የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
تُعد قناة የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 442 مشتركاً، محتلاً المرتبة 6 042 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 328 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 442 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 28 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 550، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 26، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 37.47%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 10.23% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 412 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 477 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 33.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
وصف القناة غير متوفر.
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 29 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.
14 442
المشتركون
+2624 ساعات
+1347 أيام
+55030 أيام
أرشيف المشاركات
በመንፈስ ቅዱስ የተቃኙ አባቶች
የመንፈስ ቅዱስ መሰንቆ የቃኛቸው አባቶች በመንፈሳዊ ሥልጣን ላይ ሲቀመጡ ራሳቸውንም ሌሎችንም ይጠቅማሉ። በመንፈስ ቅዱስ የተቃኙ አባቶች በፈቃደ እግዚአብሔር ስለሚመሩ ክርስቲያኖች ሁሉ እግዚአብሔር በሚፈቅደው መንገድ እንዲጓዙ ያደርጋሉ። እንዲህ ማድረጋቸው ሃይማኖት እንዲጸና ቀኖና ቤተ ክርስቲያን እንዲጠበቅ ሳይታክቱ ይሠራሉ። መሥራት ብቻ ሳይሆን ራሳቸው አርአያ ሆነው ፈጽመው ያሳያሉ።
ማንበብ ይቀጥሉ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://eotc-gssu.org/a/በመንፈስ-ቅዱስ-የተቃኙ-አባቶች/
በመንፈስ ቅዱስ የተቃኙ አባቶች
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
✍️ FaceBook 👇
https://www.facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
✍️Twitter👇
https://twitter.com/tibeb_feleg
"የሁሉ ዓይን አንተን ተስፋ ያደርጋል፤ አንተም ምግባቸውን በየጊዜው ትሰጣቸዋለህ።" መዝ 114፡13
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ።
ሰናይ ሌሊት!
✍️Youtube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
"ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።" ማቴ 6፡33
https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion/video/7293950430143450410?is_from_webapp=1&sender_device=pc&web_id=7288000334784579078
#ሙሽራው ገብረ ክርስቶስ
ገብረ ክርስቶስ አባቱ የቁስጥንጥንያ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ እናቱ ንግሥት መርኬዛ ሲሆኑ በስለት ያገኙት ብቸኛ ልጃቸው ነው፡፡ ሥጋዊና መንፈሳዊ ትምህርትን እያስተማሩት በምግባር አሣድገውታል፡፡ ለአካለ መጠን ሲደርስም የአባቱን ንግሥና በመውረስ ቁስጥንጥንያን እንዲገዛ በማሰብ የሮሜውን ንጉሥ ልጅ አጭተው አጋቡት፡፡ እርሡ ግን ዓለምን ፍጹም በመናቅ፣ የክርስቶስን መስቀል ለመሸከም የተዘጋጀ ነበርና ሌሊት በኾነ ጊዜ ወደ ሙሽራይቱ ገብቶ እጇን ይዞ ጸሎተ ሃይማኖትን እስከ መጨረሻው ደግሞ፣ እንዳትናገር ቃል አስገብቶ፣ የተሞሸረበትን ልብስ አውልቆ ‹‹እኅቴ ሆይ እንደ ጉም ተኖ እንደ ጢስ በኖ ከሚጠፋ ተድላ ሥጋ አልገባም፤ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ይኑር ከሰይጣን ሥራ ያድንሽ የአባቴ መንግስት ኀላፊ ጠፊ ነውና እኼዳለኹ እንዳትናገሪ›› ብሎ የእራሱንም የሙሽራዋንም ድንግልና እንደጠበቀ በሌሊት ወጥቶ ሄደ፡፡
ከዚያም በመርከብ ተሳፍሮ የብዙ ቀን መንገድ የሚሆን ጎዳና በአንድ ቀን ተጉዞ አርመንያ ደረሰ፡፡ በዚያም በእመቤታችን ስም በታነጸች ቤተ ክርስቲያን ከነድያን ጋር በመቀላቀል እየለመነ ያገኘውንም ለሌሎች እየመጸወተ በጾም በጸሎት ተጠምዶ ዐሥራ አምስት ዓመት ሲኖር እመቤታችን ለገበዙ ተገልጻ ‹‹ገብረ ክርስቶስን ይዘኽ ከቤተ ክርስቲን አግባው›› አለችው፡፡ ገበዙም ኺዶ ‹‹እመቤቴ አዛኛለችና ገብተኽ ሥጋ ወደሙን ተቀበል፡፡›› አለው፡፡ ገብረ ክርስቶስም የታዘዘውን ከፈጸመ በኋላ ‹‹ዋጋዬን በውዳሴ ከንቱ ሊያጠፉብኝ ነው›› ብሎ ከእመቤታችን ፊት ቆሞ ‹‹ምሥጢሬን ለምን ገለጽሽ አኹንም ወደ ሚሻለኝ ምሪኝ›› ብሎ በመጸለይ ሥዕሏን ተሳልሞ ወደ ሌላ ሀገር ሊኼድ በመርከብ ተሳፍሮ ከእናት አባቱ ሀገር ደረሰ፡፡ የጌታ ፈቃድ ነው ብሎም ማንነቱን እንደደበቀ ሣያውቁት ከንጉሥ አባቱ ደጅ የኔቢጤ /ለማኝ/ ሆኖ ለአባቱ ውሾች የሚሰጠውን ፈርፋሪ እየተመገበ ሠላሳ ዓመት በዚያ ተቀመጠ፡፡
የአባቱ አሽከሮች እንኳን እጣቢና ቆሻሻውን ሁሉ እየደፉበት ሲያሰቃዩትና ውሾች እንዲናጠቁትም የሥጋ ውሃ ሲደፉበት ውሾቹ ግን ቁስሉን ይልሱለት ነበር፡፡ እርሱም በደል እንዳይሆንባቸው በመጸለይ፣ እየለመነ ያገኘውን እየመጸወተ፣ በጾም በጸሎት እየተጋደለ ኖረ፡፡ ከእለታት አንድ ቀን ጌታችን ስሙን ለሚጠራ፣ መታሰቢያውን ለሚያደርግ ቃልኪዳን ከሠጠው በኋላ እርሱም ታሪኩን ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ጽፎ በእጁ እንደጨበጠው ጥቅምት ዐሥራ አራት ቀን ዐርፏል፡፡
የቁስጥንጥንያው ሊቀጳጳስ አባ ቴዎፍሎስ በቅዳሴ ላይ ሳለ ‹‹ብእሴ እግዚአብሔርን በንጉሥ ቴዎድዮስ ቤት ፈልጉት፡፡›› የሚል ቃል ሰማና ቢሔድ ባረፈበት ቦታ ክርታሱን እንደጨበጠ አገኙት ሊያዩት ፈልገው አልለቅ ብሎ ፈጽሞ እምቢ አላቸው፡፡ ብዙ ምሕላና ጸሎት ከተደረገ በኋላ ለቆላቸው ቢያነቡት የንጉሥ ልጅ መኾኑንና ያሣለፈውን ተጋድሎ ተረድተዋል፡፡ እያለቀሱና ደረታቸውን እየደቁ ሥጋውን ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲወስዱት እጅግ ብዙ ተዓምራቶች በድውያንና ሕመምተኞች ላይ ተፈጽሟል፡፡ ብዙዎች ዳሰውት ከተፈወሱ በኋላ በአንጻረ መቅደስ ቀብረውታል፡፡
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
✍️ FaceBook 👇
https://www.facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
✍️Tiktok👇
https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion
አቡነ አረጋዊ ከእለታት አንድ ቀን እናቱ እድና ዜናውን ሰምታ ልትጠይቀው በመጣች ጊዜ ‹‹ለምን መጣሽ›› አላት፡፡ ‹‹ልጄ አንተ በሕጻንነትህ የናቅኸው ዓለም ለእኔ ምን ይረባኛል ብዬ ነዋ›› አለችው፡፡ እሱም አመንኩሶ ከሴቶች ገዳም አስገባት፡፡ ከሰባት ዓመት በኋላ ዘጠኙ ቅዱሣን በእምነት ወደ ምትመስላቸው ሀገረ እግዚአብሔር ኢትዮጵያ መጥተዋል፤ እናቱም አብራ ወደ ኢትዮጵያ መጥታለች፡፡ ከእነዚህም በይበልጥ የአባ ቴዎድሮስ እና የአባ ጳኩሚስ ደቀ መዝሙር የነበረ አባ ዘሚካኤል /አቡነ አረጋዊ/ በገዳመ አስቄጥስ በነበረበት ሰዓት ስለ እመቤታችን ከተጻፈው ነገረ ማርያም ጌታችን ኢትዮጵያን ዐሥራት እንደሰጣት በመስማቱ ሰባቱን አስከትሎ ወደ ኢትዮጵያ በንጉሥ አልዓማዳ ዘመን መጥተዋል፡፡ ከአባ ጰጉሚስ እንደተማሩት ሥርዐተ ምንኩስናን ማስተማር ማመንኮስ ጀመሩ፡፡ አቡነ ዘሚካኤል መጽሐፈ መነኮሰትን ከጽርእ ቋንቋ ወደ ግእዝ መልሶታል፤ የሱርስትን ቋንቋ ዐዋቂ ስለነበረ አስቀድሞ በቤተ ቀጢን ሰባት ዓመት የግእዝን ቋንቋ ከሰባቱ ጋር ተምሯል፡፡ አባ ገሪማ እስከዚህ ድረስ በሮም ነግሶ ይኖር ነበርና መልእክትን ልከውበት መንግስቱን ትቶ መጥቶ ዘጠነኛ ኹኗል፡፡ ከዐሥራ ሁለት ዓመት በኋላም በየእራሳቸው ተበታትነው ገዳም መስርተዋል፡፡
አቡነ አረጋዊም እናቱ አድናን እና ተማሪው ማትያስን አስከትሎ በአክሱም በስተ ምስራቅ ሰባ ኪሎ ሜትር ርቆ ወደ ሚገኘው ወደ ዳሞ ተራራ ኺዷል፡፡ ወደ ተራራው የሚወጣበት አጥቶ ባሰበ ጊዜ የታዘዘ ዘንዶ መጥቶ ስልሳ ክንድ በሚያህል ጅራቱ ጠምጥሞ በቅዱስ ሚካኤል ጠባቂነት ከተራራው ራስ አድርሶታል፡፡ እንዳደረሰውም ‹‹ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ›› ብሎ በማመስገኑ “ደብረ ሃሌ ሉያ” ተብሏል፡፡ ቦታው ዙሪያው ገደል በመኾኑ መውጫ አልባ የኾነውን ታላቁን የደብረ ዳሞን ገዳም የመሠረተ ሲሆን ይኽም የሀገራችን የመጀመሪያው ገዳም ነው፡፡ በአቡነ አረጋዊ ጥያቄም መሠረት በስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ደብረ ዳሞ ተራራ ላይ ዐጼ ገብረ መስቀል የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ቤተ ክርስቲያን አሠራ፡፡ ለሰራተኞች መውጪያና መውረጃ የተሰራው ደረጃ ስለተነሳ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ማንም ሰው ወደ ገዳሙ የሚደርሰው በአምሳለ ዘንዶ ከላይ በሚለቀቅለት ዐሥራ ስድስት ሜትር የተጎነጎነ ጠፈር ወገቡን ታስሮ በመጎተት ሲሆን ወደ ገዳሙ መውጣት የሚችሉት ወንዶች ብቻ ናቸው፡፡ ለሴቶች በእግረ ደብር ገዳም መሥርቶ እድናን እመመኔት አድርጎ ሹሞላቸዋል፡፡ ከዘጠኙ ቅዱሣን መካከል አቡነ አረጋዊ በግብጽ አባ እንጦንስ በመሠረቷት ገዳም በተማረው መሠረት በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ገዳማዊ ኑሮ መስራች አባት ነው፡፡ አቡነ አረጋዊ ከዐጼ ገብረ መስቀል እና ከቅዱስ ያሬድ ጋር በደቡቡ የሀገራችን ክፍል እየተዘዋወረ ወንጌልን ሲያስተምር ጋሞጎፋ ውስጥ ውሃ ከሌለበት ቦታ ደርሶ መሬቱን በመስቀል ባርኮ በአንድ ስፍራ ላይ በተዓምር አርባ ምንጮችን አፍልቋል፤ በዚህም ከተማው አርባ ምንጭ ተብሏል፡፡ በዚያም መስዋዕተ ኦሪት ይሰዋባቸው ከነበሩ ገዳማት አንዷ የሆነችውን ብርብር ማርያም ገዳምንም በመጎብኘት ወንጌልን በመስበክ አከባቢውን ባርኳል፡፡
በመጨረሻም ጌታችን ተገልጾ ‹‹መንግስትን ትተህ ስላገለገልከኝ መንግስተ ሰማያትን እርስኸለኹ…›› በማለት ልዩልዩ ቃልኪዳንን ከገባለት በኋላ ‹‹…ሞት አያስደነግጥኽም›› በማለት ተስፋውን ነግሮታል፡፡ ከዚያም መነኮሳቱን ሰብስቦ ‹‹ከዛሬ ጀምሮ በሥጋ አታዩኝም›› በማለት በእግዚአብሔር ጸጋ እንደ ሔኖክና ኤልያስ ጥቅምት ዐሥራ አራት ቀን ከሞት ፊት ተሸሸገ /ተሰወረ/፡፡
አቡነ አረጋዊ ወገብረ ክርስቶስ
#አቡነ አረጋዊ /ዘሚካኤል/
አቡነ አረጋዊ ሀገሩ ሮም ሲሆን አባቱ ንጉሠ ሮም ይስሐቅ እናቱ እድና ይባላሉ፡፡ እናት አባቱ ገብረ አምላክ ብለው ሲጠሩት፤ ዘሚካኤል የሚለው በመነኮሰበት ወቅት የወጣለት ስም ነው፤ አረጋዊ የሚለውን ወደ ኢትዮጵያ መጥተው በቤተ ቀጢን በነበሩበት ጊዜ በፍጹም ፍቅርና ትሕትና ስላገለገለ ወንድሞቹ አረጋዊ ብለውታል፡፡
ጥበብ መንፈሳዊ ሲማር አድጎ ዐሥራ አራት ዓመት ሲኾነው ከነገሥታት ወገን የምትሆን ሚስትን ቢያጩለት እምቢ ብሎ ወደ ታላቁ አባት አባ ጳኩሚስ ገዳም ገብቶ ማዕረገ ምንኩስናን ተቀበለ፡፡ በዚህም ከእንጦንስና፣ ከመቃርስ፣ ከጳኩሚስም የምንኩስና ወይም መንፈሳዊ ሐረግ አራተኛ ትውልድ ነው፡፡
የንጉሥ ልጅ በሕጻንነት ምንኩስና መቀበሉን የሰሙ ሰባት ደጋግ ቅዱሳን ከያሉበት ተሰባስበው አባ ጳኩሚስ ገዳም በመግባት ማዕረገ ምንኩስናን ተቀብለው ሁሉንም ነገር ከአባ ጳጉሚስ ጠንቅቀው እየተማሩ ለብዙ ዓመታት ከእርሱ ጋር ተቀመጡ፡፡ እነዚህም ቅዱሳን አባ ጰንጠሌዎን፣ አባ ይምዓታ፣ አባ ጉባ፣ አባ አፍጼ፣ አባ ጽሕማ፣ አባ ሊቃኖስ እና አባ አሌፍ ናቸው፡፡
ደቂቀ ሰላም ወፍቅር በመጋቤ ብርሃናት ቆሞስ አባ ተክለያሬድ ጎርጎርዮስ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ
https://vm.tiktok.com/ZMjbKw38P/
የትምህርት ማስጀመሪያ መርሐ ግብር በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥር በሚገኙ አጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች ተደረገ።
ጥቅምት 13/02/2016 (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)
የ2016 ዓ.ም በሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ሰንበት ትምህርት ቤቶች የትምህርት ማስጀመርያ መርሐ ግብር ባሳለፍነው ቅዳሜና አሁድ ተደርገው አልፈዋል። የዝግጅት ክፍላችን በቦሌ ክፍለ ከተማ በሚገኙ ሰ/ት/ቤቶች ባደረገው ዳሰሳ በአጠቃላይ ከ38 በላይ ሰ/ት/ቤቶች የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ የጀመሩ ሲሆን በአያት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ፣ በየረር ቅዱስ ኡራኤል፣ በአራብሳ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፣ በገርጂ ቅዱስ ጊዮርጊስ አብያተ ክርስቲያናት በአካል በመገኘት ከቅድመ መደበኛ ጀምሮ እስከ ላይኞቹ ክፍሎች ለመማር ማስተማር ሂደቱ አስፈላጊ የሆኑ ነገሮችን በማማሏት ትምህርት መጀመራቸውን ለመመልከት ተችሏል።
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
✍️ FaceBook 👇
https://www.facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
✍️Tiktok👇
https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion
"አስቀድሞም የወሰናቸውን እነዚህን ደግሞ ጠራቸው፤ የጠራቸውንም እነዚህን ደግሞ አጸደቃቸው፤ ያጸደቃቸውንም እነዚህን ደግሞ አከበራቸው።" ሮሜ 8፡30
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ።
ሰናይ ሌሊት!
✍️Youtube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
ቡርክታዊት በደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሰ/ት/ቤት አገልጋይ ስትሆን በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ተፈትና 617 በማምጣት ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም አልፋለች።
https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion/video/7293209441581698347?is_from_webapp=1&sender_device=pc&web_id=7288000334784579078
ከወርቃማው ሕግ አትንሸራተቱ
የተከበራችሁ የማኅበራዊ ሚዲያችን ተከታታዮች አስቀድምን ባስነበብነው የዚህ ጽሑፍ የመጀመሪያ ክፍል ሰው በእግዚአብሔር አርአያ እና ምሳሌ የተፈጠረ የፍጥረታት ንጉሥ፣ ከሌሎች ፍጥረታት ተለይቶ ዐዋቂ እና ሕያውነት ያለው፣ በፍጥረታት ላይ የሠለጠነ ባለጸጋ ፍጡር መሆኑን አቅርበን ነበር። በዚህም ምክንያት ሰው ነጻ ፈቃዱን ተጠቅሞ ሲጠፋ ከሦስቱ አካላት አንዱ ወልድ “እስመ በፈቃዱ፣ ወበሥምረተ አቡሁ ወመንፈስ ቅዱስ መጽዐ አድኀነነ” እንደ ተባለው ሰው ሆኖ ሰውን ከውድቀት አነሣው። ዘጠና ዘጠኙን ነገደ መላእክት ትቶ አንዱን ነገድ ሰውን ለመፈለግ ሰው የሆነው ለሰው ካለው ጽኑ ፍቅር የተነሣ ነው።
ማንበብ ይቀጥሉ...
👇👇👇👇👇👇
https://eotc-gssu.org/a/ከወርቃማው-ሕግ-አትንሸራተቱ-የነገረ-ሰብ/
ከወርቃማው ሕግ አትንሸራተቱ (የነገረ ሰብእ ትምህርት ጉድለት የወለደው አገራዊ ቀውስ ክፍል ሁለት)
(የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት)
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
