en
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Channel የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 14 442 subscribers, ranking 6 042 in the Religion & Spirituality category and 2 328 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 14 442 subscribers.

According to the latest data from 28 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 550 over the last 30 days and by 26 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 37.47%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 10.23% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 5 412 views. Within the first day, a publication typically gains 1 477 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 33.

📝 Description and content policy

Channel description not provided.

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 29 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

14 442
Subscribers
+2624 hours
+1347 days
+55030 days
Posts Archive
በመንፈስ ቅዱስ የተቃኙ አባቶች የመንፈስ ቅዱስ መሰንቆ የቃኛቸው አባቶች በመንፈሳዊ ሥልጣን ላይ ሲቀመጡ ራሳቸውንም ሌሎችንም ይጠቅማሉ። በመንፈስ ቅዱስ የተቃኙ አባቶች በፈቃደ እግዚአብሔር ስለሚመሩ
በመንፈስ ቅዱስ የተቃኙ አባቶች የመንፈስ ቅዱስ መሰንቆ የቃኛቸው አባቶች በመንፈሳዊ ሥልጣን ላይ ሲቀመጡ ራሳቸውንም ሌሎችንም ይጠቅማሉ። በመንፈስ ቅዱስ የተቃኙ አባቶች በፈቃደ እግዚአብሔር ስለሚመሩ ክርስቲያኖች ሁሉ እግዚአብሔር በሚፈቅደው መንገድ እንዲጓዙ ያደርጋሉ። እንዲህ ማድረጋቸው ሃይማኖት እንዲጸና ቀኖና ቤተ ክርስቲያን እንዲጠበቅ ሳይታክቱ ይሠራሉ። መሥራት ብቻ ሳይሆን ራሳቸው አርአያ ሆነው ፈጽመው ያሳያሉ። ማንበብ ይቀጥሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/በመንፈስ-ቅዱስ-የተቃኙ-አባቶች/ በመንፈስ ቅዱስ የተቃኙ አባቶች ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg

"የሁሉ ዓይን አንተን ተስፋ ያደርጋል፤ አንተም ምግባቸውን በየጊዜው ትሰጣቸዋለህ።" መዝ 114፡13 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Yout
"የሁሉ ዓይን አንተን ተስፋ ያደርጋል፤ አንተም ምግባቸውን በየጊዜው ትሰጣቸዋለህ።" መዝ 114፡13 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

"ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።" ማቴ 6፡33 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion/video/72939504
"ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።" ማቴ 6፡33 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion/video/7293950430143450410?is_from_webapp=1&sender_device=pc&web_id=7288000334784579078

#ሙሽራው ገብረ ክርስቶስ ገብረ ክርስቶስ አባቱ የቁስጥንጥንያ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ እናቱ ንግሥት መርኬዛ ሲሆኑ በስለት ያገኙት ብቸኛ ልጃቸው ነው፡፡ ሥጋዊና መንፈሳዊ ትምህርትን እያስተማሩት በምግባር አሣድገውታል፡፡ ለአካለ መጠን ሲደርስም የአባቱን ንግሥና በመውረስ ቁስጥንጥንያን እንዲገዛ በማሰብ የሮሜውን ንጉሥ ልጅ አጭተው አጋቡት፡፡ እርሡ ግን ዓለምን ፍጹም በመናቅ፣ የክርስቶስን መስቀል ለመሸከም የተዘጋጀ ነበርና ሌሊት በኾነ ጊዜ ወደ ሙሽራይቱ ገብቶ እጇን ይዞ ጸሎተ ሃይማኖትን እስከ መጨረሻው ደግሞ፣ እንዳትናገር ቃል አስገብቶ፣ የተሞሸረበትን ልብስ አውልቆ ‹‹እኅቴ ሆይ እንደ ጉም ተኖ እንደ ጢስ በኖ ከሚጠፋ ተድላ ሥጋ አልገባም፤ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ይኑር ከሰይጣን ሥራ ያድንሽ የአባቴ መንግስት ኀላፊ ጠፊ ነውና እኼዳለኹ እንዳትናገሪ›› ብሎ የእራሱንም የሙሽራዋንም ድንግልና እንደጠበቀ በሌሊት ወጥቶ ሄደ፡፡ ከዚያም በመርከብ ተሳፍሮ የብዙ ቀን መንገድ የሚሆን ጎዳና በአንድ ቀን ተጉዞ አርመንያ ደረሰ፡፡ በዚያም በእመቤታችን ስም በታነጸች ቤተ ክርስቲያን ከነድያን ጋር በመቀላቀል እየለመነ ያገኘውንም ለሌሎች እየመጸወተ በጾም በጸሎት ተጠምዶ ዐሥራ አምስት ዓመት ሲኖር እመቤታችን ለገበዙ ተገልጻ ‹‹ገብረ ክርስቶስን ይዘኽ ከቤተ ክርስቲን አግባው›› አለችው፡፡ ገበዙም ኺዶ ‹‹እመቤቴ አዛኛለችና ገብተኽ ሥጋ ወደሙን ተቀበል፡፡›› አለው፡፡ ገብረ ክርስቶስም የታዘዘውን ከፈጸመ በኋላ ‹‹ዋጋዬን በውዳሴ ከንቱ ሊያጠፉብኝ ነው›› ብሎ ከእመቤታችን ፊት ቆሞ ‹‹ምሥጢሬን ለምን ገለጽሽ አኹንም ወደ ሚሻለኝ ምሪኝ›› ብሎ በመጸለይ ሥዕሏን ተሳልሞ ወደ ሌላ ሀገር ሊኼድ በመርከብ ተሳፍሮ ከእናት አባቱ ሀገር ደረሰ፡፡ የጌታ ፈቃድ ነው ብሎም ማንነቱን እንደደበቀ ሣያውቁት ከንጉሥ አባቱ ደጅ የኔቢጤ /ለማኝ/ ሆኖ ለአባቱ ውሾች የሚሰጠውን ፈርፋሪ እየተመገበ ሠላሳ ዓመት በዚያ ተቀመጠ፡፡ የአባቱ አሽከሮች እንኳን እጣቢና ቆሻሻውን ሁሉ እየደፉበት ሲያሰቃዩትና ውሾች እንዲናጠቁትም የሥጋ ውሃ ሲደፉበት ውሾቹ ግን ቁስሉን ይልሱለት ነበር፡፡ እርሱም በደል እንዳይሆንባቸው በመጸለይ፣ እየለመነ ያገኘውን እየመጸወተ፣ በጾም በጸሎት እየተጋደለ ኖረ፡፡ ከእለታት አንድ ቀን ጌታችን ስሙን ለሚጠራ፣ መታሰቢያውን ለሚያደርግ ቃልኪዳን ከሠጠው በኋላ እርሱም ታሪኩን ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ጽፎ በእጁ እንደጨበጠው ጥቅምት ዐሥራ አራት ቀን ዐርፏል፡፡ የቁስጥንጥንያው ሊቀጳጳስ አባ ቴዎፍሎስ በቅዳሴ ላይ ሳለ ‹‹ብእሴ እግዚአብሔርን በንጉሥ ቴዎድዮስ ቤት ፈልጉት፡፡›› የሚል ቃል ሰማና ቢሔድ ባረፈበት ቦታ ክርታሱን እንደጨበጠ አገኙት ሊያዩት ፈልገው አልለቅ ብሎ ፈጽሞ እምቢ አላቸው፡፡ ብዙ ምሕላና ጸሎት ከተደረገ በኋላ ለቆላቸው ቢያነቡት የንጉሥ ልጅ መኾኑንና ያሣለፈውን ተጋድሎ ተረድተዋል፡፡ እያለቀሱና ደረታቸውን እየደቁ ሥጋውን ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲወስዱት እጅግ ብዙ ተዓምራቶች በድውያንና ሕመምተኞች ላይ ተፈጽሟል፡፡ ብዙዎች ዳሰውት ከተፈወሱ በኋላ በአንጻረ መቅደስ ቀብረውታል፡፡ ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

አቡነ አረጋዊ ከእለታት አንድ ቀን እናቱ እድና ዜናውን ሰምታ ልትጠይቀው በመጣች ጊዜ ‹‹ለምን መጣሽ›› አላት፡፡ ‹‹ልጄ አንተ በሕጻንነትህ የናቅኸው ዓለም ለእኔ ምን ይረባኛል ብዬ ነዋ›› አለችው፡፡ እሱም አመንኩሶ ከሴቶች ገዳም አስገባት፡፡ ከሰባት ዓመት በኋላ ዘጠኙ ቅዱሣን በእምነት ወደ ምትመስላቸው ሀገረ እግዚአብሔር ኢትዮጵያ መጥተዋል፤ እናቱም አብራ ወደ ኢትዮጵያ መጥታለች፡፡ ከእነዚህም በይበልጥ የአባ ቴዎድሮስ እና የአባ ጳኩሚስ ደቀ መዝሙር የነበረ አባ ዘሚካኤል /አቡነ አረጋዊ/ በገዳመ አስቄጥስ በነበረበት ሰዓት ስለ እመቤታችን ከተጻፈው ነገረ ማርያም ጌታችን ኢትዮጵያን ዐሥራት እንደሰጣት በመስማቱ ሰባቱን አስከትሎ ወደ ኢትዮጵያ በንጉሥ አልዓማዳ ዘመን መጥተዋል፡፡ ከአባ ጰጉሚስ እንደተማሩት ሥርዐተ ምንኩስናን ማስተማር ማመንኮስ ጀመሩ፡፡ አቡነ ዘሚካኤል መጽሐፈ መነኮሰትን ከጽርእ ቋንቋ ወደ ግእዝ መልሶታል፤ የሱርስትን ቋንቋ ዐዋቂ ስለነበረ አስቀድሞ በቤተ ቀጢን ሰባት ዓመት የግእዝን ቋንቋ ከሰባቱ ጋር ተምሯል፡፡ አባ ገሪማ እስከዚህ ድረስ በሮም ነግሶ ይኖር ነበርና መልእክትን ልከውበት መንግስቱን ትቶ መጥቶ ዘጠነኛ ኹኗል፡፡ ከዐሥራ ሁለት ዓመት በኋላም በየእራሳቸው ተበታትነው ገዳም መስርተዋል፡፡ አቡነ አረጋዊም እናቱ አድናን እና ተማሪው ማትያስን አስከትሎ በአክሱም በስተ ምስራቅ ሰባ ኪሎ ሜትር ርቆ ወደ ሚገኘው ወደ ዳሞ ተራራ ኺዷል፡፡ ወደ ተራራው የሚወጣበት አጥቶ ባሰበ ጊዜ የታዘዘ ዘንዶ መጥቶ ስልሳ ክንድ በሚያህል ጅራቱ ጠምጥሞ በቅዱስ ሚካኤል ጠባቂነት ከተራራው ራስ አድርሶታል፡፡ እንዳደረሰውም ‹‹ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ›› ብሎ በማመስገኑ “ደብረ ሃሌ ሉያ” ተብሏል፡፡ ቦታው ዙሪያው ገደል በመኾኑ መውጫ አልባ የኾነውን ታላቁን የደብረ ዳሞን ገዳም የመሠረተ ሲሆን ይኽም የሀገራችን የመጀመሪያው ገዳም ነው፡፡ በአቡነ አረጋዊ ጥያቄም መሠረት በስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ደብረ ዳሞ ተራራ ላይ ዐጼ ገብረ መስቀል የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ቤተ ክርስቲያን አሠራ፡፡ ለሰራተኞች መውጪያና መውረጃ የተሰራው ደረጃ ስለተነሳ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ማንም ሰው ወደ ገዳሙ የሚደርሰው በአምሳለ ዘንዶ ከላይ በሚለቀቅለት ዐሥራ ስድስት ሜትር የተጎነጎነ ጠፈር ወገቡን ታስሮ በመጎተት ሲሆን ወደ ገዳሙ መውጣት የሚችሉት ወንዶች ብቻ ናቸው፡፡ ለሴቶች በእግረ ደብር ገዳም መሥርቶ እድናን እመመኔት አድርጎ ሹሞላቸዋል፡፡ ከዘጠኙ ቅዱሣን መካከል አቡነ አረጋዊ በግብጽ አባ እንጦንስ በመሠረቷት ገዳም በተማረው መሠረት በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ገዳማዊ ኑሮ መስራች አባት ነው፡፡ አቡነ አረጋዊ ከዐጼ ገብረ መስቀል እና ከቅዱስ ያሬድ ጋር በደቡቡ የሀገራችን ክፍል እየተዘዋወረ ወንጌልን ሲያስተምር ጋሞጎፋ ውስጥ ውሃ ከሌለበት ቦታ ደርሶ መሬቱን በመስቀል ባርኮ በአንድ ስፍራ ላይ በተዓምር አርባ ምንጮችን አፍልቋል፤ በዚህም ከተማው አርባ ምንጭ ተብሏል፡፡ በዚያም መስዋዕተ ኦሪት ይሰዋባቸው ከነበሩ ገዳማት አንዷ የሆነችውን ብርብር ማርያም ገዳምንም በመጎብኘት ወንጌልን በመስበክ አከባቢውን ባርኳል፡፡ በመጨረሻም ጌታችን ተገልጾ ‹‹መንግስትን ትተህ ስላገለገልከኝ መንግስተ ሰማያትን እርስኸለኹ…›› በማለት ልዩልዩ ቃልኪዳንን ከገባለት በኋላ ‹‹…ሞት አያስደነግጥኽም›› በማለት ተስፋውን ነግሮታል፡፡ ከዚያም መነኮሳቱን ሰብስቦ ‹‹ከዛሬ ጀምሮ በሥጋ አታዩኝም›› በማለት በእግዚአብሔር ጸጋ እንደ ሔኖክና ኤልያስ ጥቅምት ዐሥራ አራት ቀን ከሞት ፊት ተሸሸገ /ተሰወረ/፡፡

አቡነ አረጋዊ ወገብረ ክርስቶስ #አቡነ አረጋዊ /ዘሚካኤል/ አቡነ አረጋዊ ሀገሩ ሮም ሲሆን አባቱ ንጉሠ ሮም ይስሐቅ እናቱ እድና ይባላሉ፡፡ እናት አባቱ ገብረ አምላክ ብለው ሲጠሩት፤ ዘሚካኤል የሚለ
አቡነ አረጋዊ ወገብረ ክርስቶስ #አቡነ አረጋዊ /ዘሚካኤል/ አቡነ አረጋዊ ሀገሩ ሮም ሲሆን አባቱ ንጉሠ ሮም ይስሐቅ እናቱ እድና ይባላሉ፡፡ እናት አባቱ ገብረ አምላክ ብለው ሲጠሩት፤ ዘሚካኤል የሚለው በመነኮሰበት ወቅት የወጣለት ስም ነው፤ አረጋዊ የሚለውን ወደ ኢትዮጵያ መጥተው በቤተ ቀጢን በነበሩበት ጊዜ በፍጹም ፍቅርና ትሕትና ስላገለገለ ወንድሞቹ አረጋዊ ብለውታል፡፡ ጥበብ መንፈሳዊ ሲማር አድጎ ዐሥራ አራት ዓመት ሲኾነው ከነገሥታት ወገን የምትሆን ሚስትን ቢያጩለት እምቢ ብሎ ወደ ታላቁ አባት አባ ጳኩሚስ ገዳም ገብቶ ማዕረገ ምንኩስናን ተቀበለ፡፡ በዚህም ከእንጦንስና፣ ከመቃርስ፣ ከጳኩሚስም የምንኩስና ወይም መንፈሳዊ ሐረግ አራተኛ ትውልድ ነው፡፡ የንጉሥ ልጅ በሕጻንነት ምንኩስና መቀበሉን የሰሙ ሰባት ደጋግ ቅዱሳን ከያሉበት ተሰባስበው አባ ጳኩሚስ ገዳም በመግባት ማዕረገ ምንኩስናን ተቀብለው ሁሉንም ነገር ከአባ ጳጉሚስ ጠንቅቀው እየተማሩ ለብዙ ዓመታት ከእርሱ ጋር ተቀመጡ፡፡ እነዚህም ቅዱሳን አባ ጰንጠሌዎን፣ አባ ይምዓታ፣ አባ ጉባ፣ አባ አፍጼ፣ አባ ጽሕማ፣ አባ ሊቃኖስ እና አባ አሌፍ ናቸው፡፡

ደቂቀ ሰላም ወፍቅር በመጋቤ ብርሃናት ቆሞስ አባ ተክለያሬድ ጎርጎርዮስ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ https://vm.tiktok.com/ZMjbKw38P/
ደቂቀ ሰላም ወፍቅር በመጋቤ ብርሃናት ቆሞስ አባ ተክለያሬድ ጎርጎርዮስ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ https://vm.tiktok.com/ZMjbKw38P/

የትምህርት ማስጀመሪያ መርሐ ግብር በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥር በሚገኙ አጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች ተደረገ። ጥቅምት 13/02/2016 (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የ2016 ዓ.ም በሰንበት ትምህርት ቤቶች
+5
የትምህርት ማስጀመሪያ መርሐ ግብር በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥር በሚገኙ አጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች ተደረገ። ጥቅምት 13/02/2016 (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የ2016 ዓ.ም በሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ሰንበት ትምህርት ቤቶች የትምህርት ማስጀመርያ መርሐ ግብር ባሳለፍነው ቅዳሜና አሁድ ተደርገው አልፈዋል። የዝግጅት ክፍላችን በቦሌ ክፍለ ከተማ በሚገኙ ሰ/ት/ቤቶች ባደረገው ዳሰሳ በአጠቃላይ ከ38 በላይ ሰ/ት/ቤቶች የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ የጀመሩ ሲሆን በአያት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ፣ በየረር ቅዱስ ኡራኤል፣ በአራብሳ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፣ በገርጂ ቅዱስ ጊዮርጊስ አብያተ ክርስቲያናት በአካል በመገኘት ከቅድመ መደበኛ ጀምሮ እስከ ላይኞቹ ክፍሎች ለመማር ማስተማር ሂደቱ አስፈላጊ የሆኑ ነገሮችን በማማሏት ትምህርት መጀመራቸውን ለመመልከት ተችሏል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

"አስቀድሞም የወሰናቸውን እነዚህን ደግሞ ጠራቸው፤ የጠራቸውንም እነዚህን ደግሞ አጸደቃቸው፤ ያጸደቃቸውንም እነዚህን ደግሞ አከበራቸው።" ሮሜ 8፡30 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናል
"አስቀድሞም የወሰናቸውን እነዚህን ደግሞ ጠራቸው፤ የጠራቸውንም እነዚህን ደግሞ አጸደቃቸው፤ ያጸደቃቸውንም እነዚህን ደግሞ አከበራቸው።" ሮሜ 8፡30 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

ቡርክታዊት በደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሰ/ት/ቤት አገልጋይ ስትሆን በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ተፈትና 617 በማምጣት ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም አልፋለች። https:
ቡርክታዊት በደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሰ/ት/ቤት አገልጋይ ስትሆን በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ተፈትና 617 በማምጣት ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም አልፋለች። https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion/video/7293209441581698347?is_from_webapp=1&sender_device=pc&web_id=7288000334784579078

ከወርቃማው ሕግ አትንሸራተቱ የተከበራችሁ የማኅበራዊ ሚዲያችን ተከታታዮች አስቀድምን ባስነበብነው የዚህ ጽሑፍ የመጀመሪያ ክፍል ሰው በእግዚአብሔር አርአያ እና ምሳሌ የተፈጠረ የፍጥረታት ንጉሥ፣ ከሌሎ
ከወርቃማው ሕግ አትንሸራተቱ የተከበራችሁ የማኅበራዊ ሚዲያችን ተከታታዮች አስቀድምን ባስነበብነው የዚህ ጽሑፍ የመጀመሪያ ክፍል ሰው በእግዚአብሔር አርአያ እና ምሳሌ የተፈጠረ የፍጥረታት ንጉሥ፣ ከሌሎች ፍጥረታት ተለይቶ ዐዋቂ እና ሕያውነት ያለው፣ በፍጥረታት ላይ የሠለጠነ ባለጸጋ ፍጡር መሆኑን አቅርበን ነበር። በዚህም ምክንያት ሰው ነጻ ፈቃዱን ተጠቅሞ ሲጠፋ ከሦስቱ አካላት አንዱ ወልድ “እስመ በፈቃዱ፣ ወበሥምረተ አቡሁ ወመንፈስ ቅዱስ መጽዐ አድኀነነ” እንደ ተባለው ሰው ሆኖ ሰውን ከውድቀት አነሣው። ዘጠና ዘጠኙን ነገደ መላእክት ትቶ አንዱን ነገድ ሰውን ለመፈለግ ሰው የሆነው ለሰው ካለው ጽኑ ፍቅር የተነሣ ነው። ማንበብ ይቀጥሉ... 👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/ከወርቃማው-ሕግ-አትንሸራተቱ-የነገረ-ሰብ/ ከወርቃማው ሕግ አትንሸራተቱ (የነገረ ሰብእ ትምህርት ጉድለት የወለደው አገራዊ ቀውስ ክፍል ሁለት) (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu