234
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ትፈለጋላችሁ!!!
የት/ቤታችን የቀድሞ ተማሪዎች ፣መምህራንና የአስተዳደር ሰራተኞች ፣ ሾላ (መገናኛ) እና አካባቢው የምትገኙ ባላሃብቶች፣ መላው የአካባቢያችን ነዋሪዎች :- ትውልድን በዕውቀትና በስነ-ምግባር በማነፅ ለበርካታ አመታት አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘውና ለሃገራችን በርካታ ስራ የሰሩ ግለሰቦችን ያፈራው የወጣቶች ገነት ቅ/1ኛ እና የመጀመሪያ ት/ቤት ለሚቀጥለው ዓመት የሚያከብረውን 50ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና ሌሎች ጉዳዮችን በማስመልከት ስራዎችን ከእናንተ ጋር በጋራ ለመስራት ስላሰብን እዚህ ግሩፕ ውስጥ በመቀላቀል እንወያይ በማለት ጥሪ እናቀርባለን ።
- መልዕክቱ ለሌሎችም እንዲደርስ ግሩፑ ውስጥ ያላችሁ አባላት ስልካችሁ ላይ የሚገኙ ሰዎችን Add እንዲሁም የግሩፑን ሊንክ ሼር በማድረግ ይተባበሩ።
ት/ቤቱ
https://t.me/WotatochGenet
Repost from Yeka Education
➡“ከ150ሺህ የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ውስጥ ያለፉት 70 ሺህ ብቻ ናቸው!” -ትምህርት ሚኒስቴር
➪የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች የማለፊያ ነጥብ ያስመዘገቡት 40 በመቶ ብቻ መሆናቸውን ትምህርት ሚኒስቴር ገለጸ!
➪የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተናን ከወሰዱ 150 ሺህ ገደማ ተማሪዎች ውስጥ ያለፉት 40.6 በመቶ ብቻ መሆናቸውን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ካስፈተኗቸው ተማሪዎች ውስጥ የማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡት 17.23 ብቻ መሆናቸውን ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡
➪የትምህርት ሚኒስቴር ይህንን ያስታወቀው ትላንት አርብ የተጠናቀቀውን የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና አፈጻጸም አስመልክቶ ዛሬ ቅዳሜ ሐምሌ 8፤ 2015 በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው። በዚህ ዓመት ለመጀመሪያ ጊዜ መሰጠት የተጀመረውን የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ተማሪዎች ከባለፈው ሳምንት ሰኔ 30 እስከ ትላንት አርብ ሐምሌ 7 ደረስ ሲወስዱ ቆይተዋል፡፡
https://t.me/WotatochGenet
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆 ከላይ ያለዉን የግሩፓችንን ሊንክ ሰለካችን ላይ ለሚገኙ ለት/ቤታችን ቀድሞ ተማሪዎች፣ ሰራተኞች፣ የሾላ (መገናኛ) አካባቢ ነዋሪዎች እና ጓደኞቻችን በመላክ እና ሼር በማድረግ እና የገሩፕ አባላትን በማብዛት ወደፊት ለምናከናዉናቸዉ የተለያ ተግባራ ራሳችንን ዝግጁ እናድርግ፡
የወጣቶች ገነት 1ኛ ደረጃ ት/ቤት በአዲስ አበባ ከተማ ሾላ ገበያ አካባቢ የሚገኝ እና ለበርካታ አመታት ለማህበረሰቡ የዕውቀት ቤት በመሆን እያገለገለ ይገኛል። በዚህ ት/ቤት ተምረውና ለቁም ነገር በቅተው በተለያዬ ሃገርና የሙያ መስክ ላይ የሚገኙ የቀድሞ ተማሪዎች እንዳሉ ይታወቃል። በዚህ ዓመት ት/ቤቱ የቀድሞ የት/ቤታችን ተማሪዎችን እና ሰራተኞችን በአካልና በሌሎች አማራጮች በማሰባሰብ የተለያዩ ስራዎችን ለመስራት ስላሰበ እዚህ ቻናል ውስጥ ያላችሁ አባላት በግሩፑ ሊንክ https://t.me/WotatochGenet በመጠቀም ግሩፑን በመቀላቀልና ስልካችሁ ላይ የሚገኙ የቀድሞ ተማሪዎችና ሰራተኞችን Add በማድረግ ወይም የግሩፑን ሊንክ https://t.me/WotatochGenet በመላክ Share በማድረግ እንድንሰባሰብና ግሩፑ ላይ ሃሳቦችን እንድንለዋወጥ እንጠይቃለን።
Repost from 𝕖𝕕𝕦𝕔𝕒𝕥𝕚𝕠𝕟 ️️️𝕗𝕠𝕣 𝕒𝕝𝕝 📚
ኮምፒውተራችሁ እየተንቀራፈፈ ተቸግራችኋል?እንግዲያውስ ፍጥነቱን ሊጨምሩ የሚችሉ ነገሮችን እናያለን😊።
📌1. Power option
- Start menu ላይ power option ብላቹ ፈልጉ ከሚመጣላቹ window ውስጥ high performance የሚለውን ምረጡ
📌2.Disable unwanted start up programs
- ይሄ ኮምፒዩተራችንን በምንከፍትበት ጊዜ ያለ እኛ ፍቃድ ፕሮግራሞችን እየከፈተ ፍጥነቱን ከሚቀንሱ ነገሮች አንዱ ነው። ይሄን ለመከላከል
- Task manager ላይ መግባት (ይሄን ለማግኘት start menu ላይ right click አድርጎ ማግኘት ይቻላል አልያም Ctrl Alt እና delete የሚለውን አንድ ላይ መጫን) ከሚመጣው window ውስጥ start up ላይ በማድረግ የማትፈልጉትን ፕሮግራሞች disable ማድረግ።
- እዚህ ጋር impact የሚለው high ከሆነ disable ባታረጉ ይመረጣል።
📌3.Defragment and optimize drive Start menu search bar ላይ defragment ብሎ መፈለግ
- Window ሲመጣላቹ የምትፈልጉትን driver መርጣቹ optimize ማድረግ
📌4.Delete unnecessary temporary file Start menu ላይ right click አድርጎ run የሚለውን መምረጥ አልያም window key እና R ን ከ ኪቦርዳችን ላይ አንድ ላይ መጫን
%temp% ብሎ ጽፎ enter መጫን የሚመጣላቹ folder ላይ ያሉ ፋይሎችንctrl + A ተጭነን ሁሉንም ሲመርጥልን ማጥፋት
ድጋሚ run ቦክሱን ከፍታቹ temp ብሎ መጻፍ ከሚመጣላቹ folder ውስጥ ያሉ ፋይሎችን ሁሉ ማጥፋት አሁንም ለ ሶስተኛ ጊዜ run ቦክስ ላይ prefetch ብሎ መጻፍ የሚመጣላቹ folder ውስጥ የሚገኙ ፋይሎችን ማጥፋት።
- እነዚህን የምናጠፋበት ምክንያት ጊዜያዊ እና space የያዙ ፋይሎች ስለሆኑ ነው። ምንም አይነት ችግር አያመጡም።
📌5. Clean up Memory
- This pc ውስጥ ገብታቹ የምፈልጉት local ዲስክ ላይ right click በማድረግ property መምረጥ Disk clean up የምትለውን icon click ማድረግ የሚመጣውን የ warning box ok ማድረግ እዚህ ጋ recycle bin ውስጥ ያሉ ፋይሎች ሳይቀሩ ነው የሚጠፉት
📌6. Reduce run time service
Run box ከፍታቹ msconfig ብሎ መጻፍ ቀጥሎ ከሚመጣው window service የሚለውን መጫን በመቀጠል hide all microsoft service የሚለውን tick ማድረግ በመቀጠል disable የምትለዋን icon click ማድረግ
📌7. Registry tweaks
- Run box መክፈት(window key + R) regedit ብሎ መጻፍ
Hkey -current user Control panel Mouse Mouse hover time valueን ወደ 10 መቀየር
እዛው folder ላይ desktop መምረጥ Menu show delay
Valueን ወደ 10 መቀየር
📌8. visual effects
- Start menu ላይ System ብሎ መፈለግ Advanced system setting መምረጥ
Advance ውስጥ በመግባት setting መምረጥ Adjust for best performance መምረጥ
ቀጥሎ የምትፈልጉት ነገር ካለ ቲክ በማድረግ መምረጥ በመጨረሻም ከላይ ያሉትን ከጨረስን በኋላ ኮምፒዩተራችንን Restart ማድረግ
┈┈┈••✦✦••┈┈┈
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
🍁 Join : @Aksipspg
🍁 Join : @Aksipspg
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
┈┈┈••✦✦••┈┈┈
Repost from Addis Ababa Education Bureau
ቀን 3/11/2015 ዓ.ም
ቢሮው ለመምህራን ፣ ርዕሳነ መምህራን ፣ ሱፕርቫይዘሮችና አሰልጣኞች የሚሰጠውን የትራንስፖርት አገልግሎት ውል አደሰ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ከአዲስ አበባ ከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት ጋር በመዋዋል በየዓመቱ ለመምህራን ፣ ርዕሳነ መምህራን ፣ ሱፕርቫይዘሮችና አሰልጣኞች የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲቀርብ የሚያደርግ ሲሆን ለ2016 ዓ.ም አግልግሎቱ ያለምንም መስተጋጎል እንዲቀርብ ለማድረግ ቢሮው ውሉን አድሳል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ስር በመንግስት ትምህርት ቤቶች ውስጥ በማስተማር ሙያ ላይ ያሉ መምህራን ፣ ርዕሳነ መምህራን ፣ ሱፕርቫይዘሮችና አሰልጣኞች የትራንስፖርት አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ቢሮ በዓመት 117,312,000 ብር ወጪ ያደርጋል፡፡
በውል ማደስ መርሃ ግብር ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛው አለሙ፣ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ማኔጅመንት አባላትና ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ተሳትፈዋል፡፡
ለወጣቶች ገነት 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ወላጆች ፣መምህራን እና ተማሪዎች እንድሁም የት/ት ባለድርሻ አካላት በሙሉ
ቀደም ሲል ለተማሪዎች ፣ በማስታወቂያ እና በት/ቤታችን ቴሌግራም የፊታችን እሁድ ሀምሌ 2/11/2015 የተማሪዎች ሰርተፊኬት እንደሚሰጥ ማሳወቃችን ይታወቃል። በመሆኑም ሁሉም የተማሪ ወላጆች፣ ተሸላሚ ተማሪዎች እሁድ ከጠዋቱ 2:30 እድትገኙ እናሳስባለን።
እንድሁም ሁሉም መምህር በተለይም ስም ጠሪ መምህራን በእለቱ ተገኝተን ሰርተፊኬት እድትሰጡ እናሳስባለን።
ማሳሰቢያ ማርፈድ እና መቅረት አይፈቀድም ሁሉም ወላጅ በሰአቱ እና በእለቱ ሰርተፊኬቱን እድወስድ እያሳሰብን በእለቱ ያልተገኘ ወላጅ በድጋሜ የማናስተናግድ በመሆኑ ሁሉም በእለቱ እድገኝ በጥብቅ እናሳስባለን።
ምን አልባት ተማሪዎች ያልነገሯቸው፣ ማስታወቂያም ሆነ ቴሌግራም ላላዩ፣ ላልሰሙ፣ ላላወቁ (መረጃ ለሌላቸው) ሁላችንም ሸር አድርጉላቸው ለምታውቋቸው በሙሉ ።
