en
Feedback
ጫክ ቢራ ✞ ✟ ✞ መካነ_ኢየሱስ_ማ/ም

ጫክ ቢራ ✞ ✟ ✞ መካነ_ኢየሱስ_ማ/ም

Open in Telegram

Chakbirra Mekane Eyesus Congregation ✟ ✞ ✟ “Behold upon the mountains the feet of him that bringeth good tidings, that publisheth peace! Nah1፥15 Join as Chakbira Youth's official Channel&Group @Chakbirra @Chakbira 👈Discussion

Show more
202
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+130 days
Posts Archive
ለፈገግታ ያህል 😁 አንድ ጊዜ ኢየሱስ ስለ ትዳር ጉዳይ ለባሎች ሲያስተምር አንዴ ካገቡ በኃላ ከአንዷ ሚስታቸው ውጪ ወዴትም ወለምዘለም ማለት እንደማይችሉ ነገራቸው ይሄን  ትምህርቱን የሰሙት  ደቀ መዛሙርቱም ምን እንዳሰቡ ባላቅም ቃል በቃል... “የባልና የሚስት ጒዳይ እንዲህ ከሆነ አለማግባት ይሻላል” ብለው መለሱለት 😊   — ማቴዎስ 19፥10 ታዲያ እንዴት እንዲሆንላቸው ነበር ያሰቡት 😁?  አንዳንዴ መጽሐፍ ቅዱሳቹን ስታነቡ እንደዚህ ዓይነት ፈገግ የሚያስብሉ ነገሮችን ታገኛላቹ🥰 ከ አዶናይ የተወሰደ @Chakbirra

. . የቻርልስ እስፐርጀን ጸሎት ይህ ጸሎት በ 1856 በምሽት የጸለየው ጸሎት ነው። "ጌታ ሆይ እባክህን ሕዝብህን አድን። ሕዝብህን አድን። ጸሎቴ በፊትህ መሆን እንደሚገባው እንዳልሆነ አምናለሁ፤  በጸጋህ እርዳኝ። በሰጠኸኝ ዕድሜና ጸጋ እንደሚገባ እንዳልሰበክሁ የተሰወረ አይደለም። ጌታ ሆይ በኔ በደል ሌሎችን ቸል አትበል። ሕዝብህን አድን፤ በእረኛው ጥፋት መንጋውን አትምታ። ይቅር በላቸው አባት ሆይ፣ ምሕረትህ ከነርሱ ጋር ትሁን። ይቅርታን ያላገኙ ብዙዎች በዚህ አሉ። ይድኑ ዘንድ ምን ያህል እንደደከምን አንተ ታውቃለህና። የሰው ልብ በእውነት ጠንካራ ነው አባት ሆይ፣ ነፍሱም እንደብረት የጠነከረች ነች። ደምና ሥጋ ሰውን ለመለወጥ አይችሉም፤ መጋቢው ተስፋ ያደርጋል፣ አገልጋይህም ያምናል፡፡ ግን ሁለቱም ማዳን አይሆንላቸውም። ጌታ ሆይ አንተ ግን በኃይልህ ትችላለህ። አንተ ካልሳብካቸው ሊከተሉህ አይችሉም። የእሥራኤል አምላክ ሆይ በዚህ ዓመት ደግሞ ይህችን ቤተ-ክርስቲያን እርዳ። ሕዝብህን በጸሎት ባርክ፣ የሥጋን ነገር በመንፈስ ይገድሉ ዘንድ አበርታቸው፣ በዚህ ብቻ ሳይሆን በሁሉ ሥፍራ ኢየሩሳሌምን ለምስጋና እስክታደርጋት ድረስ እንዳያርፉ እርዳቸው፣ የጸሎትን ሃይል ጨምርላቸው  ጌታ ሆይ። የምንጮኸውና የምናነባው ስለቤተክርስቲያንህ ብቻ አይደለም፡፡ ስለ ዓለም ሁሉ እንጂ። በከንቱ እንደማልደክም አልተናገርኸኝምን? ለባሪያዎችህስ ይህንኑ አላልክምን? እንግዲያውስ በሰዎች መዳን አጥግበን፡፡ ‹ዝናብና በረዶ ከሰማይ እንደሚወርድ ምድርን እንደሚያረካ ታበቅልና ታፈራም ዘንድ እንደሚያደርጋት ዘርንም ለሚዘራ እንጀራንም ለሚበላ እንደሚሰጥ እንጂ ወደ ሰማይ እንደማይመለስ ከአፌ የሚወጣ ቃሌ እንዲሁ ይሆናል› ተብሎ እንደተጻፈ ቤተ-ክርስቲያንህን አስፋ። አስፋልን ጌታ ሆይ። ዛሬም በዚህ ምሽት ቃልህ በከንቱ አይመለስ። ባሪያህ በቅን ልብ በርህራኄና በፍቅር የክብሩን ወንጌል እንዲሰብክ እርዳው። መንፈስ ቅዱስ ሆይ ና! ያላንተ ምንም ማድረግ አንችልምና በትሕትና እንጋብዝሃለን፡፡ በአብርሃም ይስሐቅና ያዕቆብ ላይ የነበርክ የከበሩ ሕልሞችን ለሰዎች ትንቢትን ለነቢያት የሰጠህ በሐዋርያትና በቀደመችው ቤተ-ክርስቲያን ላይ ያደርህ ታላቁ የእግዚአብሔር መንፈስ ሆይ በዚህ ምሽት ከኛ ጋር ሁን። በአንተ መገኘት ይህች ምድር ትናወጥ፣ ነፍሳትም ልባቸውን ከፍተው የከበረውን ቃልህን ይስሙ፣ ሥጋ ለባሽ ሁሉ አንተን በማወደስ ሐሤት ያድርግ። ለዘላለም ለሚኖረውና ከፍ ላለው ለአብ፣ ለወልድና ለመንፈስ ቅዱስ ክብር ይሁን።” አሜን ከ GoodChristian book የተወሰደ @Chakbirra

She is so adorable 😍 isn't she? Stay blessed a little soul 🥰🙏

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#TsigeDuguma ፈረንሳይ ፓሪስ ላይ በ800 ሜትር የሴቶች ፍጻሜ ለሀገሯ ኢትዮጵያ የብር ሜዳሊያ ያስገኘችው ፅጌ ዱጉማ ከውድድሩ በኃላ " JESUS IS LORD ! " የሚል ጽሁፍ አሳይታለች። ፅ
+3
#TsigeDuguma ፈረንሳይ ፓሪስ ላይ በ800 ሜትር የሴቶች ፍጻሜ ለሀገሯ ኢትዮጵያ የብር ሜዳሊያ ያስገኘችው ፅጌ ዱጉማ ከውድድሩ በኃላ " JESUS IS LORD ! " የሚል ጽሁፍ አሳይታለች። ፅጌ ስሟ ተጽፎ ደረቷ ላይ ከተለጠፈበት ወረቀት የጀርባ ክፍል ላይ ነው ይህን መልዕክት ፅፋ ገብታ ያስተላለፈችው። የዘንድሮ የፓሪስ ኦሎምፒክ የመክፈቻ ስነስርዓት በክርስቲያኖች ዘንድ ቁጣ ቀስቅሶ እንደነበር ይታወሳል። #TikvahEthiopia @tikvahethiopia @tikvahethsport

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#TsigeDuguma ፈረንሳይ ፓሪስ ላይ በ800 ሜትር የሴቶች ፍጻሜ ለሀገሯ ኢትዮጵያ የብር ሜዳሊያ ያስገኘችው ፅጌ ዱጉማ ከውድድሩ በኃላ " JESUS IS LORD ! " የሚል ጽሁፍ አሳይታለች። ፅ
+3
#TsigeDuguma ፈረንሳይ ፓሪስ ላይ በ800 ሜትር የሴቶች ፍጻሜ ለሀገሯ ኢትዮጵያ የብር ሜዳሊያ ያስገኘችው ፅጌ ዱጉማ ከውድድሩ በኃላ " JESUS IS LORD ! " የሚል ጽሁፍ አሳይታለች። ፅጌ ስሟ ተጽፎ ደረቷ ላይ ከተለጠፈበት ወረቀት የጀርባ ክፍል ላይ ነው ይህን መልዕክት ፅፋ ገብታ ያስተላለፈችው። የዘንድሮ የፓሪስ ኦሎምፒክ የመክፈቻ ስነስርዓት በክርስቲያኖች ዘንድ ቁጣ ቀስቅሶ እንደነበር ይታወሳል። #TikvahEthiopia @tikvahethiopia @tikvahethsport

የአምልኮ መሪዎች ዛሬ ድንቅ የአምልኮ ጊዜ ነበረን ተባረኩ !
የአምልኮ መሪዎች ዛሬ ድንቅ የአምልኮ ጊዜ ነበረን ተባረኩ !

Repost from Dr. Eyob Mamo
ሕይወትህ ሪሴት (Reset) ማድረግን ሲፈልግ አንዳንድ ጊዜ በየቀኑ የምሰራበት ላፕቶፕ የከፈትኩት ስክሪን ላይ ይቆምና አልንቀሳቀስ ይለኛል፡፡ ብዙ ሞክሬ አልሆን ሲለኝ እንደገና ለማስጀመር ሪሴት (Reset) አደርገዋለሁ፡፡ አንዳንድ ጊዜ በእጄ የምጠቀምበት ስልክ ፍጥነቱ ይቀንስብኛል፣ አልፎ አልፎም “አልታዘዝ” ይለኛል፡፡ ይህንና ያን ሞክሬ እምቢ ሲለኝ እንደገና ለማስጀመር ሪሴት (Reset) አደርገዋለሁ፡፡ አንዳንድ ጊዜ እነዚህን ኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎቼን ቫይረስ ሲለክፍብኝ እንደገና ለማስጀመር ሪሴት (Reset) አደርገዋለሁ፡፡ ሕይወት አንዳንድ ጊዜ ሪሴት ማድረግን ትፈልጋለች፡፡ ካለአግባብ ያታገለንን የሕይወት ሁኔታ እንደገና ለማስጀመር ሪሴት (Reset) ማድረግን የሚጠይቀን ሁኔታና ጊዜ አለ፡፡ • ለረጅም ጊዜ ብዙ ታግለን አልንቀሳቀስና እልፍ አላደርግ ያለን የስራ ዘርፍ በመቀየር እንደገና ለማስጀመር ሪሴት (Reset) ማድረግን ሊጠይቅ ይችላል፡፡ • ለራእያችንና ለዓላማችን ምቹ ያልሆነ አካባቢ በመሆን ብዙ ከከረምንና ከታገልን በኋላ አላስኬድና አላንቀሳቅስ ሲለን ስፍራን በመቀየር እንደገና ለማስጀመር ሪሴት (Reset) ማድረግን ሊጠይቅ ይችላል፡፡ • ጤና-ቢስና ብዙ መርዛማ ችግሮች የተጠናወቱትን የግልም ሆነ የቡድን ጓደኝነትን ለማስተካከል ብዙ ታግለን ያተረፍነው ጊዜን ማቃጠልና በስሜት መንደድ ሲሆን እንደገና ለማስጀመር ሪሴት (Reset) ማድረግን ሊጠይቅ ይችላል፡፡ • ካለፍላጎታችንና ካለዝንባሌያችን ጀምረነው በፍጹም አልሄድና አልገፋ ያለንን የትምህርት ዘርፍ እንደገና ለማስጀመር ሪሴት (Reset) ማድረግን ሊጠይቅ ይችላል፡፡ ሕይወት አንዳንድ ጊዜ ሪሴት ማድረግን ትፈልጋለች፡፡ ሆኖም ያንን ከማድረግህ በፊት . . . • እርምጃህ እንደ ትዳር የመሰሉ ቃል ኪዳን የገባህባቸውን ሁኔታዎች የማይነካ መሆኑን አረጋግጥ፡፡ • ሪሴት የማድረግ እርምጃህ በቀጥተኛም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ የሚነካቸውና የሚመለከታቸውን ሰዎች በቅድሚያ ማሳወቅህን አትዘንጋ፡፡ • ሪሴት በማድረግህ ምክንያት የሚነኩ ሰዎች ካሉ ልባዊ ይቅርታን መጠየቅን አትዘንጋ፡፡ • እንደገና በማስጀመርና ሪሴት (Reset) የማድረግ ሰበብ ታግለህና ጸንተህ ማለፍ ከሚገባህ ነገር ለመሸሽ እንዳትተቀምበት ተጠንቀቅ፡፡ • እንደገና የማስጀመሩና ሪሴት (Reset) የማድረጉ ሂደት ሊያስከፍልህ የሚችለውን ዋጋ በሚገባ ተምነህ ተነሳ፡፡ • እንደገና መጀመርና ሁሉን ነገር ሪሴት (Reset) ማድረግ እጃችን የሚያስገባው ነገር የመኖሩን ያህል ከእጃችንም የሚያወጣው ነገር እንዳለ በመገንዘብ ጥንቃቄን አድርግ፡፡ • እንደገና የማስጀመርና ሪሴት (Reset) የማድረግ ሁኔታ ሂደት እንጂ ክስተት ስላልሆነ በግል ለማሰብ፣ ሰውን ለማማከር፣ እቅድን ለማውጣትና በቂ ዝግጅት ለማድረግ ጊዜን መውሰድህን አትዘንጋ፡፡ https://t.me/Dreyob https://m.youtube.com/user/naeleyob623 https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/

ነገ እሮብ ጠዋት 2:00 ሰዓት ጀምሮ በወንጌል ስርጭት ቡድን ላላቹ አባላት የወንጌል ስርጭት ስልጠና ስለሚኖረን ማስታወሻ እና መጽሀፍ ቅዱስ ይዛቹ እንድትመጡ🙏 @Chakbirra