ባባን ታማኝነት፣ ትህትና እና የውስጥ ንፅህና በመመልከት የቃዲሪያን መንገድ በቻይና እንዲመሩ እና እንዲያስፋፉ ኢጃዛ (መንፈሳዊ ፈቃድ) ሰጧቸው። ይህ ክስተት የቃዲሪያ ጠሪቃ በቻይና መሬት ላይ በይፋ ስር እንዲሰድ ማዕዘን ድንጋይ ሆነ።
ሂ ባባ መንገዱን ሲመሩ የነበራቸው አቀራረብ ከሌሎቹ የቻይና ሱፊ መሪዎች እጅግ የተለየ እና ማራኪ ነበር፦ ሂ ባባ በዱንያዊ (አለማዊ) ክብርና ስልጣን ላይ ምንም ፍላጎት አልነበራቸውም። ተከታዮቻቸውም ጊዜያቸውን በጸጥተኛ ዚክር (ኸፊይ) እና በቁርዓን ንባብ እንዲያሳልፉ ይመክሩ ነበር። በመላው ሰሜን ምዕራብ ቻይና እየተዘዋወሩ በርካታ ሙሪዶችን አፍርተዋል። እነዚህ ሙሪዶች በኋላ ላይ ጦሪቃን በተለያዩ የቻይና ግዛቶች አስፋፍተዋል።
ሂ ባባ በ1719 እ.ኤ.አ. በተወለዱባት ሊንዢያ ከተማ አረፉ። የእሳቸው ማረፍ ተከታዮቻቸውን እጅግ ያሳዘነ ቢሆንም፥ የእሳቸው መንፈሳዊ መገኘት ግን አልጠፋም። ከተለያዩ የቻይና ክፍሎች የሚመጡ ሙስሊሞች የእሳቸውን መቃብር ለመጎብኘት እና ዱዓ ለማድረግ ወደዚህ ስፍራ ይመጣሉ። በአሁኑ ጊዜም የሂ ባባ ስም ሲነሳ የቻይና ሙስሊሞች የሚዘክሩት የእሳቸውን ትህትና፣ ሰላማዊነት እና እስልምናን በቻይና ባህል ውስጥ በጥበብ የማስረፅ ችሎታቸውን ነው።
*በቻይና ከቃዲሪያ ውጪ ነቀሽበንዲያ፤ ኩብራዊያን .. የመሳሰሉ ጦሪቃዎች ይገኛሉ።
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 400 |
| 18 | #የሰይዲና_ኸድር_ቅዳሜ
በአንድ የቱርክ መንደር ውስጥ የሚኖር በጣም ደግና አላህን ፈሪ ገበሬ ነበር። ሁልጊዜም ዱዓ ሲያደርግ “ያ አላህ! የሰይድና ኸድርን ፊት ሳላይ እንዳትገለኝ፣ አንዴ እንኳ ቤቴ መጥቶ ማዕዴን እንዲባርክልኝ አድርግ” እያለ ይማጸን ነበር። በአንድ የብርድ ወራት፣ አንድ በጣም የቆሸሸ፣ ልብሱ የተቀደደና የሚያስጠላ ሽታ ያለው ደሃ አረጋዊ መጥቶ በሩን አንኳኳ። ገበሬውና ባለቤቱ ግን ምንም ሳይጸየፉ በፍቅር ተቀብለው፣ እግሩን አጥበው፣ ካላቸው ምርጥ ምግብ አቅርበው አስተናገዱት። አረጋዊውም መግቦቱን አክብሮ ዱዓ አድርጎላቸው ሄደ። በነገታውም በተመሳሳይ ሰዓት፣ ሌላ በጣም ተሳዳቢ፣ ቁጡና ክፉ የሚናገር ለማኝ መጣ። ገበሬው አሁንም በትዕግስት አስተናግዶት ሸኘው። በሦስተኛው ቀንም ሌላ እንግዳ መጥቶ አስተናገዱ።
በዚያው ሰሞን ገበሬው በህልሙ አንድ ታላቅ መሪ አገኘና “ያ አላህ፣ ይሄን ያህል ዘመን ኸድርን አሳየኝ እያልኩ ስለምንህ ለምን አልመጣልኝም?” ብሎ ጠየቀ። በህልሙ የተገለጠው መሪም ሳቅ አለና፦
“የመጀመሪያው ቀን የመጣው ኸድር ነበረ፤ የቤታችሁን ንጽሕናና ቸርነት አየ።
በሁለተኛው ቀን የመጣውም ኸድር ነበረ፤ የእናንተን ትዕግስትና ስነ-ምግባር ፈተነ። በሦስተኛው ቀንም የመጣው ኸድር ነበረ፤ በረከቱን ጥሎላችሁ ሄደ።
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 419 |
| 19 | #አራጁ
ይህችን የቁስ አለም አልፈልጋትም፤
ጀነትንም አይደለም ምፈልገው፤
ከውሰርን አይደለም ምመኘው፤
የምፈልገው አንተን ብቻ ነው።
ጠዋፍ አደረግን ከሰላታችን ቂብላ፤
የኢብራሂም ግቢ ሩህ የምትሞላ፤
ከሶፋ መርዋ ሀጀራ ስትሮጥ በጭንቀት፤
በሶምሶማ ስሮጥ እኔም ለመጥራራት፤
አበበ ትዝ ቢለኝ ሩጫዬን አቀለጥኩት፤
ከኢስማኢል እጅም ዋንጫ ተቀበልኩት፤
ደሞ ስጠጣው ያንን ጣፋጭ ዘምዘም፤
እጅግ መጣፈጡ ነፍስን ያድሳል ለዘላለም።
ደሞ ከአረፋ ተራራ በ9 ኛው ቀን ከጫፉ ወጥቼ፤
የመላኢካን ጥሪ የጌታን ውዳሴ ሰምቼ፤
ያረብ እያልኩት እንባዬን ዘርቼ፤
አቤት ያ አብዲ ሲለኝ መቋቋም አቃተኝ፤
የኔ ከሪም በእዝነቱ አካቦ አቀፈኝ፤
ለሊቱን ለማደር ሀጃጁ ሲታደም፤
ምቾቱ የእንቅልፍ እንዲህ አይነገርም፤
ደሞ የኢዱ ቀን ኡዱሂያ ሲታረድ፤
ኢስማኢል አለኝ ሙክቱን እረድ፤
ጅብሪልን ጠየቅኩት ሙክት ስጠኝ ብዬ፤
እሱም እየሳቀ ኢስማኢልን ሳታርድ ለምንብዬ?
ነፍሳቸውን ለሚያርዱት ሽልማቱ ምንድነው?
አሁን ሀቅ ብለሀል ሙክቱን አመጣው፤
ቢስሚላሂ ተብሎ ሊፀዳ ታረደ፤
የነብሳያችን ቆሻሻ ከእንግዲህ ተወገደ፤
እንዲህ እያልን በብዙ ነጎድን፤
ከሩሁ አለም ከሀጅ ተመለስን።
@abduftsemirr
@abduftsemier | 445 |
| 20 | #ሁለቱ_ነገስታት
ዛሬ የሰይዲና ኸድርና ሰይዲ ኢልያስ (ዐሰ) በአረፋ ዲዋን የሚመሩበት የጉባዔ እለት ነው። ታላቁ ሸይኽ ኢብን አቢ እንደሚያብራሩት፣ የሰይድና ኸድርና የሰይድና ኢልያስ መገናኘት የሁለት ዓለማት መገናኘት ነው።
-ሰይድና ኸድር የባጢን (የምስጢር እውቀት) መገለጫ አድርገው ይመስሏቸዋል። ሰይድና ኢልያስን ደግሞ የ"ዛሂር" (የሸሪዓው እውቀት) ጠባቂ አድርገው ያዩዋቸዋል።
ሰይድና ኸድርና ሰይድና ኢልያስ የሚመሩት ታላቅ የመንፈሳዊ አካላት ጉባኤ ለሚመጣው ዓመት በምድር ላይ ስላለው ሰላም፣ በረከት፣ የዝናብ መዝነብና የሰዎች ሲሳይ (ርዝቅ) ዱዓ ይደረጋል፣ ውሳኔዎችም ይተላለፋሉ።
ሼህ ናዚም ስለዚህ ቀን እንደገለጹት፣ በዚህ ዕለት በሰይድና ኸድርና በሰይድና ኢልያስ መሪነት ታላቅ መንፈሳዊ ስብሰባ (ዲዋን) ይደረጋል። በዚህ ስብሰባ ላይ የነቅሸበንዲያ ሰንሰለት መሻይኾች በሙሉ ይሳተፋሉ። እሳቸው «በዚህ ዕለት አላህ ለሰው ልጆች የሚሰጠውን እዝነት፣ ሲሳይ (ርዝቅ) እና ጥበቃ የሚከፋፍሉት እነሱ ናቸው፤ ስለዚህ ልባችሁን ሰብስባችሁ ዱዓ አድርጉ» ይሉ ነበር።
ሼህ መህሙድ ኢፈንዲ፣ በዚህ ዕለት ሌሊቱን በሰላት (በተሃጁድ) ማሳለፍ፣ ጧት ላይ ሰደቃ መስጠት፣ እና የአላህን በረከት መለመን እንደሚገባ ያስተምራሉ። በተለይም በቱርክ ውስጥ በዚህ ዕለት ሰዎች ምኞታቸውንና ዱዓቸውን በወረቀት ጽፈው ከሮዝ (የጽጌረዳ) ዛፍ ስር የማስቀመጥ ባህል ስላላቸው፣ ሼህ መህሙድ «ምክንያቱ ሰይድና ኸድር በሮዝ ዛፎች አቅራቢያ ስለሚዘዋወሩና ለዱዓችሁ አሚን እንዲሉ ስለሚፈለግ ነው፤ ነገር ግን ዋናው ነገር ዱዓው ከአላህ መሆኑን ማመንና ልብን ማጥራት ነው» ብለዋል።
*ከጉባዔውም ከትልቆቹም ያገናኘን!
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier | 375 |
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
