Werabe City Government Communication Affairs Office
Open in Telegram
Werabe Communication Social Media Links👇 @ https://m.facebook.com/Werabecommunication @ https://twitter.com/Werabecommu @https://www.werabecity.com
Show more2 936
Subscribers
+124 hours
-117 days
-1630 days
Posts Archive
“የግብርና ስራችንን በማዘመን የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በ2018 በጀት ዓመት ከታረሰው መሬት 50 በመቶውን በክላስተር መሸፈን ተችሏል!” - የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ዘይኔ ቢልካ
የጳግሜ 1 የዕመርታ ቀን ፕሮግራም ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ!
01-13-2018 [ወራቤ ከተማ ኮሙኒኬሽን]
"ባለፉት አመታት የከተማ ግብርና ስራዎችን የተሻለ ውጤታማ ለማድረግ በተለይም በ2018 የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በተሰሩ ስራዎች አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል"
አቶ ያሲን ከሊል
የወራቤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ
ከ120 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ በመንግሥትና በሕዝብ የጋራ ተሳትፎ የተገነባው የቅበት ከተማ አስተዳደር የከንቲባ ጽሕፈት ቤት ሕንፃ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ!
https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1361217519556491/?app=fbl
+3
#እንኳን_ደስ_አላችሁ_አለን!
የአልከሶ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት በ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ባስመዘገበው የላቀ ውጤት በክልሉ ተሸላሚ ሆኗል!
በወራቤ ከተማ አስተዳደር የአልከሶ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት በ2018 ዓ.ም በ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ባስመዘገበው የላቀ የትምህርት ውጤት በክልሉ 3ኛ ደረጃ በመያዝ የዕውቅና ሰርተፊኬት እና የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶለታል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ በተካሄደው የትምህርት ጉባኤ ላይ ነው የዕውቅና ሽልማቱ የተበረከተው።
በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ፤ አለን!!
ነሐሴ 29፣ 2018 [ወራቤ ኮሙኒኬሽን]
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህገወጥ የመሬት ወረራ መከላከል ቴክኒክ ኮሚቴ የወራቤ ከተማ አስተዳደር የእስካሁን ህገወጥ የመሬት ወረራ መከላከል የተግባር አፈፃፀምን ገምግሟል!
https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1359456803065896/?app=fbl
+8
የዘንድሮው የጳጉሜ ቀናቶች በሚከተሉት ስያሜዎች ይከበራሉ!
#ጳጉሜ 1 - "የእመርታ ቀን"
#ጳጉሜ 2 - "የማንሰራራት ቀን"
#ጳጉሜ 3 - "የጽናት ቀን"
#ጳጉሜ 4 - "የኅብር ቀን"
#ጳጉሜ 5 - "የነገ ቀን" በሚል እንደሚከበር የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ማሳወቁ የሚታወስ ነው።
የወራቤ ከተማ አስተዳደርም የጳጉሜ ቀናቶችን በስያሜያቸው መነሻ የተለያዩ ተግባራትን ለማስፈጸም ኮሚቴ በማዋቀር ወደተግባር ገብቷል።
በዚሁ መሠረትም የተቋቋመው ኮሚቴ በየዕለቱ በሚከናወኑ ተግባራት ዙሪያ በመወያየት አቅጣጫ አስቀምጧል።
ነሐሴ 28፣ 2018 [ወራቤ ከተማ ኮሙኒኬሽን]
+3
#እንኳን_ደስ_አላችሁ_አለን!
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ በዛሬው ዕለት በወልቂጤ ከተማ ባካሄደው ዓመታዊ ሴክቶሪያል ጉባኤ ላይ ስልጤ ዞን 1ኛ ደረጃ በማየዝ የዋንጫ እና ዴስክ ቶፕ ኮምፒተር ተሸልሟል።
በተመሳሳይ በዚሁ የጉባኤ መድረክ ላይ የወራቤ ከተማ አስተዳደር፡ ሀብት በማፈላለግና የማስተባበር ሥራዎችን በመስራት በአጭር ጊዜ ውስጥ የዘሞባቴ ጤና ጣቢያ እንዲገነባና ሥራ እንዲጀምር በማድረግ ላበረከተው አስተዋጽኦ፤ በክልሉ ከሚገኙ ወረዳዎች እና ከተማ አስተዳደሮች የተሻለ በመፈጸም በልዩ ተሸላሚነት የእውቅና ሰርተፊኬት ተበርክቶለታል።
በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ፤ አለን!!
ነሐሴ 26፣ 2018 [ወራቤ ኮሙኒኬሽን]
የወራቤ ከተማ አስተዳደር ዜጎች በሕጋዊ መንገድ የውጭ ሀገር የሥራ ዕድል እንዲያገኙና ሕገወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል ያለመ የንቅናቄ መድረክ በቀበሌ ደረጃ አካሂዷል!
https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1357917939886449/?app=fbl
+7
የወራቤ ከተማ ብልፅግና ኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን በዝግጅት ምዕራፍ በተሰሩ ስራዎች ላይ ድጋፍና ክትትል ለማድረግ የስራ ስምሪት ሰጠ!
ነሐሴ 26፣ 2018 [ወራቤ ከተማ ኮሙኒኬሽን]
የወራቤ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ቅርንጫፍ ፅ/ቤት በ2019 በጀት ዓመት ዝግጅት ምዕራፍ በኮሚሽኑ እና በፓርቲ አደረጃጀቶች የተከናወኑ ተግባራትን በቅርበት ድጋፍና ክትትል ለማድረግ ለከተማው ኮሚሽን አመራሮች የስራ ስምሪት ሰጥቷል።
የድጋፍና ክትትሉ ዋና ዓላማ፡ የኮሚሽኑን ተቋማዊ አቅም በየደረጃው ማጠናከር፤ የታችኛውን የኮሚሽን አደረጃጀት ወጥ በሆነ መልኩ በመደገፍና በመከታተል ተጠያቂነትና ግልፀኝነት ያለው አሰራር መስፈን፤ አሰራሮችን በማዘመን የፓርቲውን ጥንካሬ ማረጋገጥ ነው።
የኮሚሽኑ ዋና ሰብሳቢ ክብርት ወ/ሮ ሙስሊያ መሀመድ በመድረኩ እንደገለፁት የኮሚሽኑ ዋና ዓላማ በየጊዜው የፓርቲውንና የኮሚሽኑን አደረጃጀቶች ኢንስፔክሽንና ሱፐርቪዥን ማድረግ ነው።
በተግባር ሂደትም በሚስተዋሉ ጉድለቶች ላይ ፈጣን ግብረ-መልስና ምክረ-ሀሳብ በመስጠት የፓርቲውን ጥንካሬ ማሳደግ እንደሚገባ ዋና ሰብሳቢዋ አስገንዝበዋል።
በተዘጋጀው የክትትልና ድጋፍ ቼክ-ሊስት ላይ የጋራ መግባባት በመፍጠርና ለአመራሩ የስራ ስምሪት በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል።
+9
ከተማ አስተዳደሩ የ2018 በጀት ዓመት የእስካሁን የገቢ አሰባሰብ አፈጻጸምን ገመገመ!
ነሐሴ 26፣ 2018 [ወራቤ ከተማ ኮሙኒኬሽን]
የወራቤ ከተማ አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት የመደበኛና የማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ አሰባሰብ እስካሁን ያለበትን አፈጻጸም ገምግሟል።
የዕለቱን መድረክ የመሩት የወራቤ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ናስር ቡሽራ የከተማዋን የገቢ አቅም ለማሳደግ ሁሉንም የገቢ አማራጮች በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባ ገልጸዋል።
አቶ ናስር አክለውም ከተማዋ ያላትን የገቢ አቅም በሙሉ በመጠቀም በቂ ገቢ ማሰባሰብ ለከተማዋ ልማትና ዕድገት ወሳኝ በመሆኑ የገቢ ምንጮችን በመለየትና በተገቢው መንገድ በማስከፈል የገቢ አሰባሰቡን ውጤታማ ማድረግ እንደሚገባ አመላክተዋል።
የገቢ አሰባሰቡን ውጤታማነት ለማሳደግም ጠንካራ የአፈጻጸም አቅም በመገንባት የሚጠበቀውን ገቢ በወቅቱ በመሰብሰብና በተቋማት መካከል በቅንጅት በመስራት ላይ ትኩረት መስጠት ተገቢ መሆኑ ተጠቁሟል።
በተለይም የአፈር ግብር፣ የህንፃ ግብርና ሌሎች የገቢ ምንጮችን በሕግና በአሰራር መሠረት በማስከፈል የከተማዋን ገቢ ማሳደግ እንደሚገባ ተነስቷል።
የማዘጋጃ ቤታዊና የመደበኛ ገቢ አሰባሰብንም በማጠናከር ለውጤታማነቱ የሚመለከታቸው አካላት በቅንጅት እንዲሰሩ አቅጣጫ ተሰጥቷል።
በተጨማሪም የካዳስተር ክፍያ ያለባቸው አካላት በወቅቱ ክፍያቸውን በመፈጸም የከተማዋን የልማት አቅም ለማሳደግ የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል።
በመድረኩ የ2018 በጀት ዓመት የእስካሁን የገቢ አሰባሰብ አፈጻጸም በመገምገም የታዩ ክፍተቶችን ለመሙላትና የገቢ አቅምን የበለጠ ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራዊ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።
በኢፌዴሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አማካሪ በአቶ ዳንኤል ዳርጌ የተመራው የልዑካን ቡድን በወራቤ ከተማ አስተዳደር እየተከናወኑ ያሉ የክረምት ወራት ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ድጋፍና ክትትል አድርጓል!
https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1356156646729245/?app=fbl
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እና የስልጤ ዞን ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በወራቤ ከተማ አስተዳደር የሚገኘውን ሜላያን ፓርክ ተዟዙረው ጎበኝተዋል።
https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1355547346790175/?app=fbl
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የኢንስፔክሽን ቡድን በወራቤ ከተማ አስተዳደር በተለያዩ ቀበሌዎች ከተረጂነት ወደ አምራችነት ለመሸጋገር እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች ላይ የመስክ ምልከታ አድርጓል!
https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1354650643546512/?app=fbl
በወራቤ ከተማ አስተዳደር ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ተቋም እና በከተማ አስተዳደሩ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት የጋራ አዘጋጅነት ዜጎች በሕጋዊ መንገድ የውጭ ሀገር የሥራ ዕድል እንዲያገኙና ሕገወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል ያለመ ከተማ አቀፍ የንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል!
https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1354476680230575/?app=fbl
+3
በወራቤ ከተማ ነአልከሶ 01 ቀበሌ የውሃ ፕሮጀክት የሙከራ ሥራ ጀመረ!
ነሐሴ 21፣ 2018 [ወራቤ ከተማ ኮሙኒኬሽን]
በወራቤ ከተማ አስተዳደር አልከሶ 01 ቀበሌ የተገነባው የውሃ ፕሮጀክት የሙከራ ሥራውን ጀምሯል።
የሙከራ ሥራው የፕሮጀክቱን የውሃ አቅርቦት አሠራር እና የመሠረተ ልማት አፈጻጸም በተግባር ለመፈተሽና ወደ ሙሉ አገልግሎት ከመግባቱ በፊት የሚኖሩ ጉድለቶችን ለመለየት ያለመ መሆኑ ተመላክቷል።
ፕሮጀክቱ በአልከሶ 01 ቀበሌ የሚገኙ ነዋሪዎች የንጹህ ውሃ ተጠቃሚነትን በማሳደግ የኑሮ ጥራትን ለማሻሻል የሚያግዝ ሲሆን የሙከራ ሥራው በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ ፕሮጀክቱን ወደ ሙሉ አገልግሎት ለማስገባት አስፈላጊ ሂደት መሆኑ ተጠቅሷል።
የወራቤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ያሲን ከሊል እና የከተማ አስተዳደሩ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ናስር ቡሽራ እንዲሁም ሌሎች የሚመለከታቸው አመራሮችና ባለድርሻ አካላት የስራ እንቅስቃሴውን ምልከታ አድርገዋል።
#እንኳን_ደስ_አላችሁ_አለን!
በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ የሚገኘው የሀይረንዚ ልዩ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በ2018 የትምህርት ዘመን ሀገር አቀፍ ብሄራዊ ፈተና ያስፈተናቸውን 103 ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ አሳልፏል።
ከእነዚህ ተማሪዎች ውስጥም፦
1. 550 እና በላይ ወ = 2 ሴ = 02 ድ= 4።
2. ከ500 -549.99 ወ= 48 ሴ = 17 ድ = 65።
3. ከ450 - 499.99 ወ= 23 ሴት =8 ድ= 31።
4 . ከ400 - 449 ወ= 02 ሴ = 01 ድ = 3።
በትምህርት ቤቱ ከ600 የተመዘገበ ከፍተኛ ውጤት 563.2 ሲሆን ዝቅተኛ ውጤት 436. 63 ውጤት ማስመዝገብ ችለዋል።
የ12 ኛ ክፍል ተፈታኞች ውጤታቸውን ዛሬ ከምሽቱ 1 ስዓት ጀምሮ ማየት ይችላሉ!
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ነሐሴ 19፣ 2018 [ወራቤ ከተማ ኮሙኒኬሽን]
የ12 ክፍል ተፈታኞች ውጤታቸውን ዛሬ ከምሽቱ 1 ስዓት ጀምሮ ማየት ይችላሉ አለ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት።
የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርቲፊኬት ፈተና ውጤት የሚገለጽባቸው አድራሻዎች ይፋ ሆኗል።
በ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን (Link) በመጠቀም ማየት የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ አሳውቋል።
በተያያዘም ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልግ https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በማቅረብ ምላሹንም በተመሳሳይ ማስፈንጠሪያ በኩል መከታተል የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ ያሳውቃል።(ኤፍኤምሲ)
ውጤት የሚገለጽባቸው ማስፈንጠሪያዎች፡-
📌በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et
📌ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram
📌አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ!
==========================
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ (ሰዐወ) የመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልእክት የነቢዩን መውሊድ ስናከብር ከሕይወታቸው እየተማርን፤ የተማርነውንም ለሀገረ መንግሥት ግንባታችን እየተጠቀምን እንዲሆን አደራ እላለሁ ብለዋል፡፡
ያስተላለፉት ሙሉ መልእክትም እንደሚከተለው ቀርቧል፦
እንኳን ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) የመውሊድ በዓል አደረሳችሁ
የነቢዩ መሐመድ ታሪክ ትውልድን ለበጎ ከሚቀርጹ ታሪኮች መካከል አንዱ ነው፡፡ የተጠሩበትን ዓላማ ማክበር፤ ለተጠሩበት ዓላማ ዋጋ መክፈል፤ የተጠሩበትን ለሌሎች ማካፈል፤ የተጠሩበትን አክብሮ መኖር - እነዚህ ሁሉ ሺ መጻሕፍት የሚወጧቸው ትምህርቶች ናቸው፡፡
ነቢዩ የተጠሩበትን ዓላማ በሚገባ ስለተገነዘቡ አክብረው ኖረዋል፡፡ የተጠሩት ለተራና ርካሽ ነገር እንዳልሆነ ተገንዝበዋል፡፡ የተጠሩት ትውልድን ለመቅረጽና ታሪክን ለመቀየር መሆኑን አምነዋል፡፡ ያንንም በቃላቸው፣ በሥራቸውና በኑሯቸው አክብረውት ነኖረዋል፡፡ ለታላቅ ሀገራዊ ዓላማ ተጠርተናል ብለን የምናምን ከሆነ ይህ የነቢዩ ሕይወት ታላቅ ትምህርት ይሆነናል፡፡ የተጠራንበትን ዓላማ በንግግራችን፣ በሥራችንና በሕይወታችን እንግለጠው፡፡
ነቢዩ ለተጠሩበት ዓላማ ዋጋ ከፍለዋል፡፡ ከቦታቸው ተሰደዋል፤ ምግብና መጠለያ ተነፍገዋል፤ ከቤተሰቦቻቸው ተለይተዋል፡፡ ለሞት በሚያበቁ ፈተናዎች ውስጥ አልፈዋል፡፡ ጦርነት ተከፍቶባቸዋል፡፡ ነገር ግን ሁሉንም በአላህ ኃይል አሸንፈዋል፡፡ ክብር ያለ መከራ አይገኝምና፡፡ እውነተኛ ሰው ለዓላማው እንደ ነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ)ዋጋ ይከፍላል፡፡ ዓላማው የሚያስገኘውን ክብርና ጥቅም ብቻ ሳይሆን ዓላማው የሚያስከፍለውን መሥዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ይሆናል፡፡
ነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) ከአላህ የደረሳቸውን መልእክት ለራሳቸው ብቻ አላስቀሩም፡፡ የተጠሩበትን ለሌሎች ለማካፈል ተግተዋል፡፡ መጀመሪያ በጣት ለሚቆጠሩ ሰዎች፣ በኋላም ለቅርብ ሱሐባዎች፣ በመጨረሻም ለዓለም መልእክቱን አዳርሰዋል ፡፡ እሳቸው የዘሩት ዘር እያፈራና እየጎመራ ተጉዟል፡፡ ዓላማችንን እኛ ማወቃችንና ማመናችን ብቻ ጥቅም የለውም፡፡ ሌሎች እንዲያውቁና እንዲያምኑ ልክ እንደነቢዩ ተገትተን መድከም አለብን፡፡
የነቢዩን መውሊድ ስናከብር ከሕይወታቸው እየተማርን፤ የተማርነውንም ለሀገረ መንግሥት ግንባታችን እየተጠቀምን እንዲሆን አደራ እላለሁ፡፡
በድጋሚ መልካም የመውሊድ በዓል ይሁንልን።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም
