en
Feedback
Addis Admass

Addis Admass

Open in Telegram

የአዲስ አድማስ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ ===== አዲስ አድማስ https://bit.ly/2V1zyZQ ፌስቡክ↠ https://bit.ly/2V0I6jx ትዊተር↠ https://bit.ly/33fDhaP ቴሌግራም↠ https://bit.ly/2JgeCvG ዩቲዩብ ↠ https://bit.ly/3q2hXiv የእርስዎና የቤተሰብዎ

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Addis Admass

Channel Addis Admass (@adissadmas) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 18 741 subscribers, ranking 12 020 in the News & Media category and 1 849 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 18 741 subscribers.

According to the latest data from 06 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 244 over the last 30 days and by 2 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 10.21%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 8.19% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 1 914 views. Within the first day, a publication typically gains 1 535 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 8.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“የአዲስ አድማስ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ ===== አዲስ አድማስ https://bit.ly/2V1zyZQ ፌስቡክ↠ https://bit.ly/2V0I6jx ትዊተር↠ https://bit.ly/33fDhaP ቴሌግራም↠ https://bit.ly/2JgeCvG ዩቲዩብ ↠ https://bit.ly/3q2hXiv የእርስዎና የቤተሰብዎ”

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 07 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

18 741
Subscribers
+224 hours
+1157 days
+24430 days
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+121
in 0 channels
August '26
+362
in 6 channels
Get PRO
July '26
+614
in 7 channels
Get PRO
June '26
+261
in 2 channels
Get PRO
May '26
+350
in 2 channels
Get PRO
April '26
+303
in 2 channels
Get PRO
March '26
+330
in 1 channels
Get PRO
February '26
+285
in 1 channels
Get PRO
January '26
+371
in 1 channels
Get PRO
December '25
+295
in 1 channels
Get PRO
November '25
+169
in 1 channels
Get PRO
October '25
+443
in 6 channels
Get PRO
September '25
+727
in 5 channels
Get PRO
August '25
+956
in 3 channels
Get PRO
July '25
+1 043
in 6 channels
Get PRO
June '25
+572
in 4 channels
Get PRO
May '25
+2 185
in 3 channels
Get PRO
April '25
+182
in 1 channels
Get PRO
March '25
+86
in 4 channels
Get PRO
February '25
+52
in 1 channels
Get PRO
January '25
+157
in 4 channels
Get PRO
December '24
+158
in 3 channels
Get PRO
November '24
+160
in 2 channels
Get PRO
October '24
+135
in 6 channels
Get PRO
September '24
+103
in 2 channels
Get PRO
August '24
+337
in 1 channels
Get PRO
July '24
+528
in 1 channels
Get PRO
June '24
+372
in 0 channels
Get PRO
May '24
+275
in 0 channels
Get PRO
April '24
+549
in 0 channels
Get PRO
March '24
+888
in 2 channels
Get PRO
February '24
+779
in 3 channels
Get PRO
January '24
+589
in 2 channels
Get PRO
December '23
+436
in 0 channels
Get PRO
November '23
+362
in 3 channels
Get PRO
October '23
+248
in 1 channels
Get PRO
September '23
+166
in 0 channels
Get PRO
August '23
+149
in 0 channels
Get PRO
July '23
+150
in 0 channels
Get PRO
June '23
+337
in 0 channels
Get PRO
May '23
+314
in 0 channels
Get PRO
April '23
+397
in 0 channels
Get PRO
March '23
+273
in 0 channels
Get PRO
February '23
+304
in 0 channels
Get PRO
January '23
+423
in 0 channels
Get PRO
December '22
+431
in 0 channels
Get PRO
November '22
+178
in 0 channels
Get PRO
October '22
+255
in 0 channels
Get PRO
September '22
+368
in 0 channels
Get PRO
August '22
+482
in 0 channels
Get PRO
July '22
+686
in 0 channels
Get PRO
June '22
+229
in 0 channels
Get PRO
May '22
+133
in 0 channels
Get PRO
April '22
+39
in 0 channels
Get PRO
March '22
+75
in 0 channels
Get PRO
February '22
+55
in 0 channels
Get PRO
January '22
+46
in 0 channels
Get PRO
December '21
+67
in 0 channels
Get PRO
November '21
+101
in 0 channels
Get PRO
October '21
+94
in 0 channels
Get PRO
September '21
+74
in 0 channels
Get PRO
August '21
+134
in 0 channels
Get PRO
July '21
+178
in 0 channels
Get PRO
June '21
+180
in 0 channels
Get PRO
May '21
+103
in 0 channels
Get PRO
April '21
+60
in 0 channels
Get PRO
March '21
+85
in 0 channels
Get PRO
February '21
+2 721
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
07 September+15
06 September+2
05 September+31
04 September+21
03 September+23
02 September+17
01 September+12
Channel Posts
ሚኒስትሩ ለመንግሥት ሠራተኞች ያስተላለፉት መልዕክት ለመንግሥት ሠራተኞቻችንም ተመሳሳይ የለውጥ ጥሪ አቀርባለሁ። በቅርብ ጊዜ ውስጥ የመንግሥት አገልግሎቶች በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በሚታገዙ ሥርዓቶች
ሚኒስትሩ ለመንግሥት ሠራተኞች ያስተላለፉት መልዕክት ለመንግሥት ሠራተኞቻችንም ተመሳሳይ የለውጥ ጥሪ አቀርባለሁ። በቅርብ ጊዜ ውስጥ የመንግሥት አገልግሎቶች በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በሚታገዙ ሥርዓቶች እየተደገፉ ይሄዳሉ። ይህ ለውጥ ሥራን የሚነጥቅ ሳይሆን ሥራን የሚያከብር ይሆናል ሠራተኛውን ከድግግሞሽ ተግባራት ነጻ አውጥቶ ለፈጠራና ለውሳኔ ሰጪነት ያበቃል። ነገር ግን ይህንን ዕድል መጠቀም የሚችለው በዲጂታል ክህሎት የታጠቀ ሠራተኛ ብቻ ይሆናል። ዶ/ር በለጠ ሞላ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር

2
ትራምፕ ጨረቃን “የእኛ ናት” ማለታቸው አነጋጋሪ ሆኗል የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በትሩዝ ሶሻል ማህበራዊ ገጻቸው ላይ ጨረቃ የአሜሪካ ንብረት መሆኗን በመግለጽ “ጨረቃ የኛ ናት” የሚል ጽ
ትራምፕ ጨረቃን “የእኛ ናት” ማለታቸው አነጋጋሪ ሆኗል የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በትሩዝ ሶሻል ማህበራዊ ገጻቸው ላይ ጨረቃ የአሜሪካ ንብረት መሆኗን በመግለጽ “ጨረቃ የኛ ናት” የሚል ጽሑፍ እና የአሜሪካ ሰንደቅ ዓላማ ያለበትን ምስል አጋርተዋል። ከዚህ ልጥፍ ጥቂት ደቂቃዎች በፊትም፣ ለአሜሪካ የጠፈር ኃይል (Space Force) የተዘጋጁ አዲስ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) የዩኒፎርም ምስሎችን ይፋ አድርገዋል። ይህ የጨረቃ የይገባኛል ጥያቄ እና ዩኒፎርሞቹ ከታዋቂው ፊልም ከ«ስታር ዋርስ» (Star Wars) ወታደሮች ጋር በመመሳሰላቸው በማህበራዊ ሚዲያ ከፍተኛ መሣለቂያና መነጋገሪያ ሆነዋል። ይሁን እንጂ፣ አሜሪካን ጨምሮ ከ100 በላይ አገሮች የፈረሙት የ1967ቱ የውጪ ጠፈር ስምምነት ማንም አገር ጨረቃን ወይም ሌሎችን የሰማይ አካላት በባለቤትነት መያዝ እንደማይችል በግልጽ ይከለክላል። የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ… https://t.me/AdissAdmas
651
3
የታንዛኒያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሉሁ ባለቤት ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ የታንዛኒያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሉሁ ሀሰን ባለቤት ሀፊድ አሜር ሀሰን በልብ ሕመም ሕክምና ሲደረግላቸው ቆይተው በዛንዚባር ሆስፒታል
የታንዛኒያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሉሁ ባለቤት ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ የታንዛኒያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሉሁ ሀሰን ባለቤት ሀፊድ አሜር ሀሰን በልብ ሕመም ሕክምና ሲደረግላቸው ቆይተው በዛንዚባር ሆስፒታል ሕይወታቸው አልፏል። የቀብር ሥነ ሥርዓታቸው በዛንዚባር ኪዚምካዚ መንደር እየተዘጋጀ መሆኑን የአገሪቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ዴኦግራቲየስ ንዴጀምቢ አስታውቀዋል። የግብርና ምሁር የሆኑት አሜር ከፕሬዝዳንት ሳሚያ ጋር ከ1978 ጀምሮ ለአሥርተ ዓመታት የቆየ ትዳር የነበራቸው ሲሆን፣ አራት ልጆችን አፍርተዋል። ባለቤታቸው ኃላፊነት ከጨበጡ በኋላ እምብዛም በአደባባይ ሳይታዩ፣ አልፎ አልፎ በኦፊሴላዊ ኹነቶች ላይ ብቻ ከጎናቸው ይገኙ ነበር። የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ… https://t.me/AdissAdmas
982
4
ት/ሚኒስቴር በትግራይ ዩኒቨርሲቲዎች ላይ ከባድ ውሳኔ አስተላለፈ "ታጣቂዎች ካልወጡ ተማሪ አንመደብም" ትምህርት ሚኒስቴር በትግራይ ክልል የሚገኙ መቐለ፣ አክሱም፣ አዲግራት እና ራያ ዩኒቨርሲቲዎች ግ
ት/ሚኒስቴር በትግራይ ዩኒቨርሲቲዎች ላይ ከባድ ውሳኔ አስተላለፈ "ታጣቂዎች ካልወጡ ተማሪ አንመደብም" ትምህርት ሚኒስቴር በትግራይ ክልል የሚገኙ መቐለ፣ አክሱም፣ አዲግራት እና ራያ ዩኒቨርሲቲዎች ግቢዎቻቸውን ከማንኛውም ወታደራዊ እንቅስቃሴ ነጻ እንዲያደርጉ ዛሬ ሰኞ ጷጉሜን 2 ቀን 2018 ዓ.ም. ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል። ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የፈረሙበትና ለአራቱ ዩኒቨርሲቲዎች የተጻፈው ደብዳቤ፣ በካምፓሶቹ ውስጥ የጦር ቁስለኞች እና ታጣቂዎች መቀመጣቸው መረጋገጡን ገልጾ፤ ይህ ሁኔታ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱን ከሲቪል ተልዕኳቸው ውጭ ለወታደራዊ ዓላማ በማዋል የተማሪዎችን ሕይወት ለአደጋ የሚያጋልጥ መሆኑን አሳስቧል። በዚህም መሠረት ዩኒቨርሲቲዎቹ በግቢዎቻቸው የሚገኙትን ታጣቂዎች በአስቸኳይ እንዲያስወጡ እና ሀብቶቻቸው ለወታደራዊ አገልግሎት እንዳይውሉ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲያደርጉ ታዟል። የዩኒቨርሲቲ ግቢዎች ከማንኛውም ወታደራዊ እንቅስቃሴ ነፃ መሆናቸው በአግባቡ ካልተረጋገጠ ተማሪዎችን እንደማይመድብ ያስታወቀው ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ፣ ውሳኔው የተማሪዎች ደኅንነት እስኪረጋገጥ ድረስ ተፈጻሚ እንደሚሆን አስጠንቅቋል። የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ… https://t.me/AdissAdmas
909
5
አቶ ልደቱ አያሌው በAI ያቀናበሩትን የዘፈን አልበም ሊለቁ ነው አንጋፋው ፖለቲከኛ አቶ ልደቱ አያሌው በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ያቀናበሩትን "ሀሳብን በዜማ" የተሰኘ የ12 ዘፈኖች አልበም ለ
አቶ ልደቱ አያሌው በAI ያቀናበሩትን የዘፈን አልበም ሊለቁ ነው አንጋፋው ፖለቲከኛ አቶ ልደቱ አያሌው በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ያቀናበሩትን "ሀሳብን በዜማ" የተሰኘ የ12 ዘፈኖች አልበም ለአዲስ ዓመት ስጦታነት ሊለቁ ነው። ፖለቲከኛው የፖለቲካ ፍልስፍናቸውን እና በህይወት ዙሪያ ያላቸውን እይታ በዚህ የሙዚቃ ስራ እንደሚገልጹ አሳውቀዋል። ይህ አዲስ አልበም ከመስከረም 1 ጀምሮ ዘፈኖቹ በቅደም ተከተል ለህዝብ ይፋ እንደሚደረጉ ተነግሯል። በቴክኖሎጂ ታግዞ የተሰራው ይህ የኪነጥበብ ስራ በህብረተሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ጉጉትን ፈጥሯል። #LidetuAyalew #EthiopianMusic #AIArt #HasabenZema #Ethiopia
1 346
6
አእምሮን ከኮምፒውተር ጋር የሚያገናኘው "NEO" ቴክኖሎጂ ለገበያ ቀረበ ቻይና የሳንቲም ያህል መጠን ያለው እና አእምሮን ከኮምፒውተር ጋር የሚያገናኝ "NEO" የተባለ ቴክኖሎጂ ለገበያ እንዲቀርብ ፈ
አእምሮን ከኮምፒውተር ጋር የሚያገናኘው "NEO" ቴክኖሎጂ ለገበያ ቀረበ ቻይና የሳንቲም ያህል መጠን ያለው እና አእምሮን ከኮምፒውተር ጋር የሚያገናኝ "NEO" የተባለ ቴክኖሎጂ ለገበያ እንዲቀርብ ፈቃድ ሰጥታለች። በጽንግሁዋ ዩኒቨርሲቲ እና በኒውራክል ቴክኖሎጂ የተሰራው ይህ መሳሪያ፣ የሰዎችን የእንቅስቃሴ አቅም ለመመለስ ለገበያ እንዲቀርብ ፈቃድ ያገኘ የመጀመሪያው በአእምሮ ውስጥ የሚተከል ቴክኖሎጂ ሆኗል። የኢሎን መስክ ኒውራሊንክ (Neuralink) አሁንም በሙከራ ላይ ባለበት ወቅት፣ ይህ መሳሪያ ደህንነቱ የተጠበቀ በመሆኑ ቀድሞ የንግድ ፈቃድ ማግኘት ችሏል። ይህ ቴክኖሎጂ ሙሉ በሙሉ የእጅና የእግር ሽባነት ላጋጠማቸው ሰዎች የሚጠቅም ሲሆን፣ የአእምሮ ሕብረ ሕዋሳትን ሳይጎዳ በውጫዊው ሽፋን ላይ ብቻ በማረፍ ይሰራል። በሆስፒታሎች በተደረጉ ሙከራዎችም ታካሚዎች በሃሳባቸው ብቻ ዕቃዎችን በመጨበጥ መብላትና መጠጣት እንዲችሉ በማድረግ ሙሉ ስኬት አሳይቷል። የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ… https://t.me/AdissAdmas #ChinaTech #BrainComputerInterface #NEO #Technology #FutureTech
1 328
7
ለአዲስ ዓመት በዓል ከ4 ሺህ በላይ እንስሳትን ለማረድ ዝግጅቱ ተጠናቋል አዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ለአዲሱ ዓመት በዓል ከ4 ሺህ 500 በላይ የቁም እንስሳት (ከ3 ሺህ በላይ በሬዎች እና ከ1 ሺህ
ለአዲስ ዓመት በዓል ከ4 ሺህ በላይ እንስሳትን ለማረድ ዝግጅቱ ተጠናቋል አዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ለአዲሱ ዓመት በዓል ከ4 ሺህ 500 በላይ የቁም እንስሳት (ከ3 ሺህ በላይ በሬዎች እና ከ1 ሺህ 500 በላይ በግና ፍየሎች) እርድ ለማከናወን ጥንቃቄ የተሞላበት ዝግጅት መደረጉን አስታወቀ። በአገልግሎቱ መሰረትም ማንኛውም የከተማዋ ነዋሪ በግና ፍየልን በ300 ብር፣ እንዲሁም በሬዎችን ደግሞ በ2ሺ 100 ብር የቄራ የእርድ አገልግሎት ማግኘት እንደሚችል ተጠቁሟል። ሕብረተሰቡ ጤናማና ጥራታቸው የተጠበቁ ሥጋዎችን በንጽህና እንዲያገኝ ወደ ቄራዎች ድርጅት መምጣት እንደሚገባው ጥሪ ቀርቧል። የአዲስ አበባ ከተማ የአርሶ አደርና የከተማ ግብርና ኮሚሽን ማህበረሰቡ ከልኳንዳ ሥጋ ሲገዛ በቄራ መታረዱን ማረጋገጥ እንዳለበት አሳስቧል። በሌላ በኩል በቅርጫ ወቅት የሚታረዱ እንስሳትን ጤንነት በቦታው ለመመርመር ተንቀሳቃሽ ቄራዎችን በቀጣይ ወደ ሥራ ለማስገባት ዕቅድ መኖሩ የተገለጸ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ የቁም እንስሳት ማህበርም ወደ ከተማዋ የሚገቡ እንስሳት በቂ መሆናቸውንና ሕገ-ወጥ እርዶችን ለመከላከል ከጸጥታ አካላት ጋር እየተሠራ መሆኑን ገልጿል። የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ… https://t.me/AdissAdmas #AddisAbaba #EthiopianNewYear #AbattoirsEnterprise #Ethiopia #HolidayNews
1 208
8
ከእምዬ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የተበረከተችልን ጥቂት ቀናትን የያዘች የመሸጋገሪያ ወር ስጦታ አለችን፡፡ ይህቺ ወር ከሌሎች ወር የተቀነሱ ቀናትን ይዛ የተሰራች ጭማሪ ወር ናት፡፡ ጥበበኞቹ አበው አስራሁለት ወራት እኩል ሰላሳ ሰላሳ ቀናትን ይዘው የተረፉትን ቀናት በ13ኛ ወር ውስጥ ሆነው እንዲጠቃለሉ አድርገዋል፡፡፡ ስሟንም ጳጉሜ ብለዋታል፡፡ ጳጉሜ ማለት በግሪክ ቋንቋ ጭማሪ ማለት ነው፡፡ ጳጉሜ እንደተጨማሪ እድል የተሰጠችን ገፀበረከታችን አድርገን ልንወስዳት እንችላለን፡፡ አሮጌውን ዓመት አገባድደን አዲሱን ዓመት ከመጀመራችን በፊት ያለች ሰከን ብለንና ተረጋግተን ትናንትን እየመዘንን ለነገ የምንዘጋጅባት የማሰቢያ ወራችን ነች፡፡ ይህቺ የጳጉሜ ወር በሐገራችን አብዛኛው አካባቢ በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ አምስቱን ቀናት በሙሉ እየፀለዩና ፀበል እየተፀበሉ ለአዲሱ ዓመት ራሳቸውን የሚያዘጋጁባት፤ በዓመቱ ውስጥ ከሠሯቸው ስህተቶች የሚነፁባት፤ መንፈሳቸውን የሚያድሱባት ትንሽ ጊዜ የምትመስል ነገር ግን ትልቅ ትርጉም የምትሠጥ የትንሽ ትልቅ ወራችን ናት፡፡ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በአንድ ፅሁፋቸው ‹‹ ……… የኢትዮጵያን የዘመን አቆጣጠር ለየት ከሚያደርጉት ነገሮች አንዱ ጳጉሜ የምትባል አሥራ ሦስተኛ ወር ስላለችን ነው፡፡ የቤት ኪራይና የወር ደመወዝ የማንከፍልባትና የማንቀበልባት፤ መብራትና ውኃ ግን ከነሐሴ ወር ጋር ጨምረው የሚያስከፍሉባት፤ ሲሻት አምስት፣ ሲያስፈልጋት ስድስት፣ ስትፈልግ ደግሞ ሰባት የምትሆን ወር ናት፡፡ እንዲያውም ከአሥራ ሁለቱ የኢትዮጵያ ወሮች ጳጉሜ በብዙ መንገድ የተለየች ናት፡፡ በአንድ በኩል በጣም ትንሿ ወር ናት፡፡ ሲቀጥልም ወርኃዊ በዓላት የማይውሉባት ወር ናት፡፡ እንዲያም ሲል ደግሞ ከሌሎች ወሮች በተለየ የቀኖቿ መጠን የሚቀያየሩ ብቸኛ ወር ናት፡፡ ከሌሎች የኢትዮጵያ ወሮች በተለየም ስሟ ኢትዮጵያዊ ያልሆነ ወር ናት፡፡ በሁለት ዘመናት መካከልም እንደ መሸጋገሪያ የምትታይ ወርም ናት፡፡…. ›› በማለት ገልፀዋታል፡፡ አሮጌው ዓመት ጉዞው ተገባዷል ታሪኩ ግን አላለቀም፡፡ ሞት ብቻ ነው የሰው ልጅን ታሪክ የሚቋጨው፡፡ እስትንፋሱ ያልተቋረጠ፣ ትንፋሹ ያልቀዘቀዘ ሰው በአዲስ ዓመት ደብተር አዲስ ታሪክ እየፃፈ ኑረቱን ይቀጥላል፡፡ አዲሱ ዓመት ያልተጀመረባት፤ ነገር ግን ምን እንደሚፃፍባት የምንመረምርባት ጊዜ ናት ጳጉሜ፡፡ ያለፈው ዓመት ማብቂያ የአዲሱ ዓመት መጀመሪያ ዋዜማ በመሆኗ ጳጉሜን ለየት ያደርጋታል፡፡ ጳጉሜ ራስን መመልከቻ መስታወት ናት፡፡ አሮጌው መልካችንን ምንም ሳትደብቅ የምታሳይ፤ የወደፊት መልካችንን በዓይነ-ህሊናችን የምትስል ራሳችንን ማያ ናት፡፡ ካለፈው የሕይወት ተሞክሯችን መልካሙን ነገር ወስደን፣ ደካማውን ጎናችንን እንድናሻሽል ህይወታችንን በዓይነ-ህሊና መነፅራችን የምንጎበኝበት የንስሃና የተሃድሶ ዕድል የምናገኝበት ምርጥ ጊዜአችን ናት፡፡ ጳጉሜ አሮጌውን ዓመት ካዲሱ ዓመት የምታገናኝ ድልድይ ናት፤ የትናንት ማንነታችንን ከአዲሱ ማንነታችን ጋር የምታዋህድ ቅመምም ናት፡፡ አሮጌው ዓመት ወደኋላ ቀርቷል፤ አዲሱ ዓመት ደግሞ ከፊትለፊታችን ተገትሯል፡፡ ጳጉሜ አሮጌውን በሰከነ መንፈስ መርምረን ባገኘነው ዕውቀት ከፊታችን ያለውን አዲሱን ዓመት በተሻለ ተሞክሮ፣ ስሜትና ብርታት እንድንመራው ትንሽ የማሰቢያ ጊዜና እረፍት የምትሰጠን አማካይ ጊዜ ናት፡፡ ይህቺ ወር የሕይወታችንን ሩጫ ገታ አድርገን፣ ትንፋሽ ወስደን፣ ቆም ብለን የምናስብባት ተጨማሪ ቀናችን ናት፡፡ ጳጉሜን ላሰበበትና ራሱን ለገመገመባት የውሸት መኖርና የእውነት መኖር (living versus existing) ምን እንደሆነ ግንዛቤ ያገኝባታል፡፡ ወደኋላህ ዞር ብለህ የምታየው ሕይወትን እንድትረዳበት ነው፤ የተረዳኸውን የምትኖርበት ግን ዛሬን በመጀመር የወደፊትህን ጭምር ነው፡፡፡ ከአንድ ዓመት ወደሌላ ዓመት ዝም ብሎ መዘዋወር እሱ እውነተኛ መኖር አይደለም፡፡ አሮጌውን ዓመት አገባድደን ወደአዲሱ ዓመት ስንቀላቀል አዕምሯዊና ስሜታዊ ለውጥ ካላመጣን የእውነት ኖርን አይባልም፡፡ ቢያንስ ካለፈው ዓመት የሚሻል ቅንጣት ለውጥ ሊኖረን ይገባል፡፡ አዲሱን ዓመት ደስ ብሎን የምንቀበለው በቀናት መለዋወጥ፣ በዓመታት መቀያየር ብቻ ሳይሆን በለውጥ መስመር ውስጥ ስናልፍ ነው፡፡ ኢኮኖሚያዊ ችግራችንን በስራና በአዲስ ክህሎት ስንቀርፍ፣ መንፈሳዊ ድህነታችንን ስንገረስስ፣ ክፉ ልማዳችንን ስንተው፣ እውቀት ስንጨምር፣ በስሜት ብስለታችን ላይ ጉልህ ልዩነት ስናመጣ፣ ስህተታችንን ላለመድገም ለራሳችን ቃል ስንገባ፣ ለነፍሳችን ደስታ አንድ እርምጃ ወደፊት ስንራመድ፣ ራሳችንን ሳንሆን ባባከንነው ጊዜ ተፀፅተን ወደራሳችን ስንመለስ፣ ወዘተ መልካም ነገሮችን ማሟላት ስንችል የምንቀበለው አዲስ ዓመት የደሰታና የፍስሃ ይሆንልናል፡፡ ወዳጄ ሆይ… ‹‹በከንቱ የጠፋ ጊዜ መልሶ አይገኝም! (Lost time is never found again)›› እንዲል ቤንጃሚን ፍራንክሊን ዕድሜህን በዋል ፈሰስ አታባክነው፡፡ ጳጉሜን ከተጠቀምክባት የመታደስ፣ የመለወጥ፣ የመሻሻል፣ የማገገም፣ ወደራስህ የመመለስና ከራስህ ጋር እርቅ የምትፈፅምባት ውድ ስጦታህ ናት፡፡ የአዲስ ማንነትህ መብቀያ ዘር ናት፡፡ የሚቀጥለው ዓመት ወይም ሌላ ጊዜ ይደርሳል እያልክ ዛሬህን አታባክን፡፡ አስብና ወስን፤ ወስንና ጀምር፡፡ ጳጉሜን ስለራስህ አስብባት፣ ትናንትህን ገምግምባት፣ ወደፊትህን ወጥንባት፣ አካሄድህን መርምርባት! ከራስሀ ጋር ሳትታረቅ አዲሱን ዓመት አትጀምር!! አዲስ ዓመት ከትናንትህ ጋር የምትዋጋበት አዲስ የጦር ግንባር አይደለም፤ ይልቁንስ እርቅ ፈፅመህ በአዲስ ማንነት የምትጀምርበት ልዩ ቀንህ ነው፡፡ አዲሱ ዓመት የሠላም፣ የፍቅር፣ የእድገትና እና እርስበርስ የምንስማማበት፤ ከግል ጥቅም ይልቅ የሐገር ጥቅም የምናስቀድምበት፤ ፍትህ ላጣው ወገናችን የምንቆምበት፣ ለተቸገረው የምንደርስበት፣ ለተራበው የምናጎርስበት ዓመት እንዲሆን ሁላችንም ከራሳችን የመንደር ሳጥን ወጥተን ሀገራዊ፣ ወገናዊና ኢትዮጲያዊ መንፈስ ተላብሠን ከልጅ እስከ አዋቂ፣ ከሊቅ እስከ ደቂቅ በአንድነት ሆ ብለን የምንነሳበት ዓመት ያድርግልን…!!!!! ቸር ጊዜ! መልካም አዲስ ዓመት!! ------------------------------------------ እሸቱ ብሩ ይትባረክ (እ.ብ.ይ.) ሠኞ ጳጉሜ
1 115
9
ከራስህ ጋር ሳትታረቅ አዲሱን ዓመት አትጀምር!! (Be peaceful with you first) (እ.ብ.ይ.) ትናንት የዛሬ መነሻ ነው፡፡ ያለፈ ጊዜ አለፈ የሚባለው ቀኑ እንጂ ታሪኩ አይደለም፡፡ ታሪ
ከራስህ ጋር ሳትታረቅ አዲሱን ዓመት አትጀምር!! (Be peaceful with you first) (እ.ብ.ይ.) ትናንት የዛሬ መነሻ ነው፡፡ ያለፈ ጊዜ አለፈ የሚባለው ቀኑ እንጂ ታሪኩ አይደለም፡፡ ታሪኩ ቀሪና ቀጣይ ነው፡፡ እሱ ነው እውቀትና ብልሃት የሚሰጠን፤ ታሪኩ ነው ሞራላችንና ሰብዕናችን ላይ እንዲሁም ስሜታችን ላይ ከፍተኛ ሚና የሚጫወተው፡፡ በትናንት የጊዜ ባቡር ባንሳፈር የዛሬ ጉዞ ላይ መድረስ አንችልም፡፡ ለዚህ ነው ዊሊያም ሼክሰፔር ‹‹ያለፈው ነገር ላሁኑ መቅድም ነው (What is past is prologue.)›› የሚለው፡፡ የትኛውም መጨረሻ የሌላ ነገር መጀመሪያ ነው፡፡ ያለቀ ዓመትም የአዲስ ዓመት ብስራት ነው፡፡ እኛ ኢትዮጵያውያኖች አሮጌው ዘመን ሲያልቅ አዲሱ ዓመት ላይ ዘው ብለን አንገባም፤ ባለቀውና አዲስ በሚጀምረው ዓመት መካከል ማረፊያ ጥቂት ቀናቶች አሉን፡፡ እነዚህን ቀናት በጉያዋ ሸጉጣ የያዘችው ወር ደግሞ ጳጉሜ ትባላለች፡፡ ካሮጌው ዓመት እንደተክለበለብን መጥተን እንደተክለበለብን ከአዲሱ ዓመት ጋር አንቀላቀልም፡፡ ፍሬን መያዣ፣ ራሳችንን ማስከኛ፣ የኋሊታችንን መመልከቻ የስክነት ጊዜ አለን፡፡ ⬇️⬇️
1 299
10
ቀደም ሲል በጨው ላይ አዮዲን በመጨመር የእንቅርት (Goiter) በሽታን መከላከል እንደተቻለው ሁሉ፣ አሁን ደግሞ በስንዴ ዱቄት እና በጨው ላይ ፎሊክ አሲድ እና አዮዲንን አንድ ላይ በመቀላቀል (Do
ቀደም ሲል በጨው ላይ አዮዲን በመጨመር የእንቅርት (Goiter) በሽታን መከላከል እንደተቻለው ሁሉ፣ አሁን ደግሞ በስንዴ ዱቄት እና በጨው ላይ ፎሊክ አሲድ እና አዮዲንን አንድ ላይ በመቀላቀል (Double Fortification) መመገብ የችግሩ ዘላቂ መፍትሄ እንደሆነ ተገልጿል። የኢቻ ፉድ ኮምፕሌክስ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ወንዱ ይፍሩ እንደገለጹት፣ የበለጸገ ዱቄት ማለት በፋብሪካ የማቀናበር ሂደት ወቅት የሚያጣቸውን የተፈጥሮ ማዕድናት (እንደዚንክ እና አይረን) እንዲሁም ቫይታሚን ቢ ኮምፕሌክስን መልሶ እንዲያገኝ የማድረግ ሂደት ነው። ድርጅቱ ስራ ሲጀምር 82 ሰራተኞች የነበሩት ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ዘመናዊ ኑማቲክ (Pneumatic) ማሽነሪዎችን በመትከል የማምረት አቅሙን በማሳደግ የሰራተኞቹን ቁጥር ወደ 170 አድርሷል። ፋብሪካው ለተጨማሪ የቪታሚንና ማዕድናት ግብዓቶች (Pre-mix) የወጭ ምንዛሬ ወጪ ቢያወጣም፣ የሕብረተሰቡን የመግዛት አቅም ያገናዘበ እና የጎላ የዋጋ ልዩነት የሌለው ምርት በሸገር፣ በአዲስ አበባ እና በሌሎች የክልል ከተሞች በጅምላ እና በወኪሎች በኩል እያከፋፈለ ይገኛል። ድርጅቱ በዱቄት ማበልጸግ ላይ ሳይወሰን ወደፊት ፓስታ፣ መኮሮኒ እና ብስኩት ላይ የበለጸጉ የምግብ አይነቶችን ለማቅረብ ዝግጅቱን አጠናቋል። በኢትዮጵያ የምግብ እና መድሃኒት ባለስልጣን እና በሌሎች ሕጋዊ አካላት በኩል የምግብ ማበልጸግ አሰራር ግዴታ (Mandatory) እየሆነ የመጣ ሲሆን፣ ቁጥጥሩም ተጠናክሮ ቀጥሏል። በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ካሉት ከ240 በላይ የዱቄት ፋብሪካዎች መካከል ጥቂቶቹ የማበልጸግ ሂደቱን የጀመሩ ሲሆን፣ በርካታ የጨው ፋብሪካዎችም የፎሊክ አሲድ እና የአዮዲን ቅልቅል አሰራርን በመተግበር ላይ ይገኛሉ።
2 063
11
ኢቻ ፉድ ኮምፕሌክስ የዱቄት ማበልጸግ ስራ የጀመረበትን አንደኛ ዓመት አከበረ ኢቻ ፉድ ኮምፕሌክስ የዱቄት ማበልጸግ (Food Fortification) ስራ የጀመረበትን አንደኛ ዓመት እና የድርጅቱን የ
ኢቻ ፉድ ኮምፕሌክስ የዱቄት ማበልጸግ ስራ የጀመረበትን አንደኛ ዓመት አከበረ ኢቻ ፉድ ኮምፕሌክስ የዱቄት ማበልጸግ (Food Fortification) ስራ የጀመረበትን አንደኛ ዓመት እና የድርጅቱን የ14ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ምክንያት በማድረግ በትናንትናው ዕለት የማሕበረሰብ ግንዛቤ ማስጨበጫ እና የምስጋና ፕሮግራም አካሂዷል። በሸገር ከተማ፣ በገላን ክፍለ ከተማ፣ ፊዳ አዋሽ ወረዳ የሚገኘው ይህ የዱቄት ፋብሪካ፤ በስንዴ፣ በጨው እና በዘይት ላይ የሚደረግ የምግብ ማበልጸግ ስራ በአገር አቀፍ ደረጃ እና ለሕብረተሰብ ጤና ያለውን ከፍተኛ ጥቅም አስመልክቶ ከዘርፉ ባለሞያዎች እና ከፋብሪካው አመራሮች ጋር ገለጻ አድርጓል። በቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የነርቭ ህክምና ክፍል ስራተኛ እና የ"Alliance for Birth Defects" መስራች ዶክተር ነቢያት ተስፋዬ እንደገለጹት፣ በኢትዮጵያ በየዓመቱ ወደ 40 ሺሕ የሚጠጉ ሕጻናት ከነርቭ ዘንግ ክፍተት (Neural Tube Defects / Spina Bifida) ጋር ተያይዘው ይወለዳሉ። በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ይህ ቁጥር እስከ 300 ሺሕ ይደርሳል። ይህ የጤና ችግር በዋነኝነት በእርግዝና ወቅት የቫይታሚን ቢ9 (ፎሊክ አሲድ/Folic Acid) ዕጥረት ምክንያት የሚከሰት ሲሆን፣ እናቶች እርጉዝ ከመሆናቸው ከ3 ወራት በፊት ጀምሮ በፎሊክ አሲድ የበለጸጉ ምግቦችን ወይም ተጨማሪ የቪታሚን ክኒኖችን በመውሰድ በቅድመ መከላከል (Primary Prevention) በቀላሉ ማስቀረት ይቻላል። በአገር አቀፍ ጥናቶች መሰረት በወሊድ ዕድሜ ላይ ከሚገኙ የኢትዮጵያ ሴቶች መካከል ከ50 በመቶ በላይ የሚሆኑት የፎሊክ አሲድ ዕጥረት አለባቸው። ⬇️⬇️
1 941
12
እንዲሁም ከአሜሪካ በቀጥታ በኢትዮጵያ ውስጥ ወደሚገኙ የባንክ አካውንቶች በሕጋዊ መንገድ ገንዘብ ማስተላለፍ ይቻላል። የባንክ አካውንቱ ምንም ዓይነት የወርሃዊ የአገልግሎት ክፍያ (Monthly Maintenance Fee) የሌለው ሲሆን፣ የደንበኞች ድጋፍ አገልግሎት ደግሞ በ24 ሰዓት በአማርኛ፣ ኦሮምኛ፣ ትግርኛ እና እንግሊዝኛ ቋንቋዎች ይቀርባል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ (NBE) እ.ኤ.አ. ኦገስት 7 ቀን 2026 ባወጣው ይፋዊ የመረጃ ዝርዝር መሰረት መላ ፋይናንስ (Mela Finance Inc.) በሕጋዊ መንገድ የተመዘገበ እና ፍቃድ የተሰጠው የገንዘብ አስተላላፊ ተቋም መሆኑ ተረጋግጧል። መደበኛ ያልሆኑ (Informal/Parallel) የሃዋላ መንገዶች የተሻለ የምንዛሬ ተመን ቢያቀርቡም ለኪሳራ፣ ለማጭበርበር እና ለሕግ ጥሰቶች የሚያጋልጡ ናቸው። መላ በሕጋዊ መስመር የሚደረጉ ዝውውሮችን አስተማማኝ፣ ፈጣን እና ተወዳዳሪ በሆነ ዋጋ ለማቅረብ "ይሰራል" ነው የተባለው። የመላ (Mela) ዋና ስራ አስፈጻሚ እና መስራች አዕላፍ ሚደቅሳ እንደገለጹት፣ "ማሕበረሰባችን መቼም ቢሆን ስርዓት፣ ዓላማ ወይም ሃላፊነት ጎድሎት አያውቅም። የጎደለው የእነርሱን ሃላፊነቶች ታሳቢ አድርገው የተሰሩ የፋይናንስ ስርዓቶችን ነው። መላ የማሕበረሰባችንን የፋይናንስ ህይወት ደረጃ በደረጃ ለማጠናከር የተመሰረተ ነው" ብለዋል። እ.ኤ.አ. በ2024 የተመሰረተው መላ፣ የተቋሙ መስራቾች በአሜሪካ ከ16 ዓመታት በላይ በመኖር አብረው ያሳለፉትን እና የተረዱትን የዲያስፖራውን የፋይናንስ ችግር ለመፍታት የተገነባ ነው። በቀጣይም ፕላትፎርሙ የዲጂታል ዕቁብ (Digital Equb) አሰራርን፣ የማሕበረሰብ እና የንግድ ድርጅቶች ክፍያዎችን (Merchant Payments)፣ በአገር ቤት የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን የሚያስችሉ የሞርጌጅ/የቤት ብድር መመቻቸቶችን በደረጃ እንደሚያካትት አስታውቋል።
2 222
13
አዲሱ ኒዮባንክ ለኢትዮጵያውያን ዲያስፖራዎች ምን ይዞ መጣ? በውጭ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን የፋይናንስ ፍላጎት መሰረት ያደረገ የመጀመሪያው የዲጂታል ባንክና የፋይናንስ
አዲሱ ኒዮባንክ ለኢትዮጵያውያን ዲያስፖራዎች ምን ይዞ መጣ? በውጭ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን የፋይናንስ ፍላጎት መሰረት ያደረገ የመጀመሪያው የዲጂታል ባንክና የፋይናንስ ፕላትፎርም የሆነው "መላ" (Mela Finance Inc.) ይፋዊ የስራ ማስጀመሪያ ፕሮግራሙን አካሂዷል። ከቀደሙት የሙከራ ሂደቶች (Early Beta) በኋላ ይፋ የተደረገው ይህ አዲስ ፕላትፎርም፣ በዋነኝነት በዩናይትድ ስቴትስ (አሜሪካ) የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የባንክ አገልግሎት፣ የደመወዝ ክፍያ (Payroll) እና ሕጋዊ የሆነ የገንዘብ ሃዋላ በቀጥታ ወደ ኢትዮጵያ ማስተላለፍ የሚያስችል አሰራርን ያቀረበ ነው። በስደት የሚኖሩ በርካታ ኢትዮጵያውያን የደመወዝ ክፍያቸውን በአንድ ባንክ፣ የዕለት ተለት ወጪያቸውን በሌላ አካውንት፣ እንዲሁም በአገር ቤት የሚገኙ ቤተሰቦቻቸውን ለመደገፍ፣ የትምሕርት ቤት ወጪ ወይም የቤተሰብ ንግድ ስራዎችን ለማገዝ ደግሞ የተለያየ የሃዋላ ድርጅት ወይም መደበኛ ያልሆኑ (Informal) አማራጮችን ለመጠቀም ይገደዳሉ። በተጨማሪም እንደዕቁብ ያሉ ባሕላዊ የቁጠባ ዘዴዎች እና የቤት መስሪያ ብድር (Mortgage) ሂደቶች በተበታተነ መልኩ የሚከናወኑ ናቸው። መላ ይህንን የፋይናንስ መበታተን እና መደራረብ ለማስቀረት፣ ሁሉንም የዲያስፖራውን የፋይናንስ ፍላጎቶች በአንድ አስተማማኝ እና ዲጂታል ፕላትፎርም ስር ለማቀናጀት ያለመ እንደሆነ ገልጿል። በዚህም መሰረት ደንበኞች በቀጥታ ገቢ የሚደረጉ ገንዘቦችን እና የደመወዝ ክፍያዎችን መቀበል፣ የባንክ አካውንቶችን ማገናኘት እና ዝውውር ማድረግ ይችላሉ። ⬇️⬇️
1 983
14
ነዳጅ ለመስረቅ የሞከሩ ከ30 በላይ ሰዎች በመርዛማ ጋዝ ታፍነው ሞቱ በናይጄሪያ ሪቨርስ ግዛት ከነዳጅ ቧንቧ ላይ በሕገወጥ መንገድ ቤንዚን ለመስረቅ የሞከሩ ከ37 በላይ ሰዎች በመርዛማ ጋዝ ጭስ ታፍ
ነዳጅ ለመስረቅ የሞከሩ ከ30 በላይ ሰዎች በመርዛማ ጋዝ ታፍነው ሞቱ በናይጄሪያ ሪቨርስ ግዛት ከነዳጅ ቧንቧ ላይ በሕገወጥ መንገድ ቤንዚን ለመስረቅ የሞከሩ ከ37 በላይ ሰዎች በመርዛማ ጋዝ ጭስ ታፍነው ሞቱ። ከ100 በላይ ሰዎች በሌሊት በጀልባዎች ሄደው ነዳጅ ለመቅዳት ሲሞክሩ በደረሰው በዚህ አደጋ በርካቶች የጠፉ ሲሆን፣ አንዳንዶችም ተዝለፍልፈው ወደ ወንዝ ውድቀዋል። የናይጄሪያ የፀጥታ አካላትና የባሕር ኃይል ሕገወጥ የነዳጅ ስርቆትን ለማስቆም ጠንካራ እርምጃዎችን እየወሰዱ ይገኛሉ። አገሪቱ የነዳጅ ምርቷን ለማሳደግ እና የደኅንነት ችግሮችን ለመቅረፍ ጥረት እያደረገች ቢሆንም፣ አደገኛ የሆኑ የነዳጅ ስርቆት ድርጊቶች አሁንም ለብዙዎች ሕይወት መጥፋትና ለአካባቢ ብክለት ምክንያት እየሆኑ ናቸው። በኒጀር ዴልታ ክልል የሚፈጸመው የነዳጅ ቧንቧዎች ስርቆትና ሕገወጥ ማጣራት ለብዙ አስርት ዓመታት የቆየ ችግር ሲሆን፣ ድርጊቱ ለሰው ሕይወት ማጣት፣ ለአካባቢ ብክለትና ለኢኮኖሚ ውድመት ምክንያት በመሆኑ በፀጥታ አካላትና በተሟጋቾች ዘንድ በጥብቅ ተኮንኗል። የአገሪቱ የባሕር ኃይልና ሌሎች የፀጥታ ተቋማት በውሃ መስመሮችና በጥብቅ ደኖች ውስጥ የሚሸሸጉ የነዳጅ ዘራፊዎችን ለማስቆም የተቀናጀ ዘመቻ እያካሄዱ ይገኛሉ። BBC- የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ… https://t.me/AdissAdmas
1 785
15
የአከራይና ተከራይ ውል እድሳት እስከ ጳጉሜን 5 ድረስ ተራዘመ በአዲስ አበባ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የአከራይና ተከራይ ውል እድሳት እስከ ጳጉሜን 5 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ መራዘሙን የአዲስ አበባ
የአከራይና ተከራይ ውል እድሳት እስከ ጳጉሜን 5 ድረስ ተራዘመ በአዲስ አበባ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የአከራይና ተከራይ ውል እድሳት እስከ ጳጉሜን 5 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ መራዘሙን የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ተዋቡ ቀስቅስ እንደገለጹት፣ እስካሁን ከ70% በላይ የሚሆኑ አከራይና ተከራዮች ውላቸውን አድሰዋል። ነገር ግን በየማዕከላቱ ያለውን ሰልፍና መጨናነቅ ለመቀነስ እንዲሁም ከከተማ ውጭ የነበሩ ሰዎችን ለማስተናገድ ሲባል ተጨማሪ ጊዜ መስጠት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል። አገልግሎቱ በየማዕከላቱና በ"መሶብ" ማዕከል ከጥዋት እስከ ምሽት እየተሰጠ ይገኛል። ስለሆነም አከራዮችና ተከራዮች ማንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ በመያዝ ውላቸውን ማደስ አለባቸው። በተሰጠው የጊዜ ገደብ ውል የማያድሱ ወገኖች ቅጣት የሚጠብቃቸው በመሆኑ አሁኑኑ እንዲያድሱ ጥሪ ቀርቧል። የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ… https://t.me/AdissAdmas #አዲስአበባ #የቤትውልእድሳት #የአከራይተከራይውል #ጳጉሜን5 #AddisAbaba #Ethiopia
1 670
16
በአዲስ ከተማ «ሸማ ተራ» ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ውሏል በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 «ሸማ ተራ» አካባቢ ተከስቶ የነበረው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር+3
በአዲስ ከተማ «ሸማ ተራ» ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ውሏል በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 «ሸማ ተራ» አካባቢ ተከስቶ የነበረው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጸ። የክፍለ ከተማው ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ እቴማር ጌታቸው እንደገለጹት፤ አደጋውን በፍጥነት ለማጥፋት የእሳት አደጋ ሠራተኞችና የአካባቢው ነዋሪዎች ትልቅ ትብብር አድርገዋል። በአሁኑ ወቅት የአደጋው መንስኤና የደረሰው የጉዳት መጠን እየተጣራ እንደሚገኝ የተገለፀ ሲሆን፣ የተደረገው ፈጣን ርብርብ አደጋው ወደ ሌሎች አካባቢዎች እንዳይስፋፋ አድርጓል። የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ… https://t.me/AdissAdmas #AddisAbaba #AddisKetema #ShemaTera #FireSafety #AMN #EthiopiaNews
1 979
17
ኤርትራዊቷ ሞዴል ስኒት ሀብተአብ በሚስ ወርልድ ታሪካዊ ድል ተቀዳጀች ኤርትራዊቷ ሞዴል ስኒት ሀብተአብ ተወልደመድኅን በዓለም አቀፉ «ሚስ ወርልድ» የውበት ውድድር የመጀመሪያውን ዙር የሕዝብ ድምፅ በ
ኤርትራዊቷ ሞዴል ስኒት ሀብተአብ በሚስ ወርልድ ታሪካዊ ድል ተቀዳጀች ኤርትራዊቷ ሞዴል ስኒት ሀብተአብ ተወልደመድኅን በዓለም አቀፉ «ሚስ ወርልድ» የውበት ውድድር የመጀመሪያውን ዙር የሕዝብ ድምፅ በበላይነት አጠናቃለች። ስኒት በግምት 13.8 ሚሊዮን ድምፅ በማግኘት አንደኛ በመውጣት ወደ ቀጣዩ የውድድር ደረጃ አልፋለች። ይህ ውድድር ኤርትራ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓለም አቀፉ «ሚስ ወርልድ» የውበት መድረክ ላይ የተሳተፈችበት በመሆኑ ለአገሪቱ ትልቅ አዲስ ክስተት ሆኗል። ለዚህ ታሪካዊ ስኬቷ ከመላው አፍሪካ እና በውጭ አገር ከሚኖሩ ኤርትራውያን ከፍተኛ የድምፅ ድጋፍ አግኝታለች። በዚህም መሠረት ኤርትራን ወክላ በቀጣዮቹ የዓለም አቀፍ ውድድር ዙሮች የምትፎካከር ይሆናል። የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ… https://t.me/AdissAdmas
1 636
18
ከጦር መርከቦች እስከ ወርቃማ አዳራሽ፤ ትራምፕ ሁሉም ነገር በስማቸው እንዲጠራ ይፈልጋሉ "እኔ ከሄድኩ በኋላ የሚያስታውሰኝ የለም" ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዋሽንግተን ዲሲ በሚገኙ ትላልቅ ሕንፃዎ
ከጦር መርከቦች እስከ ወርቃማ አዳራሽ፤ ትራምፕ ሁሉም ነገር በስማቸው እንዲጠራ ይፈልጋሉ "እኔ ከሄድኩ በኋላ የሚያስታውሰኝ የለም" ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዋሽንግተን ዲሲ በሚገኙ ትላልቅ ሕንፃዎችና መታሰቢያዎች ላይ ስማቸውን ለማስጻፍ አጣዳፊ ሥራ ውስጥ መሆናቸውን ዘ ኢንዲፔንደንት ዘግቧል። ትራምፕ ከኒውዮርክ ማጋዚን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ «እኔ ከሄድኩ በኋላ ስሜን ማንም አይጽፈውም» ሲሉ እውነቱን ተናግረዋል። አሁኑኑ ስማቸው እንዲነሳ በማሰብም በሕንፃዎች፣ በፖሊሲዎች፣ በሳንቲሞችና በጦር መርከቦች ላይ ስማቸውንና ምስላቸውን እያስቀመጡ ይገኛሉ። ከእነዚህ ሥራዎቻቸው መካከል ትልቁ የኋይት ሀውስን አንድ ክንፍ በማፍረስ እየገነቡት ያለው ወርቃማ የመዝናኛ አዳራሽና የጦር ማዕከል ነው። ጥይት የማይበሳውና ከመሬት በታች ምሽግ ያለው ይህ ትልቅ ሕንፃ፣ የእሳቸውን ስም ሊይዝ እንደሚገባው ተናግረዋል። ምንም እንኳን አሰራሩ ሕጋዊ አይደለም በሚል ክስ ቢቀርብበትም፣ የከፍተኛው ፍርድ ቤት ግንባታው እንዲቀጥል ፈቅዷል። ትራምፕ ከዚህ በተጨማሪ የሕክምናና የፋይናንስ ፕሮግራሞችን በስማቸው መሰየም ጀምረዋል። አሜሪካ ከእንግዲህ የምትሰራቸውን አዳዲስ የጦር መርከቦችም በስማቸው እንዲጠሩ ይፈልጋሉ። ይህ ሁሉ አጣዳፊ እንቅስቃሴ ከሥልጣን በኋላ ስማቸውና ታሪካቸው ሳይጠፋ እንዲኖር የሚያደርጉት ጥረት መሆኑን የኢንዲፔንደንት ዘገባ ያመለክታል፡፡ የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ… https://t.me/AdissAdmas
1 653
19
በኢትዮጵያ በድርቅና በግጭት ምክንያት የተደቀነው አሰቃቂ የረሃብ አደጋ (ቢቢሲ) በኢትዮጵያ በኤል ኒኖ ምክንያት የተከሰተው የአየር ንብረት መዛባት በብዙ አካባቢዎች ከባድ ድርቅ፣ በሌሎች ቦታዎች ደግ
በኢትዮጵያ በድርቅና በግጭት ምክንያት የተደቀነው አሰቃቂ የረሃብ አደጋ (ቢቢሲ) በኢትዮጵያ በኤል ኒኖ ምክንያት የተከሰተው የአየር ንብረት መዛባት በብዙ አካባቢዎች ከባድ ድርቅ፣ በሌሎች ቦታዎች ደግሞ የጎርፍ አደጋ አስከትሏል። በተለይም በትግራይ እና በአፋር ክልሎች በዝናብ እጥረት ምክንያት ሰብሎች በመድረቃቸው እና መኖ በመታጣቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ከብቶች እየሞቱ ይገኛሉ። እንደ ቢቢሲ ዘገባ ከሆነ የዘንድሮው የኤል ኒኖ አደጋ ባለፉት አሥርታት ከተከሰቱት ሁሉ እጅግ የከፋው ሊሆን እንደሚችል ተመራማሪዎች አስጠንቅቀዋል። የአየር ንብረት ለውጡ ያመጣውን ችግር በክልሉ የነበረው ጦርነትና የጸጥታ ማጣት የበለጠ አብሶታል። በትግራይ ክልል 2.45 ሚሊዮን ሰዎች የአስቸኳይ ጊዜ የምግብ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሲሆን፣ አርሶ አደሮችም ከአካባቢያቸው ተንቀሳቅሰው ከብቶቻቸውን ለማዳን የጸጥታው ሁኔታ አልፈቀደላቸውም። በተጨማሪም የመልሶ ማቋቋም እና የእርዳታ አቅርቦቶች በመቋረጣቸው ምክንያት ችግሩ በቀጣዮቹ ዓመታት ሊባባስ እንደሚችል የክልሉ ኃላፊዎች ገልጸዋል። ይህ አደጋ ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን አጎራባች አገራትንም እየጎዳ ይገኛል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እንደገለጸው፣ ኤል ኒኖ በዓለም ዙሪያ ተጨማሪ 49 ሚሊዮን ሰዎችን ለከባድ ረሃብ ሊዳርግ ይችላል። በኢትዮጵያ፣ በኤርትራ እና በጂቡቲ የዝናብ እጥረት ሲከሰት፤ በሶማሊያ፣ በኬንያ እና በደቡብ ሱዳን ደግሞ እስከ ሦስት ሚሊዮን የሚደርሱ ሰዎች በጎርፍ ምክንያት ከቀዬአቸው ሊፈናቀሉ ይችላሉ። የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ… https://t.me/AdissAdmas
1 656
20
ትኩስ ፒዛ በሄሊኮፕተር የሚያደርሰው ሬስቶራንት በአሜሪካ አላስካ ግዛት የሚገኘው «ፍላይት ዴክ ፒዜሪያ» የተባለው ሬስቶራንት፣ ደንበኞቹ የሚያዙትን ትኩስ ፒዛ በቀጥታ በሄሊኮፕተር ከሰማይ ወደ ደጃፍ+1
ትኩስ ፒዛ በሄሊኮፕተር የሚያደርሰው ሬስቶራንት በአሜሪካ አላስካ ግዛት የሚገኘው «ፍላይት ዴክ ፒዜሪያ» የተባለው ሬስቶራንት፣ ደንበኞቹ የሚያዙትን ትኩስ ፒዛ በቀጥታ በሄሊኮፕተር ከሰማይ ወደ ደጃፍ ማድረስ የሚያስችል አስገራሚ አሰራር ጀምሯል። ይህ አዲስ አገልግሎት ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈ ሲሆን፣ ፒዛውን በሄሊኮፕተር ለማስመጣት የሚጠየቀው የማድረሻ ክፍያ ከራሱ ከፒዛው ዋጋ እጥፍ መሆኑ ታውቋል። ይሁን እንጂ የአካባቢው ነዋሪዎች ከፍተኛውን ወጪ ከፍለው አገልግሎቱን ለመሞከር ትልቅ ፍላጎት አላቸው። ደንበኞች የፒዛውን ጣዕም ብቻ ሳይሆን ሄሊኮፕተር ደጃፋቸው ላይ አርፋ ትኩስ ፒዛ ስታስረክብ የሚሰማቸውን ልዩ ስሜት በጣም ወደውታል ተብሏል። ሬስቶራንቱ ከፍተኛ የማድረሻ ክፍያ ቢጠይቅም በሰዎች ትዕዛዝ መጨናነቁን ጠቁሟል።
1 805