en
Feedback
ወጣቶች ገነት ቅ/አ እና 1ኛ ደረጃ ት/ት ቤት

ወጣቶች ገነት ቅ/አ እና 1ኛ ደረጃ ት/ት ቤት

Open in Telegram
234
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
14ተኛው የኪነጥበብ ውድድር የተገኙ ሽልማቶች

እንኳን ለ1444ኛ የኢድ አል አደሀ አረፋ በአል በሰላም አደረሳችሁ
እንኳን ለ1444ኛ የኢድ አል አደሀ አረፋ በአል በሰላም አደረሳችሁ

Repost from N/a
የ2015ዓ/ም የክፍል ውስጥ ዝውውር ፖሊስ።
+2
የ2015ዓ/ም የክፍል ውስጥ ዝውውር ፖሊስ።

1.ሐሙስ ሰኔ 22/2015 ዓ.ም በጣቢያ ሀላፊ ፣ለሱፐርቫይዘሮች፣ ለፈታኝ እና ጤና ባለሙያዎች በተመደቡበት የፈተና ጣቢያ ኦረንቴሽን ይሰጣል 2.አርብ ሰኔ 23/2015 ዓ.ም ለ8ኛ እና 6ኛ ክፍል ተ
1.ሐሙስ ሰኔ 22/2015 ዓ.ም በጣቢያ ሀላፊ ፣ለሱፐርቫይዘሮች፣ ለፈታኝ እና ጤና ባለሙያዎች በተመደቡበት የፈተና ጣቢያ ኦረንቴሽን ይሰጣል 2.አርብ ሰኔ 23/2015 ዓ.ም ለ8ኛ እና 6ኛ ክፍል ተማሪዎች በተመደቡበት የመፈተኛ ጣቢያ ኦረንቴሽን ይሰጣል 3.ከሰኔ 26-27/2015 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ይሰጣል፡፡ 4.ከሰኔ 28-30/2015 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ይሰጣል፡፡ ✅በመሆኑም ሁሉም የግል እና የመንግስት ት/ቤቶች እና ወላጆች ተማሪዎች ወደ ተመደቡበት የፈተና ጣቢያ በተቀመጠው ፕሮግራም መሠረት ተገኝተው ፈተናቸውን በአግባቡ እንዲወስዱ በማድረግ የበኩላቹህን አስተዋጽኦ እንድታበረክቱ አደራ እንላለን በጋራ እርብርብ የተማሪዎቻችንን ውጤት እና ስነምግባር እናሻሽላለን!!

የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ለማሻሻል አገር አቀፍ ሕዝባዊ ንቅናቄ ሊካሄድ ነው የትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ለማሻሻል የትምህርት ባለድርሻዎችንና ሕብረተሰቡን ያሳተፈ አገ
የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ለማሻሻል አገር አቀፍ ሕዝባዊ ንቅናቄ ሊካሄድ ነው የትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ለማሻሻል የትምህርት ባለድርሻዎችንና ሕብረተሰቡን ያሳተፈ አገር አቀፍ የህዝብ ንቅናቄ ሊያካሄድ መሆኑን አስታውቋል። አገር አቀፍ ንቅናቄው ሰኔ 25/2015 የመንግሥት ከፍተኛ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በይፋ እንደሚጀመር ተገልጿል። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ አገር አቀፍ ንቅናቄው ሕብረተሰቡ የትምህርት መሠረተ-ልማት በማሻሻል የመማር ማስተማሩን ሂደት በባለቤትነት እንዲደግፍ ለማድረግ መሆኑን ገልጸዋል። የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት የማሻሻል ሥራ ለመንግሥት ብቻ የተተወ ኃላፊነት አለመሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትሩ፤ በየደረጃው ያለው ማሕበረሰብና ልዩ ልዩ አካላት ተሳትፏቸውን ሊያሳድጉ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡ አብዛኞቹ የመጀመሪያ፣ መካከለኛና ኹለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ንጹህና በቂ ውሃ እንደማያገኙ፣ የኤሌክትሪክ፣ የመፀዳጃ፣ የመማሪያ፣ የቤተ መጻህፍት፣ የቤተ ሙከራ፣ የስፖርት ማዘውተሪያና ሌሎችም ችግሮች እንዳሉባቸው ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡ በአገሪቱ የመጀመሪያና ኹለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚስተዋሉ ዋነኛ የትምህርት መሰረተ ልማት ችግሮችን ለመፍታት እየተሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል። በዚህም ባለሀብቶች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ አርቲስቶች፣ ዲያስፖራ አባላት፣ ልዩ ልዩ አደረጃጀቶች፣ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያሆኑ የበጎ አድርጎት ድርጅቶች፣ ማሕበራትና ሌሎችም የትምህርት ሥራ አጋሮችና ባለድርሻዎች በንቅናቄው የድርሻቸውን እንዲወጡ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ትብብር ይመለከታል!! 👉ከዚህ በታች ያሉት የቴሌግራም ቻናሎች የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ እና የየካ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የቴሌግራም ቻናል ሲሆን በከተማ አስተዳደሩ እስከ
ትብብር ይመለከታል!! 👉ከዚህ በታች ያሉት የቴሌግራም ቻናሎች የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ እና የየካ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የቴሌግራም ቻናል ሲሆን በከተማ አስተዳደሩ እስከ ትምህርት ቤት ድረስ የተከናወኑ እንዲሁም ሀገራዊ ፣ አህጉራዊ እና አለማቀፋዊ የትምህርት መረጃዎች እና የተለያዩ ጥያቄዎች ተደራሽ የሚደረጉበት ናቸው:: 👌 በመሆኑ በመጭው ክረምት የተለያዩ ትምህርት ተኮር ስራዎች በአግባቡ ተደራሽ ይሆኑ ዘንድ 👉 ለመምህራን 👉ለተማሪዎች 👉ለተማሪ ወላጆች  እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በማስተዋወቅ እንድትተባበሩን በትህትና እንጠይቃለን አዲስ አበባ ት/ቢሮ የቴሌግራም ቻናል 👇👇👇👇👇 👇👇👇👇👇 https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau የየካ ክፍለ ከተማ ት/ጽ/ቤት የቴሌግሬም ቻናል 👇👇👇👇 👇👇👇👇 https://t.me/dam76

+7
ENGLISH gr6 model 3.pdf3.73 KB

+1
አንበሳና አይጥ.pdf0.37 KB

Repost from Yeka Education
በየካ ክፍለ ከተማ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል የፈተና ጣቢያ የሆኑ ት/ቤቶች እና የሌሎች አስፈታኝ ት/ቤቶች ድልድል መረጃ
+1
በየካ ክፍለ ከተማ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል የፈተና ጣቢያ የሆኑ ት/ቤቶች እና የሌሎች አስፈታኝ ት/ቤቶች ድልድል መረጃ

የ6ኛ ክፍል ፈተና አወሳሰድ ኦረንቴሽን
+7
የ6ኛ ክፍል ፈተና አወሳሰድ ኦረንቴሽን

በመዲናዋ ለቀጣዩ የትምህርት ዘመን ምዝገባ የልደት የምስክር ወረቀት ማቅረብ ግዴታ ነው ተባለ አርብ ሰኔ 2 ቀን 2015  ለ2016 የትምህርት ዘመን ምዝገባ፤ ወላጆች የልጆቻቸውን የልደት ምስክር ወረቀት የማቅረብ ግዴታ እንዳለባቸው የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አስታወቀ። ምዝገባውን ከአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ጋር በቅንጅት እያከናወነ እንደሆነም ገልጿል። ኤጀንሲው “የልደት ምዝገባ ለኹሉም ተማሪ” በሚል መሪ ቃል ባዘጋጀው ንቅናቄ በትናንትናው ዕለት የተማሪዎች የልደት ምዝገባ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ ኹለት አሳይ አንደኛና ኹለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አከናውኗል። የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ዮናስ አለማየሁ በወቅቱ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ በአገሪቱ ከሥነ-ህዝብ ለውጥ ጋር ቀጥተኛ ተያያዥነት ያለው በመሆኑ የሕዝብ ብዛትና እድገትን ማወቂያ መንገድ ነው። ይህም መንግሥት ለሚያከናውናቸው ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ እቅዶችና የአስተዳደራዊ አገልግሎቶች ዝግጅት የመረጃ ምንጭ ይሆናል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ መብት በመሆኑ መንግሥታት ይህን መብት ለማስፈጸም አስፈላጊውን አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወስዱ ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ያዛሉ። ይህም አገራት ከወሳኝ ኩነት ምዝገባ ማግኘት የሚገባቸውን ጥቅም እንዲያገኙ ያደርጋል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ በአዲስ አበባ ለ2016 የትምህርት ዘመን ምዝገባ ወላጆች የልጆቻቸውን የልደት ምስክር ወረቀት ማቅረብ እንደሚኖርባቸው ገልጸዋል።  “በንቅናቄው ኹለት ጉዳዮችን እያከናወነ ነው። አንደኛ ለተማሪዎች የወሳኝ ኩነት ምዝገባ የሚኖረውን ጠቀሜታ ማስገንዘብ ሲሆን፤ ኹለተኛ የልደት ምዝገባ ማከናወን ነው” ያሉት ዮናስ፤ መንግሥት ኅብረተሰቡ የሚፈልገውን ለማሟላት የወሳኝ ኩነት መረጃ ያስፈልገዋል፤ ለዚህም ለ2016 የትምህርት ዘመን ምዝገባ የልደት ምስክር ወረቀት ማቅረብ አስገዳጅ ሆኗል ብለዋል። በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መብራቱ ደሴ በበኩላቸው፤ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ “የልደት ምዝገባ ለኹሉም ተማሪ” በሚል መሪ ቃል በአሳይ አንደኛና ኹለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የልደት ምዝገባ መጀመሩን አብስረው፤ በአሳይ ትምህርት ቤት ብቻ ለአንድ ሺሕ ኹለት መቶ ተማሪዎች የልደት ምዝገባ ለማድረግ እቅድ መያዙን ገልጸዋል። በ2016 የትምህርት ዘመን አንድም ተማሪ ያለ ልደት ካርድ ምዝገባ እንዳይካሄድ ተወስኗል ያሉት ኃላፊው፤ በትምህርት ቤቶች የልደት ምዝገባ እስከ ሰኔ ወር መጨረሻ ድረስ በክፍለ ከተማው በሚገኙ በኹሉም ትምህርት ቤቶች እንደሚሰጥ ገልጸዋል። በዚህም የልደት ሰርተፍኬት የሚሰጠው ከዚህ በፊት የልደት ሰርተፍኬት ለሌላቸው ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። #አዲስ ማለዳ

Repost from Yeka Education
የ2015ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል የመልስ ወረቀት 👉የ8ኛ ክፍል ለሁለቱም ስርዓተ ትምህርት ተመሳሳይ ወይም አንድ አይነት ነው፡፡ 👉ለ6ኛ ክፍል ለአፋን ኦሮሞ ስርዓተ ትምህርት ለሁሉም የትምህርት
+3
የ2015ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል የመልስ ወረቀት 👉የ8ኛ ክፍል ለሁለቱም ስርዓተ ትምህርት ተመሳሳይ ወይም አንድ አይነት ነው፡፡ 👉ለ6ኛ ክፍል  ለአፋን ኦሮሞ ስርዓተ ትምህርት ለሁሉም የትምህርት ዓይነት ተመሳሳይ ወይም አንድ አይነት  ነው፡፡ 👉ለ6ኛ ክፍል አማርኛ ስርዓተ ትምህርት የመልስ ምርጫዎቹ  ለእንግሊዝኛ  ትምህርት A:B:C;D ሲሆን ሌሎቹ የትምህርት አይነቶች በአማርኛ ፊደል ሀ፤ለ፤ሐ፤መ ስለሆነ በተላከው የመልስ ወረቀት መሰረት ሞዴል ፈተና እንዲለማመዱ መደረግ አለበት፡ 👉ሁሉም የመንግስት እና የግል ት/ቤት የ6ኛ ፣8ኛ እና 12ኛ ክፍል የሞዴል ፈተና በወጣው ፕሮግራም ማለትም -ከሰኔ 7-9/2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና ይሰጣል፡፡ - ከሰኔ 7-8/2015 ዓ.ም የ6 እና 8ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና ይሰጣል :: 👌የመልስ መስጫ ቅጹ በተቀመጠው የመልስ መስጫ ቅጽ መሠረት ማስፈተን ይኖርበታል:: 👌አድሚሽን ካረድ ፕሪንት ለማድረግ ያስቸገራቹህ በአስቸኳይ ሪፖርት አድርጉ የየካ ክፍለ /ት/ጽ/ቤት

ን፡- 01/10/2015 ዓ.ም ማስታወቂያ የልደት የምስክር ወረቀት ለሌላችሁ ተማሪዎች ለቀጣይ የ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የትምህርት ቤት ምዝገባ ሲከናወን ተመዝጋቢዎች የልደት ሰርተፍኬት እንዲያቀርቡ እንዲደረግ በተላለፈዉ መመሪያ መሰረት በት/ቤታችን የልደት ምስክር ወረቀት የሌላቸዉ ተማሪዎች ነገ አርብ ሰኔ 2/2015 ዓ.ም ከወረዳ ወሳኝ ኩነት ጽ/ቤት በሚመጡ ባለሙያዎች ሰለሚሰጥ ሰርተፍኬቱ የሌላቸዉ ተማሪዎች ዛሬ ቤት እንዲሞላ የላክነዉን ፎርም በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ በትክክል በመሙላት እና በተጨማሪም 👉🏽 200 ብር ፣ 👉🏽 የእናት እና አባት (አሳዳጊ) መታወቂያ ኮፒ እና 👉🏽 የተማሪዉን 1 ፎቶ በመያዝ ወላጆች ከተማሪዉ ጋር አብራችሁ እንድትገኙ እናሳሰባለን፡፡ የልደት ሰርተፍኬት ሳይኖረዉ ተማሪዉ የሚሞላ ፎርም በአጋጣሚ ወደቤቱ ይዞ ካልመጣ ፎርሙን እዚህም መሙላት ሰለሚቻል ወላጁ ነገ ጠዋት ሌሎች ከላይ የተጠቀሱትን አስፈላጊ ነገሮች ይዞ መገኘት ይኖርበታል፡፡ ት/ቤቱ

It was a beautiful day. We thank all volunteers, the school administration, the Woreda Health office, st Paul pharmacy, Black lion pharmacy, Aster volunteers, GIV Society and everyone involved in this noble deed. We’re grateful to Abreham & the GIV team for their excellent coordination and commitment. You’re such a blessing to all of us. Thank you🙏🏽

ቀን 27/9/2015 ዓ.ም በአብዮት የመጀ/ደ/ት/ቤት የሚማሩ ልዩ ፍላጎት የሚሹ ተማሪዎች በእንሆ ፍቅር በጎ አድራጎት ድርጅት የተለያየ ሆስፒታል ተውጣጥተው በመጡ ዶክተሮች በወጣቶች ገነት ት/ቤት ለ
ቀን 27/9/2015 ዓ.ም በአብዮት የመጀ/ደ/ት/ቤት የሚማሩ ልዩ ፍላጎት የሚሹ ተማሪዎች በእንሆ ፍቅር በጎ አድራጎት ድርጅት የተለያየ ሆስፒታል ተውጣጥተው በመጡ ዶክተሮች በወጣቶች ገነት ት/ቤት ለ28 ተማሪዎች ነፃ ህክምና ድጋፍ ተደረገላቸው፡፡ እኛም በት/ቤታችን ስም እንሆ ፍቅር በጎ አድራጎት ድርጅትን እናመሰግናለን፡፡