አባወራ abawora
Open in Telegram
አባወራ፦አባትነት፣ ባልነት፣ ወንድነት፣ ራስነት +251-9-11-67-46-87 https://www.youtube.com/@abawora
Show more1 536
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-230 days
Posts Archive
1 537
ልብአልባው አልጫ፣ ምን ጽድቁን ቢያውቅ አይፈጽመውም!
=====================================
ትውልድን የሚያፈርሰው ዕውቀት ማጣት ብቻ አይደለም፤ እንደውም ያወቀውን እውነት ለመኖር ወኔ ማጣት ነው። ሰው ልቡን፣ ማንነቱን፣ መሠረቱንና እሴቱን ሲያጣ ጽድቁን ቢያውቅም በፈተና ጊዜ ለመፈጸም ይሳነዋል። ይህ ነው አልጫነት፤ የአባወራውም ጥሪ ይህን የጠፋውን ልብ እንደገና ማንሳት ነው! 👇👇👇
https://abawera.substack.com/p/934?r=5gza3&utm_campaign=post&utm_medium=web&showWelcomeOnShare=true
1 537
ተዋጊው ግንበኛ!
==========
ቅጥር ሲፈርስ ማዘን ብቻ አይበቃም፤ መነሳት ያስፈልጋል። ፍርስራሹን እያየን ምክንያት ከመቁጠር ይልቅ፣ የፈረሰውን እንደገና ለመገንባት ቁጭታችንን ወደ ርዕይ፣ ርዕያችንንም ወደ ተግባር መለወጥ አለብን! PDF አለው👇
https://abawera.substack.com/p/692?r=5gza3&utm_campaign=post&utm_medium=web&showWelcomeOnShare=true
1 537
ሴቷን በወንዱ ላይ ትውልድን በእሴቱ ላይ በማሳመጽ ማምከን: በሐሰተኛ ትርክት
==================================
ስለ ትዳር የምትማሩትን “የቅድመ ጋብቻ ሥልጠና” ብለው የሚግቷችሁን ተጠንቀቁ! ኦርቶዶክሳዊው ቤተሰብ ነባር ከኾነው የአባቶቹ እሴት ተነጥሎ፣ መክኖ እንዲጠፋ በራሱ ሆዳደር ሊቃውንት ሴቷን በአመጸኝነት ወንዱን በእንከፍ፣ ምስኪን ጃንደርባነት ይነዱታልና! በየቤታችን እየተለመደ የመጣውን ምስል ታዘብ!👇
https://abawera.substack.com/p/628?r=5gza3&utm_campaign=post&utm_medium=web&showWelcomeOnShare=true
1 537
“አውራ አምባ” ኢትዮጵያዊ እሴት ወይንስ እንደ የስካንዲኔቪያ ሀገራት የጥፋት ተምሳሌት!
=================================
ማኅበረሰቡን ከታሪኩና ከባህላዊ እሴቶቹ ነጥሎ የሚያወጣ የሐሰተኛ ትርክት መርዝ ከማንኛውም ውጫዊ አደጋ በላይ አጥፊ ነው። "ሀገር በቀል" ተብሎ የሚነገረው የ”አውራ አምባ” (አውራ አልባ) ማኅበረሰብ ሐሳብም ከውጭ የተቀዳ የሶሻሊስት አስተሳሰብ እንጂ እውነተኛ ኢትዮጲያዊ የአባቶቻችን እሴት አይደለም!👇👇👇
https://abawera.substack.com/p/1a9?r=5gza3&utm_campaign=post&utm_medium=web&showWelcomeOnShare=true
1 537
ውድቀትን አስከታዩ እብሪት በትኅትና ሲሸለም ይከፋል!
==================================
እብሪት ሁልጊዜ በእብሪት መልክ አይመጣም፤ ትዕቢትም እንዲሁ። አንዳንድ ጊዜ ትኅትናን፣ መንፈሳዊነትን እና የታላላቅ ሰዎችን ውርስ እንኳን ልብስ አድርጎ ይመጣል።
👇👇👇
https://abawera.substack.com/p/587?r=5gza3&utm_campaign=post&utm_medium=web&showWelcomeOnShare=true
1 537
“ለመንግሥተ ሰማያት በንጽሕና” ኖረው፣ መክነው፣ ያለወራሽ ከጠፉ ማኅበረሰቦች እንማር!
=================================
አን አብ የትዳርን ተቋም እንደ ሥጋዊ ባርነት በመቁጠር ከወንድ ሥልጣንና ከተፈጥሯዊ ሥርዓት ያደረገችው አመጽ፣ ሼከርስን ያለወራሽ አስቀርቶ ከምድረ ገጽ አጥፍቷቸዋል።ይህ ጽንፈኛ የ«ንጽህና» ርዕዮት የፈጠረው የጥፋት መንገድ፣ ዛሬም ቤተሰብንና ማኅበራዊ እሴቶችን ከሚያመክኑ አጥፊ ትርክቶች ለመጠበቅ ትምህርት ይሰጠናል!👇👇👇
https://abawera.substack.com/p/403?r=5gza3&utm_campaign=post&utm_medium=web&showWelcomeOnShare=true
1 537
“ጸድቃ የምታጸድቀኝን እንጂ አግዛኝ፣ ወልዳልኝ የምታከብረኝን...”: ጃንደርባ ኾኖ እንዲጠፋ በሊቃውንቱ የተፈረደበት ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ!
==================================
ከላይ በርዕሱ ላይ የተጻፈውን በመንፈሳዊነት ስም የሚነገር ራስወዳድነት “በአንዱ መምህራችን ስንማር የነበረውና የእኔም የረጅም ጊዜ ጸሎት የነበረው እኮ ይህ ነበር ...” ሲል አንዱ በውስጥ መስመር የላከልኝ ነው! በራሳችን “መምህራን” የተጋረጠብንን አስከፊ፥ አደገኛ አጥፊ አደጋ ገብታችሁ አንብቡ!👇👇👇
https://abawera.substack.com/p/1d3?r=5gza3&utm_campaign=post&utm_medium=web&showWelcomeOnShare=true
1 537
"ለመረዳዳት" ስንጋባ በዛን "ለመንግሥተ ሰማይ" ስንጋባ ጠፋን
=================================
“እግዚአብሔር አምላክም አለ፦ ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም፤ የሚመቸውን ረዳት እንፍጠርለት”
በዚህ ታሪካዊ፥ መጽሐፋዊ፥ መለኮታዊ፥ አባታዊ፥ ባህላዊ ኃይለቃል ላይ ትዳራችን ሲመሠረት ተጋግዘን፣ ተረዳድተን፣ ልጆች ወልደን፣ በዛን!
ነገር ግን ሲሰሙት ደስ በሚለው አባቶቻችን በተለየ ሲናገሩት ባልሰማነው ባዕዳን አምጥተው በደባለቁት ኃይለቃል
"የትዳር ዋነኛው ዓላማ መንግሥተ ሰማይ ለመውረስ ነው"
በሚለው "መንግሥተሰማይን" ስናስብ፣ እያሰብን፣ እናስባለን ስንል፣ ለማሰብ ብለን. . . ስንኖር ጋብቻ የሚፈጸምበት፣ የሚቀጥልበት ወሲቡን፣ ፍሬውም ልጆቹን፣ ትውልድን ረስተን፣ ዘንግተን፤
አንድም ከአባቶቻችን ከአባታችንም በላይ "እናውቃለን" ብለን በእብሪት ታጅረን፤ ለኦርቶዶክሳዊው ቤተሰብ ማኅበረሰብ ውድቀት ጥፋቱን አስከተለ፤
መከነ፣ ጠፋ፣ እየጠፋንም ነው!
በራሳችን ሐሰተኛ ትርክት በሚዘሩ "ሊቃውንት"
https://youtu.be/btGHQSZ8HWo
1 537
ጃንደርባነትን ለተቀበለ ትውልድ ማደጎ ማሳደግን “እንደ ሽልማት” ማቅረብ
================================
ስም ማንነትን ይቀርጻል፤ ማንነትም አኗኗርን ይወስናል። ስለዚህ ጃንደርባነትን እንደ ክብር ስም ለትውልድ መስጠት፣ ብሎም ማደጎን እንደ ሽልማት ማቅረብ አንድ የትውልድ ጥፋት አዙሪት ነው።👇👇👇
https://abawera.substack.com/p/9de?r=5gza3&utm_campaign=post&utm_medium=web&showWelcomeOnShare=true
1 537
የሚመቸውን ረዳት
============
እግዚአብሔር አምላክም አለ፦ ሰው ብቻውን ይኾን ዘንድ መልካም አይደለም፤ የሚመቸውን ረዳት እንፍጠርለት። ይህን ነበር የሰርጋችን ዕለት ሊቃውንቱ የሚያስተምሩን ዛሬ ቆዳ ቀይረዋል፤ የበግ ለምድ ለብሰዋል “የትዳር ዓላማ መንግሥተ ሰማይ እንጂ ሌላው ትርፍ ነው” ተብለናል!👇👇👇
https://abawera.substack.com/p/5e6?r=5gza3&utm_campaign=post&utm_medium=web&showWelcomeOnShare=true
1 537
ጃንደርባነት የጸደቀለት ትውልድ እርሱን እውን ለማድረግ (ራሱን ለማምከን) ይሠራል
==================================
ልጅ (ትውልድ)ስሙን ያምናል፣ ለምሳሌ፤ “በባርነት ያልተገዛ ነፃ ትውልድ” ይህ ስም የእርሱ፥ እርሱም እንደኾነ ያምናልና ሲጠራበት ይኖራል፤ እንደስሙ መኖር ሲጀምር የዘወትር መገለጫው ይኾናል፤ እርሱም በየትኛውም አጋጣሚ በንቃትም ይኹን በደመነፍስ ድርጊቱን ይወስናል፤ ከዚያም የተጠራበትን ስም የሚመጥን ትውልድ ይኾናል!👇👇👇
https://abawera.substack.com/p/c63?r=5gza3&utm_campaign=post&utm_medium=web&showWelcomeOnShare=true
